ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 544 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 544 名订阅者。

根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.50% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 921 次浏览,首日通常累积 2 563 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 544
订阅者
+424 小时
-357
+2230
帖子存档
የተቋሙ ከፍተኛ ሥራ አመራር የዋና መስሪያ ቤት ዕድሳት ሥራ ያለበትን ደረጃ ጎበኘ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ዕድሳት ያለበትን ደረጃ በመስክ በመገኘት ገምግሟል። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የተመራው የከፍተኛ ሥራ ቡድን ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ይዞታ እየተከናወነ ያለውን የቢሮ፣ የካፍቴሪያና የስብሰባ አዳራሽ ዕድሳት እና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል። በአምስት ሎቶች የተከፋፈለውን የዕድሳት ጨረታ ያሸነፈው ብራይት ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ተወካዮች እንደገለፁት 29 ብሎክ ያለውን የቢሮ ዕድሳት ሥራ ለማፋጠን ለ14 ንዑሳን ተቋራጮች ተሰጥቷል። የአጠቃላይ ሥራውን 60 በመቶ ድርሻ የሚይዘው የውስጥ ለውስጥ መንገድ የቅየሳ ሥራ ተጠናቆ የፍሳሽ መውረጃውን የማስተካከልና ልል አፈር የማንሳት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። ይሁንና የመንገድ ሥራውን ሊያዘገዩ የሚችሉ የሲሚንቶ እጥረትና በሥራ አካባቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ትራንስፎርመሮችን ቦታ የማስለቀቅ ሥራ በፍጥነት እልባት እንዲያገኝ ጠይቀዋል። አጠቃላይ ሥራው 37 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን የገለፁት ተወካዮቹ ሥራውን በተያዘው ጊዜ ለመጨረስ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ለሥራ አመራር ቡድኑ አስረድተዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው የዕድሳት ሥራው በተያዘው በጀት፣ የጊዜ ሰሌዳና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ አሳስበዋል። ለዚህም የተቋሙ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ ሥራው እንዲፋጠን የጀመረውን ድጋፍ እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥተዋል። የተቋሙን ዋና መስሪያ ቤት አሁን ካለበት ወደ ኮተቤ ማዛወር ያስፈለገው ተቋሙ በየዓመቱ ለኪራይ የሚያወጣውን ወጪ ለማስቀረትና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ከዓመት በላይ ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር ተቋርጦ የቆየው መቀሌ ከግሪድ ጋር ተገናኝቷል ........///........ በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ከዓመት በላይ ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር ተቋርጦ የቆየው የመቀሌ ከተማ ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል(ግሪድ) ጋር ተገናኝቷል። መስመሩ ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ጋር የተገናኘው ከአላማጣ መሆኒ በተዘረጋው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ከተጠናቀቀ በኋላ ነው። በመስመሩ ፍተሻና የጥገና ሥራ ላይ በሰሜን ምስራቅ ሪጅን አስተባባሪነት ከሁሉም ሪጅን የተውጣጡ የማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የመስመሩ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመር በትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ መልሶ ሥራ ለማስጀመር የተጀመረውን ሥራ የሚያፋጥነው ይሆናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሁመራ እስከ ሽሬ ድረስ የተዘረጋው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቋል። ይሁንና ለሽሬ ኃይል የሚሰጠው ከተከዜ እስከ አክሱም በተዘረጋው መስመር ስምንት ቦታዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማጋጠሙ ጥገናው ወደ ተከዜ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በውል ይዘትና አስተዳደር ክፍተት እንዳያጋጥም ተቋሙ ትኩረት አድርጎ እየተሰራ ነው ………..///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከሀገር ውስጥና ከውጭ ድርጅቶች ጋር የሚያደርጋቸው ስምምነቶችች ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ እንዳይዳርጉት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን የተቋሙ የህግ መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ እንደገለጹት በውል ክፍተት ምክንያት ተቋሙ ለተጨማሪ ወጪ እንዳይዳረግ እና የተቋሙን ጥቅም ለማስከበር የህግ ምክር አገልግሎትና አስተያየቶች እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡ የሥራ ተቋራጭም ሆነ የአገልግሎት ሰጪ የውል ስምምነቶች ለትርጉም እንዳይጋለጡና በውል ክፍተት ተቋሙ ለተጨማሪ ወጪ እንዳይዳረግ ውሎች ከመፈረማቸው በፊት የህግ አስተያየት እየተሰጠባቸው ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ አሻሚ የሚሆኑ አንቀፆች፣ የቃላት አጠቃቀም እና ተጠያቂነትን ሊያመጡ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲሁም ወደ ድርድር ሲገባ በሰነዱ ላይ መካተት በሚገባቸውና በማይገባቸው ጉዳዮች ላይ የህግ ምክር አገልግሎትና አስተያየት እየተሠጠ ይገኛል፡፡ ውል የመፈረም ሥልጣን ያላቸው ኃላፊዎች ውሉን ከመፈረማቸው በፊት የህግ አስተያየት እና ማረጋገጫ እንዲሰጥባቸው በመደረጉ ከውል ጋር በተያያዘ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶች እየቀነሱ መምጣታቸውንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ሶስት ወራት 100 በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ የህግ ምክር አገልግሎቶችና አስተያየቶች መሰጠታቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም

የክሊኒኩን አገልግሎት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል …….///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ክሊኒክ አገልግሎቱን እያሳደገና በጥራት እያቀረበ መሆኑን የጤና አገልግሎቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ
+4
የክሊኒኩን አገልግሎት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል …….///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ክሊኒክ አገልግሎቱን እያሳደገና በጥራት እያቀረበ መሆኑን የጤና አገልግሎቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ መሰረት ሙሉጌታ እንደገለፁት የተቋሙ ክሊኒክ በጤና አገልግሎት፣ በተመላላሽ ህክምና፣ በፋርማሲ፣ በላቦራቶሪ፣ በካርድ ክፍልና በሂሳብ ክፍል ተደራጅቶ አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡ ክሊኒኩ አራት የጤና መኮንኖች፣ ሦስት ፕሮፌሽናል ነርሶች፣ ሁለት ላቦራቶሪ ቴክኖሎጂስቶች፣ አንድ ፋርማሲስት እና አንድ ድራጊስትን ጨምሮ በ17 ሠራተኞች አገልግሎቱን እየሰጠ መሆኑን ሥራ አስኪያጇ ገልፀዋል፡፡ የህክምና አገልግሎቱን ለማሳደግና የታካሚዎችን ምልልስ ለመቀነስ የጠቅላላ ሀኪሞችና የስፔሻሊስቶች ቅጥር አስፈላጊ በመሆኑ የሌሎች ተቋማትን ልምድ በመውሰድ ቅጥሩን በተቋሙ ሥራ አመራር ለማስፈቀድ መታሰቡን ሥራ አስኪያጇ ጠቁመዋል፡፡ ክሊኒኩ ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ሴቶች የተፈጠረላቸውን መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ችሎታቸውን ማሳየት አለባቸው ተባለ ………///…….. ሴቶች የስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማምጣት የተደረጉ ልዩ ድጋፎችን ተጠቅመው በተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ ችሎታቸውን ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኤዳኢ እንደገለፁት በተቋሙ የሚሰሩ ሴት ሠራተኞችን መብትና ጥቅማቸውን ለማስከበር ከመሠረታዊ የሠራተኛ ማህበሩ ጋር በመሆን በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ ድርጅቱ ሴቶችን ለማብቃትና ወደ ውሳኔ ሰጨነት ቦታ ለማምጣት የሚያስችሉ አሰራሮችን በመዘርጋት በትምህርትና ስልጠና አፈጻጸም መመሪያ መሠረት በዲፕሎማ፣ በዲግሪ እና በማስተርስ የትምህርት መርሐግብር በማወዳደር ትምህርት እንዲያገኙ መደረጉን ዳይሬክተሯ ገልፀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ በተቋሙ የሚሰሩ ሴት ሠራተኞች የቅድመ ወሊድ ክትትልና በወሊድ ጊዜም ድርጅቱ ውል በገባባቸው ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች በድርጅቱ ሙሉ ወጭ ተሸፍኖ አገልግሎቱን እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡ ድርጅቱ በሚያወጣቸው ክፍት የሥራ መደቦች ላይ ዝቅተኛውን መስፈርት የሚያሟሉ ሴት አመልካቾች ወደ ውድድር እንዲገቡ መደረጉን የጠቀሱት ዳይሪክተሯ በሥራ ላይ ያሉ ሴቶችም በሚወጡ የዕድገትና ዝውውር ቦታዎች በልዩ ድጋፍ ቅድሚያ ተጠቃሚ እየተደረጉ ነው ብለዋል፡፡ ሴት ሠራተኞች የተፈጠረላቸውን ምቹ አጋጣሚ ተጠቅመው ችሎታቸውን አጉልተው በማውጣት ራሳቸውንና ድርጅታቸውን መጥቀም አለባቸው ሲሉ ዳሬክተሯ አሳስበዋል፡፡ በሁሉም የሥራ ቦታዎች የሴቶችን፣ ህጻናትንና ወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ በማጎልበት መብትና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ የሚያግዝ ሥልጠና ለተጠሪ ሴት ሠራተኞች መሰጠቱ ተገልጿል፡፡ በተቋሙ ውስጥ ያለውን ሠራተኛ በሥርዓተ-ጾታ ፅንሰ ሀሳብና ማካተት እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚረዱ ስልጠናዎች በኃይል ማመመንጫዎችና በሪጅን ላሉ ኃላፊዎች ተሰጥቷል፡፡ “ሴትን አከብራለሁ፣ ጥቃቷንም እከላከላለሁ” ዓለም አቀፍ የጸረ-ጾታዊ ጥቃት ዘመቻ በዓለም ለ31ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ለ17ኛ ጊዜ ከህዳር 16 - ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከ17 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ማመንጨት ችሏል …….///……. በቅርቡ ወደ ኦፕሬሽን ከገቡ 16 የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች 17 ነጥብ 7 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን በጄነሬሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የፕላኒንግ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት ከጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኦፕሬሽን ከገቡ 16 የንፋስ ተርባይኖች 17 ጌጋ ዋት ሠዓት ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ 17 ነጥብ 7 ጌጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት የዕቅዱን 104 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡ ከዕቅድ በላይ ለማመንጨቱም በአካባቢው ያለው የንፋስ ኃይል ፍጥነት ከፍተኛ መሆኑ በምክንያትነት ተነስቷል፡፡ ፕሮጀክቱ የፍተሻ ሥራ ላይ በነበረበት የመስከረም ወር ላይ 3 ነጥብ 3 ጌጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ በጥቅምት ወር ላይ የነበረው የአካባቢው የንፋስ ፍጥነት በአማካኝ 8 ነጥብ 9 ሜትር/ሰከንድ እንደነበር ያነሱት ሥራ አስኪያጇ ይህም ሁሉም የንፋስ ተርባይኖቹ ማመንጨት በሚችሉት አቅም (40 ሜጋ ዋት) በቋሚነት እንዲያመነጩ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ወደ ኦፕሬሽን በገቡ የንፋስ ተርባይኖች የመነጨው ኃይል፤ ከሌሎች መሰል ጣቢያዎች የተሻለ ኃይል ማምረት እንደሚቻል ያሳየ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ ከፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት የተገኘው ምርት እስከ አሁን ወደ ኦፕሬሽን ከገቡ ሌሎች የንፋስ ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር ሲነጻጸር በመጀመሪያ ጊዜ ይህን ያህል ኢነርጅ ያመነጨ ጣቢያ እንዳልነበረም ወ/ሮ ጥሩወርቅ አስታውሰዋል፡፡ ይህም ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የታቀደለትን የማመንጨት አቅም እንደሚያሳካ እና ወደ ፊት ወደ ኦፕሬሽን የሚገቡ ቀሪ የንፋስ ተርባይኖች አስተማማኝ የሆነ ኃይል እንደሚያመነጩ ተስፋ የሰጠ እንደሆነ ነው የተናገሩት፡፡ ከንፋስ የሚገኘውን የኃይል ምንጭ ለማሳደግ በአይሻ 2 አካባቢ ያለው አማካኝ የንፋስ ፍጥነት ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገልፀዋል፡፡ የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 48 የንፋስ ተርባይኖች የሚኖሩት ሲሆን ከዚህ ወስጥም የ32 የንፋስ ተርባይኖች የተከላ ሥራ ተጠናቋል፡፡ ከተተከሉት መካከልም 16ቱ ተርባይኖች ወደ ኦፕሬሽን ገብተው ኃይል ማምረት ጀምረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ባለፉት አራት ወራት ውሳኔ ካገኙ የፍትሐብሔር ክርክሮች ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ……..///…….. በፌዴራልና በልልል ፍርድ ቤቶች ክርክር ሲካሄድባቸው ቆይተው ለተቋሙ በተወሰኑ የፍትሐብሔር ጉዳይ የክስ መዝገቦች ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ እንዳታወቁት ክርክር ሲካሔድባቸው ከቆዩ የፍትሐብሔር ጉዳይ መዝገቦች መከከል ባለፉት አራት ወራት በ13 የክስ መዝገቦች ላይ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡ ውሳኔ ከተሰጠባቸው መዝገቦች መካከል ስምንቱ ሙሉ በሙሉ ለተቋሙ፣ ሁለቱ ለከሳሽ እንዲሁም በሁለቱ መዝገቦች ላይ ደግሞ 80 በመቶ የሚሆነው ለተቋሙ የተወሰነ መሆኑን አቶ መርክነህ አብራርተዋል፡፡ ውሳኔ የተሰጠበት አንዱ መዝገብ እንደገና እንዲታይና ውሳኔ እንዲሰጥበት ወደ ሥር ፍርድ ቤት መመለሱን ጠቁመዋል፡፡ ባለፉት አራት ወራት ለተቋሙ በተወሰኑለት የክስ መዝገቦችም ከ132 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ የገንዘብ መጠን ያላቸው 92 የፍትሐብሔር ጉዳይ የክስ መዝገቦች በክርክር ሂደት ላይ እንደሚገኙም አቶ መርክነህ ገልፀዋል፡፡ ከእነዚህ የክስ መዝከቦች መካከል በስምንቱ ላይ ተቋሙ ከሳሽ ሆኖ የቀረበ ሲሆን በ84ቱ ላይ ደግሞ ተከሳሽ እንደሆነ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ መምሪያው ከፍትሐብሔር ጉዳዮች በተጨማሪ ከወንጀልና ከካሳ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ባሉ የክስ መዝገቦች ላይ የክትትልና የድጋፍ ሥራዎች እያከናወነ ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በ2015 በጀት ዓመት በ52 የወንጀል የክስ መዝገቦች ላይ ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ አቶ መርክነህ ገልፀዋል፡፡ ዳይሬክተሩ እንደገለፁት የወንጀል የክስ መዝገቦቹ በተቋሙ ንብረት ላይ በተፈፀሙ የስርቆትና የመሰረተ ልማት ውድመት፣ የሰነድ ማጭበርበርና ከግምጃ ቤት ዕቃ የመውሰድ፣ እምነት የማጉደልና የመሸሸግ ተግባራት ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ መምሪያው ተገቢውን ክትትል የማድረግ፣ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ተገቢውን ማስረጃ የማቅረብ እንዲሁም የከሳሽነት ቃል የመስጠት ሥራዎችን እያከናወነ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ ሪጅኖች የህግ ባለሙያ እንዲመደብላቸው በማድረግ የሚፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶችን በቅርበት እንዲከታተሉ መደረጉንም አመልከተዋል፡፡ አቶ መርክነህ እንደገለፁት የወንጀል ድርጊት ፈጽመዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ከገንዘብ መቀጮ እስከ ዘጠኝ ዓመት ጽኑ እስራት የሚደርስ ውሳኔ እንዲተላለፍ ተደርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 23 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ……..///…….. የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን በኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ የግድብ ሞኒተሪንግ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ደላሽ እንዳስታወቁት የግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥ የዕይታ ፍተሻ እና የግድብ ደህንነት መከታተያ መሳሪያዎችን በመጠቀም እየተከናወነ ነው፡፡ በግልገል ጊቤ 1፣ በመልካ ዋከና፣ በቆቃ፣ በጢስ ዐባይ እና በፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የግድብ ክትትል ሥራው በዕይታ ፍተሻ እየተከናወነ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ኤልያስ ገለፃ የመቆጣጠሪያ መሳሪያ በተገጠመላቸው የጊቤ 3፣ ተከዜ፣ ገናሌ ዳዋ 3 ማመንጫ ጣቢያዎች እና በመገንባት ላይ ባሉ ማመንጫ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳሪያዎች የታገዘ ፍተሻ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የግድብ ሞኒተሪንግ ሥራዎች በግድብ ላይ ያልተጠበቀ ሁኔታ እንዳይከሰት፤ በግድቡ ላይ የውሃ መጠን ሲጨምርና ሲቀንስ እንዲሁም የግድቡን ደህንነት ስጋት ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ያልተጠበቁ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ክስተቶችን ለመከታተል እንደሚተገበር ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡ የግድብ ሞኒተሪንግ ሥራ በግድቦች ላይ ያልተለመዱ ሁኔታዎች ሲከሰቱ አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምጃ በወቅቱ በመውሰድ የግድቦችን ደህንነት ለመጠበቅ እና ማመንጫ ጣቢያዎቹ የሚጠበቅባቸውን ኃይል በአግባቡ እንዲያመርቱ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ውጤታማ የግድብ ደህንነት ክትትል ሥራ ከግድብ አሠራር እና ጥገና ሥራ ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ለመቆጣጠር ያግዛል፡፡ የግድብ ክትትል ሥራዎችን በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በአግባቡ ለማከናወን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ጨምሮ ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እንደያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡ የግድብ ክትትል ሥራ በዲዛይን ጊዜ፣ በግንባታ ሂደት፣ ግድቡ ለመጀመሪያ ጊዜ ውሃ መያዝ ሲጀምር እና ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የሚከናወን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 23 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዕውቅና ሽልማት አገኘ .......////....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመልካም ግንኙነት ላይ የተመሰረተ አሰራር በመዘርጋቱ ከኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር የዕውቅና ሽልማት አገኘ። የዕውቅና ሽልማቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብዲ ዘነበ እጅ ተቀብለዋል። ዶ/ር አብዲ በዕውቅና አሰጣጡ ወቅት እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሀገር ኩራት የሆነ ተቋም ነው። የዕውቅና ሽልማቱ የተሰጠው በተቋማቱ መካከል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ለመጣው የተቋማቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ እንደሆነ ገልፀዋል። ተቋሙ ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል መሸጥ መጀመሩ እንዳስደሰታቸው የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈፃሚው የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ወደፊት በአጎራባች ሀገራት ሊያከናውናቸው በዕቅድ የያዛቸውን ሥራዎች ለማሳለጥ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ላለፉት አራት ዓመታት በባቡር መስመሩ ላይ የኃይል መቆራረጥ ያጋጥም እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አብዲ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ከተፈረመ በኃላ ግን ችግሩ ሙሉ በሙሉ መቀረፉን አብራርተዋል። ለዚህ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮችና በሥራው ላይ ተሳትፎ ላደረጉ የቴክኒክ ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው የተቋማቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት መሻሻል በአጭር ጊዜ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻሉን ጠቅሰዋል። በሁለቱም ተቋማት በኩል ያሉ የሥራ አመራሮችና የቴክኒክ ባለሙያዎች የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ችግሮች መፍትሔ እንዲያገኙ የሰሩት ሥራ የሚበረታታ መሆኑንም ተናግረዋል። ተቋማቱ በጋራ የሚሰሯቸውን ሥራዎች አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው እየመጡ ያሉ ለውጦች የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የላቀ ደረጃ ላይ መድረሱን ማሳያ ናቸው ብለዋል። እንደ ተቋም ለተበረከተላቸው የዕውቅና ሽልማት ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ አሸብር በመግባቢያ ሰነዱ መሠረት ለኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ህዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋማቱ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ ...... ////...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር የሁለትዮሽ ግንኘነታቸውን ለማጠናከር የሚያስችል ምክክር አካሄዱ። ውይይቱ ሁለቱ ተቋማት ከዚህ ቀደም በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ሥምምነት መሰረት የተሰሩ ሥራዎችን ለመገምገምና ቀጣይ የሥራ ግንኙነቶች በሚሻሻሉበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲኣ ተናግረዋል። የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የመግባቢያ ሰነድ ሥምምነት ከመፈረሙ በፊት የኃይል አቅርቦት ችግሮች ያጋጥሙት እንደነበር ያወሱት አቶ አንዱዓለም ሥምምነቱ ችግሮቹን ከምንጩ በመለየት በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ ዕቅድ ለመፍታት ትልቅ ሚና እንደተጫወተ አብራርተዋል። የአክሲዮን ማህበሩ የኦፕሬሽን ሥራዎች ሙሉ በሙሉ በሀገር  ውስጥ ባለሙያዎች ለማከናወን በሚያደርገው ጥረት ተቋሙ ልምድ እያካፈለ እንደሚገኝ ገልፀዋል። በኢትዮ-ጅቡቲ የምድር ባቡር መስመር ላይ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ ከሁለቱም ተቋማት የተውጣጣ የቴክኒክ ቡድን መዋቀሩን የጠቆሙት አቶ አንዱዓለም በሥምምነቱ መሰረት የቴክኒክ ቡድኑ ችግር ፈቺ ጥናቶች ማካሔዱን ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ላይ የሚገኝ የስታቲክ ቫር ጀነሬተር ወደ ሥራ እንዲገባ በማድረግ የባቡር መስመሩ ከዚህ በፊት ያጋጥሙት የነበረውን የኃይል አቅርቦት ችግሮች ለመፍታት ጥረት መደረጉን ገልፀዋል። ከኃይል ሽያጭ ክፍያ ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ለማስተካከል ሁለቱ ተቋማት የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸውን ያስታወሱት አቶ አንዱዓለም ከቅጣት ጋር የተያያዙ አንዳንድ ክፍያዎች እስካሁን ያላለቁ ቢሆንም ዋና ዕዳቸውን ግን መከፈል እንደቻሉ ጨምረው ጠቁመዋል። የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብዲ ዘነበ በበኩላቸው የኃይል ሽያጭ ክፍያዎች በወቅቱ እንዲከፈሉ ለማድረግ ተቋማቸው ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። በውይይቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት ዋና አስፈፃሚዎችን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ህዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+3