EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 572 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 356,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 572 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 24,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.83% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 035 次浏览,首日通常累积 2 465 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 572
订阅者
+1924 小时
+197 天
+2430 天
帖子存档
15 572
+9
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
---//---
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሹፌር 2ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም. የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መስረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 37 ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ ስለሆነ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 18 ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 እንዲሁም ከተራ ቁጥር 19 እስከ 37 ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የታደሰ መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
በሳፕ የ2ኛው ምዕራፍ ላይ በሚተገበረው የመጋዘን አስተዳደር ሞጁል ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው
---///---
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ሀብት ዕቅድ ሥርዓት (Enterprise Resource Planining) የሚያዘምነው የሳፕ ሁለተኛው ምዕራፍ ትግበራ አካል በሆነው የመጋዘን አስተዳደር ሞጁል ላይ ለመጋዘን አስተዳደር ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠት መጀመሩን የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ አስታወቀ፡፡
በዘርፉ የንብረት፣ ሪስክ እና ኢንሹራንስ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳህሌ ደግፍ እንዳስታወቁት ተቋሙ እየተጠቀመበት ያለው የንብረት አስተዳደር ሞጁል ከዕቃ ግምጃ ቤት አጠቃቀም እስከ "ፕላንት እና ስቶሬጅ ሎኬሽን" ድረስ ብቻ የተገደበ ነበር፡፡
በመጋዘን ውስጥ የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማቀላጠፍ ተጨማሪ ሲስተም መተግበር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የተራዘመ የመጋዘን አስተዳደር (SAP Extended Warehouse Management) ሞጁል ከዕቃ ግምጃ ቤት አጠቃቀም እስከ ፕላንት እና ስቶሬጅ ሎኬሽን ድረስ ብቻ የነበረውን አሰራር እስከ መጋዘን ውስጥ የቦታ ምልከታ ድረስ ለማመላከት ያስችላል ብለዋል፡፡
እንደ አቶ ሳህሌ ገለፃ ሞጁሉ ሲተገበር አንድ ዕቃ የተቀመጠበትን ትክክለኛ ቦታ በመጠቆም የሠራተኛውን ድካም ለመቀነስ፣ ንብረቶች የሚገኙበትን መደርደሪያ እና ልዩ መለያ ቦታን ለማመላከት እንዲሁም ማንኛውም አካል በየትኛውም ቦታ ላይ ሆኖ ማየት ያስችላል፡፡
ይህም ንብረቶች ለታቀደላቸው ዓላማ ብቻ እንዲውሉ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት፡፡
ስልጠናው ነባርና አዲስ የመጋዘን ሠራተኞች የተለየ የመጋዘን ቁጥጥር ወይም ዕቃዎችን ለይቶ የማወቅ ችሎታና ልምድ ሳያስፈልጋቸው ሲስተምን በማወቅና በመጠቀም ሥራውን ለማቀላጠፍ ያስችላል ብለዋል።
ሲስተሙ የካይዘን አሰራር ስታንዳርድን መጠቀም ስለሚያስገድድ ከካይዘን አሰራር ጋር ተያይዘው የሚመጡ ለውጦችን መጠቀም እንደሚያስችልም ተናግረዋል።
እንደ ስራ አስኪያጁ ገለፃ የSAP EWM ሲስተም በተቋሙ መጋዘን ውስጥ የሚቀመጡ ዕቃዎች መጀመሪያ የገባው ዕቃ መጀመሪያ እንዲወጣ - First In First Out (FIFO) እና የአገልግሎት ጊዜው አጭር የሆነ ዕቃ ቀድሞ እንዲወጣ -First Expired First Out (FEFO) ደረጃዎችን መጠቀም ያስችላል።
ለሰባት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ በአዲስ አበባ ዙሪያ ከሚገኙ ሶስት ሪጂኖች እና ከዋናው ዕቃ ግምጃ ቤት የተውጣጡ 15 የዕቃ ግምጃ ቤት ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ማከፋፈያ ጣቢያው ከሕዳሴ ግድብ የመነጨዉን ኃይል በአግባቡ እያከፋፈለ ነው
....//....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመነጨዉን ኃይል በአግባቡ እያከፋፈለ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለጹ።
ኃላፊው አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለጹት የማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 750 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሰባት ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡
ጣቢያው በአሁኑ ወቅት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአራት ተርባይን እየመነጨ ያለውን 1500 ሜጋ ዋት ኃይል ከዴዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀብሎ ወደ ተለያዩ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እያሰራጨና ከግሪዱ ጋር እንደሚያገናኝ ገልጸዋል፡፡
እንደ አቶ ጥላሁን ገለጻ ጣቢያው ከደዴሳ በባለ 500 ኪሎ ቮልት አራት መስመሮች ኃይል ተቀብሎ በ400 ኪሎ ቮልት በጥምር መስመር ለሱሉሉታ፣ ለሰበታና ለገላን ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ማከፋፈያ ጣቢያው በሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና በስድስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለተለያዩ አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ የሚገኝ ሲሆን በባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ደግሞ ለሐበሻ ሲሚንቶ ፋብሪካ ኃይል እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀሪ ተርባይኖች ወደ ሥራ ሲገቡ የመነጨውን ኃይል በሙሉ ተቀብሎ በአግባቡ ለማከፋፈል ዝግጁ መሆኑንም አቶ ጥላሁን ገለጸዋል፡፡
ጣቢያው ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂዎች መገንባቱን የጠቆሙት ኃላፊው ይህም የጣቢያው ደህንነት ለመጠበቅ፣ መመስመሩ ላይ የሚኖረውን የኃይል መዋዥቅ ለመቋቋም እና የእቃ ብልሽቶች ሲያጋጥሙ ኃይል ሳይቋረጥ ችግሩን ለማስተካከል እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
ጣቢያው የአገር ውስጡን ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር ለውጭ አገራት ኃይል ለማቅረብ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የጠቆሙት አቶ ጥላሁን ጣቢያው ብሔራዊ የኃይል ቋትን በማረጋጋት በኩል ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን ታሳቢ ያደረጉ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ተርባይኖች 5 ሺ 150 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የተቋረጠውን የጅማ - ቦንጋ መስመር ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ነው
.........///........
በጅማ-ቦንጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በደረሰ ጉዳት ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት በጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ በለጠ ጫካ በሚባል ልዩ አካባቢ መስመሩ ላይ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ዛፍ በመጣላቸው ኃይል ተቋርጧል።
በዚህ የተነሳ በካፋ ዞን - በቦንጋ፣ በሚዛን አማን፣ በቤንች ሸኮ ዞን - ጀሙ፣ ምዕራብ ኦሞ ዞን - ቴፒ፣ ከፊል ሸካ ዞን - ሜጪ፣ ዲማ እና በዙሪያቸው ባሉ የወረዳ ከተሞች ኤሌክትሪክ ተቋርጣል።
ኃይል ከተቋረጠበት ሰዓት አንስቶ ችግር የደረሰበትን መስመር እና ቦታውን የመለየት እንዲሁም ለጥገና የሚያገለግሉ ባለሙያዎችና ቁሶችን ወደስፍራው የማድረስ ሥራ የተከናወነ በመሆኑ ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ግድቦቹ በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኃይል ለማሳካት የሚያስችል ውሃ ይዘዋል
……….///………
ባለፈው የክረምት ወቅት ወደ ኃይል ማመንጫ ግድቦች የገባው የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እንደሚያስችል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ ግድቦች በቂ ውሃ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
በክረምቱ ወቅት ከፍተኛ የውሃ መጠን ያከማቹ ማመንጫ ጣቢያዎች ከፍተኛ ኃይል እንዲያመነጩ በማድረግ አነስተኛ ውሃ የነበራቸው ግድቦችን የኃይል ጭነት በመቀነስ በተገቢው መጠን ውሃ እንዲይዙ መደረጉን ሥራ አስኪያጇ ተናግረዋል።
በአሁኑ ጊዜ ግድቦቹ የያዙት የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ለማሳካት እንደሚያስችል በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የነበረው ኃይል የማመንጨት አፈፃጸም ማሳያ ነው ብለዋል።
እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት ስምንት የማመንጫ ግድቦች የሞሉ ሲሆን ሁለቱ ደግሞ በበቂ ደረጃ ውሃ መያዛቸውን ነው ሥራ አስኪያጇ የጠቆሙት።
እንደ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገለፃ ግልገል ጊቤ 1ኛ፣ ፊንጫ፣ መልካ ዋከና፣ ጣና በለስ፣ ተከዜ፣ ገናሌ ዳዋ፣ ቆቃ እና ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድቦች የሞሉ ሲሆን ጊቤ 3ኛ እና አመርቲ ነሼ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ደግሞ በበቂ ደረጃ ውሃ ይዘዋል፡፡
ሁሉም ግድቦች አሁን ያላቸው የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ የታቀደላቸውን ኢነርጂ ለማመንጫት እንደሚያስችላቸውም አረጋግጠዋል፡፡
ግድቦች የያዙትን የውሃ መጠን በአግባቡ ለመጠቀም ከጥገና፣ ከውሃ አስተዳደር እና ከመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ጋር በተያያዘ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ወ/ሮ ጥሩወርቅ አመልክተዋል፡፡
የ2017 በጀት ዓመት የግድቦች የውሃ አያያዝ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር የተሻለ እንደሆነ በዳሰሳ ጥናት መረጋገጡን ጠቁመዋል፡፡
በተያዘው የበጀት ዓመት ከተለያዩ የኃይል ምንጮች ከ25 ሺ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ፍላጎትን የማስተናገድ አቅም አለው፤
...….///…...
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው የጣቢያው ተወካይ ኃላፊ ገለጹ፡፡
ኃላፊው አቶ ሀብታሙ ከበደ እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው በ 400/230 ኪሎ ቮልት ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች 1 ሺ 200 ሜጋ ቮልት አምፔር የመጫን አቅም ቢኖረውም አሁን ላይ እየሰጠ የሚገኘው ከ15 ነጥብ 6 በመቶ ያልበለጠ ነው።
ቢሾፍቱ የኢንዱስትሪ መናኸሪያ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ በአሁኑ ወቅት በርካታ ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎች በመገንባት ላይ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ኃብታሙ ማከፋፈያ ጣቢያው በግንባታ ላይ ለሚገኙና በቀጣይ የሚመጡ የኃይል ጥያቄዎችን ለመመለስ ዝግጁ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የማሻሻያና የማዘመን ሥራዎች መከናወናቸውንም ተወካይ ኃላፊዉ ጠቁመዋል፡
ግንባታው በተጠናቀቀበት ወቅት 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው 230/15 ኪሎ ቮልት ሁለት ፓወር ትራንስፎርመር ብቻ የነበረ ሲሆን በአካባቢው በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ከፍተኛ ፍላጎት በመኖሩ ምክንያት ተጨማሪ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው 230/33 ኪሎ ቮልት ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች ማስፋፈያ ተደርጓል፡፡
እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከገላን ማከፋፈያ ጣቢያ ገቢ መስመር ያለው ሲሆን በ230 ኪሎ ቮልት ለዱከም ቁጥር-2 በሁለት መስመሮች እንዲሁም ለሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
ጣቢያው አስር ባለ15 ኪሎ ቮልት እና አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እንዳሉትም አመላክተዋል፡፡
በማከፋፈያ ጣቢያው ያሉት ብሬከሮች ጂ አይ ኤስ በመሆናቸው የኃይል መቆራረጥን በመቀነስ በኩል ሚናቸው ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በትራንስፎርመሮች ውስጣዊ ችግር ምክንያት የእሳት አደጋ ቢከሰት አደጋውን ለመከላከል የሚረዳ ጨምሮ ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ከመስከረም 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ለጥገና ሥራ በተለያዩ አካባቢዎች የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐሙስ ታህሳስ 17 እና ዓርብ ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ለ24 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ታህሳስ 19 እና እሁድ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ለ 12 ሰዓት በጅማ አባ ጎሪቃ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡
ስለሆነም በአባ ከተማ፣ በተርጫ፣ በአመያ፣ በጭዳ፣ በቂራራ፣ በከርቤላ፣ በዋካ፣ በገሳ፣ በኢሰራ ከተማ፣ በጨበራ ጩርጩራ ፓርክ፣ በዘባ ገዙ ወረዳ፣ በደሳ ወረዳ፣ በማረካ ወረዳ፣ በቶጫ ወረዳ፣ በገና ወረዳ እና በዋራ ከተማዎች ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል፡፡
በተመሳሳይ ቅዳሜ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 8፡00 ሰዓት ድረስ በአዲስ ሴንተር ማከፋፈያ ጣቢያ የፓወር ትራንስፎመር ጥገና ለማከናወን ሲባል በሜክሲኮ፣ በለገሀር፣ በመስቀል አደባባይ፣ በቦሌ ማተሚያ ቤት አካባቢ፣ በገነት ሆቴል አካባቢ፣ በኢዩቤልዩ ቤተመንግስት፣ በብሔራዊ፣ በሳር ቤት፣ በዑራኤል አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ይቋረጣል፡፡
በሌላ በኩል እሁድ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 8፡00 ሰዓት ድረስ በቃሊቲ ኖርዝ ማከፋፈያ ጣቢያ የፓወር ትራንስፎመር ጥገና ለማከናወን ሲባል በቼራሊያ፣ በኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ በዩሮ ኬብል፣ በአቃቂ ስታዲየም፣ በመኮድ፣ በአየር ኃይል ካምፕ፣ በገላን ጉራ ባቡር ጣቢያ ጀርባ፣ በዋሊያ ብረታ ብረት፣ በቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የመቆጣጠሪያ ሥርዓት ለማዘመን የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
……...///……..
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የመቆጣጠሪያ ደህንነት ሥርዓት ለማዘመን እና ለማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን እና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት መምሪያ የምስራቅ አንድ ሪጅን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ጠይብ መሐመድ እንደገለፁት የመቆጣጠሪያ ደህንነት ሥርዓት የማዘመን እና አቅም የማሳደግ ሥራው በተመረጡ 69 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተግባራዊ ይደረጋል።
የጣቢያዎችን እና ማስተላለፊያ መስመሮችን የመቆጣጠሪያ ደህንነት የማዘመን እና የማሻሻል ሥራው በማዕከላዊ አንድ፣ ማዕከላዊ ሦስት እና ምስራቅ አንድ እንዲሁም ደቡብ አንድ ሪጅን ሥር በሚገኙ 15 የኃይል ማከፋፊያዎች ላይ መጀመሩንም ነው የተናገሩት።
በአሁኑ ወቅት የአምስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎች የማዘመን እና አቅም የማሳደግ ሥራ ተጠናቆ ሥራ መጀመራቸውንም ነው የገለፁት።
እንደ አቶ ጠይብ ገለፃ ፕሮጀክቱ በዋናነት በማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ትራስፎርመሮችን እና የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን ደህንነት በማዘመን ለደንበኞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማስቻል ነው።
በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ የኮንትራት እና ሱፐርቪዥን መምሪያ የምስራቅ አንድ ሪጅን አስተባባሪ አቶ ክብሮም በርሔ በበኩላቸው የሥራ ክፍሉ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ የመቆጣጠር እና በኮንትራቱ መሰረት እንዲጠናቀቅ የማድረግ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ደህንነት ለረጅም ዓመታት ሲቆጣጠሩ የቆዩ፣ የተበላሹ እና ውስንነት ያለባቸው የሪሌይ ዕቃዎችን በአዲስና ዘመናዊ መሳሪያዎች ለመቀየር ያለመ እንደሆነም ነው የገለፁት።
እንደ አቶ ክብሮም ገለፃ በጣቢያዎቹ የሚገጠሙት ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎች የማከፋፈያ ጣቢያዎቹን ደህንነት የማስጠበቅ ሥራ ወጥነት ባለው መልኩ በአንድ ሪሌይ ብቻ የማከናወን አቅም የሚፈጥሩ ናቸው።
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የመቆጣጠሪያ ሥርዓት የማዘመንና አቅም የማሳደግ ሥራውን የቻይናው ሲ.ዋይ.ጂ ሱርሚ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ እያከናወነ ሲሆን የተቋሙ የኮንትራት እና ሱፐርቪዥን መምሪያ ደግሞ በአማካሪነት እየተሳተፈ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ፕሮጀክቱን በ18 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ከ4.6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ በጀት የተያዘ ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሸፈን ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የማከፋፈያ ጣቢያው ለአገልግሎት ዝግጁ የሚሆንበት ደረጃ ላይ ደርሷል
……..///……….
የማሻ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የኤሌክትሮ ሜካኒካል መሳሪያዎች ገጠማ እና ፍተሻ ተጠናቆ የሙከራ ሥራ መከናወኑን የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አሳዬ እንደገለፁት የሰርኪዩት ብሬከሮች ተከላ፣ 50 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያላችው ሁለት ባለ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ተከላ፣ የስዊችያርድ እና ሌሎች የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ተከላና የማገናኘት ሥራ ተጠናቋል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው አጠቃላይ አፈጻጸም ከ90 በመቶ በላይ መድረሱን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የማስተላለፊያ መስመሩ ዝርጋታ እንደተጠናቀቀ ለአገልግሎት ዝግጁ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡
ከዓለም በተገኘ ከ6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር እየተገነባ የሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ እና ሶስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡
ግንባታውን ሲኖ ኃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን በአማካሪነት ደግሞ ኢ. ኤል. ሲ. (ELC) የተባለ የጣሊያን ኩባንያ እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለማሻና ለአካባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ከማድረጉ ባሻገር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን ኃይል ትስስር በማሳለጥ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የኃይል ማመንጫ ግድቡን ደህንነት ለመጠበቅ እየተሰራ ነው
……...///…..….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ አንድ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጣቢያው አስታወቀ።
የጣቢያው የጥገናና የዳም ሞኒተሪንግ ሥራ ክፍል መሪ አቶ ሀብታሙ ጌቱ እንደተናገሩት የዕይታ ፍተሻ እና የግድብ ደህንነት መከታተያ መሣሪያዎችን በመጠቀም የኃይል ማመንጫውን ግድብ ደህንነት የማረጋገጥ ሥራ እየተሰራ ነው፡፡
የግድብ ደህንነት ክትትልና ቁጥጥር ሥራው በውሃ መግቢያው (ኢንቴክ)፣ በውሃ ማስተንፈሻ (Spillways) እና በግድቡ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።
የግድቡ ስርገትን (Dam settlement) በተመለከተ በዲዛይን ወቅት በተቆፈሩና እስከ 38 ነጥብ 2 ሜትር ጥልቀት ባላቸው አምስት ጉድጓዶች ውስጥ በተቀመጡ ቀለበቶች አማካኝነት ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግ ገልጸዋል።
በተጨማሪም 1 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው በግድቡ ሥር ባለ የመሬት ውስጥ ዋሻ የታችኛው ወለል የውሃ ፍሳሽ መጠን መቆጣጠሪያዎች አማካኝነት የቁጥጥር ሥራ ይሰራል።
ይህም የግድቡን ደህንነት ስጋት ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ያልተጠበቁ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ክስተቶችን በመከላከል እና አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምጃ በወቅቱ በመውሰድ ደህንነቱን ለመጠበቅም ያግዛል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም በግድቡ የሚከናወነው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ የግድቡን ደህንነት በመጠበቅ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚጠበቅበትን ኃይል በአግባቡ እንዲያመርት ከማድረግ ባሻገር ከግድቡ በታች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ከድንገተኛ ጎርፍ ለመከላከል የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
የግድብ ክትትልና ቁጥጥር ሥራው በግድቡ ላይ በየሳምንቱና በየወሩ ፍተሻ በማካሄድ የሚከናወን መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለመጠበቅ በዲዛይን፣ በግንባታ ሂደት፣ ግድቡ ለመጀመሪያ ጊዜ ውሃ መያዝ ሲጀምር እንዲሁም በአገልግሎት ጊዜ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችን ያከናውናል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ቡድኑ ሊጉን የሚመራበት ውጤት አስመዝግቧል
……..///……..
በ11ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ድሬዳዋ ከነማን ሁለት ለአንድ በማሸነፍ ሊጉን መምራት ጀምሯል።
የኢትዮ-ኤሌክትሪክን የማሸነፊያ ጎሎች ህዳት ካሱ በ31ኛው እና ማህሌት ምትኩ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል።
ድሬዳዋ ከነማን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ጎል ብዙነሽ ሲሳይ በ86ኛው ደቂቃ አስቆጥራለች።
ኳስን ተቆጣጥሮ ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ በመድረስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ብልጫ የነበረው ሲሆን ድሬዳዋ ከነማ በበኩሉ በመልሶ ማጥቃት ጎል ለማስቆጠር ጥረት አድርጓል።
የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመሀል ተከላካይ የሆነችው ባንቺይርጋ ተስፋዬ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ተሸልማለች።
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ20 ነጥብ እና በስምንት ንፁህ ጎል ሊጉን በጊዜያዊነት እየመራ ይገኛል።
በ12ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከሲዳማ ቡና ጋር የሚጫወት ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
