ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 567 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 356 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 162 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 567 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 24، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 19، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.91‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.83‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 035 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 465 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 25 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 567
المشتركون
+1924 ساعات
+197 أيام
+2430 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+4

ሰባት የመንግሥት ተቋማት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ ........///....... በገንዘብ ሚኒስቴር እና በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ስር የሚገኙ ከሰባት ተቋማት የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ። በጉብኝቱ ወቅት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉትን ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ለሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ችሏል። ተቋሙ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የኃይል አስተላላፊ ለመባል በቅቷል ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በቀጣይም ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ተቋሙ በራሱ አቅም በጎረቤት ሀገራት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዙሪያ የማማከር እና የመገንባት ዕቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ማመንጨት አቅም ታሳቢ ያደረገ ዘመናዊ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ እንደሆነም ነው የገለፁት። ተቋሙ ከስያሜ ጀምሮ በርካታ ተግዳሮቶች እየገጠሙት እንደሚገኙ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከካሳ ክፍያ እና ከኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ጋር ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚመለከታቸው ሁሉ እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ለጎብኚዎች ስለ ተቋሙ ወቅታዊ አቋም ገለፃ አድርገዋል። አቶ አንዱዓለም በገለፃው ላይ እንደተናገሩት ባለፉት ስድስት ዓመታት የሀገሪቱ የኢነርጂ ምርት በአማካይ የ8 በመቶ  እንዲሁም የተቋሙ ዓመታዊ ገቢ በ34 በመቶ  ዕድገት አሳይቷል። በቀጣይ ዓመታት 825 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ስድስት የንፋስ እንዲሁም 775 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አምስት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ዕቅድ መያዙን አቶ አንዱዓለም ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በቀጣይ ሦስት ዓመታት 1 ሺህ 038 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና 27 አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት በ60 ኪሎሜትር ርቀት የኃይል አቅርቦት ተደራሽነትን ወደ 91 በመቶ ለማሳደግ ይሰራል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ዓመታት የአፍሪካ የኃይል የልህቀት ማዕከል ለመገንባት ማቀዱንም ነው የጠቀሱት። የገንዘብ ሚኒስትር ልዩ አማካሪና የጉብኝቱ አስተባባሪ አቶ ሐጂ ኢብሳ በበኩላቸው  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኛው ምቹ የሥራ ቦታ ለመፍጠር ያከናወናቸው ሥራዎች የሚደነቁ በመሆናቸው ሌሎች ተቋማት ከዚህ ልምድ መውሰድ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ተቋሙ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ሥራዎችና በስትራቴጂክ ዕቅዶቹ ዙሪያ ስለተደረገላቸው ገለፃም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በጉብኝቱ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን፣ ከኢትዮጵያ ፖስታ ድርጅት፣ ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር፣ ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕና ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የተውጣጡ ከ400 በላይ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

ሠራተኛው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ ……...///…….. የመንግስትን ፖሊስ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር አሸበር ባልቻ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በኮቪድ፣ በዓለም የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በእርስ በእርስ ግጭት እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ ሆና ዕድገት አስመዝግባለች፡፡ የተመበዘገበው ዕድገት ትሩፋቶቸና የመጣው ለውጥ ሀገራችን የገጠማትን ተግዳሮቶች አልፋ መሄድ እንደምትችል ከማሳየት ባለፈ ለውጡ በተቋሙ በግልጽ የሚታይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ከጨለምተኛ አመለካከት ወጥተው ትክክለኛ መረጃ በመያዝ ለአላስፈላጊ ነጣለ ትርክት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከለውጡ በፊት ምን ደረጃ ላይ እንደነበር የሚዘጋ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከለውጡ በኋላ በምን ያህል መስዋትነት እና ቁርጠኛ አመራር አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና ተቋሙ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና መዘግየት የሚያጋጥሙትን ከፍተቶች ለማስወገድ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ሠራተኞች የሚመለከቷቸውን የብልሹ አሰራር ክፍተቶች የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በመያዝ ድርጊቱን እንዲዋጉ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል፡፡ በውይይቱ ከሠራተኞች የተነሱትን የተለያዩ ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ካካሄዱት ውይይት ጎን ለጎን የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ንግር ያደረጉት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም በፋብሪካ የማይመረት በመሆኑ በደም አጦት ማንም ሰው ህይወቱን ሊያጣ አይገባም፡፡ ሠራተኛው የወገን ደራሽነቱን ደም በመለገስ በተግባር ማሳየት እንደሚገባው የተናገሩት ባለሙያዋ ደም በለገስ ከኮሌትሮል፣ ከደም ውስጥ የብረት መጠን ክምችት፣ ከካንሰርና ከሌሎች በሽታዎች የመታደግ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡ ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም የሚተካ በመሆኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት ልናድንበት ይገባል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

በሀሳብ ልዕልና እንጂ በጠመንጃ ሀገረ መንግስት አይነባም ………..///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ወይይት አካሂደዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የተቋሙ ሠራተኞች የኑሮ ውድነትን፣ ተንቀሳቅሶ ለመስራት ያለውን የጸጥታ ችግር እና የሠራተኛውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት እየተሰሩ ካሉ ሥራዎች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡ ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት የኑሮ ውድነቱ ከዓለም አቀፋዊ የዋጋ ግሽበት ጋር የሚያያዝ በመሆኑ መንግስት ችግሩን ለመቅረፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ጨምሮ በልማት ትሩፋት ሥራዎች ገበያውን የማረጋገት ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ለተነሱት ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር ባልቻ በሰጡት ምላሽ አብዛኛዎቹ የፀጥታ መደፍረስ ችግሮች ከነጠላ ትርክቶች የሚነሱ በመሆኑ ለሀሳብ ልዕልና ቦታ አልተሰጠውም ነበር፡፡ በመሆኑም መንግስት የዜጎችን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ሀገረዊ ምክከር ኮሚሽን ከማቋቋም አንስቶ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ ልዕልና እንጂ ላይ የተመሰረተ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የተያዩ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ለተፈጠሩት የጸጥታ ቸግሮች መፍትሄ ለማስገኘት የሚደረገው ጥረት የሁሉንም ተሳትፎ የሚፈልግ በመሆኑ ሁሉም ከመንግስት ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ችግርን በተመለከተ ዋና ሥራ አስፈፃሚው በሰጡት ምላሽ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር የተጀመሩ ሥራዎች እንዳሉ በመጠቆም ጥያቄው መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስ ከሚመለከተው አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

ሠራተኛው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ ……...///…….. የመንግስትን ፖሊስ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር አሸበር ባልቻ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በኮቪድ፣ በዓለም የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በእርስ በእርስ ግጭት እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ ሆና ዕድገት አስመዝግባለች፡፡ የተመበዘገበው ዕድገት ትሩፋቶቸና የመጣው ለውጥ ሀገራችን የገጠማትን ተግዳሮቶች አልፋ መሄድ እንደምትችል ከማሳየት ባለፈ ለውጡ በተቋሙ በግልጽ የሚታይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ከጨለምተኛ አመለካከት ወጥተው ትክክለኛ መረጃ በመያዝ ለአላስፈላጊ ነጣለ ትርክት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከለውጡ በፊት ምን ደረጃ ላይ እንደነበር የሚዘጋ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከለውጡ በኋላ በምን ያህል መስዋትነት እና ቁርጠኛ አመራር አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና ተቋሙ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና መዘግየት የሚያጋጥሙትን ከፍተቶች ለማስወገድ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ሠራተኞች የሚመለከቷቸውን የብልሹ አሰራር ክፍተቶች የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በመያዝ ድርጊቱን እንዲዋጉ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል፡፡ በውይይቱ ከሠራተኞች የተነሱትን የተለያዩ ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ካካሄዱት ውይይት ጎን ለጎን የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ንግር ያደረጉት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም በፋብሪካ የማይመረት በመሆኑ በደም አጦት ማንም ሰው ህይወቱን ሊያጣ አይገባም፡፡ ሠራተኛው የወገን ደራሽነቱን ደም በመለገስ በተግባር ማሳየት እንደሚገባው የተናገሩት ባለሙያዋ ደም በለገስ ከኮሌትሮል፣ ከደም ውስጥ የብረት መጠን ክምችት፣ ከካንሰርና ከሌሎች በሽታዎች የመታደግ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡ ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም የሚተካ በመሆኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት ልናድንበት ይገባል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የተቋሙ ሠራተኞች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው ........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ወይይት ማካሄድ ጀምረዋል። የውይይት መድረኩን የከፈቱት የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አሰፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ የተቋሙ ሠራተኞች መንግስት በሚሰራቸው ሥራዎች ላይ ግልፅ መረጃ ሊኖራቸው ይገባል። በመድረኩ ላይ የህልም ጉልበት ለእምርታዊ  እድገት በሚል በመንግስት የተዘጋጀው ሰነድ በንባብ ቀርቧል። በሰነዱ ላይ የሚደረገው ውይይት እንደቀጠለ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወጣ ወጣት በተአምር ህይወቱ ተርፏል …….///……. በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የወጣ ወጣት ኃይል እንዲቋረጥ ማድረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡ በዘርፉ የደቡብ ሁለት ሪጅን እንደገለፀው ወጣቱ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሳውላ በሚሄደው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ወጥቶ አልወርድም በማለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ጎፋ ዞን፣ አሪ ዞን፣ ባስኬቶ ዞን እና ኦሞ ዞን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ጋሞ ዞን በከፊል ከሦስት ሰዓታት በላይ ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ በምን ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ እንደወጣ ያልታወቀው ወጣት በአካባቢው ሽማግሌዎችና የመስተዳድር አካላት ቢለመንም ለመውረድ ግን አስቸግሮ እንደነበር መምሪያው ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች ኃይል በማቋረጥ ወጣቱ ሳይጎዳ በገመድ አስረው በማውረድ በተአምር ህይወቱን ታድገዋል፡፡ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያስተላልፉት የቮልቴጅ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መምሪያው አሳስቧል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያ ላይ የተከናወነው ጥገና ተጠናቋል …….///……… በአዲስ አበባ ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያ ችግር አጋጥሞት የነበረውን የከረንት ትራንስፎርመር መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታውቋል፡፡ ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት ስለጠበቁ መምሪያው አመስግኗል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸው የተቋረጠው ኃይል ተመልሷል .......///....... ከድሬዳዋ 3 ወደ ሀረር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የገጠመው
በሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸው የተቋረጠው ኃይል ተመልሷል .......///....... ከድሬዳዋ 3 ወደ ሀረር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የገጠመው ችግር ተጠግኖ አካባቢዎቹ ዳግም ኃይል ማግኘታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታውቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

ቡድኑ ሁለተኛ ሽንፈት አስተናግዷል ........///...... የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ከልደታ ክፍለ ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ አንድ ለባዶ በሆነ ውጤት ተረቷል። ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በተከናወነው ጨዋታ ሳሮን ሰመረ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል ለክለቧ አስቆጥራለች። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኳስ ቁጥጥር የበላይነት ወስዶ ቢጫወትም ጎልን ከመረብ ማዋሀድ ሳይችል ቀርቷል። በአንፃሩ የመከላከል አጨዋወት ስልት የተከተሉት ልደታዎች ያገኟትን ብቸኛ የግብ አጋጣሚ ወደ ጎል በመቀየር  ሶስት ነጥብ ማግኘት ችለዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ4ኛ ሳምንት መርሃ ግብር በመጪው ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀምበርቾ  ክለብ ጋር የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6