EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 921 次浏览,首日通常累积 2 563 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
+424 小时
-357 天
+2230 天
帖子存档
15 544
ከሚገነቡ ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡና ተቋሙ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተቋራጮች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል
………..///………
በፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት ፕሮጀክቱ የሚገነባለት ህብረተሰብና ተቋሙ ማግኘት ያለበትን ጥቅም እንዳያጡ ተቋራጮች በትኩረት እንዲሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አሳሰቡ።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ ከተሳተፉ ተቋራጮችና አማካሪዎች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ ተቋራጮችና አማካሪዎች በሥራ ላይ የሚገጥሟቸውን ችግሮች ለይቶ ለመደገፍ እና ፕሮጀክቶች በተመደበላቸው ጊዜና በጀት እንዲሁም የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶች በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚዘገዩ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ችግሮቹን በግልፅ ተነጋግሮ መፍታት ይገባል ብለዋል።
በግንባታው ላይ የተሳተፉ የሥራ ተቋራጮች በበኩላቸው በፕሮጀክት ትግበራ ወቅት ያጋጥሙናል ያሏቸውን ችግሮች በዝርዝር አቅርበዋል።
የዲዛይን ማፅደቅ ሂደት መጓተት፣የፕሮጀክት ማናጀሮች ከኮንትራት እና ከክፍያ ጋር የተያያዘ ውሳኔ በፍጥነት መስጠት አለመቻላቸው፣ ለግንባታ ግብዓት የሚሆኑ የሲሚንቶ እና ብረት እጥረት መኖሩ እና በፕሮጀክቶች ላይ ቴክኒካል የሥራ ለውጥ ማጋጠሙን እንደችግር አንስተዋል።
ለግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በባንኮች የውጭ ምንዛሪ ዋስትና ወይም ሌተር ኦፍ ክሬዲት በወቅቱ አለመክፈቱ፣ በወሰን ማስከበር ችግር የተነሳ አስቀድሞ መሰራት ያለበት ሥራ አለመሰራቱና የግንባታ መዘግየት መፈጠሩ፣ በሥራው ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች የሰለጠኑ አለመሆናቸውና የሥራ ላይ ውጤታማነት አነስተኛ መሆኑ እንዲሁም የግንባታ ዋጋ በየጊዜው መጨመሩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ ማድረጉንም ተቋራጮቹ ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በተቋራጮች የተነሱ ችግሮች መኖራቸውን ጠቅሰው የፕሮጀክት ዲዛይን ማፅደቅ ሥራዎችን በተቻለ መጠን ኤሌክትሮኒክ በሆነ መንገድ በማከናወን ችግሩ እንደሚቀረፍና የውጭ ምንዛሪ ዋስትና ወይም ሌተር ኦፍ ክሬዲት ጉዳይም በሂደት ላይ ያለ ጉዳይ በመሆኑ በቅርቡ እልባት እንደሚያገኝ አረጋግጠዋል።
አሁን ባለው ተጨባጭ መረጃ 50 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ወጣትና መስራት የሚችል በመሆኑ አሰልጥኖ ወደ ሥራ በማስገባት የሠለጠነ የሰው ኃይል ችግርን መቅረፍ እንደሚቻል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።
በሥራ ተቋራጮች የተነሱ ሌሎች ችግሮች እንዲቀረፉ የተቋሙ ማኔጅመንት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በቀጣይም ተቋሙ ከፕሮጀክት ተቋራጮች ጋር እየተገናኘ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 27 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ በትኩረት መስራት ይገባል
……..///………..
የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው መርሃ ግብር፣ በጀት እና ዝርዝር መስፈርት መሰረት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ከተቋሙ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ላይ በተቋራጭነት እና በአማካሪነት ከተሳተፉ ተቋማት ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚው እንደገለጹት ውይይቱ ሥራ ተቋራጮችና አማካሪዎች በፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ላይ የሚያጋጥማቸውን ችግር ለመፍታት፣ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እና በሚሰጠው ግብዓት ላይ ተመስርቶ ተቋሙ ያለበትን ክፍተት ለመሙት ያለመ ነው፡፡
ውይይቱ በሥራ ተቋራጮችና በተቋሙ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ ግንኙነት እና የመማማር ሂደት ለማጠናከር እንዲሁም ከውይይቱ የሚገኘውን ግብዓት በግንባታ ላይ ካሉት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በቀጣይ ግንባታቸው ለሚጀመሩ ፕሮጀክቶች ለመጠቀም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
የፕሮጀክት ሥራ በጊዜና በበጀት የተወሰነ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲሁም በስምምነቱ ላይ በተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ በሥራው ላይ የተሳተፉ አካላት በትብብርና በመግባባት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የተገኙት ሥራ ተቋራጮችና አማካሪዎች በበኩላቸው ከጉምሩክ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ዕቃዎችን በወቅቱ ለማስገባት ችግር እንደሚያጋጥማቸው፣ የክፍያ መዘግየት እንዳለ፣ ለግንባታ በሚያስፈልጉ ዕቃዎች ላይ ስርቆት እንደሚፈጸም እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎችን ከወደብ ወደ ሳይት በተፈለገው ፍጥነት ለማጓጓዝ ችግር እንደሚያጋጥም አንስተዋል፡፡
በአንዳንድ ቦታዎች ከፀጥታ ጋር በተያያዘ በሚፈለገው ልክ ተንቀሳቅሶ ለመስራት አለመቻሉና አማራጭ የመጓጓዣ መንገድ አለመኖሩ እንዲሁም የቪዛ ሂደቶችን ለመጨረስ የመጓተትና ተደጋጋሚ ምልልስ መኖሩ ለፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት እንደሚሆን ጠቅሰዋል፡፡
የዓለም አቀፍ የገበያ ሁኔታ በፍጥነት መለዋወጥ፤ ወቅታዊ የሆነ ምላሽ አለመስጠት እንዲሁም ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን አሟልቶ በሥራ ላይ አለመገኘት እና ሌሎችም ችግሮች በፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ላይ እየተስተዋሉ መሆናቸው በውይይቱ ላይ ተነስቷል፡፡
የፕሮጀክቶች አማካሪዎችም ግንባታው በስምምነቱ መሰረት እንዲከናወን ለማድረግ ከሥራ ተቋራጮች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች እንደሚካሄዱ በመግለጽ ለተከፈለበት ገንዘብ የሚመጥንና የጥራት ደረጃውን የሚያሟላ ሥራ እንዲከናወን ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ያሉት የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች በበኩላቸው ሳይት ላይ በተገቢውና በተቀናጀ መልኩ አቅዶ ያለመስራት፣ ተገቢውን ሠራተኛ መድቦ ያለማሰራት እንዲሁም ከአማካሪና ከተቋሙ ጋር ተቀናጅቶ ያለመስራት ሁኔታዎች በሥራ ተቋራጮች ላይ እንደሚስተዋሉ አንስተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁና በየጊዜው የጊዜ ማራዘሚያ እንዳይጠየቅባቸው የጨረታ ሰነድ ዝግጅት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
በአሰሪውም ሆነ በተቋራጮች በኩል ችግሮች እንዳሉ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከተቋሙ ጋር አብረው በሚሰሩ ሌሎች ድርጅቶች ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት በመስጠት ፕሮጀክቶችን ውጤታማ ማድረግ ይቻላል ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቶችን በወቅቱና በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ ሥራ ተቋራጮች አደረጃጀታቸውን በማጠናከር፣ የሰው ኃይል እና የግብዓት አቅርቦታቸውን በማሻሻል መስራት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡
በቀጣይም መሰል ውይይቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ እያከናወናቸው ባሉ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶ ላይ እየተሳተፉ ካሉ ሥራ ተቋራጮችና አማካሪዎች ጋርም ተመሳሳይ ውይይት ለማካሄድ ቀጠሮ ተይዟል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 26 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
የተጀመሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ተቋሙ የክትትልና ድጋፍ ሥራ እያከናወነ ይገኛል
……...///……....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአማራ ክልል ያለውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ።
በሥራ አስፈፃሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ የተመራ የልዑካን ቡድን የባህርዳር-ወልዲያ- ኮምቦልቻ ባለ400/230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ያለበትን የግንባታ ደረጃ በመስክ ተገኝቶ ገምግሟል።
ሥራ አስፈፃሚው በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት ተቋሙ በክልሉ አስተማማኝ የሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በክልሉ እየተገነቡ በሚገኙት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ላይ ለሚነሱ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ነው።
እንደ አቶ ክብሮም ገለፃ ተቋሙ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆኑ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በመሆኑም ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቁ እያደረጉ ያሉ ችግሮችን በመለየት በየደረጃው ካሉ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ለመወያየት ታቅዷል ብለዋል።
በአሁኑ ሰዓት በግንባታ ላይ የሚገኙት የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎች ሲጠናቀቁ ክልሉ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው ለቆዩት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው ያስታወቁት።
ይሁንና ፕሮጀክቱ በሚያልፍባቸው አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ምትክ መሬት ለሚያስፈልጋቸው የልማት ተነሺ የማህበረሰብ ክፍሎች አፋጣኝ ምላሽ ሳይሰጥ መዘግየቱ በግንባታ ሒደቱ ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን ጠቁመው የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ተቋሙ ከካሳ ክፍያ እና ከኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ጥያቄዎች እና ቅሬታዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ነው አቶ ክብሮም የተናገሩት።
በከፍተኛ ወጪ እየተገነቡ በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የሥርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለበባቸው አስገንዝበዋል።
በወሰን ማስከበር ችግሮች ሳቢያ በባህር ዳር ከተማ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ እና የማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራዎችን በታሰበው መልኩ ማከናወን እንዳልተቻለም ነው ሥራ አስፃሚው የገለፁት።
በጉብኝቱ ላይ የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ አንዳርጌ እሸቴን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጮች ተገኝተዋል።
የመስክ ምልከታው ዛሬም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በፕሮጀክቶቹ ግንባታ ዙሪያ ከሚመለከታቸው የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 26 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ቢሮው የአዳማ 2 የንፋስ ማመንጫ ጣቢያ መንገድን የጥገና ሥራ እያከናወነ ይገኛል
……///……..
የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የጥርጊያ መንገድ የጥገና ሥራን እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ የሲቪል ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር ግርማ መንገሻ እንዳስታወቁት 17 ኪሎ ሜትር ከሚሸፍነው የጥገና ሥራ ውስጥ በአሁኑ ወቅት 14 ኪሎ ሜትሩ ወይም 90 በመቶ የሚሆነው ተጠናቋል፡፡
ከዚህ በፊት ቢሮው በአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የ12 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና ሥራ ማከናወኑን ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሳይት ኢንጂነር ሹሜ ገለታ በበኩላቸው መንገዱ በአዳማ ወረዳ የሚገኙ ሦስት ቀበሌዎችን እንደሚያገናኝ እና ይህም ለአካባቢው ማህበረሰብ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከመንገዱ የጥገና ሥራ በተጨማሪ ለዉሃ ማስተንፈሻ የሚያገለግሉ የግንባታ ሥራዎች በሦስት ቦታዎች ላይ በአዲስ መልክ መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በጥገና ሥራው ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ከአካባቢው ሽማግሌዎች ጋር በመወያየት እና ነዋሪዎቹ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሁኑ በማድረግ ሥራው እየተከናወነ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊዎች ተናግረዋል፡፡
በጥገና ሥራ ላይ ሲሳተፉ ያገኘናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ወጣት ሙክየ ሀሮ እና አቶ ፍቃዱ ነጋሽ እንደተናገሩት መንገዱ ከተገነባ ጀምሮ ከዚህ በፊት ይደርስባቸው የነበረውን ማህበራዊ ችግር ቀርፎላቸዋል፡፡
በሥራው ላይ ተሳትፈው የሚያገኙት ገቢም ኑሯቸውን ለመደጎም እንዳገዛቸው ገልፀዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 25 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
……....///…….....
በጊቤ ሁለት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሹመት በላቸው አስታወቁ።
ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የጥገና ሥራው በዋናነት እየተከናወነ የሚገኘው ዩኒቱን በአውቶማቲክ ሲስተም የመቆጣጠሪያ ዘዴ እንዲሰራ ለማድረግ ነው።
የጥገና ሥራው የሚከናወነው የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ካሉት አራት ተርባይኖች ውስጥ በአንደኛው ዩኒት ውሃን በተፈለገው መጠን ወደ ተርባይን ለማስተላለፍ በሚያገለግሉት ሹል ጫፍ ባላቸው ስድስት የፓወር ኖዝሎች ላይ ብልሽት በማጋጠሙ እንደሆነ ነው አቶ ሹመት የተናገሩት።
የፓወር ኖዝሎቹ ውስጥ ያሉት ክፍሎች በመጎዳታቸው ሳቢያ የኃይል ማመንጫ ዩኒቱን የማመንጨት አቅም በተፈለገው መጠን በአውቶማቲክ ሲስተም መቆጣጠር እንዳልተቻለም ገልፀዋል።
በአሁኑ ሰዓት ጉዳት የደረሰባቸውን ስድስት የፖወር ኖዝሎች የውስጥ ክፍሎች በአዲስ የመቀየር ሥራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።
በውስጡ የሚገኙት ሲሊንደሮች ላይ የዘይት መፍሰስ ችግር እንዳያጋጥም የሚከላከሉ አካላትን (Sealers) በአዲስ የመቀየር ሥራም እየተከናወነ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
እየተከናወኑ የሚገኙት የጥገና ሥራዎች ሲጠናቀቁና ዩኒቱ ዳግም ወደ ሥራ ሲመለስ በሙሉ አቅሙ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ሹመት ገለፃ በጣቢያው እየተከናወኑ የሚገኙትን የጥገና ሥራዎች ከ15 ቀናት ባነሰ ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙንም ተናግረዋል።
ለጥገና ሥራው የሚያስፈልጉ አንዳንድ የመለዋወጫ ዕቃዎች ላይ ማሻሻያ በማድረግና የሞዲፊኬሽን ሥራ በመስራት ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ መታደግ እንደተቻለም ነው ሥራ አስኪያጁ ያብራሩት።
የጥገና ሥራው ከጣቢያው፣ ከተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና ከማዕከል በመጡ የተቋሙ ሠራተኞች እየተከናወነ እንደሚገኝ ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት።
የጊቤ ሁለት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን እያንዳንዳቸው 105 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ዩኒቶች ያሉትና በድምሩ 420 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ነው፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 25 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
የኘሮግራም ጥቆማ
በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን መከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በተቋሙ ማህበራዊ ሚዲያና የህትመት ውጤቶች እንዲሁም በአዲስ ዘመን በአማርኛ በየሳምንቱ በዘኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ በየአስራ አምስት ቀኑ ከሚዘጋጀው ህትመት በተጨማሪ ሳምንታዊ የሬዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞችን አዘጋጅቷል።
በመሆኑም መላው የተቋማችን ሠራተኞች፣ አመራሮች፣ ደንበኞቻችንና አጋሮቻችን በሙሉ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 12:10 እስከ 12:40 በኦሮምኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ቻናል እንዲሁም ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት እንድትከታተሉ በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ
መጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
በፕሮጀክቱ ሠራተኞች ላይ እየደረሱ ያሉት ጥቃቶች አሳሳቢ እየሆኑ መጥተዋል - የግንባታው ሥራ ተቋራጭ
የፀጥታ ችግር እና የስርቆት ወንጀሎቹ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚፃረሩ ናቸው - የአማራ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ
…......////…….....
በባህርዳር- ወልዲያ-ኮምቦልቻ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ሠራተኞች ላይ እየደረሱ ያሉት ጥቃቶች አሳሳቢነታቸው እየጨመረ መምጣቱን የግንባታው ሥራ ተቋራጭ አስታወቀ።
የታታ ፕሮጀክትስ ሊሚትድ ሴክሽን አንድ ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ፕረሰድ አር እንደገለፁት ከባህርዳር እስከ ንፋስ መውጫ ከተማ ድረስ ምሰሶዎችን ለመትከል የሚያስችሉ የመሠረት ሥራዎች 90 በመቶ፣ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተከላ 80 በመቶ እንዲሁም የኮንዳክተር ገመድ ዝርጋታ 70 በመቶ አፈፃፀም ላይ ደርሷል።
ይሁንና የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታው በሚያልፍባቸው አንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ስጋቶች፣ የወሰን ማስከበር ችግሮች እንዲሁም በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች እና ሽቦዎች ላይ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀሙ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
ግንባታውን እያከናወኑ በሚገኙት ሠራተኞች ላይ እየደረሰ ያለው አካላዊ ጥቃት እና ዝርፊያ በሥራው ላይ ትልቅ እንቅፋት እየሆነ መምጣቱንም ነው የገለፁት።
አካላዊ ጥቃቶቹ እና የዝርፊያ ወንጀሎቹ እየተፈፀሙ የሚገኙት በጦር መሳሪያ በመታገዝ ጭምር ነው ያሉት ሚስተር ፕረሰድ በዚህም ሳቢያ ጉዳት የደረሰባቸው ሠራተኞች እንዳሉም ተናግረዋል።
የወሰን ማስከበር ሥራው ሙሉ በሙሉ ባለመጠናቀቁ ምክንያት በመሬት ባለይዞታ ግለሰቦች የተለያዩ ጥቃቶች እንደሚሰነዘርባቸውም ነው ሥራ አስኪያጁ ጨምረው ያብራሩት።
እንደ ሚስተር ፕረሰድ ገለፃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍባቸው አንዳንድ አካባቢዎች የመሬት ልኬት ሥራዎች ቢጠናቀቁም በክፍያ መዘግየት ምክንያት ግንባታውን ማስቀጠል አልተቻለም።
የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶችና ሽቦዎች ላይ ተደጋጋሚ የሆኑ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀሙ በመሆናቸው በግንባታው ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል።
በፕሮጀክቱ ሠራተኞች ላይ እየተፈፀመ ያለው አካላዊ ጥቃት እና ዝርፊያ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ ግንባታውን ለማቆም እንደሚገደዱም ነው ያስታወቁት።
የአማራ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በበኩሉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍባቸው ሁሉም አካባቢዎች የሚያጋጥሙትን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ገልጿል።
በፕሮጀክቱ ላይ እያጋጠሙ ያሉት የፀጥታ እና የስርቆት ወንጀሎች የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚፃረር ነው ያለው ቢሮው የክልሉን ገፅታ የሚያጠፋ ድርጊት በመሆኑ ህገ-ወጦችን ተከታትሎ ለህግ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።
ፕሮጀክቱ የባህርዳር፣ የደቡብ ጎንደር፣ የሰሜን እና ደቡብ ወሎ ዞኖችን የሚያካልል በመሆኑ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ችግሮቹን በመፍታት ለግንባታው መፋጠን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
የሥራ ባህልን በማሳደግ ተቋሙን ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ እንደሚገባ ተገለፀ
……..///…….
የአገልጋይነት ስሜት በመፍጠርና ወጥ የሆነ የስራ ባህል በማዳበር የተቋሙን ውጤታማነት ማሳደግ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ተናገሩ፡፡
ለማህበሩ የምክር ቤት አባላት በደብረብርሀን ከተማ እየተሰጠ ያለውን የአቅም ግንባታ ስልጠና ሲከፍቱ ሊቀመንበሩ እንደተናገሩት የምክር ቤት አባላቱ ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ዕውቀት እና ክህሎት በማዳበር ለኃይል ልማት ዘርፍ ስኬት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡
የውጤት ተኮር የሥራ አፈፃፀም ምዘና ስርዓት ለተለያዩ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ተግባራዊ መደረጉን የገለፁት አቶ መኮንን ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞች በዕቅድ ላይ የተመሰረተ የላቀ የስራ አፈፃፀም ማስመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የስልጠና ተሳታፊዎች በበኩላቸው የሥራ ባህልን በማሳደግ የተቋሙን ራዕይ፣ተልዕኮ እና ዕሴት ከግብ ለማድረስ ቁርጠኛ የሆነ አገልጋይ ሠራተኛ መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በሥራ ላይ አለመግባባት በሚያጋጥምበት ወቅት በህብረት ስምምነት እና በአሰሪና ሠራተኛ ህጉ መሠረት በሰከነ መንገድ ሊፈታ እንደሚገባም አንስተዋል፡፡
ለሁለት ቀናት የሚቆየው ሥልጠና በተቋም ባህል ግንባታ፣በአሰሪና ሠራተኛ ማህበር አመራር ሚና እንዲሁም በሥራ ላይ ግጭት አፈታት እና አፈፃፀምን ማላቅ በሚያስችሉ ስልቶች ላይ ያተኮረ ነው፡፡
በደብረብርሃን ከተማ እየተሰጠ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ነው፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በምግብ አብሳይ (ሼፍ) የሥራ መደብ ላይ ክፍት የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡ መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡
15 544
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር IV የሥራ መደብ ላይ ክፍት የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡ መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡
15 544
ሠራተኛውን በፍትሐዊነት ለማትጋትና ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው
---///---
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጤት ተኮር ምዘና ስርዓት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ መሆኑን መሆኑን በተቋሙ የሰው ኃይል ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡
በመምሪያው የፐርፎርማንስ ማኔጅመንትና ሪዋርድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አእምሮ እንደገለፁት በለውጥ ሥራዎች ውስጥ የተቋማዊ ባህል ግንባታ እንደ አንድ የለውጥ መሳሪያ እየተተገበረ ነው፡፡
የሥራ አፈፃፀም ምዘና ውጤት ለዕድገትና ዝውውር እንዲሁም ለውጪ ሀገር ትምህርትና ሥልጠና ዕድሎች መመዘኛ እና መተግበሪያ የሚውል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የውጤት ተኮር ምዘና ሥርዓት ለደመወዝ ጭማሪና ለሌሎች የጥቅማ ጥቅም ውሳኔዎች ግብዓትነት እንደሚውል አስረድተዋል፡፡
በውጤት ላይ የተመሰረተ የአፈፃፀም ምዘናና አመራር ስርዓት በመዘርጋት ሠራተኛውን በፍትሐዊነት ለማትጋትና ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡
እንደ አቶ አሸናፊ ገለፃ በአፈፃፀም ትግበራ ሂደት ላይ መሻሻሎች እየታዩ ቢሆንም በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል፡፡
የሥራ ዕቅድ በአግባቡ አውጥተው ለሠራተኞቻቸው ያወረዱ፣ የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ያደረጉ፣ በምዘና ጊዜ ተገቢውን ውጤትና ግብረ መልስ የሰጡ የሥራ ኃላፊዎች ከተፈጠሩ በምላሹ በራሳቸው ተነሳሽነት ተጨማሪ ሥራዎችን በጥራት ሰርተው የሚያበረክቱ ውጤታማ ሠራተኞችን ማግኘት እንደሚቻል ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
የተቋሙን ስጋቶች ማቅለያ ስትራቴጂ ተቀርጿል
………..///……....
የተቋሙን ስጋቶች መቀነስ የሚያስችል ስትራቴጂ መቀረፁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ሪስክ ማኔጅመንት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ህሊና አለማየሁ እንደገለፁት 30 የሚደርሱ የተቋሙን ስጋቶችን ከሥራ ክፍሎች ጋር በመሆን በመለየት ቅድሚያ ሊሰጣው የሚገቡትን ደረጃ የማውጣት ሥራ ተከናውኗል።
ስትራቴጂው ከፋይናንስ፣ ከሥራ ላይ ደህንነት፣ ከሰው ኃይል፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ከመጠቀም፣ ከግብዓት አቅርቦት፣ ከህግ እና ደንብ፣ ከተቋም ውጪ በሆኑ ምክንያቶች እና ከግል አልሚዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና ስጋቶችን መለየቱን ተናግረዋል።
ወጪን መመለስ የሚያስችል ታሪፍ አለመቀረፁ እና ለኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና የሚውሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖሩ በስትራቴጂው ላይ የተለዩ ስጋቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ ክህሎት ያለው ባለሙያ እጥረት፣ ስማርት ሜትር ላይ ሊደርስ የሚችል የኃይል ስርቆት እና በፕሮጀክቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ የካሳ ክፍያ መጠየቅ ተጨማሪ ስጋቶች ናቸው።
ከግል አልሚዎች ጋር ተያይዘው የሚነሱ የታሪፍ ጉዳዮችም የተቋሙ ስጋቶች ሆነው መለየታቸውን ወ/ሮ ህሊና ተናግረዋል።
በስትራቴጂው ለእያንዳንዱ ስጋት ዝርዝር የማቅለያ ሃሳቦች መቀመጣቸውን የተናገሩት ሥራ አስኪያጇ ሪፖርቱ 80 በመቶ የሚሆኑትን የተቋሙን የሥራ ክፍሎች መዳሰሱንም ጨምረው አብራርተዋል።
ወጪን መመለስ የሚያስችሉ ታሪፎችን መተግበር እና ፕሮጀክቶች በወቅቱ እንዲጠናቀቁ በሙሉ አቅም መስራት ተቋሙ ትኩረት ሊያደርግባቸው የሚገቡ ጉዳዮች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የንብረት ውድመት እና ስርቆትን በተመለከተ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ማድረግ እንደሚገባም በስጋት ማቅለያ ስትራቴጂው ውስጥ ተካቷል ብለዋል።
በቀጣይ በሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ላይ የካሳ ክፍያ ስጋትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎች ተግባራዊ እንዲሆኑ እና ከግል አልሚዎች ጋር ተያይዞ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች እንዲደረጉ የሚያስችል አመላካች የስጋት ማቅለያ ስልት መነደፉንም ነው ወ/ሮ ህሊና የገለፁት።
የስጋት አስተዳደር ስትራቴጂን ከተቋሙ አጠቃላይ የሥራ አመራር ጋር በማዋሃድ በስትራቴጂው ተለይተው የተዘረዘሩትን ስጋቶች በወቅቱ ለማሻሻል ሁሉም የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የተቋሙን ስጋቶች በመለየት፣ ደረጃ በማውጣት እና የስጋት ማቅለያ ስትራተጂዎችን በማዘጋጀት የተሳተፉ የሥራ ኃላፊዎችን እና ሠራተኞችንም አመስግነዋል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
