ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 554 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 397,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 554 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.94% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 003 次浏览,首日通常累积 2 323 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 554
订阅者
+124 小时
+87
+1030
帖子存档
#vacancy የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማ
+1
#vacancy የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ስማችሁ ከላይ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የመሰብሰብያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

በጣቢያው የሚከናወነው የማስፋፊያ ሥራ አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ይረዳል ‎…......///…...... ‌‎በጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ሥራ በኢትዮጵያ  መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚረዳ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌዲዮን አበራ እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ሥራ ተጨማሪ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ለማግኘት የሚረዳ ነው። ‎ ‎የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ ሲጠናቀቅ በአካባቢው ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ  ኤሌክትሪክ እንደሚያቀርብ ነው የተናገሩት።  ‎ ‎በጣቢያው ተጨማሪ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር የመጫን አቅም ያለው ትራንፎርመር ለማስቀመጥ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም ነው የጠቀሱት። ‎ ‎ጣቢያው ከራይቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ኃይል ተቀብሎ በ132 ኪሎ ቮልት ለቀብሪደሃር እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ለጎዴ፣ ሀዳዋይ እና  አዳዲሌይ ከተሞች እና በዙሪያው ለሚገኙ አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ‎ ‎የማስፋፊያ ግንባታው በሪጅኑ አቅም መከናወኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች ልምድና የዕውቀት ሽግግር እንዲያገኙ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አብራርተዋል። ‎ ‎በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ሥራ ሲጠናቀቅ የጎዴ ከተማን የኢንቨስትመንት ፍሰት ከማሳደጉም ባሻገር ለኤሌክትሪክ ፍላጎት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። ‎ ‎እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን የማስፋፊያ ሥራ በአንድ ወር ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ነው።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋማቱ የጡረተኞችን ጥያቄ ለመመለስ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ገለፁ ….....///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከተቋማቱ በጡረታ የተገለሉ የቀድሞ ሠራተኞቻቸውን ጥያቄ ለመመለስ በትብብር እየሰሩ መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ሥራ አስፈጻሚዎች ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቀድሞ ሠራተኞች የተመሠረተው ‎የመብራት ኃይል የጡረተኛ ሠራተኞች ማህበር ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል። ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በጉባዔው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የማህበሩ አባላት በእድሜ ገደብ በጡረታ ቢገለሉም ለተቋማቱ እዚህ ደረጃ መድረስ ከፍተኛ መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር ረጅም ዘመን ያገለገሉ በመሆናቸው መከበር እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ተቋማቱን አገልግለው ጡረታ የወጡ ሠራተኞች መደገፍና መታገዝ አለባቸው በሚል መንፈስ የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ ፋይናንስ የሚፈልጉ ሥራዎችን የሚያከናውኑ መሆናቸውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በጡረተኞቹ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ጡረተኞች እውቀትና ልምዳቸውን በማካፈል ተቋማቱን ለማሳደግ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ ያቀረቡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጡረተኞችን ለመደገፍና ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው በበኩላቸው ጡረተኞቹ ለሁለቱ ተቋማቱ ዋጋ የከፈሉ ጀግኖች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ተቋማቱን ለማሳደግና ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ በመሆኑ ጡረተኞች ይሄን በማገዝ በኩል ሚናቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡ በጡረተኞች የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ ሁለቱ ተቋማት ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን የተናገሩት ኢንጂነር ጌቱ ለትውልድ የሚሻገር አሻራ ጥሎ ለማለፍ ከጡረተኞች ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

ማህበሩ የአባላቱን ጥቅም በዘላቂነት ለማስጠበቅ በትብብር እየሰራ ነው ‎......///....... ‎የመብራት ኃይል ጡረተኞች ማህበር የአባላቱን ጥቅም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሁሉ በትብብር እየሰራ መሆኑን የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ተሾመ መርዕድ ገለጹ። ‎ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቀድሞ ሠራተኞች የተመሠረተው ‎የመብራት ኃይል የጡረተኛ ሠራተኞች ማህበር ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል። ‎ ‎በጉባዔው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ተሾመ መርዕድ ‌‎እንደ አቻ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጡረታ የወጡ የቀድሞ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞችን የሚወክል ማህበር ባለመኖሩ እርስ በእርስ ለመገናኘት እንዲሁም ጡረተኞቹ ከድርጅቶቹ ማግኘት የሚገባቸውን ድጋፍ ለማግኘትና አብሮ ለመስራት ክፍተት ተፈጥሮ መቆየቱን አስታውሰዋል። የመብራት ኃይል ጡረተኞች ማህበር በጡረተኛ ሠራተኞች ላይ የሚስተዋለውን‎ ችግር ለመቅረፍ እና ተበታትኖ የሚገኘውን የቀድሞ ሠራተኛ በማሰባሰብ ለመብቱና ለጥቅሙ እንዲታገል እንዲሁም እርስ በእርሱ እንዲረዳዳ ለማድረግ መመስረቱን ጠቅሰዋል። አባላቱ ከወጣትነት ጊዜያቸው ጀምሮ እወቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ልምዳቸውን ሳይቆጥቡ በማገልገል ለሀገርና ለማህበረሰቡ እድገት የጀርባ አጥንት የሆኑ ሁለቱ ድርጅቶችን አሁን ላሉበት ደረጃ ማድረሳቸውን አብራርተዋል። ‎ማህበሩ አንድ የተሟላ የጡረተኞች ማዕከል መገንባት የሚያስችል ፕሮጀክት በመንደፍ የፕሮጀክት ፕሮፖዛሉን ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆኑን የገለጹት አቶ ተሾመ ነጻ የህክምናና መብራት ጨምሮ ሌሎች በአባላቱ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለማስመለስ ከሁለቱ ተቋማትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጎፋ በሚገኘው የድርጅቱ መ/ቤት ለማህበሩ ቢሮና ቁሳቁስ ማመቻቸቱም ተናግረዋል። ‎የማህበሩን ሂሳብ ለአሰራርና ለቁጥር አመች በሆነ መንገድ ለመስራት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ለአቢሲኒያ ባንክ በጻፈው ደብዳቤ የማህበሩ አካውንት ተከፍቶ በሥራ ላይ እንደሚገኝም አብራርተዋል። በዕለቱ የተሻሻለው የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብን ጨምሮ የፋይናንስና የኦዲት ሪፖርት፣ የፋይናንስና የውስጥ ኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የወርኃዊ ክፍያ ተመን እና የሥራ አስፈጻሚ አባላት የትራንስፖርት አበል ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

“የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ማስጠበቅ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ ነው” ‎ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ………///……… የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ማስጠበቅ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ በመሆኑ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ፡፡ ‎በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ለተመለመሉ የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ አባላት ሲሰጥ የቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጨምሮ የመከላከያ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተጠናቋል፡፡ ‎ በሥልጠናው ማጠናቀቂያው ላይ ለሠልጣኝ አባላቱ የሥራ መመሪያ የሰጡት ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርስ ጉዳት የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማስተጓጎል በሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ሠላም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ተናግረዋል፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ሆነው ከ30 ዓመት በላይ ሀገርን ያገለገሉት ሠልጣኝ አባላቱ ወደ ተቋሙ መምጣት የኃይል መሰረተ ልማትን ደህንነት ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ተጨማሪ ጉልበት የሚሰጥ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ከፍተኛ የኃይል መሰረተ ልማት ሥርቆት የሚስተዋሉባቸው አካባቢዎች በዘርፍ ተለይተው የከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮች ጥበቃ መጀመሩን ጠቁመዋል። የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ማስጠበቅ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ በመሆኑ ሠልጣኝ አባላቱ በሕብረተሰቡና በተቋሙ መካከል ድልድይ ሆነው በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ለሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥቶ ለማሟላት ጥረት እንደሚደረግ የተናገሩት ኢንጂነር አሸብር ተቋሙ በኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት ጥበቃ ላይ ለውጥ ለማምጣት የመከላከያ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የመከላከያ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው ሠልጣኝ አባላቱ በተመደቡባቸው ሪጅኖች በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን በመለየት፣ ትክክለኛ መረጃ በማሰባሰብና ሕብረተሰቡንና መንግስታዊ መዋቅሩን በማሳተፍ በዕቅድ ላይ ተመስርቶ የቅድመ መከላከል ሥራዎችን ማከናወን ይገባል ብለዋል። የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ማስጠበቅ የተቋማቱ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነት መሆኑን የጠቆሙት የሥራ ኃላፊዎቹ በቀጣይም በመረጃ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታና መሰል ሥራዎች ከተቋሙ ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ፣ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና በመከላከያ ሚኒስቴር ሲሰጥ የቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በተቋሙ ርዕይና ተልዕኮ፣ አሰራርና አደረጃጀት እና በቁልፍ ተቋማት መሰረተ ልማት ጥበቃ እንዲሁም በደህንነት ስጋት የመረጃ አሰባሰብ ዘዴ ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ነበር።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በከርሰምድር እንፋሎት ኃይል ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ይገባል .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከርሰምድር እንፋሎት ኃይልን በአግባቡ ለመጠቀም በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት እንደሚገባ በተቋሙ የጂኦተርማል ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡ ተቋሙ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በተከፈተው 4ኛው ዓመታዊ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (MINTEX Ethiopia 2025) ላይ በከርሰምድር እንፋሎት የኃይል ልማት ላይ እያከናወናቸው የሚገኙ ሥራዎችን እና የዘርፉን የወደፊት ዕቅዶች የሚያሳዩ መረጃዎችን ለዕይታ አቅርቧል። የኤግዚቢሽኑ አስጎብኚ የጂኦተርማል ከፍተኛ ባለሙያው አቶ ሰለሞን ከበደ እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ስብጥርን ለማሳደግና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት የሚያስችሉ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ በከርሰምድር እንፋሎት ሀብት በተፈጥሮ የታደለች መሆኗን የጠቀሱት ባለሙያው ይሁን እንጂ ዘርፉ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እና የሰለጠነ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ እምቅ ሀብቱን በአግባቡ መጠቀም እንዳልተቻለ ገልፀዋል፡፡ በዚህም ተቋሙ የከርሰምድር እንፋሎት ኃይል ግንባታ ዘርፍን ለማሳደግ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል፡፡ እንደ አቶ ሰለሞን ገለፃ ኤክስፖው የከርሰምድር እንፋሎት በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ ያለውን ድርሻ እና ፋይዳ ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ይረዳል፡፡ በማዕድን ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት እና በማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት በጋራ የተዘጋጀው 4ኛው ዓመታዊ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ እስከ ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለጎብኝዎች ክፍት መደረጉም ታውቋል። ኤክስፖውን የተቋሙ  ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች ጎብኝተውታል።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

Geothermal Solutions Expo – Mining Sector Growth Watch the TikTok video for more info 👇 https://www.tiktok.com/@ethio_power/video/7572543701210172684 EEP continues advancing clean and reliable energy for national development. The Geothermal initiative is creating sustainable power solutions that support Ethiopia’s mining sector and strengthen green economic growth. 💡 "Clean Energy for a Better Life!" #EEP #GeothermalEnergy #Ethiopia #MiningSector #CleanEnergy #SustainablePower #RenewableEnergy Official EEP Links 📌Facebook: https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌Telegram: https://t.me/EEPCommuication 📌Twitter: https://twitter.com/EEPethiopia 📌 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power-የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኃይል 📌YouTube: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌TikTok: https://tiktok.com/@ethio_power 📌 Website: https://www.eep.com.et

የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ከአደጋ ለመከላከል አባላቱ በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ ……///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ አባላት  የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ከስርቆት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ፡፡ አገልግሎቱ በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ለተመለመሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በቁልፍ ተቋማት መሰረተ ልማት ጥበቃ ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን አባላቱ ስለቁልፍ ተቋማት ምንነት፣ ሀገራዊ ፋይዳ፣ ደህንነት እና ስጋቶች በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ደህንነት እንዲያስጠብቁ ለማስቻል ያለመ ነው፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በአዋጅ ቁጥር 1278/2014 መሰረት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ቁልፍ የመሰረተ ልማቶችን ደህንነት ደረጃ(standard) የማውጣት እንዲሁም በደህንነት ጥበቃ ላይ ለሚሰማሩ ባለሙያዎች ሥልጠና የመስጠት ተልዕኮ እንዳለውም ተገልጿል፡፡ በዚህም ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ የሆነውን የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ደህንነት ለማረጋገጥ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በየ24 ሰዓቱ መረጃ በመለዋወጥ እና ጥናቶችን በማድረግ በትብብር እየሰራ መሆኑም ተብራርቷል፡፡ በቁል መሰረተ ልማቶች ጥበቃ ዙሪያ እየተሰጠ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና የሁለቱ ተቋማት ትብብር ማሳያ መሆኑንም ነው የተጠቆመው፡፡ ሠልጣኝ አባላቱ በተመደቡባቸው ሪጅኖች ከሥልጠናው ያገኟቸውን ዕውቀቶች በመተግበር፣ መረጃዎችን በማደራጀት፣ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀድሞ በመለየት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ተጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም አባላቱ ነባራዊ ሁኔታዎችን እና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ከግምት በማስገባት የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ከአደጋ የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት ተግባራትን ማከናወን እንዳለባቸው ተብራርቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በቀጣይም የ24 ሰዓት የመረጃ ልውውጡን በማጠናከር እና በኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት ላይ ያሉ ስጋቶችን በየጊዜው በመተንተን ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ሥራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አረጋግጧል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

በ2022 ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ብቻ ከ2.7 ቴራ ዋት ስዓት በላይ ኃይል ያስፈልጋል …....///.....… በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቁጥር ተከትሎ የተሽከርካሪዎች የኃይል ፍላጎት በ2017 ዓ.ም ከነበረበት 489 ሜጋ ዋት በ2022 ዓ.ም ወደ 2.7 ቴራ ዋት እንደሚያድግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያስጠናው አንድ ጥናት አመለከተ፡፡  ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ተፅዕኖ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግሪድ ሲስተም  ላይ በሚል ርዕስ ያስጠናውን ጥናት ይፋ አድርጓል፡፡  ጥናቱ የተሸከርካሪዎቹ የኃይል ፍላጎት፣ መሰረተ ልማቶች ላይ ያላቸው ተጽዕኖ፣ የቮልቴጅ መረጋጋትን ከማስተካከል አኳያ እና እነዚህን ተፅኖችን ለመቋቋም የሚያስችሉ የመፍትሄ ሀሳቦችን በዝርዝር ዳሷል፡፡ የኢፊዲሪ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ያዘጋጀውን ስትራቴጂክ እቅድ መሰረት በማድረግ የተከናወነው ጥናቱ ከ2017-2022 ዓ.ም ያለውን ጊዜ የኃይል አጠቃቀም አዝማሚያ  የሚዳስስ እንደሆነ የጥናቱ ቡድን መሪ ኢንጅነር ሀብታሙ አበበ ገልፀዋል፡፡ እንደ ኢንጅነሩ ገለፃ በዚህ ጥናት የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች በዓይነት እና በፍጆታ መጠናቸውን መለየታቸውን አመልክተው ባሶች በኃይል ፍጆታ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ ይህን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ የሚያስችል አቅም መገንባቱን  የገለፁት ኢንጂነር ሀብታሙ የብሔራዊ ኃይል ቋቱ ላይ የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከወዲሁ መስራት እንደሚገባዉ ጠቁመዋል፡፡   ጥናቱ በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል፣ በፖሊሲ ፕሮሰስ እና ለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ፣ በፕሮጀክት ቢሮ እንዲሁም ከምርምር እና ልማት ክፍል በተውጣጡ የተቋሙ ባለሙያዎች የተሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በመድረኩ የተገኙት የኢትዮ-ፓዎር አካዳሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ ውስጣዊ ትብብርን በማጠናር የተቋሙን ያልተዳሰሱ ገፅታዎች በጥናት ማስተዋወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

በቅንጅት በመስራት የዘርፉን የፋይናንስና ግዥ ሥራዎች ለማሻሻል እየሰራሁ ነው -ዘርፉ ……..///…….. ቅንጅታዊ አሰራሮችን በመዘርጋት የፋይናንስ እና ግዢ ሥራዎችን ለማሻሻል እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ የፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ግምገማ አካሂደዋል፡፡  የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ እንደገለፁት የግምገማ መድረኩ በዘርፉ የፋይናንስ እና ግዥ ሥራዎች ላይ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። መምሪያው ከግዥና ፋይናንስ ጋር የተያያዙ አሰራሮችን በማዘመን የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በማሻሻል በኩል ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም መምሪያው የዘርፉን ውጤታማነት ከፍ የሚያደርጉ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው መሰል የግምገማ መድረኮች መዘጋጀታቸው በቀጣይ አመራሩ እና ሠራተኛው ለተሻለ የሥራ አፈፃፀም እንዲነሳሱ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቶችን የፋይናንስ ወጪና ገቢ ክትትል ማድረግ፣ በወቅቱ ለሚቀርቡ የግዥ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት፣ ለሠራተኞች የሳፕ የአሰራር ሥርዓት ሥልጠና መስጠት መቻሉ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖች መሆናቸውም በግምገማ መድረኩ ላይ ተነስቷል፡፡ መምሪያው በሩብ ዓመቱ የ2017 እና 2018 በጀት ዓመት የሒሳብ ማስታረቅ ሥራ በሳፕ የአሰራር ሥርዓት መሰረት ማከናወን መቻሉ በመድረኩ ተጠቅሷል፡፡ የዘርፉ የ2017 የግማሽ በጀት ዓመት የሒሳብ ሥራዎች በውጭ ኦዲተር የማስመርመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው የተገለፀው፡፡ በዕቅድ አፈፃፀሙ ላይ በተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3