ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。

根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 537
订阅者
-724 小时
-77
+2630
帖子存档
photo content

የስምንት ጉድጓዶችን ቁፋሮ እስከ ሰኔ 2014 ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….////……. የአሉቶ የከርሰ ምድር የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ የመጀመሪያዎቹን ስምንት ጉድጓዶች ቁፋሮ እስከ ሰኔ 2014 ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ሪካርዶ ባልሶቲ ገለፁ፡፡ አስተባባሪው እንደገለፁት የመጀመሪያው ጉድጓድ ቁፋሮ 3 ሺህ ሜትር ድረስ ተከናውኖ ጉድጓዱን በሲሚንቶ የመለበጥ ሥራ ተጠናቋል፡፡ አንድ ጉድጓድ ለመቆፈር በአማካይ እስከ 75 ቀናት ይፈጃል ያሉት አስተባባሪው የመቆፈሪያ ማሽኖችን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በማንቀሳቀስ ለመትከል የሚፈጀውን ጊዜ ጨምሮ እስከ ታህሳስ ወር መጨረሻ ድረስ የሦስት ጉድጓዶች ቁፋሮ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የቡድን መሪ ዳቪስ ሞኮሮኒ በበኩላቸው አሁን የሚደረገው ቁፋሮ የሌሎች ጉድጓዶችን መቀጠል ወይም አለመቀጠል የሚወስን ይሆናል ብለዋል፡፡ እንደቡድን መሪው ገለፃ የጉድጓዶች ቁፋሮ ከተከናወነ በኋላ የዓለም ባንክ አስተያየት የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ መሳይ ፍቃዱ እንዳስታወቁት የሁለተኛው ጉድጓድ ቁፋሮ ወደ 1 ሺህ 3 መቶ ሜትር ተከናውኗል፡፡ የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮ በይፋ የተጀመረው ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም እንደነበር ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2014 ዓ.ም.

photo content
+4

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ3 ሺህ 8 መቶ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨት ተችሏል ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት 3 ሺህ 898 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨቱን በተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ እያየሁ ሁንዴሳ እንደገለጹት በ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 4 ሺህ 783 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ 3 ሺህ 898 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ተችሏል፡፡ ‹ በበጀት ዓመቱ ማመንጨት ከተቻለው ውስጥ 3 ሺህ 778 ነጥብ 5 ጌጋ ዋት ሰዓት ከውሃ፣ 108 ነጥብ 4 ጌጋ ዋት ሰዓት ከንፋስ እንዲሁም 10 ነጥብ 7 ጊጋ ዋት ዋት ሰዓቱ ከደረቅ ቆሻሻ የመነጨ ነው፡፡ ይህም የዕቅዱን 81 ነጥብ 5 በመቶ ማሳካት እንዳስቻለ አቶ እያየሁ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በስራ ላይ ከሚገኙት 21 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ውስጥ ጢስ አባይ 2ኛ፣ ቆቃ፣ ጊቤ 3፣ አዋሽ 2ኛ እና 3ኛ እንዲሁም አዳማ 2 የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያዎች ከታቀደላቸዉ በላይ ኃይል እንዳመነጩ ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡ የተሻለ ኃይል ማመንጨት በቻሉት ጣቢያዎች ይስተዋል የነበረው የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦት መፍትሄ በማግኘቱና በዩኒቶቻቸው ላይ የጥገና ስራ በመከናወኑ ጣቢያዎቹ በሙሉ አቅማቸው ኃይል በማመንጨት አፈጻፀማቸው ከዕቅድ በላይ እንዲሆን አስችሎታል፡፡ በአንፃሩ አመርቲ ነሼ፣ መልከ ዋከና፣ ጊቤ 1 እና 2፣ ፊንጫ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና አዳማ 1 የንፋስ ማመንጫ ጣቢያ እንዲሁም ረጲ ከደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ያመነጫሉ ተብሎ ከታቀደላቸው በታች ካመነጩ ጣቢያዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡ እንደ ቆቃ፣ አዋሽ 2ኛ እና 3ኛ ያሉ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከመለዋወጫ አቅርቦት ጋር በተያያዘ አንዳንድ ዩኒቶቻቸው ለዓመታት ኃይል ማመንጨት አቁመው እንደነበር አቶ እያየሁ አስታውሰዋል፡፡ በጣቢያዎቹ ዓመታዊና የቅድመ መከላከል የጥገና ስራ ሲሰራባቸው የቆዩ በመሆኑ በዕቅዳቸው መሰረት ኃይል ላለማመንጨታቸው በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ እንደ አቶ እያዩ ገለፃ ጣቢያዎቹ በቀጣይ ጊዜያት በዕቅዳቸው መሰረት ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ በሩብ ዓመቱ የግድቦች የውሃ አስተዳደር የተሻለ እንደነበር ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው በሀገሪቱ ባለው ወቅታዊ ችግር ምክንያት የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር መቀነሱና በሙሉ አቅም ኃይል ለማመንጨት እና ሠራተኞችን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ለማሰራት ፈተና እንደነበር ተገልጿል፡፡ በ2014 በጀት ዓመት 19 ሺህ 875 ነጥብ 9 ጌጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ዕቅድ ተይዟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 15 ቀን 2014 ዓ.ም.

photo content

በራስ አቅም ጥገና የቆሙ ዩኒቶችን ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉ ተገለፀ ……////…….. በጊቤ 2 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ካሉት አራት ዩኒቶች መካከል በዩኒት አንድ እና በዩኒት ሦስት ላይ ሙሉ ጥገና በመደረጉ ተጨማሪ 180 ሜጋ ዋት ማግኘት መቻሉን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ገረመው ገልፀዋል። ጣቢያው በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን እያንዳንዳቸው 105 ሜ.ዋ የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ዩኒቶች ያሉትና በድምሩ 420 ሜ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ነው፡፡ በዩኒት አንድና ሦስት ላይ ኃይል እንደመጫን አቅማቸው ውሃን ለመመጠን በሚያገለግለው የፓወር ኖዝል መቆጣጠሪያ (needle valve) ብልሽትና እና ወደ ተርባይን የሚገባውን ውሃ በሚቆጣጠሩ የዘይት ፍሰት መቆጣጠሪያ ሲሊንደሮች (MIV servomotor piston cylinder) ላይ የዘይት መፍሰስ ችግር በማጋጠሙ ዩኒት አንድ ሙሉ ለሙሉ ሲያቆም ዩኒት ሦስት ደግሞ 1/4ኛውን ብቻ ኃይል ያመነጭ እንደነበር የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አውስተዋል፡፡ ዩኒቶቹ በሙሉ አቅማቸው እንዳያመነጩ ያደረጓቸውን ችግሮች መለየት ከተቻለ በኋላ በቅድሚያ ከተቋሙ የተለያዩ ክፍሎች በተለይም ከክላስተር ቢሮዎች፣ ከቴክኒክ ድጋፍ ክፍል እና ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የጥገና ቡድን በማዋቀር ወደ ስራ መገባቱን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ የጥገና ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ወደ ስራ በመገባቱ ዜሮ የነበረውን የዩኒት አንድ የመጫን አቅም ወደ 105 ሜ.ዋ እንዲሁም 25 ሜ.ዋ ብቻ ይጭን የነበረውን ዩኒት ሦስት ወደ 100 ሜ.ዋ ኃይል እንዲያመነጭ በመደረጉ ጣቢያው 180 ተጨማሪ ኃይል እንዲያገኝ አስችሎታል ብለዋል። በቀጣይም በዪኒት ሁለትና አራት ላይ የፍተሻና የጥገና ስራው የሚሰራ መሆኑን ጠቁመው ጣቢያው የሚጠበቅበትን ኃይል ማምረት እንዲችል በምስራቅ አፍሪካ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት (Voith) አማካኝነት በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች የጥገና ማኔጀመንት ስርዓት (maintenance management system) ስራዎች እየተሰራ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ተቋሙ ለውጭ ሙያተኞችና ኩባንያዎች በሚሊየን ሊያወጣ የሚችለውን ውጭ ማስቅት ከማስቻሉ በተጨማሪ ቅንጅታዊ አሰራር እና የእውቀት ሽግግር የተገኘበት እንደነበር ገልፀው ለጥገና ሥራው ለሚጠየቁ የዕቃ እና ተያያዥ አቅርቦቶች የተቋሙ ማኔጅመንት ለሰጠው ፈጣን ምላሽና አዎንታዊ ድጋፍ ምስጋናቸውን በማቅረብ ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2014 ዓ.

በራስ አቅም ጥገና የቆሙ ዩኒቶችን ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉ ተገለፀ ……////…….. በጊቤ 2 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ካሉት አራት ዩኒቶች መካከል በዩኒት አንድ እና በዩኒት ሦስት ላይ ሙሉ ጥገና በመደረጉ ተጨማሪ 180 ሜጋ ዋት ማግኘት መቻሉን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ገረመው ገልፀዋል። ጣቢያው በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን እያንዳንዳቸው 105 ሜ.ዋ የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ዩኒቶች ያሉትና በድምሩ 420 ሜ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ነው፡፡ በዩኒት አንድና ሦስት ላይ ኃይል እንደመጫን አቅማቸው ውሃን ለመመጠን በሚያገለግለው የፓወር ኖዝል መቆጣጠሪያ (needle valve) ብልሽትና እና ወደ ተርባይን የሚገባውን ውሃ በሚቆጣጠሩ የዘይት ፍሰት መቆጣጠሪያ ሲሊንደሮች (MIV servomotor piston cylinder) ላይ የዘይት መፍሰስ ችግር በማጋጠሙ ዩኒት አንድ ሙሉ ለሙሉ ሲያቆም ዩኒት ሦስት ደግሞ 1/4ኛውን ብቻ ኃይል ያመነጭ እንደነበር የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አውስተዋል፡፡ ዩኒቶቹ በሙሉ አቅማቸው እንዳያመነጩ ያደረጓቸውን ችግሮች መለየት ከተቻለ በኋላ በቅድሚያ ከተቋሙ የተለያዩ ክፍሎች በተለይም ከክላስተር ቢሮዎች፣ ከቴክኒክ ድጋፍ ክፍል እና ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የጥገና ቡድን በማዋቀር ወደ ስራ መገባቱን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ የጥገና ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ወደ ስራ በመገባቱ ዜሮ የነበረውን የዩኒት አንድ የመጫን አቅም ወደ 105 ሜ.ዋ እንዲሁም 25 ሜ.ዋ ብቻ ይጭን የነበረውን ዩኒት ሦስት ወደ 100 ሜ.ዋ ኃይል እንዲያመነጭ በመደረጉ ጣቢያው 180 ተጨማሪ ኃይል እንዲያገኝ አስችሎታል ብለዋል። በቀጣይም በዪኒት ሁለትና አራት ላይ የፍተሻና የጥገና ስራው የሚሰራ መሆኑን ጠቁመው ጣቢያው የሚጠበቅበትን ኃይል ማምረት እንዲችል በምስራቅ አፍሪካ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት (Voith) አማካኝነት በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች የጥገና ማኔጀመንት ስርዓት (maintenance management system) ስራዎች እየተሰራ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ተቋሙ ለውጭ ሙያተኞችና ኩባንያዎች በሚሊየን ሊያወጣ የሚችለውን ውጭ ማስቅት ከማስቻሉ በተጨማሪ ቅንጅታዊ አሰራር እና የእውቀት ሽግግር የተገኘበት እንደነበር ገልፀው ለጥገና ሥራው ለሚጠየቁ የዕቃ እና ተያያዥ አቅርቦቶች የተቋሙ ማኔጅመንት ለሰጠው ፈጣን ምላሽና አዎንታዊ ድጋፍ ምስጋናቸውን በማቅረብ ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2014 ዓ.

photo content
+5

የአዳማ ሁለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ --------//-------- የአዳማ ሁለት ባለ 230/132/15 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር እንዳስታወቁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የማስተላለፊያ መስመር ግንባታው 97 በመቶ አፈፃፀም ላይ ደርሷል ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፎች ተከፍሎ እየተገነባ ነው ያሉት አቶ መሐመድ በምዕራፍ አንድ በአዳማ ከተማ አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና በነባሩ የአዳማ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የካፓሲተር ባንክ ማስፋፊያ የዲዛይን፣ የአቅርቦት፣ የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ሥራዎችን ያጠቃልላል ተብሏል፡፡ በምዕራፍ ሁለት ደግሞ 1.7 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከነባሩ የቆቃ-ሁርሶ ወደ አዳማ ሁለት እና 3.8 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከነባሩ የአዳማ-መተሃራ ወደ አዳማ ሁለት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ሥራ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ መሐመድ ገለፃ የአዳማ ሁለት ባለ 230/132/15 ኪሎ ቮልት አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ እና የፍተሻ ስራ ተጠናቆ አገልግሎት ለመስጠት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡ 3.8 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከነባሩ የአዳማ-መተሃራ ወደ አዳማ ሁለት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ተጠናቆ ለፍተሻ ስራ ዝግጁ መደረጉንም ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ 15 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ያሉት እንደሆነም ጨምረው አብራርተዋል፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን ሲዩአን ኤሌክትሪክ (Sieyuan Co., Ltd.) የተባለ የቻይና ኩባንያ እየገነባ የሚገኝ ሲሆን ከነባሩ የአዳማ-መተሃራ እስከ አዳማ ሁለት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ያለው ግንባታ ደግሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሲቪል ኮንስትራክሽን ቢሮ በኩል እየተከናወነ ነው ተብሏል፡፡ የማማከር ሥራውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንጅነሪንግ ቢሮ እየሰራ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የፕሮጀክቱ መገንባት የአዳማ ከተማን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለመመለስና በአካባቢው ለተገነባው የኢንደስትሪ ዞን ኃይል ለማቅረብ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ.

photo content

photo content

photo content

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በአሸባሪው የትህነግ ቡድን ጥቃት የተፈፀመበት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ተዘከረ ……//……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮች እና ሠራተኞች ‹‹አልረሳውም! እኔም የኢትዮጵያ ሠራዊት ነኝ›› በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በአሸባሪው የትህነግ ቡድን ጥቃት የተፈፀመበትን አንደኛ ዓመት አስበዋል፡፡ በህዝብና በመንግሥት የተጣለባቸውን ግዳጅ ሲወጡ በጁንታው ኃይል ክህደት ለተሰው የመከላከያ ሠራዊት አባላትም የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ ዘክረዋል፡፡ በዋና መስሪያ ቤት በተካሔደው መርሃ-ግብር ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ አንዳርጌ እሸቴ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ አባላት ላይ የጁንታው ቡድን የፈፀመው አሰቃቂ ጭፍጨፋ እንኳን በኢትዮጵያውያን ዘንድ ይቅርና በዓለም ህዝብ አዕምሮም የሚረሳ አይደለም ብለዋል፡፡ የሰሜን ዕዝ ሠራዊት አባላት በትግራይ ክልል የህዝቡን ሠላም ከመጠበቅ ባሻገር ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት አዝመራ እያጨደና ከዕለት ጉርሱ በመቀነስ ትምህርት ቤትና ጤና ጣቢያ እየገነባ የቆየ የሃገር አልኝታ እንደነበር አቶ አንዳርጌ አስታውሰዋል፡፡ አሸባሪው የትህነግ ቡድን ሃገር የማፍረስ እኩይ ተልዕኮውን ለማስፈፀም ሲል ለበርካታ ንፁሃን ዜጎች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል ያሉት አማካሪው በቀቢፀ ተስፋ የተሞላው ዕቅዱ በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ በክልል ልዩ ኃይሎች እና በአካባቢ ሚሊሻዎች እየከሸፈበት እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን የጋራ ትግል ከሥልጣን የተወገደው የጁንታው ቡድን በጎንደር፣ በአፋር እና በወሎ አካባቢዎች በንፁሃን ዜጎች ላይ ከፍተኛ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶችን በመፈፀም እንዲሁም ንብረቶችን በመዝረፍና በማውደም የሽብር ተልዕኮውን በአደባባይ አሳይቷል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ የሠላማችን ዘብ በሆነው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የተፈፀመበትን አረመኔያዊና ፋሽሽታዊ ድርጊት በመቃወምና በማሰብ በቀጣይ ለሚደረጉ ልዩ ልዩ የሰው ኃይል፣ የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የሃሳብ ድጋፎች አመራሩ እና ሠራተኛው ዝግጁ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ሁሉም ተሳታፊዎች የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙርን በመዘመር ለጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን አጋርነት እና ክብር ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 24 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content