ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 544 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 544 名订阅者。

根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.50% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 921 次浏览,首日通常累积 2 563 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 544
订阅者
+424 小时
-357
+2230
帖子存档
photo content

ግሪዱን ለማዘመን የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ ……..///…….. ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠር ሥርዓቱን ለማዘመን የሚያስችል የብሔራዊ ግሪድ መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን በማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች አፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን እና አቅም ማሳደግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ገ/እግዚአብሔር እንዳስታወቁት በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ግሪድ ላይ ያሉ የሥራ ሂደቶችንና የተተከሉ ዕቃዎችን የማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ እንደ አቶ ዳዊት ገለጻ በአሁኑ ወቅት በብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል፣ በስማርት ሜትር ተከላ ሥራ እንዲሁም በመረጃ መረብ የተደገፈ የኃይል መቆራረጥ መከታተያ ዳታ ቤዝ ሥራ ላይ የማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የማዘመን ሥራዎች በግሪዱ ማከፋፈያ እና በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የሚከናወኑ መሆናቸውን አቶ ዳዊት ጠቅሰዋል፡፡ የግሪዱ መዘመን የኃይል ስርጭት ክትትልና ቁጥጥር ሥራዉን ለማዘመንና የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም የጥገናና የኦፕሬሽን ወጪዎችን ለመቀነስ ያግዛል ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፡፡ የስማርት ሜትርና የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክቶች ከዚህ በፊት የተካሄዱ ጥናቶችን መሰረት በማድረግ ወደ ሥራ እንደተገባ ያስታወሱት ዳይሬክተሩ ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ አቅም ለመጠቀም በአሁኑ ወቅት አርቲኢ (RTE) በተሰኘ የፈረንሳይ ኩባንያ ጥናት በመከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ በኩባንያው እየተካሄደ ያለው ጥናት ባይጠናቀቅም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተገነቡ የቆዩ በመሆናቸው ከዘመኑ ጋር የሚሄድ የአውቶሜሽን ሲስተም አለመኖሩ እና በማዕከሉ የሚገኝ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ባለመኖሩ ምክንያት የአሴት ማኔጅመንት ለማከናወን አዳጋች መሆናቸውን በጥናቱ መለየታቸውን አቶ ዳዊት አስረድተዋል፡፡ ግሪዱን ለማዘመን እየተሰራ ላለው ሥራ አንድ አካል የሆነው የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የግንባታ ሥራ ጂኢ ሲኖ ሀይድሮ ኮንሶርቲዮም በተሰኘ ኩባንያ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የዋናው መቆጣጠሪያ ክፍልና የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤት የመሰረት ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ግሪዱን የማዘመን ሥራዎች ከሳይበር ሴኩሪቲ የሥራ ክፍል ጋር በመቀናጀት እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 19 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+4

በጣቢያዎቹ የተጀመረው የአፈር መናድ መከላከያ ግንብ እና የመንገድ ጥገና ሥራ 60 ከመቶ ላይ ደርሷል ……///…... በአዋሽ 2ኛ እና 3ኛ የውሃ ማመንጫ ጣቢያዎች አገናኝ መንገድ ላይ እየተከናወነ ያለው የአፈር መናድ መከላከያ ግንብ ሥራ እና የመንገድ ጥገና ሥራ 60 ከመቶ መጠናቀቁን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኮንስትራክሽን ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የሲቪል ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ግርማ መንገሻ እንደተናገሩት ሁለቱን ማመንጫ ጣቢያዎች በሚያገናኘው መንገድ የተለያዩ ቦታዎች ላይ የተከሰተውን የመሬት መንሸራተት ችግር የሚቀርፉ የጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የጥገና ሥራው 90 ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ከፍታ፤ 15 ሜትር ርዝመት እና 2 ሜትር ከ40 ከፍታ፤ 21 ሜትር ርዝመትና 8 ነጥብ 4 ሜትር ከፍታ፤ 15 ሜትር ርዝመትና 4 ሜትር ከፍታ ያለው የአፈር መናድ መከላከያ ግንብ ሥራ እንዲሁም 127 ሜትር ርዝመትና 4 ሜትር ስፋት ያለው የመንገድ ጥገና ሥራዎችን እንደሚያጠቃልል ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 15 ሜትር ርዝመትና 2 ነጥብ 4 ሜትር ከፍታ እንዲሁም 15 ሜትር ርዝመትና 4 ሜትር የሚሆነው የአፈር መንሸራተት መከላከያ ግንብ ሥራ መጠናቀቁን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ 90 ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ከፍታ እንዲኖረው ተደርጎ እየተከናወነ ከሚገኘው ግንባታ ውስጥ 72 ሜትር የሚሆነው መጠናቀቁን አስታውቀዋል፤ ይህም የፕሮጀክቱን የግንባታ ሥራ አፈጻጸም 60 ከመቶ አድርሶታል ነው ያሉት፡፡ ኢንጂነር ግርማ እንዳሉት የአፈር መናድ መከላከያ የግንባታ ሥራው እንደተጠናቀቀ የመንገድ ጥገና ሥራው የሚጀመር ይሆናል፡፡ መምሪያው በ20 ሚሊየን ብር አካባቢ እያከናወነ ያለው ግንባታ በውጭ ሥራ ተቋራጭ ይሰራ ቢባል እስከ 70 ሚሊዮን ብር ያስወጣ እንደነበርም ጠቁመዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይት ኢንጂነር መስፍን ገዛኸኝ በበኩላቸው የግንባታ ሥራው የሚከናወንበት ቦታ አለታማ በመሆኑ፣ የመሰረት ቁሮው ጊዜ በመውሰዱ እና በየጊዜው በሚስተዋላው የዋጋ መናርና የገበያ መለዋወጥ ምክንያት ዕቃዎች በተፈለገበት ጊዜ መገኘት ባለመቻላቸው ፕሮጀክቱን በፕሮግራሙ መሰረት ማጠናቀቅ አልተቻለም ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱን እስከ ሰኔ 2015 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት አጠናቆ ለማስረከብ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነም ተናግረዋል፡፤ የአዋሽ 2ኛ እና 3ኛ ማመንጫ ጣቢያዎች 50 ዓመት አካባቢ አገልግሎት የሰጡና እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው የማመንጫ ጣቢያዎች ናቸው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ.ም

ለክቡራን ደንበኞቻችን እና የተቋማችን ሠራተኞች በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅ ከመጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 12:30 እስከ 1:00 በኦሮምኛ ቋንቋ ቴሌቭዥን ቻናል እንዲሁም ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት እንድትከታተሉ ጥሪ ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ ይሁንና ዛሬ ይቀርባል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ፕሮግራም የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከጉራጌ ዞን የህዝብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱት ውይይት ሲቀርብ ሰዓቱ ስለተገፋ ሊተላለፍ ባለመቻሉ ፕሮግራሙን ለጠበቃችሁ ደንበኞቻችን እና የተቋማችን ሰራተኞች ይቅርታ እየጠየቅን ሳምንት በተጠቀሰው ሰዓት የሚቀርብ መሆኑን እናስታውቃለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

በሥራ ላይ ደህንነትና ጤና አጠባበበቅን ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ ……..///…….. በሥራ ላይ ደህንነትና ጤና አጠባበቅ ዙሪያ የአሽከርካሪዎችን ክህሎትና አቅም የሚያሳድግ ስልጠና መሰጠቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የማዕከላዊ ሪጅን 3 ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደተናገሩት ስልጠናው አሽከርካሪዎች የስራ ላይ ደህንነትና የጤና አጠባበቅ ሥርዓትን እንዲተገብሩ ለማድረግ ያለመ ነው። አደጋ ተከላክሎ ማሽከርከር በሚል ርዕስ ለሦስት ቀናት ያህል በኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን ኮሌጅ መምህራን ሲሰጥ መቆየቱን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ ሠልጣኞች ከስልጠናው በቂ ዕውቀትና ልምድ መቅሰማቸውን ተናግረዋል፡፡ ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ ከ45 ዓመት በላይ እንደሰሩ የገለፁት አቶ ቦጋለ ዘላለም እንዲህ ዓይነት ስልጠና ሲወስዱ ለመጀመሪያ ጊዜያቸው እንደሆነና ስልጠናው ሙያን ከማሳደግ ባለፈ አዕምሮን እንደሚያድስ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ይህን መሰል ስልጠና መዘጋጀቱ ለተቋሙም ሆነ ለሠራተኞቹ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። ሌላኛው የስልጠናው ተሳታፊ አቶ ታሪኩ ገ/እግዚአብሔር በበኩላቸው በስልጠናው መሠረታዊ ዕውቀትና ልምድ እንደቀሰሙበት ገልፀዋል። በስልጠናው ላይ 20 የሚሆኑ የማዕከላዊ ሪጅን 3 እና የፍሊት ማኔጅመንት መምሪያ አሽከርካሪዎች የተሳተፉበት ሲሆን ስልጠናውን ለአመቻቸው ለሪጅኑ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋሙ ሴት ሠራተኞች የተሳተፉበት የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች ሩጫ ተካሄደ ....///..... መነሻና መድረሻውን አዲስ አበባ ቦሌ - አትላስ አካባቢ አድርጎ በተካሄደው የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴት ሠራተኞች  መሳተፋቸውን የተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ  እንደገለፁት ሴቶች በማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፍ ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ከፍ ማድረግ ይገባል። "ቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄ" በሚል መሪ ቃል በተካሔደው የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ 200 የሚደርሱ የተቋሙ ሴት ሠራተኞች መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ሠራተኞቹ በሩጫ ውድድሩ መሳተፋቸው ሴቶች ካለባቸው የሥራ እና የቤተሰብ ኃላፊነት ባሻገር በስፖርቱ ዘርፍ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያሳድግ ገልፀዋል። ተሳታፊዎቹ በሩጫ ውድድሩ ላይ የተቋማቸውን ገፅታ የመገንባት ሚና መጫወታቸውንም ነው ጨምረው ያብራሩት። ተቋሙ ሴት ሠራተኞቹ የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ  200 የመሮጫ ቲ-ሸርቶችን ገዝቶ ማበርከቱን ወ/ሮ ሌንሴ ገልፀዋል። እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ ከአደባባይ በዓሉ ባለፈ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመቀነስ አስተሳሰብ ላይ መስራት ይገባል። የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ አትሌቶች፣ 15 ሺህ የጤና ሯጮች፤ እንዲሁም አምባሳደሮች ተሳትፈዋል። በውድድሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ሥላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ አትሌት ለተሰንበት ግደይን ጨምሮ የተለያዩ አትሌቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም

ለክብራን ደንበኞቻችን እና የተቋማችን ሠራተኞች በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን መከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከተቋሙ ማህበራዊ ሚዲያና የህትመት ውጤቶች እንዲሁም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በየሳምንቱ በዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ ቋንቋ በየአስራ አምስት ቀኑ ከሚዘጋጀው ህትመት በተጨማሪ ሳምንታዊ የሬዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞችን አዘጋጅቷል። በመሆኑም መላው የተቋማችን ሠራተኞች፣ አመራሮች፣ ደንበኞቻችንና አጋሮቻችን በሙሉ  ከመጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ  ከምሽቱ 12:30 እስከ 1:00 በኦሮምኛ ቋንቋ  በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የቋንቋዎች ቻናል እንዲሁም  ዘወትር  አርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት እንድትከታተሉ  በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም

I am Ethiopian: ለክብራን ደንበኞቻችን እና የተቋማችን ሠራተኞች በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን መከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከተቋሙ ማህበራዊ ሚዲያና የህትመት ውጤቶች እንዲሁም በአዲስ ዘመን በየሳምንቱ በዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ ደግሞ በየአስራ አምስት ቀኑ ከሚዘጋጀው ህትመት በተጨማሪ ሳምንታዊ የሬዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞችን አዘጋጅቷል። በመሆኑም መላው የተቋማችን ሠራተኞች፣ አመራሮች፣ ደንበኞቻችንና አጋሮቻችን በሙሉ  ከመጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 12:30 እስከ 1:00 በኦሮምኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የቋንቋዎች ቻናል እንዲሁም  ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት እንድትከታተሉ በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም Fish EEP PR: ለክብራን ደንበኞቻችን እና የተቋማችን ሠራተኞች በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን መከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከተቋሙ ማህበራዊ ሚዲያና የህትመት ውጤቶች እንዲሁም በአዲስ ዘመን በአማርኛ በየሳምንቱ በዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ በየአስራ አምስት ቀኑ ከሚዘጋጀው ህትመት በተጨማሪ ሳምንታዊ የሬዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞችን አዘጋጅቷል። በመሆኑም መላው የተቋማችን ሠራተኞች፣ አመራሮች፣ ደንበኞቻችንና አጋሮቻችን በሙሉ  ከመጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ  ከምሽቱ 12:30 እስከ 1:00 በኦሮምኛ ቋንቋ  በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የቋንቋዎች ቻናል እንዲሁም  ዘወትር  አርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት እንድትከታተሉ  በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በዞኖቹ የተከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመፍታት እየተሰራ ነው ……..///……. በምዕራብ ጎጃም እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተውን የኃይል መቋረጥ ችግር ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አስታወቁ፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንዳስታወቁት በሰሜን አቸፈር፣ ሻውራ፣ ሊበን፣ ዱር ቤቴ እና መውጫ ድረስ ባሉ አካባቢዎች እየተስተዋለ ያለው የኃይል መቆራረጥ በበለስ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ ችግር በማጋጠሙ ነው፡፡ የተከሰተውን ችግር ለመፍታት በተቋሙ የሚመለከታቸው የዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች ያሉበት ቡድን ተቋቁሞ እየተሰራ እንደሆነም አንስተዋል፡፡ ባጋጠመው ችግር እና ችግሩ በሚፈታበት ሁኔታ ላይ ከአካባቢዎቹ የማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት መካሄዱንም አቶ ሙላት ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ሙላት ገለጻ በአካባቢው የተከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመፍታት የአጭር፣ የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜ ዕቅዶች ተቀርፀው እየተሰራ ይገኛል፡፡ ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ዳንግላ አካባቢ የሚገኘውን የማከፋፈያ ጣቢያ አቅም ለማሳደግ ከፍተኛ አቅም ያለው ትራንስፎርመር ዝግጁ የማድረግ እና ትራንስፎርመሩ ለሚቀመጥበት ቦታ የመሰረት ቁፋሮ ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡ በአካባቢዎቹ የሚስተዋለውን የኃይል እጥረት በመካከለኛ ጊዜ ለመፍታት ከጃዊ - በለስ ስኳር ፋብሪካ ተረፈ ምርት ተጨማሪ ኃይል ለማግኘት ከፋብሪካው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት መደረጉን አቶ ሙላት ገልጸዋል፡፡ አካባቢዎቹ እስከ ሚያዝያ ወር መጀመሪያ ባሉት ቀናት ኃይል በዳንግላ ማከፋፈያ ጣቢያ ከተጀመረው የማስፋፊያ ሥራ በጊዜያዊነት እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ችግር የገጠማቸውን ትራንስፎርመሮች በአምራች ድርጅቱ እንዲጠገን በማድረግ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ኤክስ ዲ (XD) ከተሰኘ የቻይና ኩባንያ ጋር ውል ተገብቶ ሥራ መጀመሩንም ነው ኃላፊው የተናገሩት፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ ካለው ሥራ በተጨማሪ በሻውራ አካባቢ አዲስ የማከፋፈያ ጣቢያ ለመገንባት የአዋጭነት ጥናት መጀመሩን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ ህብረተሰቡ እስከ አሁን ያሳየውን ትዕግስት በማድነቅ ተቋሙ ችግሩን እስኪፈታ ድረስ አጠናክሮ እንዲቀጥል አቶ ሙላት ጠይቀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በጎንደር- አዘዞ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው …......///…...... በጎንደር - አዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የአቅም ማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ይገርማል ማሩ እንዳስታወቁት የፓወር ትራንስፎርመር የአቅም ማሻሻያ ሥራው ጣቢያው የነበረውን 8 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ወደ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር ለማሳደግ ያለመ ነው። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የነበሩት ትራንስፎርመሮች ከፍተኛ ጭነት ለመሸከም አቅም ያልነበራቸው እና ረጅም ርቀት ተጉዘው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸግሩ በመሆኑ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ችግር ያጋጥም እንደነበር ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። የአቅም ማሻሻያ ሥራው በከተማዋ አንገብጋቢ ጥያቄ ሆኖ የቆየውን የ33 ኪሎ ቮልት መስመር የኃይል መጨናነቅ ችግር ለመፍታት እንደሚያስችል ጠቁመዋል። እንደ አቶ ይገርማል ገለፃ ሪጅኑ ለከተማዋ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት አቅሙ ከፍ ያለ ፓወር ትራንፎርመር በማምጣት የአቅም ማሻሻያ ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል። የአቅም ማሻሻያ ሥራው በአራት ወጪ መስመሮች በ33 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመስጠት ትልቅ እገዛ ያደርጋል ያሉት ሥራ አስኪያጁ ወደፊት በከተማዋ የሚገኙ አዳዲስና ነባር ኢንዱስትሪዎች ለሚያቀርቧቸው የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው የገለፁት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከዚህ ቀደም ለህብረተሰቡ በቀጥታ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሁለት ባለ 23፣ አንድ ባለ 20 እና አንድ ባለ 8 ነጥብ 4 በድምሩ 74 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው የ15 እና የ33 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመሮች ነበሩት፡፡ ከአቅም ማሻሻያ ሥራው ጎን ለጎን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ያለበትን የሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አቶ ይገርማል ጠቁመዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የተቋሙን የሰው ኃይል አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ሥምምነት ተፈረመ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍሎሪዳ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋር የሰው ኃይል አቅም ለማሳደግ የሚያስችል የመግባቢያ ሥምምነት ተፈረሙ፡፡ ሥምምነቱ በአጫጭር ሥልጠናዎች፣ በማስተርስ ዲግሪ እና በጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ሥራ ለመስራት ያለመ ነው፡፡ ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የፍሎሪዳ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክና ምርምር ጉዳዮች አሶሼት ምክትል ፕሬዝደንት ዶክተር አየናቸው አሰፋ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተቋሙ ትልቅ ሀገራዊ ለውጥ የሚያመጣና ግዙፍ ኢኮኖሚን የሚያንቀሳቅስ በመሆኑ ይህን ታሳቢ ያደረገ ብቁ የሰው ኃይል ለመገንባት ሥምምነቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከዩኒቨርሲቲው ጋር የተደረገው ሥምምነትም የተቋሙን አቅም የሚያሳድግና ሀገራዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያግዝ እንደሚሆን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና ምርምር ጉዳዮች አሶሼት ምክትል ፕሬዝደንት ዶክተር አየናቸው አሰፋ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ከተቋሙ ጋር ባደረገው ሥምምነት መሠረት ተቋሙን ወደፊት በሚያራምዱና ተጨባጭ ለውጦችን በሚያመጡ የአቅም ማጎልበቻ ሥራዎች ላይ በጋራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በኢትዮጵያ ከሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ጋር ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚያስችሉ ሥልጠናዎችን በመስጠት፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በመስራትና የተለያዩ የቢዝነስ አማራጮችን በማማከር እንደሚገኝ ምክትል ፕሬዚደንቱ አስታውሰዋል፡፡ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችም በፕሮጀክት ማኔጅመንት በማስተርስ መርሃ ግብር የኦላይን ሥልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ የተደረገው ሥምምነት ለአምስት ዓመት የሚቆይና ከአሁን በፊት የነበረውን የጋራ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እንደሚረዳ ተገልጿል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+7

ሴቶች የሚያገኙትን ዕድል ሳያባክኑ በአግባቡ እንዲጠቀሙበት ጥሪ ቀረበ ………////……. ሴቶች የሚያገኙትን ዕድል ሳያባክኑ በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ። በተቋሙ የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ሲያከብሩ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢዴኤ እንደተናገሩት ዕለቱ መከበሩ በሴቶች ላይ እየደረሱ ያሉ ጫናዎችን ለመቀነስና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ዕድል ይፈጥራል። ተቋሙ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ የድጋፍ እርምጃዎችን ተግባራዊ እያደረገ ቢሆንም አንዳንድ ሠራተኞች የድጋፍ እርምጃዎችን በአግባቡ እየተጠቀሙ እንዳልሆነ ዳይሬክተሯ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ሴቶች በተሰማሩበት መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ ተቋሙ ያስቀመጣቸውን የድጋፍ እርምጃዎች በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል። የአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዐይናለም ወ/ሚካኤል በበኩላቸው በሴቶች ላይ ያለውን የተንሸዋረረ ዕይታ ለመቀየር ሁሉም በየተሰማራበት የሥራ ዘርፍ ተግቶ በመስራት ውጤታማነቱን በተግባር ማሳየት ይኖርበታል ብለዋል ። በበዓሉ ወቅት ሥርዓተ-ፆታ እና በሴቶችና በወንዶች መካከል ስላለው አመለካከት በተመለከተ በአዳማ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት መምሪያ የሴቶች ብቃት ባለሙያ በሆኑት ወ/ሮ ጠይባ ጅማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፍ አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል። በዕለቱም ከደረጃ ዕድገት፣ ከደመወዝና ግሬድ ማሻሻያ፣ በጣቢያው የህፃናት መቆያ በሚቋቋምበት ሁኔታ እና ሌሎች መሻሻል አለባቸው የሚሉ ጥያቄዎች ከሠራተኞች ተነስተው ምላሽ ተሰጥቷቸዋል። በሠራተኞች የሚነሱ ጥያቄዎች ተቋሙ ወደፊት በሚያደርገው የደመወዝና የግሬድ ማሻሻያ ጥናት እልባት እንደሚያገኝ በኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ የሰው ኃይል አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ገነት ሙሉጌታ አስታውቀዋል። ከሠራተኞች የተነሱ ጥያቄዎችን ከሚመለከተው የሥራ ክፍል ጋር በመቀናጀት ለመፍታት እንደሚሰሩ ወ/ሮ ሌንሴ አረጋግጠዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የደቡብ ሪጅን 1 እና 2 ሴት ሠራተኞች በወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ስቴሽን ዕለቱን አክብረዋል፡፡ የሪጅኑ የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ ወይዘሮ ምስራቅ ገብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ሁሉም ሠራተኛ የተቋሙን የህብረት ስምምነት አውቆ መብትና ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የደቡብ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እና የደቡብ ሪጅን 2 ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ በበኩላቸው ሴቶች ራሳቸውን በማብቃት በሁሉም የሥራ ዘርፎች ተወዳዳሪ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ ዓለም አቀፋ የሴትች ቀን በዓለም ለ112ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ47ኛ ጊዜ "ለእህቴ ጠባቂ እኔ ነኝ" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 08 ቀን 2015 ዓ.ም

EEP Communication - Telegram 频道 @eepcommuication 的统计与分析