EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 545 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 545 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 545
订阅者
+824 小时
-227 天
+2730 天
帖子存档
15 545
የዋና መስሪያ ቤት ዕድሳት ሥራ እየተከናወነ ነው
……..///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት የዕድሳት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በተቋሙ የፋሲሊቲ ማኔጅመንት ቢሮ ገለፀ፡፡
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ፋናዬ ዘበነ እንደገለፁት ሜክሲኮ አካባቢ የሚገኘው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ያለበት ህንፃ ኪራይ በመሆኑ በበጀት ዓመቱ ኮተቤ ወደሚገኘው የተቋሙ ይዞታ ለማዘወር የቢሮዎች ዕድሳት ሥራ እየተሰራ ነው፡፡
የተቋሙን ዋና መስሪያ ቤት አሁን ካለበት ወደ ኮተቤ ማዛወር ያስፈለገበት ምክንያት ተቋሙ በየዓመቱ ለኪራይ የሚያወጣውን ወጭ ለማስቀረትና ለሥራ ምቹ አካባቢን ለመፍጠር እንደሆነ ሥራ አስኪያጇ ገልጸዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ የዕድሳት ሥራው ብራይት ኮንስትራክሽን ለተባለ ሀገር በቀል ሥራ ተቋራጭ እና ለተቋሙ የራስ ኃይል የጥገና መምሪያ በኮንትራት ተሰጥቷል፡፡
ከዕድሳት ሥራው ጎን ለጎን ማኔጅመንቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ወንበርና ጠረጴዛን የመሳሰሉ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶችን ከወዲሁ እንዲሟሉ ዝርዝር መስፈርት ተዘጋጅቶ ለግዥ ክፍል ጥያቄ መቅረቡን ወ/ሮ ፋናዬ አስታውሰዋል፡፡
ያረጁ የውሃ መስመሮችና ታንከሮች፣ መፀዳጃ ቤቶች፣ የስልክ መስመር ዝርጋታዎች በአዲስ መልክ እንዲሟሉ ኮንትራት የተገባባቸው ሥራዎች መሆናቸውን የገለፁት ስራ አስኪያጇ ከቢሮ ዕድሳት ሥራ በተጨማሪ ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ምድረ ግቢውን የማሳመርና ደረጃውን የጠበቀ የካፍቴሪያ አገልግሎት እንዲኖር ለማድረግ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የብራይት ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጭ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘርዓ ጽዮን ግርማ በበኩላቸው ከ364 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተከናወነ የሚገኘውን የዋና መስሪያ ቤት ዕድሳት ሥራ በተያዘለት የጊዜ መርሐግብር መሠረት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ዕድሳቱ ከ21 በመቶ በላይ መድረሱን የተናገሩት ዋና ሥራ አስኪያጁ ለዕድሳት ሥራው ከ28 ሺህ ኩንታል በላይ ስለሚያስፈልግ አሁን ካለው የሲሚንቶ አቅርቦት እጥረት አኳያ የማጠናቀቂያ ጊዜውን እንዳያጓትተው ስጋታቸውን ተናግረዋል፡፡
በተያያዘ ዜና በቢሮ ዕድሳቱ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የተቋሙ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የሲቪል ጥገና ስራዎች ሥራ አስኪያጅ አቶ ግርማ መንገሻ እንደተናገሩት መምሪያው በ21 ሚሊየን ብር ወጭ ለፓወር አፍሪካ ዋና መስሪያ ቤት የሚያገለግሉ ቢሮዎችንና ከ850 ሰው በላይ መያዝ የሚችለውን የተቋሙን መሰብሰቢያ አዳራሽ እያከናወነ ነው፡፡
እስካሁን በተሰራው ሥራ ዕድሳቱ 51 በመቶ መጠናቀቁን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የግብዓት አቅርቦት ችግርና የዲዛይን ለውጥ ሥራው በተያዘለት የጊዜ መርሐግብር መሰረት ለማጠናቀቅ ስጋት እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
ከአሰሪና ሠራተኛ ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ የሥራ ላይ ክርክሮች በድርድር እየተፈቱ ነው
………///………
ከአሰሪና ሠራተኛ ጋር የተያያዙ የሥራ ላይ ክርክሮች በድርድር እንዲፈቱ በመደረጉ ወደ ፍርድ ቤት የሚሄዱ የክስ መዝገቦች መቀነሳቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ አገልግሎት መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ እንገደለፁት በተቋሙ ከአሰሪና ሠራተኛ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ወደ 300 የሚጠጉ የሥራ ላይ የክርክር ጉዳዮች ነበሩ፡፡
የሥራ ክርክር ጉዳዮች ወደ ፍርድ ቤት ሳይሄዱ በድርድር እንዲፈቱ ለማድረግ ስድስት አባላት ያሉት የሥራ ድርድርና የቅሬታ ሰሚ ኮሜቴ ተቋቁሞ ጉዳዮች በድርድር እንዲፈቱ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኮሚቴው እያከናወነ ባለው ሥራ በአሁኑ ወቅት ጉዳዮቹ ወደ 33 ዝቅ ማለታቸውን ጠቁመዋል፡፡
ጉዳዮች ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዳቸው በፊት በድርድር ለመፍታት እየተሰራ ካለው ሥራ በተጨማሪ ወደ ፍርድ ቤት የሄዱ ጉዳዮችን በድርድር ለመጨረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ የሆነ የገንዘብ መጠን ያላቸው የፍትሐብሔር ጉዳዮች ክርክርና ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆነ ያስታወቁት ዳይሬክተሩ ከዚህ ውስጥ 2 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የገንዘብ መጠን ያለው ክርክር ከመደበኛ ፍርድ ቤት ውጪ በድርድርና በግልግል ዳኝነት እየታየ ይገኛል ብለዋል፡፡
የክስ መዝገቦች በድርድር እንዲዘጉ ሲደረግ ተቋሙ ለጠበቃ፣ ለዳኝነት እንዲሁም ለወጪና ኪሳራ የሚያወጣውን ተጨማሪ ወጪ እንደሚያስቀርም ገልፀዋል፡፡
ጉዳዮች በድርድር እንዲቋጩ ተቋሙ ከሚያቀርበው ጥያቄ በተጨማሪ በተቃራኒ ጎራ ተከራካሪ የሆኑ አካላት የድርድር ፍላጎት ኖሯቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት የተቋሙን ጥቅም ባስከበረ መልኩ ድርድር እንደሚካሔድም አመልክተዋል፡፡
ክርክርን በድርድር መቋጨት ተጠያቂነት የሚያመጣባቸው የሚመስላቸው አንዳንድ የሥራ መሪዎች ጉዳዮችን በድርድር ከመፍታት ይልቅ በፍርድ ቤት እንዲያልቅ መፈለጋቸው የክርክር ሂደቶችን በአጭር ጊዜ ለመቋጨት በሚሰራው ሥራ ላይ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል ብለዋል፡፡
እንደ አቶ መርክነህ ገለጻ ክርክርን በድርድር መጨረሱ የሚያወጣ መሆኑ ሲረጋገጥ፤ የክስ ጉዳዩ አመጣጥ ክፍተት ያለበት ሲሆን፤ ተቋሙ ከተቃራኒ ወገን ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት ለማስቀጠል፤ ተቋሙን ከአላስፈላጊ ወጪ ለመታደግና የባለሙያውን ጊዜ ላለማባከን እንዲሁም ተከራካሪዎች በተቋሙ ላይ ያላቸው የእኔነት ስሜት እንዳይጠፋ ለማድረግ ጉዳዮች በድርድር እንዲፈቱ ይደረጋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 19 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
ሁመራ ከተማ አካባቢው ከሳምንት ባነሰ ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ እየተሰራ ነው
……...///……....
በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ከሁለት ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦባቸው የቆዩት የሁመራ ከተማና አካባቢው ከሳምንት ባነሰ ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና የቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ እንደገለፁት ከሁመራ - ወልቃይት - ሽራሮ ድረስ ባለው የኃይል ተሸካሚ መስመር ላይ ሲካሔድ የቆየው የጥገና ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል።
ከሁመራ እስከ ሽሬ በሚገኙ 474 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተከናወነ የፍተሻ ሥራ 92 ቦታዎች ላይ በሶስቱም ጥምር መስመሮች ላይ የመቆራረጥ አደጋዎች ማጋጠሙን ተናግረዋል።
በጦርነቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደውን የሽራሮ- ሽሬ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመጠገን በስድስት ቡድኖች የተዋቀረ የጥገና ቡድን ሌት ከቀን ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ተስፋዬ ገለፃ እስካሁን በተደረገው የተከዜ - ሽሬ - ሁመራ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራ በ62 ቦታዎች ላይ የነበሩ ጉዳቶችን ሙሉ በሙሉ መጠገን ተችሏል።
ሰለኽለኻ በተባለ አካባቢ የተጎዱ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መኖራቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የጥገና ሥራውን በፍጥነት በማከናወን የሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ በሳምንት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ ይደረጋል ብለዋል።
የሽሬ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ዳግም አገልግሎት መጀመር ለሽሬ ከተማና አካባቢው እንዲሁም ለሁመራ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግም ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት።
ከተከዜ - አክሱም በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮሎት የኃይል ማስተላለፊያ ላይ በተደረገው የመጀመሪያ የፍተሻ ሥራ መስመሩ ጉዳት እንዳላጋጠመው ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል።
ከዐቢይአዲ - አድዋ ያለውን ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ለማከናወን የፍተሻ ሥራዎች ጎለ ጎን እንደሚጀመሩም ነው ያስታወቁት።
እንደ አቶ ተስፋዬ ገለፃ ከዐቢይአዲ - አድዋ ያለውን የጥገና ሥራ በማጠናቀቅ የአክሱም እና የአድዋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል መስጠት ይጀምራሉ።
እየተካሔደ ባለው የጥገና ሥራ ላይ ከሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የተውጣጡ የተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሠራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
የተቋሙ ቋሚ ንብረት ወደ ስድስት መቶ ቢሊየን ብር እየተጠጋ ነው
………./////……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቋሚ ንብረት ሀብት ወደ ስድስት መቶ ቢሊየን ብር እየተጠጋ መሆኑን የተቋሙ የንብረት ክለሳና አይ ኤፍ አር ኤስ ሪፖርቲንግ ፕሮግራም መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ይርጉ ኃይሉ እንዳስታወቁት ከተቋሙ ቋሚ ንብረት ውስጥ 382 ቢሊዮን ብሩ በንብረት ቆጠራው ጊዜ የተገኙ ንብረቶችን በአዲስ ዋጋ በመገመትና በመከለስ የተገኘ ሲሆን 212 ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው ንብረቶች ደግሞ በግንባታ ላይ ይገኛሉ፡፡
ተቋሙ ከተቋቋመ ጀምሮ እስከ 2008 ዓ.ም. ያለውን ንብረት በአዲስ ዋጋ በመከለስ እንዲሁም ከ2009 እስከ 2013 ዓ.ም ያለውን ንብረት በተገዛበትና በተገነባበት ዋጋ በማስላት የተቋሙ የቋሚ ንብረት መጠን 594 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቀዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ከቋሚ ንብረቱ ውስጥ የተቋሙ ካፒታል 317 ቢሊየን ብር ነው፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክርቤት ደንብ ቁጥር 381/2008 እንደተሻሻለው አንቀጽ2(6) መሠረት ለተቋሙ የተፈቀደ ካፒታል 120 ቢሊየን ብር ሲሆን 30 ቢሊየን ብሩ በጥሬ ገንዘብና በዓይነት የተከፈለ ነው፡፡
የተቋሙ ቋሚ ንብረትና የካፒታል መጠን ማደግን ተከትሎ የህግ ማሻሻያ ሊደረግ እንደሚችል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
የንብረት ቆጠራው ተቋሙ ንብረቱን አያውቅም እየተባለ በተለያዩ አካላት ሲነሳ የነበረውን ትችት መቀልበስ ያስቻለ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 15 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
የኤሌክትሪክ መሰረተልማት ሥርቆትን ለመከላከል ሚዲያዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
………///……..
በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተገነቡና በመገንባት ላይ ባሉ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ ሚዲያዎች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪ አቀረበ።
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ህዳር 13 እና 14 ቀን 2015 ዓ.ም በአዳማ ማከፋፈያ ጣቢያ፣ በወላይታ ሶዶ የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ እና በኢትዮ - ኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ጉብኝት አድርገዋል።
በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የሥርቆት ወንጀሎች እየተበራከቱ ነው፡፡
ለዚህም የግንዛቤ እጥረት ዋና ምክንያት መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስፈፃሚው ሚዲያዎችም ህብረተሰቡን በማንቃትና ግንዛቤ በመፍጠር መሰረተልማቱ እንዲጠበቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ተቋሙ በየጊዜው የሚፈጸሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል ከክልል እስከ ወረዳ ባለው መዋቅር ያሉ የመስተዳድር ኃላፊዎች እና ከፀጥታና ከፍትህ አካላት ጋር በመሆን የሚከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እንደተጠበቁ ሆነው ሁሉን ያካተተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 15 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
በተቋሙ የዓለም አቀፍ የሂሳብ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራብ ሥርዓት መተግበሩ ግልጽና ነፃ የሆነ ሪፖርት ለማቅረብ ያግዛል
………////……….
የዓለም አቀፍ የሂሳብ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ሥርዓት (IFRS) በተቋሙ መተግበሩ ከተለያዩ አካላት ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ግልጽ የሆነ ሪፖርት ለማቅረብ እያገዘ መሆኑን የንብረት ክለሳና አይ ኤፍ አር ኤስ ሪፖርቲንግ ፕሮግራም መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ይርጉ ኃይሉ እንዳስታወቁት በተቋሙ አይ ኤፍ አር ኤስ በመተግበሩ ከማንኛውም አካላት ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ግልፅ የሆነ ምላሽ ለመስጠት እያገዘ ይገኛል፡፡
የአይ ኤፍ አር ኤስ ፕሮጀክት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሕሊና ገዛኸኝ በበኩላቸው መንግስት አይ ኤፍ አር ኤስ እንዲተገበር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ እንደጀመረ እና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም የፋይናንስ ሥራዎች በአይ ኤፍ አር ኤስ እየተሰሩ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ ከዚህ በፊት የሂሳብ ሪፖርቱን "GAAP" በሚባል አሰራር መሰረት ሲያከናውን እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሕሊና ይህም ግልጽነት ያለው ሪፖርት በማውጣት እና ተጠያቂነትን በማስፈን በኩል ክፍተቶች እንደነበሩበት ተናግረዋል፡፡
አይ ኤፍ አር ኤስ በመተግበሩ የፋይናንስ ሪፖርቱ በአሰራር፣ በአቀራረብ፣ በአቀማመጥ እንዲሁም በአገላለጹ ግልጽነትን የሚያሳይና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል፡፡
ማንኛውም አካል ሪፖርቱን በመመልከት ተቋሙ ምን ያህል ሀብት እንዳለው፣ ምን ያህል ዕዳ እንዳለበት፤ ትርፋማነቱ፣ የዕዳ አከፋፈሉና ብድሮቹ ምን እንደሚመስሉ እንዲሁም ገቢዎቹ ከምንና ከየት እንደሆነ በግልጽ እንዲረዳ ለማድረግ ያግዛል ነው ያሉት አቶ ሕሊና፡፡
በተቋሙ የአይ ኤፍ አር ኤስ አሰራርን ለመተግበር ፒ ደብሊው ሲ ከተሰኘ ኩባንያ ጋር ሲሰራ እንደነበር ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 14 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
ለማከፋፈያ ጣቢያው የሚያስፈልገው ትራንስፎርመር ቦታው ላይ ደርሷል
………///………
በወልዲያ ዶሮ ግብር የተጀመረውን የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተፋጠኑ ነው፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ በአብዛኛው ተጠናቆ የነበረ ቢሆንም በጣቢያው ለመትከል የታሰበው ባለ 230/66/15 ትራንስፎርመር ወደ 230/33/15 በመለወጡ የተነሳ የዲዛይን ለውጥ ተደርጓል፡፡
የዲዛይን ለውጥ ማድረግ ያስፈለገው ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያገኙ ለነበሩት ለላሊበላ እና ለአካባቢው ከጣቢያው በ66 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ኃይል ለመስጠት ታስቦ የነበረውን ዲዛይን በመቀየር ከወልዲያ እስከ ጭፍራ ላሉት አካባቢዎች አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ነው፡፡
በዲዛይን ክለሳው የተነሳ ለትራንስፎርመሩ ማስቀመጫና ለባለ 66 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር የተዘጋጀውን የመሰረት ዲዛይን በመለወጥ በባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የወልዲያ፣ የሐራ ገበያ፣ የሐሮ፣ የድሬ ሮቃና የጭፍራን የኤሌክትሪክ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል የማስተካከል ሥራ የሚሰራ ይሆናል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ሳይጠናቀቅ ህወኃት በአካባቢው ሦስተኛ ዙር ጦርነት በመክፈቱ ሥራው ለጊዜው እንዲቋረጥ ተደርጎ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
በወቅቱ ከጣቢያው በቅርብ ርቀት ጦርነት የተካሄደ በመሆኑ በከባድ መሳሪያ ፍንጣሪ ተመቶ የተጎዳውን የማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል የጣሪያ ቆርቆሮ፣ የረገፈ መስታወትና ሌሎች ጉዳት ደረሰባቸውን ግንባታዎች በማስተካከል ትራንስፎርመሩን በመግጠም የፍተሻና ሙከራ ሥራ ለማከናወን ታቅዷል፡፡
ለዚህ ሥራ የሚውለውና በማከፋፈያ ጣቢያው የሚተከለው ፓወር ትራንስፎርመር ከወልዲያ ተጓጉዞ ዶሮ ግብር ማከፋፈያ ጣቢያ ደርሷል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 13 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
ሥራ አመራሩ በጥብቅ ዲሲፒሊን እየተመራ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች የተቋሙን ውጤታማነት እያሳደጉ ነው
………/////………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ ሥራ አመራር የሚያሳልፋቸው ውሳኔዎችና የሚስቀምጣቸው አቅጣጫዎች የተቋሙን ውጤታማነት እያሳደጉ መምጣታቸውን የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ ቤት ኃላፊ አስታወቁ፡፡
ኃላፊው አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት የተቋሙ ሥራ አመራር በጥብቅ ዲሲፕሊን እየተመራ በየሳምንቱ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ለመከታተል የሚያስችል ሥርዓት ዘርግቷል፡፡
አመራሩ በመናበብና በቡድን ስሜት በመንቀሳቀስ ሥርዓት አበጅቶ ተቋሙን ለመምራት የሚያግዙ የተለያዩ መመሪያዎች አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረጉ ለአፈፃፀሙ መሻሻል አስተዋጽኦ ማድረጉን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
የኃይል ማከፋፈያና ማመንጫ ጣቢያዎች መደበኛ ሥራቸው እንዳይስተጓጎልና ውጤታማ እንዲሆኑ ለማድረግ የመለወዋጫ ዕቃዎች የማዕቀፍ ግዢ ሥርዓትን በመዘርጋቱ የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝ እየሆነ መጥቷል ብለዋል፡፡
የሥራ አመራር ቡድኑ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት፣ አነስተኛ አቅም ያላቸው የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች አዋጪነት፣ የሚመረተው ኃይል ከገቢ ጋር ያለውን አፈጻጸም የተመለከቱና ሌሎች ተቋማዊ ለውጥ የሚያመጡ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን በመለየት አቅጣጫ ማስቀመጡን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 13 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
ተቋሙ የምህንድስና የማማከር አገልግሎትን በጥራት እያቀረበና እያስተገበረ ነው
……..////……..
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የምህንድስና ማማከር አገልግሎት ጥራቱን በጠበቀ ሁኔታ እያቀረበና እያስተገበረ መሆኑን የኢንጅነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት ደረጃውን የጠበቀ ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወይም ስፔሲፊኬሽን በማዘጋጀት ፕሮጀክቶች ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲጠናቀቁ እየተደረገ ነው፡፡
የጨረታ ሰነድ ዝግጅት (Bid Document standardization) የሚል ኢኒሼቲቭ በመቅረፅ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችና አሰራሮች ሲኖሩ ብቻ ለማሻሻል ዕድል የሚሰጥ ወጥ የተቋም የፍላጎት መጠየቂያ (employer requirement) በማዘጋጀት ወደ ትግበራ መገባቱ ለጥራት ማስጠበቂያ አንዱ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ተቋራጭ ወይም አቅራቢ ከተቀጠረ በኋላ ዕቃ ከመመረቱ በፊት በሚኖረው የዲዛይን ማፅደቅ ሥራ ላይ መሐንዲሶች ለሥራቸው መነሻ ከሚሆን ሰታንዳርድና ቴክኒካል ዕውቀት በተጨማሪ በፀደቀው ውል መሰረት የተቋሙን ፍላጎት ለማሳካት እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በውስን ግለሰቦች ላይ ተንጠልጥሎ የነበረን ሥራ በርካታ ባለሙያዎች እንዲሰለጥኑና በነፃነት እንዲሰሩ በማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የጥራት ውጤት እየተመዘገበ መሆኑንም ጨምረው አስረድተዋል፡፡
በተቋሙ በማማከር አገልግሎት ትልልቅ ለውጦች በመመዝገባቸው በዓለም ባንክ ፋይናንስ የሚደረጉ ፕሮጀክቶችን በማማከር ተቋሙ እንዲሰራ በመፈቀዱ የቡታጅራ - ወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ፣ የደብረ ታቦር እና የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን የማማከር አገልግሎት በጥራት እየፈፀሙ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
የቦሌ - ለሚ፣ ቂሊንጦ፣ ኮዬ አቦ፣ አዳማ 2 እና የቦሌ አየር ማረፊያ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና የ230 ኪሎ ቮልት እና የ400 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመሮችን በማሳያነት ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 13 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
ከጋሸና - አላማጣ ሲከናወን የቆየው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቀቀ
..........///........
ከጋሸና - አላማጣ ሲከናወን የቆየው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና መጠናቀቁን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የጥገና ኃላፊ አቶ ፀሐይነህ አበበ እንደገለፁት ከጋሸና - አላማጣ የተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ቢሆንም የጥገና ሠራተኞቹ በነበራቸው የሥራ ሞራልና ቁርጠኝነት በአጭር ጊዜ ሊጠናቀቅ ችሏል።
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ መጠገን ጉዳት የደረሰባቸው የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች ጥገና በሚከናወንበት ወቅት ከተሞች ኃይል እንዳይቋረጥባቸው አማራጭ ዕድል እንደሚፈጥር ገልፀዋል።
ከጋሸና እስከ አላማጣ ባለው መስመር 63 ቦታዎች ላይ ኮንዳክተሮች(የኃይል ማስተላለፊያ ሽቦዎች) ተበጣጥሰው የወደቁ ሲሆን በ120 ቦታዎች ላይ ደግሞ ጥይት ቢያርፍባቸውም ተበጣጥሰው ሳይወደቁ በፍተሻ መገኘታቸውን አቶ ፀሐይነህ አስረድተዋል።
በ20 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የነበሩ 484 ኢንሱሌተሮች እንደተሰበሩ የጠቆሙት ኃላፊው በተከናወነው የጥገና ሥራ ሙሉ በሙሉ መቀየራቸውን ተናግረዋል።
አንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች የሚገናኙበት ቦታ ላይ በጥይት በመመታቱ ምክንያት ጉዳት ደርሶበት መጠገኑንም ነው ጨምረው ያስረዱት።
እንደ አቶ ፀሐይነህ ገለፃ ተበጣጥሰው የወደቁት ኮንዳክተሮች የጉዳት መጠናቸው ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት 33 ኪሎሜትር የሚሸፍን የአዲስ ኮንዳክተር ዝርጋታ በሶስቱም ጥምር መስመሮች ላይ ተከናውኗል ሲሉም ጠቁመዋል።
በጥገና ሥራው ላይ ከሰሜን ምስራቅ በተጨማሪ የደቡብ ምዕራብ እና የማዕከላዊ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሠራተኞች መሳተፋቸውን ገልፀዋል።
የጥገና ሠራተኞቹ የነበራቸው ሥራን የመፈፀም ቁርጠኝነትና ማህበረሰቡ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ሲያደረጉት የቆዩት ርብርብ ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 12 ቀን 2015 ዓ.ም
15 545
በሩብ ዓመቱ የ 5 ነጥብ 151 ቢሊዮን ብር ኤሌክትሪክ ሽያጭ ተከናውኗል
………////…………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ለሀገር ውስጥና ለጎረቤት ሀገራት ካቀረበው ኤሌክትሪክ የ5 ነጥብ 122 ቢሊዮን ብር ሽያጭ ማከናወኑን በተቋሙ የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡
በመምሪያው የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ምኒሊክ ጌታሁን እንዳስታወቁት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ4 ነጥብ 158 ቢሊዮን ብር ኃይል ለመሸጥ ታቅዶ የ3 ነጥብ 771 ቢሊዮን ብር ሽያጭ በማከናወን የዕቅዱን 90 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡
ለከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች የ 262 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ኃይል ለማቅረብ ታቅዶ የ 241 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ሽያጭ በማከናወን የዕቅዱ 91 በመቶ መሳካቱን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
ለኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ደግሞ የ 98 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ኃይል በማቅረብ የዕቅዱን ሦስት እጥፍ በላይ ማከናወን እንደተቻለ አብራርተዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ለኢትዮ ቴሌኮም ከተከራየ ኦፕቲካል ፋይበር 22 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር፤ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ለዌብስፕሪክስ አይቲ ሶሉሽን 657 ሺህ 635 ብር ሽያጭ ተከናውኗል፡፡
ለጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት በተደረገ ኤሌክትሪክ የ19 ነጥብ 3 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ መከናወኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ለጂቡቲ ኤሌክትሪክ ኩባንያ 11 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለሱዳን ኤሌክትሪክ ኩባንያ 8 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መሸጡን አስታውቀዋል፡፡
እንደ ስራ አሰኪያጁ ገለፃ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ሶስት ወራት ለሀገርና ውስጥና ለጎረቤት ሀገራት ባቀረበው ኤሌክትሪክ የዕቅዱ አንፃር 91 በመቶ አሳክቷል፡፡
በሩብ ዓመቱ 4 ነጥብ 12 ቢሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማቅረብ ታቅዶ 3 ነጥብ አንድ ቢሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት የቀረበ ሲሆን የኃይል ሽያጩ በኪሎ ዋት ሰዓት 85 በመቶ ተከናውኗል፡፡
ከሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦት አንፃር ሲታይ ከኢትዮ - ጅቡቲ የምድር ባቡር የኃይል አቅርቦት በስተቀር የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎችና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ይወስዳሉ ተብሎ ከታቀደው መጠነኛ መቀነስ ታቶበታል፡፡
ከጎረቤት ሀገራት የኃይል ሽያጭ ደግሞ ወደ ጅቡቲ ኤክስፖርት የተደረገው ኃይል ሲጨምር ሱዳን የታቀደውን ያህል ኃይል አለመውሰዷን መረጃው ያሳያል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 12 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
