EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 537
ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለመገንባት የሚያስችል ሥምምነት ተካሔደ
......../////.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፈረንሳዩ ጀኔራል ኤሌክትሪክ እና ከቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያዎች ጋር ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለመገንባት የሚያስችለውን ሥምምነት ትናንት ተፈራረመ፡፡
ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ፣ በምስራቅ አፍሪካ የጀኔራል ኤሌክትሪክ ንዑስ ቀጣና የሽያጭ ኃላፊ አቶ ማንያዘዋል ተስፋዬ እና የሲኖ-ሃይድሮ ተወካይ ሚስተር ቲያን ሆንግጁን ናቸው፡፡
ሥምምነቱ ሁለት ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከላት ግንባታዎች የማከናወን እንዲሁም በሁሉም የኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያና ለክትትል የሚረዱ ሥርዓቶችን የመዘርጋት ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡
የፕሮጀክቱን ግንባታ ጀኔራል ኤሌክትሪክ እና ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያዎች በጋራ የሚያካሒዱት ሲሆን የማማከር ሥራውን ደግሞ ሒፋብ የተባለ የፊንላንድ ኩባንያ እንደሚያከናውን በሥምምነቱ ላይ ተገልጿል፡፡
ፕሮጀክቱ በ3 ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ የሚገባ ሲሆን ለዚህም ከ57 ነጥብ 67 ሚሊዮን ዩሮ እና ከ102 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለታል፡፡
የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ 1/3ኛው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቀረው 2/3ኛው ደግሞ በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ እንደሚሸፈን ታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 1 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
እስከ ከሜሴ ያለው መስመር ጥገና ተጠናቋል
…….///……..
ከካራቆሬ - ከሜሴ ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ከሥርጭት ኔትወርክ መስመሮች ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ በርብርብ ሲሰራ ቆይቶ ዛሬ እስከ ከሚሴ ድረስ ያሉት ከተሞች ኃይል ማግኘት ችለዋል፡፡
ከደብረብርሃን ኮምቦልቻ ድረስ ያሉት ከተሞች በ132 እና በ230 ኪሎ ቮልት መስመሮች ኃይል ያገኙ የነበረ ቢሆንም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ይሁንና የኃይል ተጠቃሚው ህብረተሰብ በፍጥነት ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበትን ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ለጊዜው በማቆየትና ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመሩን በአስቸኳይ በመጠገን ዛሬ እስከ ከሚሴ ድረስ ያሉት ከተሞች ኃይል አግኝተዋል።
የጥገና ሥራው ወደ ደሴ ከተማ ቀጥሎ እስከ ሀርቡ ባለው አካባቢ መስመሮችን የመጠገን ሥራም እየተካሄደ ነው።
አሁን አስቸኳይ ጥገና እየተደረገለት ያለው 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የከሚሴ፣ ኮምቦልቻ እና ደሴ እንዲሁም ዓለም ከተማና በምዕራብ አፋር የሚገኙ ከተሞችን ኃይል እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው፡፡
በተያያዘ ዜና በሚሌ ባቲ ያለው መስመር ላይ ሁለት ኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች በከባድ መሳሪያ በመመታቸውና ጉዳቱ ከባድ በመሆኑ ምሶሶዎቹን እንደገና የመትከል ስራ ተጀምሯል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 30 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እየተጠገነ ነው
.......///.......
ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡
ከህዳር 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደ የፍተሻ ሥራ ሠላሳ አራት በሚሆኑ በታወሮች መካከል በሚገኙ ቦታዎች ላይ 50 የመስመሮች መበጣጠስ፣ 7 የድምፅና ዳታ ማስተላለፊያ የኦፕቲካል ፋይበር መቆረጥ እና 13 ቦታዎች ላይ መስመር ሳይበጠስ ጉዳት መድረሱን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው አካባቢዎች መካከል በሰሜን ወሎ ዞን ዋድላ ወረዳ ሥር በምትገኘው የአርቢት ቀበሌ ባለ 3 ፌዝ መሥመሮችና የኦፕቲካል ፋይበር ላይ ከፍተኛ በመጣጠስ ደርሷል፡፡
ጉዳት በደረሰባቸው መስመሮች ላይ ጥገና የተጀመረ ሲሆን ጥገናውን በፍጥነት በማጠናቀቅ አካባቢዎቹ ኃይል ማግኘት እንዲችሉ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከዚህ ቀደም አሸባሪው የህወኃት ቡድን ጉዳት ያደረሰባቸውን ከደብረታቦር እስከ ገረገራ ባሉት አካባቢዎች ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመጠገን አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 28 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ከሸዋሮቢት እስከ ካራቆሬ ባሉ ከተሞች የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮችን የመጠገን ሥራ ተሰርቷል
.......////.......
በሽብርተኛውና በወራሪው የህወኃት ቡድን ጉዳት የደረሰባቸው ከሸዋ ሮቢት እስከ ካራቆሬ ባሉት ከተሞች የሚገኙ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ተጠግነው ተጠናቀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሸዋሮቢት፣ በጀውሀ፣ በሰንበቴ፣ በአጣዬና ካራቆሬ ከተሞች የሚያልፈውን የከፍተኛ መስመር በመጠገን ለስርጭት መስመሮች ኃይል መስጠት እንዲችሉ ዝግጁ የማድረግ ሥራ አጠናቋል።
ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጀመረው የሥርጭት መስመሮች የጥገና ሥራ እንደተጠናቀቀ የተጠቀሱት ከተሞችና አጎራባች የገጠር ቀበሌዎች በፍጥነት የኤሌክትሪክ ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በቀጣዮቹ ቀናት ከካራቆሬ እስከ ከሚሴ ያለው መስመር የመጠገን ሥራ የሚሰራ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 27 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ከአዳማ ንፋስ 22 ዩኒት ደም ተሰብስቧል
……///……
የአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አመራሮችና ሠራተኞች ለተጎዱና ህይወታቸውን ለማቆየት ደም ለሚፈልጉ ወገኖቻችን የቻልነውን ድጋፍ እናደርጋለን በሚል መርህ ደም ለግሰዋል፡፡
አመራርና ሠራተኞቹ ባለፈው አርብ ባደረጉት የደም ልገሳ መርሃግብር 22 ዩኒት ደም ለግሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 27 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
የሪጅኑ ሠራተኞች የደም ልገሳ በማከናወን ላይ ናቸው
…….///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ቢሮ አመራርና ሠራተኞች የህልውና ዘመቻውን ለመደገፍና የ#በቃ ንቅናቄ አካል መሆናቸውን ለማሳየት #NoMore የሚል ሰሌዳ በመያዝ ዛሬ የደም ልገሳ በማከናወን ላይ ናቸው፡፡
የደም ልገሳው የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው በተጓዳኝ ሀገር በምትፈልጋቸው ሁሉ ለማገልገልና መስዋዕት ለመሆን ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ያለመ ነው።
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ቀደም ሲል "ደማችን ለሀገራችን" በሚል መሪ ሀሳብ ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ.ም በዋና መሥሪያ ቤቱ ደም መለገሳቸውና የወር መወዛቸውን መስጠታቸው ይታወሳል፡፡
በሪጅኖችና በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች እንደ ፓስታ፣ሩዝ፣ መኮረኒና ዘይት ያሉ ደረቅ ምግቦች፣ የንጽህና መጠበቂያ ቁሶች፣ የአልባሳትና የገንዘብ ድጋፍ በመሰባሰብ ላይ ይገኛል፡፡
በጥሬ ገንዘብ ለማስገባት ለሚፈልጉም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተከፈተውን የሂሳብ ቁጥር 1000444528129 እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 27 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮችን በመጠገን ከስርጭት መስመሮች ጋር የማገናኘት ሥራ እየተሰራ ነው
.......////.......
በሽብርተኛውና በወራሪው የህወኃት ቡድን በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የደረሰውን ጉዳት በመጠገን ከስርጭት መስመሮች ጋር የማገናኘት ሥራ እየተሰራ ነው።
ወራሪው ቡድን ለቀናት ተቆጣጥሯቸው በነበሩ አካባቢዎች ካደረሰው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት በተጨማሪ በኤሌክትሪክ መሰረተልማቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገና ባለሙያዎች በተንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በጥይት ተመተው የመበጣጠስና የምሰሶዎችን መውደቅ ተመልክተዋል።
የጥገና ሥራ በተጀመረባቸው አካባቢዎች ከለገዳዲ- ደብረብርሃን - ሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ በተዘረጋው የባለ 132 እና 230 ኪሎ ቮልት መስመር የመበጣጠሰ አደጋ ቢደርስበትም እስከሸዋ ሮቢት ያለው መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ይታወሳል።
ከሽብርተኛው ቡድን ነፃ ከወጡት አካባቢዎች መካከል ከሸዋ ሮቢት እስከ ከሚሴ ድረስ ያለውን መስመር በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት ጠግኖ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስርጭት መስመሮች ጋር በማገናኘት አካባቢዎቹ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 26 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ተባለ
…….//……..
በሀገራችን እየተካሄደ ባለው የህልውና ጦርነት ለጾታዊ ጥቃት ተጋላጭ ከሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በመሆን ከጥቃት ለመከላከል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ጥሪ አቀረቡ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ16ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን የጸረ- ጾታዊ ጥቃት ቀን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የጸረ- ሙስና እና የኤች አይቪ ኤዲስ ቀንን ዛሬ ህዳር 22 ቀን 2014 ዓ.ም በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አክብረዋል፡፡
በመርሃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በተቋሙ የሴቶች፣ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኤዲኤ እንደገለጹት በዓሉን ሲከበር በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በማሰብ እና በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎች በማድረግ ሊሆን ይገባል፡፡
በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ያለችበትን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ሁላችንም ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከልና ጥቃት የሚያደርሱ አካላትን ለህግ ለማቅረብ እንዲሁም ጥቃትን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ አሰራሮች ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
የተጀመሩ ስራዎች ውጤት ባለው መልኩ እንዲከናወኑ ለማድረግና የወጡ ህጎችን በአግባቡ በመተግበር የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማጠናከር የተቋሙ ስራ አመራር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡
ቀናቶችን ከማክበር ባለፈ ተጨባጭ ውጤቶችን ለማምጣጥ የተቋሙ ስራ አመራር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሙላት የሴቶችን ጾታዊ ጥቃት ለመከላከል ሁሉም አቅሙ በፈቀደው ሁሉ በባለቤትነት ስሜት እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡
በጦርነቱ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሰራ በመሆኑ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞች ከዚህ በፊት ካደረጉት ድጋፍ በተጨማሪ በድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ከሚደረገው ድጋፍ በተጨማሪ ከጦርነቱ በኋላ የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ተጽዕኖ ለመቋቋምና ለመቀልበስ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
"ሰላም ይስፈን- በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚደርስ ጥቃት ይቁም" በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል ላይ በሴቶች መብቶች፣ የጾታዊ ጥቃት መንስኤዎችና መከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ያደረገ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡
ጽሑፍን ያቀረቡት በኢትዮጵያ ህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር የህግ ምክር አገልግሎት ሰጭ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሪት ሠላማዊት ደሳለኝ በስራ ቦታ ላይ የሚፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል በአሰሪና ሰራተኛ እንዲሁም በመንግስት ሠራተኞች አዋጆች ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን በአግባቡ በመረዳት ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
የጸረ- ጾታዊ ጥቃት ቀን በየዓመቱ ከህዳር 16 እስከ ታህሳስ 1 ቀን ይከበራል፡፡
በተያያዘ ዜና በተቋሙ የኤች አይቪ ኤዲስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ቢሮ አስተባባሪ አቶ መስፍን ደርሶ ቫይረሱ በሀገር አቀፍ ደረጃ እያሳደረቸው ስላሉ ተጽዕኖዎች እና ተቋሙ እየሰራቸው ባሉ ስራዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
አቶ ደርሶ በማብራሪያቸው ቫይረሱን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አገልግሎቶችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ እና ለቫይረሱ ተጋላጭ በሆኑ አካላት እና አካባቢዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
አለም አቀፍ የኤች አይቪ ኤድስ ቀን በሃገራችን "አገልግሎቱን ለተጠቃሚዎች በእኩል ተደራሽ ማድረግ፣ ወረርሽኙን መግታትና መቆጣጠር" በሚል መሪቃል በመከበር ላይ የሚገኝ ሲሆን የጸረ- ሙስና ቀን ደግሞ "በስነ ምግባር የታነጸ አመራር ከሙስና የጸዳች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 22 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተመቷል በሚል በድጋሚ የሀሰት ወሬ እየተነዛበት ነው
........///........
የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በመንግስት ተመቷል በሚል በሽብርተኛው የህወኃት ቡድንና በአቀንቃኞቹ የሚናፈሰው ወሬ የሀሰት ነው።
ከዚህ ቀደምም ግድቡ ተመቷል በሚል በጥፋት ቡድኑ ተመሳሳይ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ተሰራጭቶ እንደነበር ይታወሳል።
በመንግስት የተመታው የተከዜ ግድብ ሳይሆን ተከዜን ተሻግሮ ወረራ የፈፀመው የሽብር ቡድኑ ነው።
ይሁንና የተከዜ ግድብ ባለፈው ክረምት ሙሉ በመሆኑ ውሃውን እንዲፈስ በማድረግ የሀሰት ፕሮፓጋንዳውን እውነት ለማስመሰል ጥረት ሊያደርግ እንደሚጥር ይገመታል።
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ሙያተኛ ባልሆኑ ሰዎች፣ ከታለመለት ዓላማ ውጪ እንዲሰራ ከተደረገ ከፍተኛ መጠን ያለው ጉዳት ሊደርስበት እንደሚችል ይታመናል።
በመሆኑም የሽብር ቡድኑ ህዝብን ለማሸበርና ዓለም አቀፍ ትኩረት ለመሳብ ውሃውን ሊለቅ ስለሚችል በግድቡ የታችኛው ተፋሰስ አካባቢ በተለይም በጣንቋ አበርገሌ፣ በጠለምት፣ በቃፍታ ሁመራ፣ በጠገዴ፣ በአበርገሌና በወልቃይት አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ይህ መረጃ የደረሳችሁ የህብረተሰብ ክፍሎች መልዕክቱን በማስተላለፍ ትብብር እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሙሉ በሙሉ በሽብርተኛ ቡድኑ ቁጥጥር ስር ከመዋሉ በፊት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ መለዋወጫ ተሟልቶለትና ከሁለት መቶ በርሜል በላይ የተርባይን ዘይት አቅርቦት ቀርቦለት በጥሩ ሁኔታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነበር።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 21 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በድረገጽ ከ 270 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ማሰባሰብ ተችሏል
……..///…….
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም www.mygerd.com ይፋ የተደረገው ሐምሌ 18 ቀን 2013 ዓ.ም ነበር፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ባሉት አራት ወራት ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች አቅማቸው በፈቀደ መጠን ርብርብ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ በትልቅ ዓለምአቀፋዊ ጫና ውስጥ ሆነን የታየው ርብርብ አስደናቂና ከፍተኛ የትብብርና የአንድነት ስሜት የታየበት ነበር፡፡
እስከዛሬ ድረስ 1855 ለጋሾች ተሳትፈውበት 270,952 የአሜሪካን ዶላር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማሰባሰብ ተችሏል።
ከፍተኛ ንቅናቄ በመፍጠር ገንዘብ የማሰባሰብ ሥራውን ከመሩት ድርጅቶች መካከል GERD Initiative - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ MyDam - APUE፣ DFW Fundraising taskforce - DFW GERD taskforce፣ ኢትዮጵያዊነት ለአባያችን-አባያችን ለሥልጣኔያችን እንዲሁም Unity for Ethiopia Friends of Ethiopia for GERD – አስረስ ወልደማርያም ተጠቃሾቹ ናቸው፡፡
በግለሰብ ደረጃ ንቅናቄ በመፍጠር ድጋፍ ካሰባሰቡት መካከል ገንዘባችን ለግድባችን በሚል ንቅናቄ ከ5 ሺህ ዶላር በላይ ያሰባሰበው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ታዬ፣ Put your fingerprint to GERD - ዓለም ገብርኤል፣ እኔ ለሀገሬ ምን እያደረግኩላት ነው - ሶፊ፣ አለን ለግድባችን we are for GERD- አሽሪካ እና light up Ethiopia –BT ይገኙበታል፡፡
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያዊነታችን መገለጫ ሆኖ ዘመናትን ይሻገራል፡፡
#ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ያሸንፋሉ!!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 20 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማኔጅመንትና ሠራተኞች ባለፈው ሐምሌ ለህልውና ዘመቻው የአንድ ወር ደመወዛቸውን መለገሳቸውና በዓይነትና በደም ልገሳ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ ባለፈው ሳምንት አርብ ህዳር 17 ቀን 2014 ዓ.ም. ማኔጅመንቱ የኃላፊነት አበሉን ለመተው ሲወስን ሠራተኛው ደግሞ ትርፍ ሰዓት በመስራት ሊከፈላቸው የሚችለውን የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዲቀርና የተሰራው ሥራ በዕረፍት እንዲካካስ የሚያደርግ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ በዚህ ውሳኔ መሰረት አንዳንድ የሥራ ክፍሎች የትርፍ ሰዓት ክፍያ ሳይጠይቁ የሚሰጣቸውን ሥራ ለመፈፀም ተነሳሽነት ማሳየታቸውን ሰምተናል፡፡ የህልውና ድጋፉን ቀጣይ ለማድረግ ሁሉም በየአቅጣጫው የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል፡፡ እርስዎስ ለእናት አገር ጥሪ ምላሽ እርስዎ በየ ትኛው ግንባር ነዎት?
#ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!!
15 537
የዕቅድ ክለሳ እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀመጠ
.......////........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የተቋሙን አፈፃፀም ለማሻሻልና የህልውና ዘመቻው እስኪጠናቀቅ ድረስ ሊፈጠር የሚችለውን የኢኮኖሚ ጫና ከወዲሁ ለመቋቋም የሚያስችል የዕቅድ ክለሳ እንዲደረግ ወሰነ።
የሥራ አመራር ቡድኑ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን፣ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲሁም የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የኮይሻ ፕሮጀክቶች የበጀት ዓመቱ ትኩረት ሆነው እንደሚቀጥሉ ተጠቅሷል።
በተቋሙ ወጪ ቀናሽ ስልቶች እንዲተገበሩ፣ ጊዜ ሊሰጡ የሚችሉ ሥራዎች ዕቅድ እንዲከለስና ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ለማሳደግ ትኩረት እንዲሰጥ አቅጣጫ አስቀምጧል።
የሥራ አመራር ቡድኑ የበጀት ዓመቱን የኃላፊነት አበል በፍቃደኝነት በመተው አርአያነቱን ለማሳየት ወስኗል።
የትርፍ ሰዓት ሥራ ለመስራት አስገዳጅ ሁኔታ ሲያጋጥም ሠራተኛው ለሀገር በነፃ እንደሚሰጥ የዜግነት አገልግሎት በመውሰድ ሥራውን እንዲሰራና ለሥራው የዋለው ትርፍ ሰዓት በዕረፍት እንዲካካስለት ተወስናል።
ሁሉም የስራ ክፍሎች የወጪ ቅነሳ ዕቅድ እንዲያዘጋጁ አቅጣጫ ያስቀመጠው የስራ አመራር ቡድኑ የተቋሙን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ላይ ትኩረት እንዲደረግ አሳስቧል።
የሥራ አመራር ቡድኑ ውሳኔ በየደረጃው ሰራተኛው እንዲያውቀውና አምኖበት ተግባራዊ እንዲያደርገው አመራሮች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2014 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
