EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 554 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 397,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 554 名订阅者。
根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.94% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 003 次浏览,首日通常累积 2 323 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 554
订阅者
+124 小时
+87 天
+1030 天
帖子存档
15 554
በትራንስፎርመር ብልሽት ሳቢያ በከፊል ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም ተመልሷል
.....///.....
በኮምቦልቻ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል በአንደኛው ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት በከፊል ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም መመለሱን የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን አስታወቀ።
በሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል የመጫን አቅም ባለው ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ የእሳት አደጋ ምክንያት ለአንድ ወር ያህል በአካባቢው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡
በዚህም በትራንስፎርመሩ ታፕ ቼንጀር ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች እና በአካባቢያቸው በከፊል የኃይል ተቋርጦ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
ጉዳት የደረሰበትን ባለ 132/66/15 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር ጠግኖ ዳግም አገልግሎት ለማስጀመር ከሪጅኑ እና ከማዕከል የተውጣጡ የጥገና ባለሙያዎች ርብርብ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ነው የገለፁት።
በአካባቢው በከፊል ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው ዕለት ሙሉ በሙሉ መመለስ ተችሏል ያሉት አቶ በድሩ በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ባለሙያዎች በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
በተቋሙ ተግባራዊ የሚደረጉ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ደህንነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው
…….///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገኙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (IT) መሰረተ ልማቶች ለሳይበር ጥቃት እንዳይጋለጡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የሳይበር ደህንነት መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌትነት አድማሱ እንዳስታወቁት የኢንተርኔት እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሲስተም አጠቃቀም ማደጉን ተከትሎ የሳይበር ደህንነት ስጋት ተጋላጭነት በዓለም አቀፍ ብሎም በሀገር ደረጃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡
ይህን ተከትሎም በተቋሙ የሚከናወኑ የአሰራር ሥርዓቶች በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲከናወኑ የሚያግዙ እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች ላይ የሳይበር ጥቃት እንዳያጋጥም ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ጀምሮ መተግበሪያዎች፣ ኮምፒውተሮች፣ ሰርቨሮች እንዲሁም የኔትዎርክ ዕቃዎችን የሳይበር ደህንነት ለማስጠበቅ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የዲጂታላይዜሽን አሰራሮች ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆኑ በሶፍትዌሮች እና ሀርድዌሮች ግዥ ላይ የሳይበር ደህንነት መስፈርቶች እንዲሟሉ ከማድረግ ጀምሮ የተለያዩ የአሰራር ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን ተናግረዋል፡፡
ሳፕና ኢአርፒን የመሳሰሉ አሰራር ማዘመኛዎችን ጨምሮ በተቋሙና በውጭ እየለሙ የሚገኙ ሶፍትዌሮች ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት የሳይበር ደህንነት መመዘኛዎችን ማሟላታቸውንና ለጥቃት ተጋላጭ መሆንና አለመሆናቸውን ፍተሻና ክትትል እንደሚደረግባቸው ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡
ወደ ሥራ ከገቡ በኋላም በእያንዳንዱ ሲስተም ላይ የተለያዩ የሳይበር ደህንነት መከታተያ የአስራር ሥርዓቶችን በመተግበር እና ሶፍትዌሮችን በመጠቀም ደህንነታቸውን የማስጠበቅና የመቆጣጠር ሥራ እየተከናወነ ስለመሆኑ አመልክተዋል፡፡
በተጨማሪም በተቋሙ ኔትወርክ ላይ ማንኛውም ሰው ከተቋሙ ዕውቅና ውጭ ኢንተርኔትም ሆነ የተቋሙን ሲስተም መጠቀም እንዳይቻል የሚያደርጉ የደህንነት ማስጠበቂያ አሰራሮች መዘርጋታቸውን አቶ ጌትነት አስረድተዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በእያንዳንዱ ሲስተም ላይ ያሉ የጥቃት አጋላጭ ዓይነነቶችን አስቀድሞ በመለየት የመከላከል ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
የመረጃ መንታፊዎች ቴክኖሎጂዎችን ሰብሮ ከመግባት ይልቅ በሰው አማካኝነት በቀላሉ የሳይበር ጥቃት የማድረስ አቅም እንዳላቸው የጠቆሙት አቶ ጌትነት ይህን በመገንዘብም በተቋሙ በሳይበር ደህንነት ምህዳር ላይ ንቃተ ሕሊና ያለው ሠራተኛ መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
የተቋሙን የሳይበር ደህንነት ለማረጋገጥ ክፍሉ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የተቋሙ የሥራ መሪ እና ሠራተኛ ኃላፊነት እንዳለበት ተገንዝቦ በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የግዥ አፈጻጸም ሥልጠና እየተሰጠ ነው
----///---
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሁሉም የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች አዲስ በወጣው የመንግስት የልማት ድርጅቶች የግዢ አዋጅና መመሪያ አፈፃፀም ዙሪያ ሥልጠና በመሰጠት ላይ ነው።
የተቋሙ የግዥና ሎጀስቲክስ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ጽዮን ብርሃኑ እንደገለፁት የግዢ አፈፃፀም ሂደትን ማወቅ የግዥ ፈጻሚው ክፍል ብቻ ሳይሆን ግዥ እንዲፈጸምለት ጥያቄ ያቀረበው የሥራ ክፍል ሥራ መሆን ስላለበት ሥልጠናው ከተቋሙ የግዢ ባለሙያዎች በተጨማሪ ሌሎች የሥራ ክፍሎችን ጭምር ማካተቱን ገልፀዋል፡፡
ስለሆነም ስልጠናው የሚቀርቡ የግዢ ጥያቄዎች በጊዜና በጥራት ህግን ተከትለው ተፈጻሚ እንዲሆኑ እንደሚያግዝ ገልፀዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ተሳታፊ የሆኑት በተቋሙ የጤና ክፍል የጤናና ሴፍቲ ሥራ አሰኪያጅ አቶ ሆርሳ ቴሬሳ በበኩላቸው ሥልጠናው በግዢ ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቅረፍ ግዢዎችን በአግባቡ ለመፈፀም የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ እየተሰጠ የሚገኘው ሥልጠና በተቋሙ ግዢና ሎጀስቲክስ መምሪያ እንዲሁም በመንግስት ሀብት አስተዳደር እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በጋራ መዘጋጀቱ ውጤቱን የላቀና ከፍተቶችን የሚሞላ ሥልጠና ያደርገዋል ብለዋል፡፡
በተቋሙ የሚፈጸሙ የግዢ ሂደቶች ወጥነት ያለው እና ሃገራዊ የግዢ ስርዓትን በመከተል ተፈጻሚ እንዲሆኑ የሚያስችል እውቀት ከስልጠናው እያገኙ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ከልማትና ስልጠና ማዕከል ተሳታፊ የሆኑት ወ/ሮ የምስራች መኮንን ናቸው፡፡
የሠራተኛ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በበኩላቸው ሥልጠናው በግዢ አፈፃፀም ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን አሟልቶ የተሻለና ህግን የተከተለ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
+2
#ዲጂታልመጽሔት
እነሆ ነፀብራቅ ዲጂታል መጽሔት ለንባብ በቅታለች፡፡
መፅሔቷ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ወራት የተከናወኑ አበይት ጉዳዮችን ትዳስሳለች
ከስር የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን መፅሔቱን እና ሌሎች ተቋሙን የተመለከቱ መረጃዎች በቀላሉ ያግኙ!
👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536#flipbook-df_22343/2/
👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
የተቀናጀ ተቋማዊ ፖሊሲ ቀረጻ እና ማሻሻያ ስራዎች ማስጀመሪያ ዎርክሾፕ መካሄድ ጀመረ
……//….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበጀት ዓመቱ ሊያሻሽላቸው እና በአዲስ መልክ ለመቅረጽ በዕቅድ የያዛቸውን ፖሊሲዎች ዝግጅት ለማስጀመር የሚያስችል የቴክኒክ ቡድን አቋቋሞ ወደ ሥራ የሚያስገባውን የ 2 ቀናት ዎርክሾፕ ማካሄድ ጀምሯል፡፡
የዋና ስራ አስፈጻሚ ተወካይና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሕይወት እሽቱ በወርክሾፑ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ጸድቆ ተግባራዊ በተደረገው የሪፎርም ዕቅድ መሰረት ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ የፖሊሲ ቀረጻና ማሻሻያ ስራ ነው፡፡
በመሆኑም ይህ ተግባር የድርጊት መርሀ ግብር ወጥቶለት ተግባራዊ መደረጉ ተቋሙ የአሰራር ስርዓት ለማሻሻል የጀመረውን እርምጃ የሚያሳይ ነው።
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ 12 የሚሆኑ ተቋማዊ ፖሊሲዎች በተያዘው ሩብ ዓመት ተዘጋጅተው እና ተሻሽለው እንዲተገበሩ ለማስቻል የፖሊሲ ዝግጅት ቡድን ተቋቋሞ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
ለአንድ ተቋም የአሰራር ወጥነትና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲኖር አስቻይ የሚሆኑና የውሳኔ አሰጣጥ መርህን እንዲሁም ተቋማዊ ፍላጎትን የሚያንጸባርቁ ፖሊሲዎች፥ አሰራር ሂደቶችና መመሪያዎች መኖር መሰረታዊ መሆናቸውን የተናገሩት ሥራ አስፈፃሚው እነዚህ ሳይኖሩ ወይም ያሉትን ሳያሻሽሉ መቅረት ተቋማዊ ሥራን ለማሳለጥ አስቸጋሪ እንደሚያደርገው አስረድተዋል።
የሥራ ቡድኑ የተሰጠው ኃላፊነት ወሳኝ መሆኑን ሥራው ከሌሎች መደበኛ ሥራዎች እኩል ተይዞ በከፍተኛ ትኩረት መከናወን የሚገባው መሆኑን ገልጸው ሁሉም የቡድኑ አባላት ለስራው በቂ ጊዜ መድበውና የተቀመጠውን አሰራር ተከትለው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡
የሰው ሀብት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው ፖሊሲ በከፍተኛ ደረጃ የሚዘጋጅና የሚተገበር፥ እንዲሁም ወሰኝ የሆኑ ጥቂት ጉዳዮችን ይዞ የተቋሙን ዋና ዋና ፍላጎቶችን የሚያመላክት ሰነድ በመሆኑ አዘጋጆች ከተቋሙ ስትራቴጂ ጋር አገናዝበውና አዋህደው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡
የሚዘጋጀው ፖሊሲ ሂደትን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ዝግጅት መደረጉን የገለፁት በዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የፕሮሰስ ፓሊሲና የለውጥ ስራ አመራር ዳይሬክተርና አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ ፖሊሲዎቹን በ 40 ቀናት ውስጥ አዘጋጅቶ ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል፡፡
ሂደቱን በከፍተኛ ጥራት በተቀመጠው ጊዜ ለማከናወን እንዲቻል ይህ የማስጀመሪያ ዎርክሾፕ የፖሊሲ ዝግጅት 12 ቡድኖችን በሁለት በመክፈል ለሁለት ቀናት የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው ሂደቱን የሰፖርት ፕሮሰስና ፖሊሲ ማኔጅመንት ስራ ክፍሎች በበላይነት እንደሚያስተባብሩት ገልጸዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
ተቋሙ የያዘውን ርዕይ ለማሳካት የባለሙያውን አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ
-----------///-------------------
በኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በሚከናወኑ የኤሌክትሮ ሜካኒካል እና የሲቪል ግንባታ ሥራዎች ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ለአንድ ወር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት የተቋሙ የራስ ኃይል በሀገር ውስጥና በውጭ ለማከናወን የያዘውን ርዕይ ለማሳካት የባለሙያውን አቅም በማሳደግ የሰርተፊኬት ባለቤት እንዲሆን ማድረግ ይጠይቃል።
ተቋሙ በትምህርት ያልተደገፉ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን የሰርተፊኬት ባለቤት ለማድረግ የስልጠና ስርዓት ቀርፆ ስልጠናዎችን በራስ አቅም መስጠት መጀመሩን ተናግረው በቀጣይ መሠል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ከመረጃ አያያዝ ጀምሮ የፕሮጀክቶቹን አፈፃፀም ለማሻሻል ሠራተኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል።
በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ስልጠናው የራስ ኃይልን አሁን ካለበት ደረጃ ለማሳደግ ከፋተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
አካዳሚው በሠራተኞች ላይ የሚስተዋሉ የክህሎትና የዕውቀት ክፍተቶችን በመለየት በራስ አቅም ስልጠናዎችን ለመስጠት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ ከተቋሙ ተልዕኮ ጋር በተያያዘ ብቃት ያለው ባለሙያ ለማፍራት እስከ ደረጃ 5 ባለሙያዎችን ለማሰልጠን አቅዶ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተወካይ አቶ ግርማ ዘለቀ እንደተናገሩት ስልጠናው ሠራተኞች በልምድ ያገኙትን እውቀት ከንድፈ ሃሳብ ጋር በማቀናጀት ሥራቸውን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ ለማድረግ፣ ሥራውን ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ለማከናወን፣ ከሥራ ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን እና አለመግባባቶችን ለመቅረፍ ያግዛል።
በዘርፉ የሀብት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ መንበረ ክፍሌ በበኩላቸው ሠራተኞች እየሰሩበት ያለው የሥራ ፀባይ ራሳቸውን በትምህርት እንዳያሳድጉና የሚፈልጉት ደረጃ ላይ እንዳይደርሱ ማድረጉን አንስተዋል፡፡
ችግሩን ለመቅረፍ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ስልጠናውን በማመቻቸቱ አመስግነው ሠልጣኖች ስልጠናው መነሻ እንጅ መዳረሻ አለመሆኑን ተገንዝበው በቀጣይ ራሳቸውን በተለያዩ መንገዶች ማብቃት እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል፡፡
በራስ አቅም በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ላይ እየሰሩ የሚገኙ ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ የተሠጠው ስልጠና ከዚህ በፊት በሠራተኞች ሲነሱ የነበሩ ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ደግሞ የተቋሙ መሠረታዊ የሠራተኞች ማህበር ጸሐፊ አቶ ሀይሉ ወልዴ ናቸው፡፡
የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከስልጠናው ዘመኑን የዋጀ ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ዕውቀትና ክህሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
በዕለቱም ለአንደ ወር በቆየው ስልጠና ላይ የተሳተፉ 41 የሲቪል እና 12 የኤሌክትሮ መካኒካል ግንባታ ባለሙያዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
በኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ እንስት ባለሙያዎች ዕውቅና ተሰጠ
…....///…...
የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር (EWiEN) በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በፈጠራና በአስተዳደር እንዲሁም በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተፅዕኖ ለፈጠሩ ሴቶች ዕውቅና ሰጠ፡፡
የዕውቅና መርሃግብሩ ሴት ባለሙያዎች በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ ለማስተዋወቅ፣ ለማበረታታት እና ክብር ለመስጠት እንዲሁም ወጣት ሴቶች በዘርፉ እንዲሰማሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በመርሃግብሩ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን እና ሰብስቴሽን ፕሮግራም መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራን ጨምሮ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ተጨማሪ ሁለት ሴቶች ዕውቅና እና ሽልማት ተበርክቷል፡፡
ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ በዕውቅና ሥነስርዓቱ ላይ በሀገሪቱ በ160 ቦታዎች ላይ የስማርት ሜትር ፕሮጀክትን በማስተግበር ተቋሙ የገቢ አቅሙን እንዲያጠናክር እና የኃይል ብክነትን በመቀነስ ረገድ ለተጫወቱት የአመራርነት ሚና ዕውቅናው ስለተሰጣቸው ማህበሩን አመስግነዋል፡፡
የቮልቴጅ ቁጥጥር ሥርዓትን በመዘርጋት በሰመራ፣ አዲጋላ እና ባህርዳር በተደጋጋሚ ሲያጋጥም የነበረውን የቮልቴጅ መዋዠቅ በማረጋጋት እና የኃይል መቆራረጥን በመቀነስ ረገድ የነበራቸው ሚና ለሽልማት እንዳበቃቸውም ተናግረዋል፡፡
እንደ ወ/ሮ ሃይማኖት ገለፃ በኢነርጂ ዘርፉ ላይ መሰል የዕውቅና እና ሽልማት ፕሮግራሞች መዘጋጀታቸው ለሌሎች ሴት ባለሙያዎች መነሳሳትን የሚፈጥር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡
ዕውቅናው በቀጣይ በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ በሚያከናወኑ በርካታ ፕሮጀክቶች ላይ በትጋት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ትልቅ የሞራል ስንቅ እንደሆናቸውም ነው ያብራሩት፡፡
በዛሬው ዕለት በተካሄደው መርሃግብር ከቀረቡት ስድስት ዕጩዎች መካከል ወ/ሮ ሰላማዊት ስለሺ በኢንጂነሪንግ ዘርፍ እንዲሁም ወ/ሮ ነፃነት በኃይሉ በኤሌክትሪክ አቅርቦት ዘርፍ የዓመቱ የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች በመባል ተመርጠዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
በዘርፉ የሴቶችን ተሳተፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ
…….///….…
በኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ውስጥ የሴቶችን ተሳትፎ እና የውሳኔ ሰጪነት ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር (EWiEN) ለአምስተኛ ጊዜ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ዓመታዊ መርሃግብር በሒልተን ሆቴል እያካሔደ ይገኛል።
በመርሃግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካይ ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ተቋሙ ሴቶች በኢነርጂ ዘርፉ ውስጥ የሚኖራቸውን ሚና እና ተፅዕኖ ፈጣሪነት ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል።
ተቋሙ የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀዋል።
እንደ ወንድወሰን(ዶ/ር) ገለፃ መርሃግብሩ ሴቶች በዘርፉ ላገኙት ስኬት ዕውቅና ከመስጠት ጎን ለጎን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን ለመስራት ያግዛል።
ማህበሩ በዘርፉ የሴት ባለሙያዎችን ዕድገት እና ተሳትፎ ከፍ ለማሳደግ እያደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያደንቁ ገልፀው ተቋሙ በሁሉም ደረጃዎች የሴት ባለሙያዎችን ቁጥር ለመጨመር በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
በመርሃግብሩ ላይ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የተሳተፉ ተቋማትና ድርጅቶች ምርታቸውንና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት አውደርዕይ የተከፈተ ሲሆን በዘርፉ የሴቶች ተሳትፎ ዕድገት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የፓናል ውይይትም እየተካሔደ ይገኛል።
ማህበሩ በዓመቱ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በፈጠራና በአስተዳደር እንዲሁም በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተፅዕኖ ለፈጠሩ ሴቶች ዕውቅና ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር (EWiEN) በኢነርጂ ዘርፍ ያለውን የሥርዓተ-ፆታ ክፍተት ለማመጣጠን በማሰብ በአምስት ሴት ባለሙያዎች የተመሠረተ ለትርፍ ያልተቋቋመና መንግሥታዊ ያልሆነ ማህበር ነው፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
ጣቢያው ተጨማሪ ደንበኞችን እየጠበቀ ነው
…….///…….
የቀብሪደሃር ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ የኃይል ፈላጊ ደንበኞችን እየጠበቀ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢብራሂም ሰዒድ እንደገለፁት ጣቢያው 22 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ቢኖረውም በአሁኑ ወቅት ለደንበኞች እያቀረበ ያለው 3 ነጥብ 3 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ ነው፡፡
ቀሪው 19 ነጥብ 2 ሜጋ ዋት ኃይል አዲስ ደንበኞችን እየጠበቀ እንደሚገኝ ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡
ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት በቀብሪደሃር ከተማና በዙሪያው የሚገኙ አስራ ሁለት ቀበሌዎች ከጣቢያው የኤሌክትሪክ ኃይል እየቀረበላቸው ሲሆን ሽላቦ፣ ላሰንከሪ እና ዋርዴር ከተሞች ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል በማግኘት ላይ ናቸው፡፡
በ2012 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የቀብሪደሃር ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 132 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር ኃይል የሚቀበል ሲሆን አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር አንድ የኃይል ትራንስፎርመር አለው፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
🌍 Africa’s rivers are unlocking a clean-energy revolution!
…….///…….
Africa holds 17% of the world’s hydropower potential, yet only a small portion has been developed. This means the power to transform our future is already flowing across the continent.
Ethiopia is at the forefront with landmark projects like GERD, Gibe III, Koysha, and Genale Dawa III—turning natural water resources into reliable, renewable energy that lights homes, drives industries, and strengthens regional cooperation.
Hydropower delivers more than electricity:
💧 Stabilizes solar and wind
💧 Strengthens climate resilience
💧 Fuels economic growth
💧 Expands access to electricity
💧 Supports peace & regional integration
Africa’s rivers shaped our history—now they can shape a cleaner, brighter, net-zero future for all. ⚡️
👉 Read the full article here:
https://www.eep.com.et/?article=the-conductors-current-how-africas-rivers-are-powering-a-net-zero-future
#AfricaEnergy #Hydropower #Ethiopia #SustainableDevelopment #CleanEnergyFuture
💡 "Clean Energy for a Better Life!"
📌Facebook: https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌Telegram: https://t.me/EEPCommuication
📌Twitter: https://twitter.com/EEPethiopia
📌 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power-የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኃይል
📌YouTube: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌TikTok: https://tiktok.com/@ethio_power
📌 Website: https://www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 554
ጣቢያው ለጅግጅጋና አካባቢው ነዋሪዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ነው
……///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢው ነዋሪዎች እና በከተማዋ ዙሪያ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ፡፡
የጣቢያው ኃላፊ አቶ ደምለው ተሾመ እንዳስታወቁት 60 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው የማከፋፈያ ጣቢያው በስምንት ወጪ መስመሮች ለክልሉ ዋና ከተማ ጅግጅጋና ለአካባቢው ከተሞች 30 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ ይገኛል፡፡
ጣቢያው በ 33 ኪሎ ቮልት ለፋፈም፣ ለቶጎ ጫሌ፣ ለቀብሪበያህ፣ ለጭናክሰን እና በአከባቢው ለሚገኙ ከተሞች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ጣቢያው ካለው አቅም 30 ሜጋ ዋት የሚሆነው ደምበኞችን በመጠባበቅ ላይ በመሆኑ ባለሀብቶች በአቅራቢያቸው የተዘጋጀላቸውን ኃይል እንዲጠቀሙበት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
እንደ አቶ ደምለው ገለፃ ጣቢያው አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር እና ሁለት ባለ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡
የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ በ132 ኪሎ ቮልት ከሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ መልሶ በ132 ኪሎ ቮልት ለደገሀቡር ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያስተላልፋል፡፡
ጣቢያው ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
