EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 546 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 546 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 546
订阅者
+824 小时
-227 天
+2730 天
帖子存档
15 544
ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ
እንኳን ለ2015 ዓ. ም በሰላም አደረሳችሁ!
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤናና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ!!
አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
15 544
የደጀን ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራ በተያዘው በጀት ዓመቱ ይጠናቀቃል
……../////……….
የደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራ በ2015 በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ኤሌክትሮ መካኒካል ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ተድላ ሰይፉ እንደገለፁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥንድ ገቢ መስመር፣ አምስት ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው 63 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ባለ 230/66/15 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር እና 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር ያሉት በመሆኑ እስከ አንድ መቶ ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም አለው፡፡
በራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ቢሮ እየተገነባ የሚገኘው የደጀን ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የስዊች ያርድ ተከላ ስራ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ሁለት ባዝባሮችን ለማገናኘት የሚያገለግለው (coupler bay) እና የሰዎችንና መሳሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያገለግለው (earthing system) ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
እስካሁን በተከናወኑት ሥራዎች የፕሮጀከቱ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራ አፈፃፀም 52 ነጥብ 8 በመቶ መጠናቀቁን ኢንጂነር ተድላ ገልፀዋል።
የግንባታ ግብዓት በተለይም የሲሚንቶ አቅርቦት እጥረት የግንባታ ሂደቱን ፈታኝ ካደረጉት ችግሮች መካካል አንዱ መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ተድላ ችግሩንም ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት መደረጉን ተናግረዋል፡፡
የጣቢያው መገንባት በቢቸና የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ያለውን የኃይል መጨናነቅ ከማስቀረቱ በተጨማሪ ለደጀን ከተማ ነዋሪዎችና በአካባቢው ለሚገኙ ኢንደስትሪዎች እንዲሁም ለተለያዩ ወረዳዎችና ዞኖች የኤሌክትሪክ ኃይል መስጠት የሚያስችል ነው፡፡
የደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አጠቃላይ አፈፃፀም 54 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጳጉሜን 02 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
ፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ 740 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዷል
..........///........
የፊንጫ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2015 በጀት ዓመት 740 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ማቀዱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በጽ/ቤቱ የፕላኒንግ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለፁት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ግድብ ኃይል ለማመንጨት የሚያስፈልገውን ውሃ በመገባደድ ላይ ባለው የክረምት ወራት ሙሉ ለሙሉ ይዟል።
ይህም ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችለው ሥራ አስኪያጇ አስታውቀዋል።
የኃይል ማመንጫው እያንዳንዳቸው 33 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ተርባይኖች ሲኖሩት በሶስቱ ተርባይኖች 100 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ላይ ይገኛል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ አንደኛው ተርባይን ለጊዜው ለጥገና ሥራ የቆመ ሲሆን በተያዘው በጀት ዓመት የጥገና ሥራውን የሚጀመር ይሆናል።
የፊንጫ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአሮሚያ ብሔራዊ ከልላዊ መንግስት ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጳጉሜን 01 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
ተቋሙ በኤሌክትሮ ሜካኒካል ያሰለጠናቸውን ቴክኒሺያኖች አስመረቀ
........./////.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለስድስት ወራት ያህል በኤሌክትሮ ሜካኒካል ያሰለጠናቸውን 27 ወንድ እና 4 ሴት ሰልጣኝ ቴክኒሺያኖችን በግዮን ሆቴል አስመርቋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ለተመራቂዎች እና ለተመራቂ ቤተሰቦች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ወንደሰን ካሳ እንደተናገሩት የተቋሙ ማሰልጠኛ ማዕከል ላለፉት 61 ዓመታት ሙያዊ ስልጠናዎችን በመስጠት ለሀገር አቀፍ ኃይል ልማት ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያዎችን አበርቷል።
ከፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የስልጠና ማዕከሉን በህንጻ፣ በማቴሪያል፣ በአሠራርና በቴክኖሎጂ ይበልጥ ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ተቋሙ የተመሰረበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ እንዲያግዘው በዘርፉ በዕውቀት እና ክህሎት የዳበረ የሰው ኃይል ለማፍራት እየሰራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደ አዲስ ከተቋቋመበት ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ ማሰልጠኛ ማዕከሉ ለ7ኛ ጊዜ ሰልጣኞች ማስመረቁን ያወሱት አቶ ተማም ተመራቂዎቹ ወደ ስራ በሚሰማሩበት ወቅት ከነባር ሙያተኞች ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራ እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል።
የኃይል ማመንጫ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ዮናስ ተስፋዬ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሀገራዊ የኃይል አቅርቦት ባሻገር አፍሪካን በኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ለማስተሳሰር እየሰራ የሚገኝ አንጋፋ ተቋም መሆኑን ገልፀው ተመራቂዎችም ይህንን ታሳቢ በማድረግ ለትልቅ ዓላማና ግብ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ደረጀ ገዛኸኝ በበኩላቸው ተመራቂዎች ወደ ሥራ ስትገቡ የሥራ ደህንነትን ባከበረ መልኩ በትጋትና በብቃት ልትሰሩ ይገባል ብለዋል።
ተመራቂዎቹ ከምረቃ ማግስት በኃይል ማመንጫዎች እና በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ወደ ስራ የሚሰማሩ በመሆናቸው ከስራቸው ጎን ለጎን ማኑዋሎችን በማንበብ ራሳቸውን ማብቃት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።
የተቋሙ መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ማህበሩ በሥነ ስርዓቱ ላይ ተመራቂዎች የማህበሩ አባል በመሆን ለሠራተኛው ብሎም ለተቋሙ የጋራ ተጠቃሚነት እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የተማሪዎች ተወካይ ወጣት መሠረት ፋንታሁን በበኩሉ ስልጠናውን የሰጡት መምህራን ሰልጣኞቹ በእውቀትና በክህሎት የዳበረ አቅም እንዲኖራቸው ላደረጉት ጥረት በተመራቂዎች ስም ምስጋናውን አቅርቧል።
በቀጣይ ለሥራ በሚሰማሩበት ቦታ ሁሉ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በትጋትና በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጧል።
ተመራቂዎቹ በስድስት ወራት ቆይታቸው በንፋስ ኃይል ቴክኖሎጂ፣ በአይሲቲ፣ በኤሌክሪሲቲ፣ በዲዝል ቴክኖሎጂ፣ በሙያ ደህንነት እና በውሀ ኃይል የሙያ መስኮች በቂ ዕውቀትና ክህሎት ማግኘታቸውን በምረቃ ስነስርአቱ ላይ ተገልጿል።
የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች እና መምህራን የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 29 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
............////.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ውይይቱ መንግስት ሠላምን ለማስከበር እያደረገ ያለውን ጥረት፣ ከለውጡ በኋላ የታዩ ፖለቲካዊ ለውጦችና በአሸባሪው የህወኃት ቡድን ለሦስተኛ ጊዜ የተከፈተውን ጦርነት ለመመከት መንግስት በጀመረው እርምጃ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው።
ሀገራዊ ለውጡ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ለውጦች እንዲመጡ እድል እንደፈጠረ የጠቆሙት ኃላፊው ለውጡን ያልተቀበለው የአሸባሪው የህወኃት ቡድን ግን የትግራይን ህዝብ መደበቂያ በማድረግ ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት መጀመሩን ተናግረዋል።
መንግስት ከቡድኑ ጋር ያለውን የፖለቲካ ልዩነት በሠላማዊ መንገድ ለመፍታት የተለያዩ አማራጮችን በማስቀመጥ ሲስራ እንደነበርም አስታውሰዋል።
ይሁን እንጅ የሽብር ቡድኑ የመንግስትን የሠላም ጥሪ ወደ ጎን በመተው ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነትን ማወጁ ለሰላም ፍላጎት እንደሌለው ያሳያል ብለዋል።
መንግሥት የያዘው የሠላም አማራጭ ምንጊዜም የማይዘጋ እንደሆነ ያነሱት አቶ ሙላት የሽብር ቡድኑ ይህን የማይቀበል ከሆነ ግን የህዝቡን ሰላም ለማረጋገጥና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ ገልፀዋል።
የመንግሥት የሠላም አማራጭና ጥሪ አሁንም የማይዘጋ እንደሆነና ከቡድኑ ጋር ያለውን ልዩነት በሠላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል።
የሽብር ቡድኑ ወደ ሠላም አማራጭ እንዲመለስ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጫና እንዲያደርጉ ግፊት ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
አሸባሪው ቡድን የከፈተውን ጦርነት በድል ለማጠናቀቅ ሁሉም ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች መንግስት ለሰላም የሰጠውን ዋጋ አድንቀው ለዜጎች ደህንነት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
እያንዳንዱ የመንግስት ሠራተኛና ዜጋ በተሰማራበት መስክ ኃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት ለሀገሩ የድርሻውን እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል።
በውይይቱ ላይ ከሠራተኞች አስተያየቶችን ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የተቋማዊ ባህል የአሰራር ሥርዓት ማሻሻያ ጥናት ተጠናቀቀ
………….///………..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ልማት መምሪያ ሲካሄድ የቆየው የተቋማዊ ባህል እና ግብ ተኮር የቡድን አሰራር ሥርዓት ማሻሻያ ጥናት መጠናቀቁን በመምሪያው የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ አንዷለም ኪዳኔ እንደገለፁት የጥናቱ ዓላማ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተቋማዊ ባህልን በጥናት በመዳሰስ የቡድን አሰራር ባህሉን ለማጎልበት የሚያስችሉ ሀሳቦችንና አማራጮችን ለማመላከት ነው፡፡
በተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ አማካኝነት የተከናወነው ጥናት በተቋሙ የኮርፖሬት ቢዝነስ አስተሳሰብን ለማሳደግና ተፈላጊ ተቋማዊ ባህልን ለማዳበር የሚያስችሉ አማራጮችን የሚያመላክት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የጥናቱ መጠናቀቅ ተቋሙ እያከናወነ ላለው ሁለንተናዊ ለውጥ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት መሆኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ለአንድ ተቋም ውጤታማነት ተቋማዊ ባህል ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ተቋማዊ ባህልን ለመገንባት የሚያስችሉ የአፈፃፀም ሥራ አመራር፣ የምዘና፣ የሽልማትና ማበረታቻ ሥርዓትን ለማሳደግ መመሪያዎችን የመከለስ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በተቋም ደረጃ የተቋማዊ ባህል እና ግብ ተኮር የቡድን አሰራር ሥርዓት ማሻሻያ ጥናት መተግበሩ ተቋማዊ አሰራሮችና የሥራ አመራር ተግባራትን ድርሻ የሚያጎላ ነው፡፡
ይህም የተቋሙ ዕቅድ እርስ በርስ የተናበበ እንዲሆንና የቡድን አስተሳሰብ እንዲጎለብት እንደሚያደርግ አቶ አንዷለም አስረድተዋል፡፡
ሥራ አስኪያጁ እንዳብራሩት ከጥናቱ በተጨማሪ በተቋሙ ተፈላጊ የሆነውን ግብ ተኮር ባህልና የቡድን አሰራር ለማጎልበት የሚያስችሉ የአመራር አቅም ግንባታ ፕሮግራምች፣ የአመራር ዘዬ የሚያንፀባርቅ የስራ መሪዎች መጽሐፈ ዕድ(Managers Handbook)፣ የስራ መሪዎች ስልጠናና ልማት እንዲሁም የአፈፃጸም ምዘናዎችን የሚመለከቱ ረቂቅ መመሪያዎች ተዘጋጅተዋል፡፡
በጥናቱ የተመለከቱ እርምጃዎችን እስከ ቡድን ድረስ ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ስልቶችን በመንደፍ ትግበራ መጀመሩን ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል፡፡
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የደቡባዊ ኤሌክትሪሲቲ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት ተፈረመ
........////.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለደቡባዊ ኤሌክትሪሲቲ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ ለማከናወን ሀዮሰንግ ኮርፖሬሽን ከተሰኘ የኮሪያ ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የሀዮሰንግ ኮርፖሬሽን ተወካይ ሚስተር ሀዩንግ ሶ ዩ ናቸው።
ከኩባንያው ጋር የተደረገው ስምምነት በደቡባዊ የኤሌክትሪክሲቲ ግሪድ ላይ አዳዲስ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመገንባትና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራዎችን ለማከናወን ነው፡፡
ስምምነቱ 420 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታና የሦስት አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የዲዛይን፣ ዕቃዎችን የማምረትና የማቅረብ፣ የመገንባት፣ የሙከራና ፍተሻ ሥራዎችን ለማከናወን እንዲሁም የሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራዎችን ያጠቃልላል።
በፕሮጀክቱ ከወላይታ ሶዶ - ሽግዳን ባለ 230 ኪሎ ቮልት፣ ከሽግዳን - ጥርጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት፣ ከወላይታ ሶዶ -ሽግዳን ከሚዘረጋው መስመር ላይ ተቀጥሎ ወደ አርባ ምንጭ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እንዲሁም አዲስ ከሚገነባው አርባ ምንጭ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ነባሩ አርባ ምንጭ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ የሚዘረጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመሮቹ የሚገነቡ ይሆናል፡፡
በተቋሙ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ግንባታ ፕሮግራም አንድ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሁለት ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር እንደተናገሩት ከወላይታ ሶዶ -ሽግዳን የሚዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር 240 ኪሎ ሜትር፣ ከሽግዳን- ጥርጋ የሚዘረጋው 77 ኪሎ ሜትር ይኖረዋል።
በተጨማሪም ከወላይታ ሶዶ-ሽግዳን ከሚዘረጋው መስመር ላይ ተቀጥሎ ወደ አርባ ምንጭ የሚዘረጋው 93 ኪሎ ሜትር እንዲሁም አዲስ ከሚገነባው አርባ ምንጭ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ወደነባሩ አርባ ምንጭ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ 10 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንደሚኖረው ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
በደቡብ ኦሞ ሽግዳን ከተማ ላይ ባለ 230 ኪሎ ቮልት፣ በአርባ ምንጭ ከተማ ላይ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እና በደቡብ ኦሞ አካባቢ ጥርጋ በሚባል ቦታ ላይ ባለ 132 ኪሎ ቮልት አዲስ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡም አስታውቀዋል።
በነባሮቹ የአርባ ምንጭ 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት እና በወላይታ ሶዶ 2 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የአቅም ማሳደግና የማስፋፊያ ሥራ እንደሚከናወን ነው የገለፁት፡፡
የፕሮጀክቱን ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱንና የፕሮጀክቱ በጀት ሙሉ በሙሉ ከኮሪያ ኤክዚም ባንክ በተገኘ ከ178 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሆነ ብድር እንደሚሸፈን ስምምነት መደረጉን አቶ መሐመድ ገልፀዋል፡፡
ከዲዛይን ጀምሮ ያሉ የፕሮጀክቱን የተለያዩ ሥራዎችን ለማመከር ባዩክሳ ፓወር (Byucksa power Co.Ltd) የተሰኘ የኮሪያ ኩባንያ ተቀጥሮ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የፕሮጀክቱ መገንባት ፕሮጀክቶች በሚከናወኑበት አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እና በደቡብ ኦሞ አካባቢ ለሚገኙ የስኳር ፋብሪካዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያለመ በመሆኑ በተያዘው በጀት እና ጊዜ እንዲጠናቀቅ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
በ2015 በጀት ዓመት አምስት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ታቅዷል
………///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 በጀት ዓመት የአንድ ኃይል ማመንጫ እና አራት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶች ግንባታ አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት ማቀዱን አስታወቀ፡፡
በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱአለም ሲአ እንደገለፁት አሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ እንዲሁም ደጀን ደብረማርቆስ፣ ቡታጅራ ወራቤ እና ጊቤ 3ኛ-አዲስ አበባ 2ኛ ሰርኪዩት በተያዘው በጀት ዓመት ይጠናቀቃሉ ተብለው የተያዙ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡
በመጀመሪያው ምዕራፍ 72 ሜጋ ዋት እንደሚያመነጭ የሚጠበቀው አሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ ፕሮጀክት አጠቃላይ ሥራው 81 ነጥብ 48 በመቶ መድረሱንና ቀሪውን ግንባታ በበጀት ዓመቱ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አቶ አንዱአለም ገልፀዋል፡፡
በነባሩ የጊቤ 3ኛ - አዲስ አበባ መስመር ላይ አንድ ሰርኪዩት ለመጨመር ታስቦ የሚገነባው ፕሮጀክትም 86 ነጥብ 21 በመቶ ደርሷል፡፡
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ደጀን ከተማ በመገንባት ላይ የሚገኘውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከደጀን ደብረማርቆስ በመዘርጋት ላይ ያለውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርም በበጀት ዓመቱ በማጠናቀቅ ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው፡፡
በተጨማሪም 12 ነጥብ 5 በመቶ አፈፃፀም ላይ የደረሰውን የቡታጂራ ወራቤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ መታቀዱንም ነው አቶ አንዱአለም የገለፁት፡፡
የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ፕሮግራም 2 ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ደስታለም ኃይሉ በበኩላቸው የቡታጅራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የዲዛይን ስራ ተጠናቆ የሲቪል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ በዕቅድ ለተያዙ ፕሮጀክቶች የሚውል የሎጂስቲክስ አቅርቦት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ ደስታለም የሲሚንቶ እጥረት እንዳያጋጥምም ከዞንና ወረዳ አስተዳደር አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራን ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም በኤሌክትሪካል መሀንዲስ 1ኛ፣ በሜካኒካል መሀንዲስ 1ኛ፣ በሲቪል መሀንዲስ 1ኛ፣ በኮንትሮልና ኢንስትሩመንቴሽን መሀንዲስ 1ኛ እና በኃይድሮሎጂስት 1ኛ የስራ መደቦች በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ሜክሲኮ ኬኬር በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት ህንጻ 2ኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡
15 544
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በኦፊስ ሰርቪስ ፐርፎርመር 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የፅሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ኬኬር ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናስታውቃለን፡፡
15 544
ለኬንያ የሚሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን በሶስት ምዕራፎች የተከፈለ ነው
…….///……..
ኢትዮጵያ ለኬንያ የምትሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን በሶስት ምዕራፎች የተከፈለ መሆኑን የተቋሙ የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንደገለፁት 25 ዓመታት በሚቆየው የውል ስምምነት ውስጥ የሚሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ ይተገበራል፡፡
ከህዳር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ለሚቀጥሉት ተከታታይ ሶስት ዓመታት የኃይል ጭነት በማይበዛበት (Off-peak hours) የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጩ 65 ሜጋ ዋት እንዲሁም የኃይል ጭነት ከፍ በሚልበት ሰዓት (Peak hours) 200 ሜጋ ዋት እንዲሆን ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
በሁለተኛው ምዕራፍ ለሦስት ዓመታት የሚቆይ የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ይቀርባል ያሉት አቶ ህይወት በስምምነቱ መሠረት የኃይል ጭነት በማይበዛበት ሰዓት 150 ሜጋ ዋት እንዲሁም የኃይል ጭነት ከፍ በሚልበት ሰዓት 400 ሜጋ ዋት ለሽያጭ እንደሚቀርብ ገልፀዋል፡፡
በሦስተኛው እና የመጨረሻው ምዕራፍ ውሉ እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በሁሉም ሰዓታት 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ለማቅረብ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል፡፡
አንድ ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በሰዓት በ6 ነጥብ 5 የአሜሪካ ሳንቲም እንደሚቀርብ አቶ ህይወት የገለፁ ሲሆን ከአምስት ዓመታት በኃላ በተቋሙ ጠያቂነት አሁን በተደረሰው የታሪፍ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ድርድር እንደሚኖር ጨምረው አብራርተዋል፡፡
እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ኬንያ የታሪፍ ቅናሽ ጥያቄ በማቅረቧ፣ ከአስር ዓመት በፊት ስምምነት ላይ ተደርሶበት የነበረው 400 ሜጋ ዋት ላይ መጠኑ እንዲቀነስላት በመጠየቋ እና ፕሮጀክቱ በታሰበው ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ባለመደረጉ ድርድሩ እንዲዘገይ ምክንያት ሆኗል፡፡
የሁለቱ ሃገራት የኃይል ሽያጭ ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ ባሁኑ ሰዓት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን የመፈተሽ ሥራ እየተከናወነ ሲሆን በቀጣዩ ዓመት ህዳር ወር መጀመሪያ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጩ በይፋ እንደሚጀመር አቶ ህይወት ገልጸዋል፡፡
የኢትዮ - ኬንያ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ ኢትዮጵያ ለምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ለማቅረብ ላቀደችው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ከጅቡቲ ጋር የኃይል ሽያጭ እያካሔደች ሲሆን ከሶማሌ ላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሟ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 20 ቀን 2014 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
