EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 545 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 545 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 545
订阅者
+824 小时
-227 天
+2730 天
帖子存档
15 546
በምስራቅ ሸዋ ዞን ብቻ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የብረት ምሶሶ ስርቆት ተፈጽሟል
...........//////...........
በምስራቅ ሸዋ ዞን በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ብቻ በ2014 ዓ.ም ግምቱ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ የባለ 230 ኪሎ ቮልት እና የባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሶሶዎች የተለያዩ አካላት ተፈታተው በዘራፊዎች መወሰዳቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመካከለኛ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን እና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።
መምሪያው በምስራቅ ሸዋ ዞን ከሚገኙ ስድሰት ወረዳዎች ከተወጣጡ የዞንና የወረዳ ጸጥታ እና የፍትህ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ እየተፈፀመ ባለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሶሶዎች ስርቆት ዙሪያ በአዳማ ከተማ የግንዛቤ እና የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡
በመድረኩ ላይ የሪጅኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የኦፕቲካል ግራውንድ ፋይበር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በፍቃዱ በቀለ በዞኑ በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የስርቆት ጉዳት በምስል እና በጹሁፍ የታገዘ ገለፃ አድረገዋል፡፡
ሥራ አስኪያጁ እንደገለጹት ሆን ተብሎ እና በተደራጀ መንገድ የብረት ምሰሶዎችን መስረቅ፤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ስር መኖሪያ ቤቶችን መገንባት፤ ዛፎችን መትከል፤ አንዳንድ የማህበረሰብ ክፍሎች ችግሮች ሲፈጠሩ ለሚመለከተዉ አካል አለማሳወቅ፤ በአንዳንድ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች አመራሮች ለጉዳዩ ትኩረት አለመስጠት የሚያጋጥሙ ችግሮች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በ2014 ዓመት ብቻ 4 ሺህ 484 የተለያዩ የብረት ምሶሶ አካላት በስርቆት በመወሰዳቸው በተቋሙ ላይ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት መደረሱንና ይህም የነዳጅ ወጪዎችን እና በስርቆቱ ምክንያት የተቋረጠው መስመር መልሶ እስኪጠገን የባከነውን ኃይል እንደማያካትት አቶ በፍቃዱ አስገንዝበዋል።
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው በበኩላቸው እንደገለጹት አካባቢው የብረት ማቅለጫዎችን ጨምሮ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች እና ፋብሪካዎች የሚገኙበት በመሆኑ በቀላሉ ተሰርቀው ወደ ብረት ማቅለጫ ኢንዱስትሪዎች የመሄድ ከፍተኛ ተጋላጭነት የሚታይበት ነው።
በሚፈፀመው ስርቆት የተነሳ በአካባቢው ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት በመሆን በህብረተሰቡ ዘንድ ቅሬታ እንደፈጠር ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዋና ዓላማም በአከባቢው እየተካሄደ ያለውን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሶሶ ስርቆት ያለበትን ደረጃ ከዞኑ እና ከወረዳዎቹ ለተወጣጡት ከፍተኛ አመራሮች በማስረዳት ድርጊቱን ለመከላከል እና ለማስቀረት እንዲሁም ጥፋተኞች አስተማሪ ቅጣቶች በሚያገኘበት ሁኔታ የጋራ መግባበት ለመፍጠር መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል ፡፡
የምስራቅ ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አጀማ እንደተናገሩት ስርቆቱ ከአካባቢው ማህበረሰብ የተሰወረ ባለመሆኑ የመድረኩ ተሳታፊዎች በየደረጃው ባለው መዋቅር ተጠቅመው ማህበረሰቡን በማወያየት ወንጀሉን የመከላከል እና ከፍተኛ የሀገር ሀብት የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ሆርዶፋ በበኩላቸው የውይይት መደረኮች መዘጋጀት ያለባቸው ስርቆት ሲፈፀም ብቻ ባለመሆኑ ተቀራርቦ መስራት የሚቻልበት የግንኙነት መስመር መዘርጋት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ተቀባይ ከሌለ ሌባ ስለማይኖር የብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎች ምን ዓይነት ብረቶችን ተረክበው እያቀለጡ እንደሆነ መፈተሽ ይገባል ብለዋል።
የመካከለኛ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን እና ጥገና ቢሮ 2 ሺህ 923 ነጥብ 98 ኪ.ሜ. የሚሸፍን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና 26 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በሥሩ ያስተዳድራል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 26 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የጣና በለስ-ጃዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ ዛሬ ኃይል መስጠት ይጀምራል
.....///......
የስርቆት ወንጀል ተፈፅሞበት ለአንድ ሳምንት ኃይል መስጠት ያቋረጠው የጣና በለስ- ጃዊ ባለ132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ ዛሬ ኃይል መስጠት እንደሚጀምር የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት ኃይል መስጠት ከጀመረ ሁለት ዓመት ያልሞላው የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀመው የስርቆት ወንጀል ያደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ነበር።
ሙሉ ለሙሉ የወደቁትን ሦስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በእንጨት በመቀየር እንዲሁም በገመድ መሳሳብ ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ሁለት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን ባሉበት በመጠገን ጊዜያዊ መፍትሔ ለመስጠት ተሞክሯል ብለዋል።
የስርቆት ወንጀል የተፈፀመበት ቦታ ተራራማ መሆኑ የጥገና ሥራውን ለማከናወን ፈታኝ ሆኖ እንደነበር አቶ ውበት ገልፀዋል።
በእንጨት የተቀየሩትን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በዘላቂነት ወደፊት በብረት ለመቀየር መታሰቡንም ነው ዳይሬክተሩ ያብራሩት።
የስርቆት ወንጀል ፈፅመዋል የተባሉ የተወሰኑ ተጠርጣሪዎችን ከክልሉ የመሠረተ ልማት፣ ከዞን እና ከወረዳ አመራሮች ጋር በመነጋገር በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ በከፍተኛ ወጪ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶዎችና ሽቦዎችን ከመሰል ዝርፊያዎች እንዲጠብቅና አጥፊዎችን ለፀጥታ አካላት እንዲጠቁም አቶ ውበት ጥሪ አቅርበዋል።
የጥገና ቡድኑ አስተባባሪ የሆኑት አቶ አምባው ጋሻው በቡከላቸው በኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የነበሩ ከ150 እስከ 200 የሚደርሱ የመወጣጠሪያ ብረቶች ላይ ስርቆት መፈፀሙን በፍተሻ ሥራ ማረጋገጣቸውን ገልፀዋል።
የጥገና ሥራውን ለማከናወን የአካባቢው ማህበረሰብና የበለስ ስኳር ፕሮጀክት ከፍተኛ ድጋፍ እንዳደረጉላቸው አስተባባሪው ተናግረዋል።
የጃዌ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት በልስቲ ኑሬ እንደገለፀው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ስርቆት የሚፈፅሙ አካላት ላይ መንግሥት ጠንከር ያለ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት አሳስቧል።
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን ከስርቆትና መሰል ወንጀሎች ለመከላከል ከአካባቢው ወጣቶች ጋር በጋራ እንደሚጠበቁም ነው ወጣት በልስቲ የተናገረው።
የጣና በለስ- ጃዌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በተፈፀመበት የስርቆት ወንጀል ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል መስጠት ማቋረጡን መዘገባችን ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 26 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠርና ማህበራዊ መስተጋብርን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
………..///////………
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምሥራቅ ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ለሠራተኛው ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠርና ማህበራዊ መስተጋብርን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት ሪጅኑ ከ2 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የማስተላለፊያ መስመሮችና በ13 የማከፋፈያ ጣቢያዎች መደበኛ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች ያከናውናል፡፡
በሪጅኑ መደበኛ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በሚገባ ለማከናወን ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ በተለያዩ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ይህን ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በአዲጋላ፣ በሁርሶ፣ በሀረር እና ድሬዳዋ ከተማ ባሉ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት፣ አካባቢን አረንጓዴ ለማድረግ ችግኞችን የመትከል እና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡
በድሬዳዋ ቁጥር 3 የማከፋፈያ ጣቢያ የተሰራው ሦስት መቶ ሜትር ርዝመት እና 5 ሜትር ስፋት ያለው የኮንክሪት አስፓልት መንገድ እና ግቢውን የማስዋብ ሥራ እንዲሁም የመኪና ማጠቢያ ግንባታ ትልቅ ማሳያ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
በሌላ በኩል በሪጂኑ ያለው ሠራተኛ ጤናውን ለመጠበቅ፣ የእርስበርስ ግንኙነቱን ለማጠናከር እና ማህበራዊ መስተጋብሩን የበለጠ ለማሳደግ የእግር ኳስ ጤና ቡድን ተመስርቷል።
የጤና ቡድኑ አስተባባሪ አቶ ማቲያስ ብዙነህ እንደገለፁት ቡድኑ የተመሰረተው በትርፍ ሰዓት ስፖርትን በማዘውተር ከእንቅስቃሴ ጉድለት ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ የጤና ችግሮችን በመቀነስ ጤናማ እና ለመደበኛ ሥራው ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችል ሠራተኛ ለማፍራት ታስቦ ነው፡፡
የጤና ቡድኑ ወደ ፊት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በሚዘጋጁ የጤና ስፖርት ክለቦች ውድድር ላይ በመሳተፍ ተቋሙን ለማስተዋወቅ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስተባባሪው ጠቁመዋል፡፡
ቡድኑንን ለመመስረት የቀረበውን ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ትብብር ላደረጉት የሪጅኑ ኃላፊ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አስተባባሪው በቀጣይ ቡድኑን በትጥቅና በሞራል በመደገፍ ተቋሙ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 25 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
24 የፋይናንስ፣ የክዋኔና ቴክኒካል የኦዲት ምርመራዎች ተከናውነዋል
………..//////……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት 24 የፋይናንስ፣ የክዋኔና ቴክኒካል የኦዲት ምርመራ ማከናወኑን የተቋሙ የውስጥ ኦዲት መምሪያ ገለፀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገ/እግዚአብሔር መዝገበ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 28 የፋይናንስ፣ ክዋኔና የቴክኒክ ኦዲቶችን ለማከናወን ታቅዶ 24 የኦዲት ምርመራዎች ተከናውነዋል፡፡
የኦዲት ምርመራዉ በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ አብዛኞቹን የሥራ ዘርፎች ባካተተ መልኩ የተካሄደ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ የተከናወኑት የፋይናንስና የቴክኒካል ኦዲት ምርመራዎች በውል አስተዳደር፣ በግዢ ስርዓት፤ በካሳ ክፍያ፣ በሠው ኃይልና የንብረት አያያዝና አጠቃቀም ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ደረጃውን የጠበቀ የምህንድስና ምክር አገልግሎት ስለመሰጠቱ፤ በዉል ስምምነት ጊዜ ስለመኖሩ የታክስ ጉዳዮች፣ በተቋሙ የገንዘብ አስተዳደር እና አጠቃቀም፤ የፍተሻ እና ጥገና ሥራዎች ላይ፤ የፍተሻና ሙከራ ሥራ ላይ ስላለው የቁጥጥር ስርዓት እንዲሁም ሌሎች የኦዲት ይደረግልን ጥያቄዎች በበጀት ዓመቱ ትኩረት የተደረገባቸው የኦዲት ምርመራ ሥራዎች መሆናቸውም አስረድተዋል፡፡
ምርመራው የተቋሙን የስጋት ተጋላጭነትና አስተዳደርን፣ የቁጥጥር ስርዓቱን፣ በተቋሙ ከፍተኛ በጀት ወጪ የሚያወጣባቸው እና በአብዛኛው እንደ ችግር የሚነሱ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ የተካሄደ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ እንዳሉት የኦዲት ምርመራ ሥራው በተቋሙ ያለዉን የአሠራር ስርዓት በማስተካከል ያለዉን ክፍተት በወቅቱና በአግባቡ ለማስተካከል ያግዛል፡፡
የኦዲት ሥራው በአመዛኙ በታሰበው መሰረት መጠናቀቁን የገለፁት ዳይሬክተሩ ለኦዲት ሥራ ወደተለያዩ የሥራ ክፍሎች በሚሄዱበት ጊዜ በአንዳንድ የሥራ ክፍሎች ለምርመራው የሚያስፈልጉ የሠውና የሠነድ መረጃዎችን በተሟላ እና በወቅቱ በማቅረብ በኩል ክፍተቶች መስተዋላቸውን ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 25 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ሀገራዊ አንድነትን ለማፅናት በመነጋገርና በመደማመጥ ሁሉም በሙያው ተግቶ መሥራት አለበት
………/////………..
በፖለቲካው የተገኘውን ድል በኢኮኖሚው መድገም እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ አሳሰቡ፡፡
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚው እንደገለፁት ሀገራዊ አንድነትን ለማፅናት በመነጋገርና በመደማመጥ ሁሉም በሙያው ተግቶ መሥራት አለበት፡፡
ተቋሙ ከሚሰራቸው መደበኛ ሥራዎች በተጨማሪ በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ፈጣን ምላሽ በመስጠት በጦርነቱ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በአስቸኳይ ጠግኖ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ነጻነታችን በደም እንዳስከበርን ሁሉ ድህነትን በላባችን ሰርተን በማስወገድ የታፈረችና የተከበረች ሀገር ለመገንባት የተሰጠንን ሥራ በአግባቡ ማከናወን አለብን ብለዋል፡፡
እንደ አቶ ደመረ ገለጻ ፍትህ የሰፈነባት፣ ዘረኝነት የከሰመባት እና በኢኮኖሚ ያደገች አገር መገንባት የመንግስትና ህዝብ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫች ሊሆን ይገባል፡፡
ኢትዮጵያ ያሉባትን የሰነበቱ የፓለቲካ ስብራቶች በመጠገን እና ከጎጥ አስተሳሰብ በመውጣት በአንድነት የፀናች ሀገር ለመመስረት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎችም የብሔር ፖለቲካ መዘዙ የከፋ መሆኑን መንግስት ተገንዝቦ ለማስተካከል ቁርጠኛ እንዲሆንና ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመገንባት በጎጥና በዘር መደራጀትን እንዲያስቀር ጠይቀዋል፡፡
በሀገሪቱ የተፈጠረውን አለመረጋጋት ተጠቅመው የኢኮኖሚ አሻጥር በመስራት በአቋራጭ ለመክበርና ህዝብን ለማማረር የሚሰሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ መውሰድ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
ሲንከባለሉ የመጡና በቂ ሀገራዊ ስምምነት በሌላቸው ጉዳዮች ላይ ተመካክሮ እልባት ላይ ለመድረስ በሰከነ መንፈስ ሀገራዊ ምክክሩን መደገፍ እንደሚያስፈልግም በውይይቱ ላይ ተነስቷል።
በጦርነት ላይ ሆኖ የተሳካ ምርጫ በማካሄድ የአዲስ መንግስት ምስርታ መካሄዱ፣ የህዳሴ ግድብ ሶስተኛ ዙር የውኃ ሙሊትን በስኬት በማጠናቀቅ ኃይል ማመንጨት መቻሉ፣ በአረንጓዴ አሻራ 6 ቢሊዮን ችግኝ መተከሉ እና የስንዴ ምርትን በማሳደግ አንድ ቢሊዮን ብር መዳኑ ከሀገራዊ ስኬቶች መካከል መሆናቸው ተብራርቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ለፕሮጀክቱ ግንባታ መሬታቸውን የለቀቁ ነዋሪዎች ምትክ መሬት እንዲሰጣቸው ጠየቁ
………..////……….
አዲስ ለተገነባው የአዳማ 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መሬታቸውን የለቀቁ ነዋሪዎች ከተማ አስተዳደሩ ምትክ መሬት እንዲሰጣቸው ጠየቁ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ ማከፋፈያ ጣቢያውን ሲጎበኙ ነዋሪዎቹ ምትክ መሬት ስላልተዘጋጀላቸው መቸገራቸውን ገልፀውላቸዋል፡፡
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢያቸው በመገንባቱ መደሰታቸውን የገለፁት የነዋሪዎቹ ተወካዮች አካባቢያቸው የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሆን ጠይቀዋል።
በተወካዮች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ሥራ አስፈፃሚው መሬታቸውን ለፕሮጀክቱ ግንባታ የለቀቁ አርሶ አደሮች ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸው ከአዳማ ከተማ አስተዳደር ጋር ስምምነት ተደርሶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተጨማሪ ውይይት እንደሚካሄድ ለነዋሪዎቹ ተወካዮች ገልፀዋል።
የኃይል ጥያቄውን በተመለከተም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመነጋገር ምላሽ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡
ይህን መነሻ በማድረግም ሥራ አስፈፃሚው ከአዳማ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር ባደረጉት ውይይት ለፕሮጀክቱ ግንባታ የተነሱት የአስራ ሁለት ቤቶች የካሳ ክፍያ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡
ይሁንና ምትክ ቦታ ስላልተዘጋጀላቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን ግንባታ ለማጠናቀቅ ችግር መፍጠሩን አንስተዋል፡፡
የአዳማ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በሪሶ ዶሪ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለተነሱ እንዲሁም ከኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ለሚነሱ የመሬት ባለቤቶች ምትክ ቦታ እንዲዘጋጅላቸው ለከተማው መሬት አስተዳደር የሥራ መመሪያ እንደሚሰጡ አረጋግጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአዳማ 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ከነባሩ የቆቃ ሁርሶ ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጋር ለማገናኘት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ የብረት ምሰሶ ተከላ ስራ ተጠናቆ የገመድ ዝርጋታ ሊጀመር መሆኑን በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይለ ጊዮርጊስ ገልፀዋል።
230 ኪሎ ቮልት አቅም ያለው የአዳማ II ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አራት ፓወር ትራንስፎርመሮች ያሉት ሲሆን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሲገባ ለአዳማ ከተማ አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በተቋሙ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ጥቃት ታስቧል
...........//////..........
በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ሁለተኛ ዓመት መታሰቢያ "መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት ታስቧል፡፡
በመታሰቢያ ፕሮግራሙ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላትና ሠራተኞች የተሳተፉ ሲሆን ዕለቱ መታሰቡ በዋጋ የማይተመን ሕይወታቸውን ስለሀገር ክብር መስዋዕትነት የከፈሉ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላትን ለማስታወስ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ህብረተሰቡ ከማስተላለፊያ መስመሩ ንክኪ እንዲርቅና ራሱን ከአደጋ እንዲጠብቅ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች ሊጠናከሩ ይገባል
..........//////...........
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት በቅርቡ ኃይል ማስተላለፍ በሚጀምርበት ወቅት ህብረተሰቡ ራሱን ከአደጋ እንዲጠብቅ እና ከመስመሩ ንክኪ እንዲርቅ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተጠቆመ።
መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ሲጀምር ስለሚደረጉ ጥንቃቄዎች እንዲሁም ለመስመሩ ስለሚደረጉ ጥበቃዎችና በመስመሩ ላይ እየደረሱ ያሉ ጉዳቶችን መከላከል በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ከኮንሶ ዞን የሥራ ኃለላፊዎች፣ እንዲሁም መስመሩ በዞኑ ከሚያልፍባቸው የወረዳና የቀበሌ የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች ጋር ውይይት ተካሂዷል።
የዞኑ መቀመጫ በሆነችው ካራት ከተማ ላይ በተካሄደው የምክክርና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ የዞን፣ የወረዳ እና የቀበሌ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
በውይይቱ ወቅትም ፕሮጀክቱ ስለሚኖረው ፋይዳ፣ በፕሮጀክቱ ላይ እየተስተዋሉ ስላሉ የተለያዩ ችግሮች እንዲሁም መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ በሚጀምርበት ወቅት ስለሚደረጉ ጥንቃቄዎች የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው ገለፃ አድርገዋል።
መስመሩ በተዘረጋበት ኮሪደር ላይ ወደ ፊት የግንባታ ሥራዎች እንዳይከወኑና ቋሚ ተክሎች እንዳይተከሉ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች የሚያደርጉትን ክትትል አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
አቶ ቴዎድሮስ እንዳሉት ህፃናት በወንጭፍና ምሶሶዎች ላይ በመውጣት ኢንሱሌተሮችን በመሰባበር፣ የማስጠንቀቂያ ምልክቶችን እየነቀሉ ስለሆነ ከድርጊታቸው እንዲታረሙ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
መስመሩ በቅርቡ ኃይል ማስተላለፍ የሚጀምር መሆኑን ተከትሎ ህፃናት በመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎችና በመስመሩ ሽቦዎች ላይ እንዳይወጡና ህብረተሰቡ ከመስመሩ ንክኪ እንዲርቅ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የግንዛቤ ሥራው እንዲጠናከር ሥራ አስኪያጁ ጠይቀዋል።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበዬሁ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት ተስፋ የተጣለበት መሆኑን ገልፀው በመሰረተ ልማት ጥበቃው የተስተዋሉ ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠልና ያሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል በቅርበት ክትትል እንደሚደረግ ገልፀዋል።
መስመሩ በሚያልፍባቸው በሌሎች ዞኖች የተከሰቱ የስርቆት እና የወሰን ማስከበር ችግሮች ወደ ፊት በዞኑ ላይ እንዳይስተዋሉ ሳይዘናጉ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
በመስመሩ ላይ ኃይል ሲለቀቅ በህብረተሰቡ ላይ አደጋ እንዳያደርስ የወረዳና የቀበሌ አመራሮቸ ከወዲሁ ታች ወርደው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በዞኑ የፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ከራሌ አራሳ እና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊው አቶ ጉራሾ ለሚታ እንደተናገሩት መስመሩ የጋራ ሀብት መሆኑን በመረዳት ህዝቡ ዘበኛ በመሆን በጋራ ጥበቃ ማድረግ ይኖርበታል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፋት የወረዳና የቀበሌ አመራሮች በበኩላቸው የህብረተሰቡን መልካም እሴት ለማስቀጠልና ህፃናት በመስመሩ ኢንሱሌተር ላይ እያደረሱት ያለውን ጉዳት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማስቆም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፍት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የሁመራ - ወልቃይት - ሽሬ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እየተጠገነ ነው
……….////………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን ለመጠገን የተጀመረው ሥራ እንዲሳኩ ርብርብ ላደረጉ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ በየደረጃው ላሉ አመራሮች እና የፀጥታ አካላት ምስጋናውን አቀረበ፡፡
በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት በጦርነቱ ሳቢያ ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በአጭር ጊዜ አጠናቆ ህብረተሰቡ ብርሃን እንዲያገኝ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡
ጥገናው ከተጠናቀቀው የወልዲያ አላማጣ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በተጨማሪ የሁመራ - ወልቃይት - ሽሬ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያ የፍተሻ እና የጥገና ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ከሁመራ እስከ ሽሬ ባለው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በተደረገ የፍተሻና ጥገና ሥራ 67 ቦታዎች ላይ የኮንዳክተር እንዲሁም 3 ቦታዎች ላይ የፋይበር ኦፕቲክስ መቆራረጥ አጋጥሟል፡፡
የሁመራ እና ወልቃይት ከተሞችና አካባቢያቸው ለረጅም ጊዜ ኃይል ተቋርጦ የቆየ በመሆኑ በአጭር ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያኙ ይሰራል ብለዋል፡፡
የወልዲያ - አላማጣ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ አገልግሎት መጀመሩ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት የጠቆሙት አቶ ሀብታሙ በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል ያገኙ የነበሩትን የሰቆጣ፣ ላሊበላ፣ ማይጨውና አጎራባች ከተሞች በቀላሉ ኃይል እንዲያገኙ የሚያስችል ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡
የመልሶ ጥገና ሥራው ከሰሜን ሪጅን በስተቀር የሁሉንም ሪጅን የጥገና ባለሙያዎች በማቀናጀት በመሰራቱ የላቀ ውጤት መመዝገቡን ነው ሥራ አስፈፃሚው የጠቆሙት፡፡
ሠራተኞችን ለሥራ ዝግጁ የማድረግ፣ የጥገና ግብዐቶችንና የመለዋወጫ ዕቃዎችን የማሰባሰብ ሥራዎች ቀድመው በመሰራታቸው እየተከናወኑ ያሉ የጥገና ሥራዎች በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቁ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች በጥገና ሥራው ላይ ያሳዩት ሞራልና ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ በአፋጣኝ እንዲያገኝ እያደረጉት ያለው ርብርብ አክብሮት የሚቸረው እንደሆነም ገልፀዋል፡፡
በጥገና ሥራው ላይ ከተቋሙ ባለሙያዎች በተጨማሪ በየአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን በማሳተፍ በቅንጅት እንዲሰራ መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡
የጥገና ሥራውን እያከናወኑ ላሉ ባለሙያዎች እየተደረገ ያለው አቀባበል መልካም መሆኑን ያወሱት አቶ ሀብታሙ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳድሮች መጠለያዎችን ከማዘጋጀት ጀምሮ ልዩ ልዩ ድጋፎችን እያደረጉ እንደሚገኙም አስታውቀዋል፡፡
የጥገና ሥራዎቹ እንዲሳኩ ርብርብ እያደረጉ ላሉ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ መስተዳደር አመራሮች እንዲሁም የፀጥታ አካላት ምስጋቸውን አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የማስተላለፊያ መስመሩ በተያዘለት መርሃግብር ሥራ እንጂጀምር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እተሰራ ነው
……../////……….
የኢትዮ - ኬንያ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በተያዘለት መርሃግብር ኃይል ማስተላለፍ እንጂጀምር ለማድረግ የሚስተዋሉ ችግሮች በአስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ተጠየቀ፡፡
በኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ እየተስተዋሉ ያሉ ስርቆቶችንና የወሰን ማስከበር ችግሮችን መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ እና መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ በሚጀምርበት ወቅት ስለሚደረጉ ጥንቃቄዎች በየደረጃው ከሚገኙ የጋሞ ዞን አመራሮችና ከቀበሌ የአደረጃጀት ተወካዮች ጋር በአርባ ምንጭ ከተማ ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ ስለ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ ገፅታና የግንባታ ሥራው አሁን ስለደረሰበት ሁኔታ፣ በኢትጵያና ኬኒያ መካከል ስለተፈረመው የኃይል ሽያጭ ስምምነት፣ እንደውሉ ባይፈፀም በሀገራችን ላይ ሊከሰት ስለሚችለው ቅጣት እና ስለፕሮጀክቱ ፋይዳ በተመለከተ የኢትዮ - ኬኒያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የኮንቨርተር ስቴሽን ፕሮጀክት የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
መስመሩ በሚያልፍበት የጋሞ ዞን ውስጥ ብቻ ከ10 ቶን በላይ የተለያየ ብረት፣ 8 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኦፕቲካል ግራውንድ ፋይበር ኬብል እንዲሁም 7 የኦፕቲካል ፋይበር ማገናኛ ሳጥኖች እንደተሰረቁ ገልፀዋል።
ጋሞ ዞንን ጨምሮ መስመሩ በሚያልፍባቸው አራት ዞኖች የተፈጸመውን ስርቆት ለመጠገን ተቋሙ ከ16 ሚሊዮን በላይ የቻይና ዩዋን እና 20 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉንም ተናግረዋል።
ከስርቆቱ በተጨማሪ በዞኑ የምዕራብ አባያ ወረዳ በ2007 ዓ.ም ካሳ ተከፍሎባቸው እስከ አሁን ያልተነሱ 16 ቤቶች እንዳሉና በአርባ ምንጭ ከተማ እና በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአዳዲስ ቤቶች ግንባታ የተከናወነ መሆኑ ነው የተገለፀው።
በመስመሩ ላይ የሚስተዋሉ የወሰን ማስከበር እና የስርቆት ችግሮችን በአስቸኳይ መፍትሔ በመስጠት በውሉ መሰረት ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ እና ሀገሪቱን ከቅጣት ለመታደግ ሁሉም በኃላፊነት መስራት እንዳለበትም አቶ ቴዎድሮስ ጠይቀዋል።
መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ በሚጀምርበት ወቅት በህብረተሰቡ ላይ አደጋ እንዳያስከትል የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ በርገኔ በቀለ በበኩላቸው በኘሮጀክቱ እየተስተዋሉ ላሉ ችግሮች በወቅቱ መፍትሄ ለመስጠት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየተስራ መሆኑንም ተናግረዋል።
መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ሲጀምር በህብረተሰቡ ላይ ጉዳት እንዳያደርስ መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የተጀመሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
ከስርቆት ጋር በተገናኘ የተያዙ የወንጀል ጉዳዮች በፍጥነት እልባት እንዲያገኙና ከወንጀሉ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት ይሰራል ብለዋል፡፡
እንደ አማካሪው ገለጻ ካሳ ተከፍሏቸው እስከ አሁን ላልተነሱ ቤቶች ምትክ ቦታ በመስጠት የመስመሩን ኮሪደር ከወሰን ማስከበር ነጻ ለማድረግ በየደረጃው ያሉ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች መፍትሄ እንዲሰጡም አቅጣጫ ተቀምጧል ።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መድረኩ በፕሮጀክቱ ላይ የነበራቸውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት እንዳገዛቸው በመግለጽ ችግሮችን ለመፍታት በሚሰራው ሥራ ላይ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
የሃይማኖት ተቋማትን፣ ት/ቤቶችን፣ እድሮችንና ሌሎች የተለያዩ መድረኮችን በመጠቀም የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን ለመስጠት እና መሰረተ ልማቱን ከስርቆት ለመታደግ በኃላፊነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
በውይይቱ ላይ የዞን፣ የወረዳና የአርባ ምንጭ ከተማ የፍትህና የጸጥታ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፤ የወረዳና የቀበሌ አስተዳዳሪዎች እንድሁም የቀበሌ አደረጃጀት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
በቀጣይ በኮንሶና ደራሼ ልዩ ወረዳ ተመሳሳይ ውይይቶች ለማካሄድ ዕቅድ ተይዟል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 22 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በበለስ ጃዊ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ዝርፊያ በመፈፀሙ ኃይል ተቋርጧል
........../////.............
ከጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ወደ ጃዊ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በሌቦች በመፈታታቸው ኃይል መቋረጡን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንዳስታወቁት ዝርፊያው የተፈፀመው አይማ ገብርኤል ቀበሌ ጌሾ ወንዝ አካባቢ ነው።
ሦስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በሌባ በመፈታታታቸው መውደቃቸውንና አንድ ተጨማሪ ምሰሶ በመሳሳብ ጉዳት ደርሶበት መውደቁን ተናግረዋል።
በዚህ የተነሳ ለበለስ ስኳር ፕሮጅክት፤ ለጃዊና አካባቢው የሚሰጠው የጃዊ ኤሌትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ መቋረጡን አቶ ውበት ገልፀዋል።
በመሆኑም የወደቁትን ምሰሶዎች ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ደርሶ ጥገና መጀመሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ ጥገናውን ለማጠናቀቅ እስከ አንድ ሳምንት ሊፈጅ እንደሚችል ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡ የደረሰው ጉዳት እስኪጠገን በትዕግስት እንዲጠብቅና ዘራፊዎችን ለፀጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
