EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 530 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 328,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 530 名订阅者。
根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.84%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.05% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 323 次浏览,首日通常累积 2 492 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 530
订阅者
-324 小时
-97 天
+630 天
帖子存档
15 527
ተቋሙ በደም ልገሳ በመሳተፉ እውቅና አገኘ
……………./////…………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደም እጥረት ላለባቸው ወገኖች እንዲውል በማሰብ ባበረከተው አስተዋጽኦ ከብሔራዊ የደም ባንክ እውቅና አገኘ፡፡
ዛሬ ማምሻውን በስካይላይት ሆቴል በተካሄደው የእውቅና ፕሮግራም ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ ሰራተኞቻቸውን በማስተባበር በትግራይ በተካሄደው የህግ ማስከበርና በኮቪድ 19 ወረርሽን የደም እጥረት እንዳያጋጥም ደም የለገሱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ተቋማቱ እውቅናውን ከጤና ሚኒስትር ተቀብለዋል፡፡
በዚህ አጋጣሚ በደም ልገሳ መርሃግብሩ ላይ የተሳተፋችሁትንና ደም ለመለገስ ፈልጋችሁ በተለያዩ ምክንያቶች ሳትለግሱ የቀራችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞችን የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያመሰግናል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
ፕሮጀክቱ ሁለት አምቡላንሶችን በስጦታ እና በግዥ ማሟላቱን ገለፀ
…………../////………….
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ለሚከሰት የኮቪድ 19 እና ሌሎች የጤና ሥጋቶች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያግዙ አንቡላንሶች መሟላታቸውን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለፁ፡፡
ለፕሮጀክቱ አንዱን አምቡላንስ በስጦታ ሌላኛውን አምቡላንስ ደግሞ በግዥ እንዲሟሉ ያደረገው የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር መሆኑን ኢንጂነር ክፍሌ ገልፀዋል፡፡
ይህም በግድቡ ግንባታ ወቅት ለሚያጋጥሙ የኮቪድ 19 እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ሥጋቶች ፈጣን የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት ያስችለናል ብለዋል፡፡
የሁለቱ አምቡላንሶች ዋጋ 2 ነጥብ 63 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጣ በመግለፅ ለተደረገው ድጋፍ የጤና ሚኒስቴርን አመስግነዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 26 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
ለግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኃይል ለማቅረብ እየተሰራ ነው
………….///……………
ለግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለፁት ለምርቃት ዝግጁ ለሆነው ለቡሬ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ሁለት አማራጮች ተይዘው ጥናት ሲካሔድባቸው ቆይተዋል፡፡
ለፓርኩ ኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከባህርዳር ማከፋፈያ ጣቢያ በዳንግላ- ቡሬ በኩል 69 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር እንዲሁም ከደብረ-ማርቆስ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ፓርኩ የሚሄድ 92 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር የመዘርጋት አማራጮች ተለይተው የቴክኒክና የፋይናንስ ትንተና እንደተካሄደባቸው ገልፀዋል፡፡
በተደረገው የቴክኒክና የፋይናንስ ትንተና መሠረት ከባህርዳር-ዳንግላ እንዲመጣ የታሰበው የማስተላለፊያ መስመር ባለ 132 ኪሎ ቮልት በመሆኑ ፓርኩ በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር የኃይል መዋዠቅ ሊያጋጥም እንደሚችል አመልክቷል፡፡
በዚህም ምክንያት ከደብረ-ማርቆስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ጀምሮ እስከ ቡሬ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ድረስ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የማከፋፈያ ጣቢያ ለመገንባት መታቀዱን ነው አቶ ሞገስ ያብራሩት፡፡
ፕሮጀክቱን ለማከናወን ዓለምአቀፍ ጨረታ እንዲወጣ ተደርጓል ያሉት ኃላፊው የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን እና የማከፋፈያ ጣቢያውን ገንብተው ለማስረከብ ብቃት ያላቸው ሥራ ተቋራጮች እስከ የካቲት 05 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ክፍት በተደረገው ጨረታ ላይ እየተሳተፉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ የወሰን ማስከበር ጉዳይ ለፕሮጀክት ግንባታ መጓተት ምክንያት እንዳይሆን ከወዲሁ ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ቀደም ሲል በመንግሥትና የግል አጋርነት ይገነባሉ ተብለው ከተለዩት መካከል አንዱ እንደነበር የጠቆሙት ኃላፊው በተለያዩ ምክንያቶች ዕውን ሊሆን አለመቻሉን ገልፀዋል፡፡
ለቡሬ፣ ለቡልቡላ፣ ለባከርና ለይርጋለም የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኃይል ለማቅረብ አሸናፊው ተቋራጭ ከተለየ በኋላ ፕሮጀክቱን በ12 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 26 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
በሳይት ላይ መስራት ያለበት ሥራ ተሰርቷል - የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ
………../////……….
የአይሻ II የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት ከሚኖሩት 48 የንፋስ ተርባይኖች መካከል የአርባዎቹን ተርባይኖች ተከላና የፍተሻ ሥራ በተያዘው በጀት ዓመት በማጠናቀቅ ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር ለማገናኝት እየሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙሉቀን ተሰማ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ 120 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ከሚተከሉት 48 የንፋስ ተርባይኖች መካከል የ24ቱ ተከላ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡
ሁሉንም ተርባይኖች ለመትከል የሚያስችል የመሠረት ቁፋሮና የኮንክሪት ሙሌት ስራ መጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡
አራት ተርባይኖችን ለመትከልም ንፋስ የሚቀንስበት ወቅት እየተጠበቀ መሆኑንና ተጨማሪ አራት ተርባይኖች ደግሞ ከወደብ ወደ ፕሮጀክት ሳይቱ እየተጓጓዙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
አቶ ሙሉቀን እንደገለፁት በሳይት ላይ መስራት ያለበት ሥራ የተሰራ በመሆኑ ቀሪዎቹን 16 ተርባይኖች በማምረት ተከላውን ለማከናውን አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል፡፡
ከተወሰኑ የማጠናቀቂያ ሥራዎች በቀር የፕሮጀክቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታም ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል ብለዋል፡፡
የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 94 በመቶ፣ የተርባይን ጀነሬተሮች ፍብረካ እና ማጓጓዝ 70 በመቶ፣ የፍተሻና ሙከራ ሥራ 47 በመቶ፣ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ደግሞ 70 ነጥብ 25 በመቶ ደርሷል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 25 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
ከተቋሙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ 33 ነጥብ 1 በመቶዎቹ በራስ አቅም የተገነቡ ናቸው
……………..////……………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችንና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን በራስ ኃይል የመገንባት አቅሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን የሲቪል ስራዎች ቢሮ ገለፀ፡፡
የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃይለ ጊዮርጊስ እንደገለፁት ተቋሙ ከባለ 45 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በራስ ኃይል መገንባት የጀመረው ከ1973 ዓ.ም ጀምሮ ነበር፡፡
ቢሮው በሰው ኃይልና በመሳሪያ ተደራጅቶ በአሁኑ ሰዓት እስከ 400 ኪሎ ቮልት ድረስ ያሉ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አቶ ሰሎሞን ተናግረዋል::
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙት የከፍተኛ መስመሮች ውስጥ 30 ነጥብ 3 በመቶው እንዲሁም ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ 33 ነጥብ 1 በመቶዎቹ በራስ ኃይል ቢሮ የተገነቡ መሆናቸውን አቶ ሰለሞን አስታውቀዋል፡፡
እንደ አቶ ሰሎሞን ገለፃ ቢሮው ከአዳዲስ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በ59 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ እና በ37 ማከፋፈያ ጣቢያዎች አቅም የማሳደግ ስራ አከናውኗል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 24 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
የግድቡ ግንባታ በታቀደለት መርሃግብር እየተከናወነ ነው
...........////.........
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በታቀደለት መርሃግብር እየተከናወነ መሆኑን በስፍራው በመገኘት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም የገመገሙት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚሩስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ አባላት አረጋገጡ፡፡
ሚኒስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታው ሂደት በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ መሆኑን ምልከታ በማድረግ በግንባታው ላይ እየተሳተፉ ካሉት ተቋራጮች፣ አማካሪ ድርጅትና ከባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል ፡፡
የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በዕቅዱ መሰረት እንዲጠናቀቅና አስቀድሞ በሁለት ዩኒቶች ኃይል ለማመንጨት የተያዘው ዕቅድ እንዲሳካ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 23 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ ከሁሉም ህብረተሰብ የሚጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት ነው
……………../////……………
የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች በአረንጓዴ ልማት መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን ለመንከባከብ ውሀ የማጠጣት ተግባር አከናወኑ፡፡
በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ደርባ ፊንጫ በተባለ አካባቢ በ2012 ዓ/ም የክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ለመንከባከብ በወጣው መርሃ ግብር መሠረት ዛሬ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በቦታው ተገኝተው ችግኞቹን ውሃ አጠጥተዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ የቴክኒክ አማካሪ አቶ አንዳርጌ እሸቴ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብም ለጽድቀት መጠኑ ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
ችግኞቹ የተተከሉበት አካባቢ በአባይ ተፋሰስ ሥር የሚገኝ በመሆኑ ከወዲሁ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ መሠራቱ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በደለል እንዳይሞላ ያግዛል ብለዋል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ችግኞች የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከፍ ከማድረጋቸው ባሻገር ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት በመሆኑ የግድቦቻችንን ዕድሜ እንደሚጨምር አማካሪው ገልፀ ዋል፡፡
ችግኞቹም ከእንስሳት ንኪኪ ተጠብቀው በጥሩ የዕድገት ሁኔታ ላይ በመገኘታቸው መደሰታቸውን በመጥቀስ የአካባቢው ህብረተሰብ ላከናወነው ተግባር አመስግነዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት አስተዳድር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ችግኞችን የመንከባከብና ውሀ የማጠጣት ፕሮግራሙ ከየሥራ ክፍሉ የተወጣጡ አመራሮችና ሠራተኞች የተሳተፉበት በመሆኑ ውጤታማ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት ደግሞ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ ከሁሉም ህብረተሰብ የሚጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት ነው፡፡
ሀገሪቱ የጀመረችውን የአረንጓዴ ልማት መርሃ ግብር ለማሳካት ባለፈው ዓመት ክረምት ላይ 5 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 21 ቀን 2013 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
