EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 567 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 356,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 567 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 24,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.83% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 035 次浏览,首日通常累积 2 465 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 567
订阅者
+1924 小时
+197 天
+2430 天
帖子存档
15 567
ሰባት የመንግሥት ተቋማት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ
........///.......
በገንዘብ ሚኒስቴር እና በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ስር የሚገኙ ከሰባት ተቋማት የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ።
በጉብኝቱ ወቅት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉትን ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ለሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ችሏል።
ተቋሙ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የኃይል አስተላላፊ ለመባል በቅቷል ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በቀጣይም ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ተቋሙ በራሱ አቅም በጎረቤት ሀገራት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዙሪያ የማማከር እና የመገንባት ዕቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ማመንጨት አቅም ታሳቢ ያደረገ ዘመናዊ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ እንደሆነም ነው የገለፁት።
ተቋሙ ከስያሜ ጀምሮ በርካታ ተግዳሮቶች እየገጠሙት እንደሚገኙ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከካሳ ክፍያ እና ከኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ጋር ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚመለከታቸው ሁሉ እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ለጎብኚዎች ስለ ተቋሙ ወቅታዊ አቋም ገለፃ አድርገዋል።
አቶ አንዱዓለም በገለፃው ላይ እንደተናገሩት ባለፉት ስድስት ዓመታት የሀገሪቱ የኢነርጂ ምርት በአማካይ የ8 በመቶ እንዲሁም የተቋሙ ዓመታዊ ገቢ በ34 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
በቀጣይ ዓመታት 825 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ስድስት የንፋስ እንዲሁም 775 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አምስት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ዕቅድ መያዙን አቶ አንዱዓለም ገልፀዋል።
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በቀጣይ ሦስት ዓመታት 1 ሺህ 038 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና 27 አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት በ60 ኪሎሜትር ርቀት የኃይል አቅርቦት ተደራሽነትን ወደ 91 በመቶ ለማሳደግ ይሰራል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ዓመታት የአፍሪካ የኃይል የልህቀት ማዕከል ለመገንባት ማቀዱንም ነው የጠቀሱት።
የገንዘብ ሚኒስትር ልዩ አማካሪና የጉብኝቱ አስተባባሪ አቶ ሐጂ ኢብሳ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኛው ምቹ የሥራ ቦታ ለመፍጠር ያከናወናቸው ሥራዎች የሚደነቁ በመሆናቸው ሌሎች ተቋማት ከዚህ ልምድ መውሰድ እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
ተቋሙ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ሥራዎችና በስትራቴጂክ ዕቅዶቹ ዙሪያ ስለተደረገላቸው ገለፃም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጉብኝቱ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን፣ ከኢትዮጵያ ፖስታ ድርጅት፣ ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር፣ ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕና ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የተውጣጡ ከ400 በላይ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
ሠራተኛው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ
……...///……..
የመንግስትን ፖሊስ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር አሸበር ባልቻ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በኮቪድ፣ በዓለም የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በእርስ በእርስ ግጭት እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ ሆና ዕድገት አስመዝግባለች፡፡
የተመበዘገበው ዕድገት ትሩፋቶቸና የመጣው ለውጥ ሀገራችን የገጠማትን ተግዳሮቶች አልፋ መሄድ እንደምትችል ከማሳየት ባለፈ ለውጡ በተቋሙ በግልጽ የሚታይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች ከጨለምተኛ አመለካከት ወጥተው ትክክለኛ መረጃ በመያዝ ለአላስፈላጊ ነጣለ ትርክት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከለውጡ በፊት ምን ደረጃ ላይ እንደነበር የሚዘጋ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከለውጡ በኋላ በምን ያህል መስዋትነት እና ቁርጠኛ አመራር አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ይሁንና ተቋሙ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና መዘግየት የሚያጋጥሙትን ከፍተቶች ለማስወገድ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡
ስለሆነም ሠራተኞች የሚመለከቷቸውን የብልሹ አሰራር ክፍተቶች የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በመያዝ ድርጊቱን እንዲዋጉ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል፡፡
በውይይቱ ከሠራተኞች የተነሱትን የተለያዩ ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ካካሄዱት ውይይት ጎን ለጎን የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡
የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡
መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ንግር ያደረጉት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም በፋብሪካ የማይመረት በመሆኑ በደም አጦት ማንም ሰው ህይወቱን ሊያጣ አይገባም፡፡
ሠራተኛው የወገን ደራሽነቱን ደም በመለገስ በተግባር ማሳየት እንደሚገባው የተናገሩት ባለሙያዋ ደም በለገስ ከኮሌትሮል፣ ከደም ውስጥ የብረት መጠን ክምችት፣ ከካንሰርና ከሌሎች በሽታዎች የመታደግ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡
ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም የሚተካ በመሆኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት ልናድንበት ይገባል ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
በሀሳብ ልዕልና እንጂ በጠመንጃ ሀገረ መንግስት አይነባም
………..///………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ወይይት አካሂደዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የተቋሙ ሠራተኞች የኑሮ ውድነትን፣ ተንቀሳቅሶ ለመስራት ያለውን የጸጥታ ችግር እና የሠራተኛውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት እየተሰሩ ካሉ ሥራዎች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡
ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት የኑሮ ውድነቱ ከዓለም አቀፋዊ የዋጋ ግሽበት ጋር የሚያያዝ በመሆኑ መንግስት ችግሩን ለመቅረፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ጨምሮ በልማት ትሩፋት ሥራዎች ገበያውን የማረጋገት ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡
ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ለተነሱት ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር ባልቻ በሰጡት ምላሽ አብዛኛዎቹ የፀጥታ መደፍረስ ችግሮች ከነጠላ ትርክቶች የሚነሱ በመሆኑ ለሀሳብ ልዕልና ቦታ አልተሰጠውም ነበር፡፡
በመሆኑም መንግስት የዜጎችን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ሀገረዊ ምክከር ኮሚሽን ከማቋቋም አንስቶ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ ልዕልና እንጂ ላይ የተመሰረተ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የተያዩ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ለተፈጠሩት የጸጥታ ቸግሮች መፍትሄ ለማስገኘት የሚደረገው ጥረት የሁሉንም ተሳትፎ የሚፈልግ በመሆኑ ሁሉም ከመንግስት ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡
የመኖሪያ ቤት ችግርን በተመለከተ ዋና ሥራ አስፈፃሚው በሰጡት ምላሽ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር የተጀመሩ ሥራዎች እንዳሉ በመጠቆም ጥያቄው መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስ ከሚመለከተው አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
ሠራተኛው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ
……...///……..
የመንግስትን ፖሊስ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር አሸበር ባልቻ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በኮቪድ፣ በዓለም የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በእርስ በእርስ ግጭት እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ ሆና ዕድገት አስመዝግባለች፡፡
የተመበዘገበው ዕድገት ትሩፋቶቸና የመጣው ለውጥ ሀገራችን የገጠማትን ተግዳሮቶች አልፋ መሄድ እንደምትችል ከማሳየት ባለፈ ለውጡ በተቋሙ በግልጽ የሚታይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች ከጨለምተኛ አመለካከት ወጥተው ትክክለኛ መረጃ በመያዝ ለአላስፈላጊ ነጣለ ትርክት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከለውጡ በፊት ምን ደረጃ ላይ እንደነበር የሚዘጋ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከለውጡ በኋላ በምን ያህል መስዋትነት እና ቁርጠኛ አመራር አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ይሁንና ተቋሙ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና መዘግየት የሚያጋጥሙትን ከፍተቶች ለማስወገድ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡
ስለሆነም ሠራተኞች የሚመለከቷቸውን የብልሹ አሰራር ክፍተቶች የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በመያዝ ድርጊቱን እንዲዋጉ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል፡፡
በውይይቱ ከሠራተኞች የተነሱትን የተለያዩ ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ካካሄዱት ውይይት ጎን ለጎን የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡
የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡
መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ንግር ያደረጉት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም በፋብሪካ የማይመረት በመሆኑ በደም አጦት ማንም ሰው ህይወቱን ሊያጣ አይገባም፡፡
ሠራተኛው የወገን ደራሽነቱን ደም በመለገስ በተግባር ማሳየት እንደሚገባው የተናገሩት ባለሙያዋ ደም በለገስ ከኮሌትሮል፣ ከደም ውስጥ የብረት መጠን ክምችት፣ ከካንሰርና ከሌሎች በሽታዎች የመታደግ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡
ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም የሚተካ በመሆኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት ልናድንበት ይገባል ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
የተቋሙ ሠራተኞች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው
........///.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ወይይት ማካሄድ ጀምረዋል።
የውይይት መድረኩን የከፈቱት የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አሰፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ የተቋሙ ሠራተኞች መንግስት በሚሰራቸው ሥራዎች ላይ ግልፅ መረጃ ሊኖራቸው ይገባል።
በመድረኩ ላይ የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት በሚል በመንግስት የተዘጋጀው ሰነድ በንባብ ቀርቧል።
በሰነዱ ላይ የሚደረገው ውይይት እንደቀጠለ ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወጣ ወጣት በተአምር ህይወቱ ተርፏል
…….///…….
በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የወጣ ወጣት ኃይል እንዲቋረጥ ማድረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡
በዘርፉ የደቡብ ሁለት ሪጅን እንደገለፀው ወጣቱ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሳውላ በሚሄደው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ወጥቶ አልወርድም በማለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ጎፋ ዞን፣ አሪ ዞን፣ ባስኬቶ ዞን እና ኦሞ ዞን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ጋሞ ዞን በከፊል ከሦስት ሰዓታት በላይ ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡
በምን ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ እንደወጣ ያልታወቀው ወጣት በአካባቢው ሽማግሌዎችና የመስተዳድር አካላት ቢለመንም ለመውረድ ግን አስቸግሮ እንደነበር መምሪያው ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች ኃይል በማቋረጥ ወጣቱ ሳይጎዳ በገመድ አስረው በማውረድ በተአምር ህይወቱን ታድገዋል፡፡
የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያስተላልፉት የቮልቴጅ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መምሪያው አሳስቧል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያ ላይ የተከናወነው ጥገና ተጠናቋል
…….///………
በአዲስ አበባ ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያ ችግር አጋጥሞት የነበረውን የከረንት ትራንስፎርመር መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታውቋል፡፡
ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት ስለጠበቁ መምሪያው አመስግኗል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
በሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸው የተቋረጠው ኃይል ተመልሷል
.......///.......
ከድሬዳዋ 3 ወደ ሀረር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የገጠመው ችግር ተጠግኖ አካባቢዎቹ ዳግም ኃይል ማግኘታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታውቋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም
15 567
ቡድኑ ሁለተኛ ሽንፈት አስተናግዷል
........///......
የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ከልደታ ክፍለ ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ አንድ ለባዶ በሆነ ውጤት ተረቷል።
ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በተከናወነው ጨዋታ ሳሮን ሰመረ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል ለክለቧ አስቆጥራለች።
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኳስ ቁጥጥር የበላይነት ወስዶ ቢጫወትም ጎልን ከመረብ ማዋሀድ ሳይችል ቀርቷል።
በአንፃሩ የመከላከል አጨዋወት ስልት የተከተሉት ልደታዎች ያገኟትን ብቸኛ የግብ አጋጣሚ ወደ ጎል በመቀየር ሶስት ነጥብ ማግኘት ችለዋል።
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ4ኛ ሳምንት መርሃ ግብር በመጪው ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀምበርቾ ክለብ ጋር የሚጫወት ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
