ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 546 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 546 名订阅者。

根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 546
订阅者
+824 小时
-227
+2730
帖子存档
ተቋማዊ ባህልን የሚያሻሽሉ ማኑዋሎች ፀድቀው ተግባራዊ ተደረጉ ……..//////……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተቋም ደረጃ የተናበበና ወጥነት ያለው የአመራር ዘይቤ እና ባህል መፍጠር የሚያስችል
ተቋማዊ ባህልን የሚያሻሽሉ ማኑዋሎች ፀድቀው ተግባራዊ ተደረጉ ……..//////……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተቋም ደረጃ የተናበበና ወጥነት ያለው የአመራር ዘይቤ እና ባህል መፍጠር የሚያስችል የሥራ መሪዎች መጽሐፈ ዕድ (Managers’ handbook) ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ መዋሉን የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ እንደገለፁት በተቋሙ ጠንካራ ባህል እንዲኖር ለማስቻል በተቋሙ ውስጥ በሁሉም ክፍሎች፣ እርከኖችና የስራ ዘርፎች (መስኮች) ወጥ የሆነ የስራ አመራር አተገባበር መኖሩ ፋይዳው የላቀ ነው፡፡ የተዘጋጀው የሥራ መሪዎች መጽሐፈ ዕድ የድርጅቱን የሥራ አመራር አተገባበር እና ፍልስፍና የሚወስን እና የሚያስተዋውቅ በመሆኑ ከተቋማዊ ባህል ግንባታ አንፃር ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡ በተያያዘ ዜና ተቋማዊ መማማርን እና የራስን አቅም የማጎልበት ባህል እንዲዳብር ለማበረታታት አሰልጥኖ የማብቃት() እና የግል አቅም ማጎልበቻ ዕቅድ ማኑዋሎች ተዘጋጅተው ተግባራዊ መደረጋቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ እንደሥራ አስኪያጁ ገለፃ የማኑዋሎቹ ወደ ሥራ መግባት በተቋሙ የሚኖረውን የዕውቀት ሽግግር ከማቀላጠፍ ባለፈ የቡድንና የግለሰብን አፈፃፀም በማሳደግ ተቋሙ ውጤት እንዲያመጣ የሚያስችለው ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

የወልዲያ አላማጣ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ ........../////.......... በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ጉዳት ደርሶበት ሲጠገን የሰነበተው የወልዲያ አላማጣ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች የቴክኒክ ድጋፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቴ እንዳስታወቁት ዛሬ ያለዕረፍት በተሰራው የጥገና ሥራ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና እና የተሰበሩ ኢንሱሌተሮች ቅየራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ መስመሩን መፈተሽ ተጀምሯል፡፡ በአንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የደረሰው ጉዳት በቀጣይ እንደሚጠገን የገለፁት አቶ ተስፋዬ የምሰሶው ጉዳት ግን መስመሩን ኃይል ከመስጠት የሚያግደው እንዳልሆነ ተናግረዋል። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎች ከሦስት ሳምንት ያላነሰ ጊዜ የሚፈልገውን ሥራ በአንድ ሳምንት በማጠናቀቃቸው አመስግነዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው የተቋሙ ሠራተኞች ለሦስተኛ ጊዜ ጉዳት የደረሰበትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በፍጥነት በመጠገን ከህዝብ ጎን መቆማቸውን በተግባር በማሳየታቸው ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል። በቀጣይ በሚከናወኑ ቀሪ የጥገና ሥራዎች ላይ ከዚህ በተሻለ በትብብር በመስራት የተቋሙን መልካም ሥም የሚያስጠብቅ ተግባር እንዲያከናውኑ አሳስበዋል። ከወልዲያ እስከ አላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ ያለው መስመር ጥገና መጠናቀቅ ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲያገኙ የነበሩት ላሊበላ፣ ሰቆጣና ቆቦ እንዲሁም ማይጨው እና አካባቢያቸው ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል። በመሆኑም የጥገና ሥራው በመጠናቀቁና ኃይል የመስጠት ሙከራው በስኬት በመከናወኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጥገና ባጠናቀቀባቸው አካባቢዎች ኃይል ማግኘት የሚቻል መሆኑን እናስታውቃለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

ከወልዲያ - አላማጣ ያለው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት መልሶ ጥገና ሥራ 85 በመቶ ደርሷል ........../////.......... በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ከወልዲያ እስከ አላማጣ ባለው መስመር የወደመውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር የመጠገን ሥራ 85 በመቶ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንዳስታወቁት እስከ አንድ ወር እንደሚወስድ የተገመተው የመልሶ ጥገና ሥራ ከሰሜን ሪጅን በስተቀር ከሁሉም ሪጅኖች የተውጣጡ ባለሙያዎች ስለተሳተፉበት ከተጠበቀው ጊዜ ፈጥኖ ወደመጠናቀቅ እየተቃረበ ነው፡፡ የጥገና ባለሙያዎቹ ሥራዎችን ተከፋፍለው እየሰሩ በመሆኑ ቀሪ ሥራዎችን በቀጣዮቹ ሦስት ወይም አራት ቀናት ውስጥ ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥርጭት መስመሮች ዝግጁ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ ጥገና በርብርብ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት አቶ በድሩ በአንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የደረሰው ጉዳት በቀጣይ እንደሚጠገን ገልፀዋል፡፡ የአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ምንም ችግር እንደሌለበት በመረጋገጡ የመስመሩ ጥገና እንደተጠናቀቀ ቀደም ሲል ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ያገኙ የነበሩት ላሊበላና ሰቆጣ ከተሞችና አካባቢያቸው ኃይል መስጠት ይቻላል ብለዋል፡፡ እንደ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ገለፃ ለጥገና ሥራው አስቀድሞ ዝግጅት ስለተደረገ በሥራው ላይ የገጠመ ችግር የለም፡፡ በሥራው ላይ በቀን በአማካይ ከሁለት በላይ የጥገና ባለሙያዎችና የገልበት ሠራተኞች እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የሁመራ ወልቃይት መስመርን ለመጠገን የፍተሻ ሥራ የጀመሩት ባለሙያዎች እስከ ተከዜ ወንዝ ያለውን ፍተሻ ያጠናቀቁ ሲሆን ከተከዜ ባሻገር ያለውን ፍተሻ ለመስራት ወደስፍራው ማቅናታቸውን በስፍራው ካሉ ባለሙያዎቻችን መረዳት ችለናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም በዳይሬክሽናል ድሪሊንግ ኢንጅነር 2ኛ፣ ኢሬትድ ድሪሊንግ ኢንጅነር 2ኛ እና ዌልደር 3ኛ የስራ መደቦች በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ.ም በዋናው መ/ቤት ሜክሲኮ በሚገኘው ኬኬር ህንጻ 2ኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

photo content

የጡረታ ጊዜ ክፍያን ወደ 150 በመቶ ማሳደጉን ማህበሩ አስታወቀ ……….////……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር አባላቱ ጡረታ በሚወጡበት ወቅት የሚፈፅመውን ክፍያ ወደ 150 በመቶ ከፍ ማድረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር አስታውቋል። የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም አገልግሎታቸውን አጠናቀው በጡረታ በክብር ለሚሰናበቱ የማህበሩ አባላት ይከፍል የነበረውን የአንድ ወር ደመወዝ በማሻሻል ወደ አንድ ወር ተኩል አሳድጓል። አባላቱ በማህበሩ የነበራቸውን ቆይታ ታሳቢ ያደረገ 150 በመቶ፣ 115 በመቶ እና የአንድ ወር ደመወዝ ክፍያ ተግባራዊ መደረጉን የገለፁት አቶ መኮንን ከመጪው ታህሳስ ወር ጀምሮ እስከ ሁለት ወር ደመወዝ የሚደርስ ክፍያ ለመፈፀም መታቀዱንም ተናግረዋል። ክፍያውም ምንም ተቀናሽ ሳይኖር የሠራተኛው ሙሉ ደመወዝ (Gross salary) በጡረታ ለሚሰናበቱ አባላቶቹ እየከፈለ እንደሚገኝ የገለፀው ማህበሩ እስከአሁንም እንደየደመወዝ መጠናቸው ለአንድ አባል እስከ 60 ሺህ ብር የሚደርስ ክፍያ መፈፀሙን አስታውቋል። ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታትም በጡረታ በክብር ለተሰናበቱ አባላቶቹ ከ2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መክፈሉን ገልፀዋል፡፡ ማህበሩ የአባላቱን ጥቅም ለማስጠበቅ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ ባሻገር ከአባላቱ የሚሰበስበውን ገንዘብ የተሻለ ወለድ በሚያስቡ ባንኮች በዝግ አካውንት በማስቀመጥ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከባንክ ወለድ ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱንም ነው ያስታወቁት። አቶ መኮንን እንደገለፁት ማህበሩ የተቋሙን አቅም ታሳቢ ባደረገ መልኩ የሠራተኛውን ጥቅምና መብት ለማስከበር እየተሰራ ነው። በ2007 ዓ.ም እንደ አዲስ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ከ4000 በላይ አባላቶች አሉት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ደህንነት ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ኃላፊዎቹ አረጋገጡ ……../////…………. የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ተሸካሚ የብረት ማማዎችን ከስርቆት ለመታደግ እና የጥገና ባለሙያዎች ያለስጋት ሥራቸውን እንዲያከናውኑ ለማድረግ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማከፋፈያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የተመራ ቡድን ከኦሮሚያ ክልል እና ከዞን አመራሮች ጋር የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ውይይት አካሂዷል፡፡ ሥራ አስፈፃሚው በውይይቱ ላይ እንደገለፁት የህዳሴ - ዴዴሳ - ሆለታ ከፍተኛ መስመር የፍተሻ እና የጥገና ሥራ ለማከናወን በተለይም በወለጋ አካባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል፡፡ ከፊንጫ ወደ ደብረማርቆስ ለተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራ ለማከናወን በወለጋ እና አካባቢው ያለው የፀጥታ ችግር እክል መፍጠሩን ለዞን አመራሮቹ ገልፀውላቸዋል። የካሳ ክፍያ ተከፍሏቸው ከተነሱ በኋላ በመስመሩ ሥር ባሕር ዛር እንደገና በማደጉ ምክንያት ለመቁረጥ ሲሞከር ከህግ ውጪ ድጋሚ የካሳ ክፍያ የሚጠይቁ ግለሰቦች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡ የኢትዮ - ኬንያ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በቅርቡ በ 5 መቶ ሺህ ቮልት ወደ ኬኒያ ኃይል ማስተላለፍ ስለሚጀምር የአካባቢው ህብረተሰብ ላይ ጉዳት እንዳያደርስ የብረት ማማዎች ላይ ከመንጠላጠል፣ ሽቦዎችንና ብረቶችን ከመነካካት እንዲቆጠብ ከዞን ጀምሮ እስከ ቀበሌና ጎጥ ድረስ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች እንዲከናወኑ ሥራ አስፈፃሚው ጠይቀዋል። በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ኢዳኤ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ለሀገር ያላቸው ፋይዳ ጉልህ መሆኑን ገልፀው በተጠቀሱት አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ለማድረግ በርካታ ኦፕሬሽኖች እየተሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፍተሻ እና የጥገና ባለሙያዎች ያለምንም ስጋት ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ የፀጥታ ኃይሎች እጀባና ጥበቃ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል፡፡ የብረት ማማዎችን ከስርቆት ለመታደግ ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እስከ ቀበሌ ድረስ ባለው የመንግስት መዋቅር ይከናወናል ብለዋል። በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፀጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ጄነራል አበበ ገረሱ በበኩላቸው በወለጋና አካባቢው ያለው የሸኔ እንቅስቃሴ እየተደረገበት ባለው የተቀናጀ ኦኘሬሽን እየተዳከመ መምጣቱን ገልፀዋል፡፡ ይሁንና አሁንም የፀጥታ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የፍተሻና ጥገና ሥራዎችን ለሚያከናውኑ የተቋሙ ባለሙያዎች በልዩ ኃይልና በሚሊሻዎች የተቀናጀ ጥበቃና እጀባ እንደሚከናወን አስታውቀዋል። የህዳሴ - ዴዴሳ - ሆለታ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሚያልፍባቸው የምዕራብ ወለጋ፣ የምስራቅ ወለጋ እና የምዕራብ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪዎች በበኩላቸው የአካባቢያቸውን ሠላም ለማስጠበቅ ተቀናጅተው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ ኃላፊዎቹ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ይበልጥ ተቀራርበው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ የክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ጉታ ላቶሬ በበኩላቸው የካሳ ክፍያ ሳይከፈላቸው በስህተት የተዘለሉ አርሶአደሮች ካሉ ተጣርቶ ሊከፈላቸው ይገባል ያሉ ሲሆን ካሳ ሙሉ በሙሉ የተከፈላቸው ግን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ ዛፎቻቸውን እንዲያነሱ ይደረጋል ብለዋል። አምስት መቶ ኪሎ ቮልት ያላቸው የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚገኙት ከህዳሴ - ዴዴሳ - ሆለታ እንዲሁም በኢትዮ - ኬንያ መስመሮች ብቻ በመሆኑ የመስመሮቹን ደህንነት ለማስጠበቅ፣ ከስርቆት ለመከላከል እና በፍተሻና ጥገና ጊዜ የፀጥታ ስጋቶችን ለማስወገድ ሁሉም በኃላፊነት ሊሰራ ይገባል ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የመልሶ ጥገና ሥራውን በአጭር ጊዜ አጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመር ሁሉም ሪጅኖች በርብርብ እየሰሩ ነው ........../////.......... በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በፍጥነት በመጠገን ለረጅም ጊዜ በጨለማ ውስጥ የቆየው ህብረተሰብ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ የተቋሙ ሁሉም ሪጅን የጥገና ባለሙያዎች ርብርብ መስራት ጀምረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መሥመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት በተጀመረው የመልሶ ጥገና ሥራ የምሥራቅ፣ የደቡብ ምዕራብ፣ የደቡብ፣ የመካከለኛ እና የሰሜን ምስራቅ ሪጅን የጥገና ቡድኖች ወደ ስፍራው በማቅናት ሥራቸውን ጀምረዋል፡፡ የቀሩት ሪጅኖችም የቴክኒክ ባለሞያዎችን ወደ ሥፍራው ለመላክ ዝግጅት ማጠናቀቃቸው ገልፀዋል፡፡ የወልዲያ- አላማጣ የባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መሥመር ጥገና በትናንትናው ዕለት መጀመሩን የገለፁት ኃላፊው ከተጀመረው ሥራ ጎን ለጎን ከባህርዳር - አላማጣ የባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ለማከናወን የፍተሻ ሥራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡ የመስመሩ መጠገን ከዓመት በላይ ኃይል ተቋርጦባቸው የቆዩ የላልይበላና ሰቆጣ ከተሞች እንዲሁም ሌሎች የዋግኸምራ ዞን አካባቢዎች መብራት እንዲያገኙ ያስችላል። ከወልዲያ ዶሮ ግብር አካባቢ በህወኃት ተዘርፎ በተወሰደው ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ ምትክ እየተገነባ በሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ በድሬ ሮቃ፣ ሀራ ገበያ እና ጭፍራ መስመር ያሉ የአፋር ከተሞች ኃይል እንዲያገኙ ይደርጋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

ሰቆጣና ላሊበላ ከአላማጣ ኃይል እንዲያገኙ የሚያደርግ ጥገና ተጀምሯል ……..//////……… በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ጉዳት የደረሰበት የወልዲያ - አላማጣ የባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መሥመር ጥገና ተጀመረ፡፡ የመስመሩ መጠገን ከዓመት በላይ ኃይል ተቋርጦባቸው የቆዩት የላሊበላና ሰቆጣ ከተሞች እንዲሁም ሌሎች የዋግኸምራ ዞን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መሥመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት ከወልዲያ ዶሮ ግብር ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ አላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ በተደረገ ፍተሻ 50 ቦታዎች ላይ የኮንዳክተር ጉዳትና መበጣጠስ ተከስቷል፡፡ በአንድ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በመሳሪያ የመመታት አነስተኛ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ በአላማጣ ማከፋፋያ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ ጣቢያው ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰበት ተረጋግጧል፡፡ አላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ቀደም ሲል ከባህርዳር፣ አሸጎዳ እና ኮምቦልቻ ከተዘረጉ መስመሮች ኃይል ያገኝ እንደነበር የጠቀሱት ኃላፊው ከባህርዳር - አላማጣ የተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መሥመር እስኪጠገን ድረስ ከኮምቦልቻ - አላማጣ ያለውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት መሥመር የመጠገን ሥራ ዛሬ ተጀምሯል፡፡ ጥገናው ሲጠናቀቅ ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የላሊበላ፣ ሰቆጣና ማይጨው መስመሮች ዳግም ኃይል እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡ በፍጥነት ኃይል እንዲያገኝ ታስቦ በተንቀሳቀሰው የጥገና ቡድን ውስጥ የሰው ኃይል ብዛት በመጨመር ሥራ መጀመሩን የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚፈልገው እገዛ የሚኖር ከሆነ ታይቶ ጥያቄው እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ላለፉት ሁለት ዓመታት ኃይል የተቋረጠበት የወልቃይት ሁመራ አካባቢ ኃይል ማግኘት እንዲችል የደረሰውን ጉዳት መጠን የሚለዩ ባለሙያዎች ወደ ሥፍራው መንቀሳቀሳቸውን አቶ ተስፋዬ አስታውቀዋል፡፡ ባለሙያዎቹ በሚልኩት የጉዳት ሪፖርት ላይ ተመስርቶ የጥገና ሥራው እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮ ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከፍተኛ አደጋ እንዳያስከትል በየደረጃው ያሉ አመራሮች ጉዳዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ………////…….. የኢትዮ ኬንያ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኃይል ለመስጠት እንዲችል እንቅፋት የሚሆኑ ጉዳዮች ተለይተው በፍጥነት እልባት እንዲሰጣቸው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው አሳሰቡ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ እና የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ሊጀመር መሆኑን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ ከተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱና የደረሰበት ደረጃ፣ በሁለቱ ሀገሮች መካከል ስለተፈረመው የኃይል ሽያጭ ውል እና በውሉ መሰረት እንደሀገር ግዴታችንን ባንወጣ ስለሚከተለው ችግር እንዲሁም ፕሮጀክቱ ስላለው ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ ገለፃ አቶ ክብሮም አድርገዋል፡፡ በተለይ መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች በህገ ወጥ መንገድ በወረራ የተገነቡ አዳዲስ ቤቶች መኖራቸውን፣ ተገቢው ካሳ ተከፍሏቸው በወረዳና በከተማ አስተዳደሮች ቤቶቹ እንዲነሱ አለመደረጋቸው እና በኃይል ማስተላለፊያ ግዙፍ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ማስቆም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውን በመግለጽ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ መስመሩ በቅርቡ ኃይል ማስተላለፍ ስለሚጀምር ህብረተሰቡ ከታወር ንክኪ እንዲርቅ እና እንዲጠነቀቅ በክልሉ የአስተዳደር መዋቅር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የሚሰጥበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቀዋል፡፡ በመስመሩ ላይ ስላሉት ችግሮች የወላይታና ጋሞ ዞኖች እንዲሁም የኮንሶ ልዩ ወረዳ አመራሮች በቂ ግንዛቤ እንዳላቸው እና ከዚህ በፊትም ከየዞኖቹ ጋር በነበሩ የጋራ መድረኮች ላይ እንደ አጀንዳ ተነስቶ ውይይት እንደተደረገበትና ችግሮቹን ለመፍታት አቅጣጫዎች ስለመቀመጡ ተነስቷል፡፡ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተደዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው በበኩላቸው መስመሩ ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ሥራ ሲጀምር የተጠቀሱት ችግሮች በፍጥነት ካልተቀረፉ ከፍተኛ አደጋ ስለሚያስከትል በየደረጃው ያሉ አመራሮች ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መሥራት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም ለህብረተሰቡ በተለያዩ መንገዶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንዲሰራ ያሳሰቡት ርዕሰ መስተዳድሩ በመስመሩ ላይ ኤሌክትሪክ ስለሚለቀቅ ለጥንቃቄ ብቻ ሳይሆን ስርቆትን አስመልክቶም ግንዛቤ ማስጨበጥ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡ የኤሌክትሪክ መሰረተልማት ስርቆትን በተመለከተ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት የተያዙ መዝገቦች በፍጥነት ውሳኔ እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ እንዲሰራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአርባምንጭ ከተማ በሚዘጋጀው የአመራር መድረክ ላይ የዞንና ወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የፖሊስ ኮሚሽነሮች፣ የከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የሠላምና ፀጥታ ኃላፊዎች፣ የዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና ልዩ አማካሪዎች ከስርቆትእና ወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው በተነሱት ጉዳዮች ላይ በፍጥነት እልባት እንዲሰጡና እንዲያስፈጽሙ ርዕሰ መስተዳድሩ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ በህጋዊ መንገድ ከይዞታቸው ለሚነሱት ተነሺዎች በአጭር ቀናት ውስጥ ቦታ እንዲዘጋጅ፣ መነሳት ያለባቸውም እንዲነሱና ጉዳዮን የሚከታተል ግብረ ኃይል በፍጥነት እንዲቋቋም አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

አልማዝ ገብቻለሁ ብላለች ሰው ሃይል

photo content
+6

በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የገጠመው ብልሽት ተጠግኗል ……….////………. በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ በብልሽት ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁሞ የነበረው ባለ 132/66/33 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመር ተጠግኖ ወደ ሥራ መመለሱን የምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጥገናና ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳስታወቁት ካለፈው ሰኞ ማለዳ ጀምሮ ባልታወቀ ብልሽት ምክንያት መስራት አቁሞ የነበረው ትራንስፎርመር ከአምስት ቀናት አድካሚ የፍተሻና የጥገና ሥራ በኋላ ዛሬ ሥራ ጀምሯል፡፡ 25 ሜጋ ቮልት አልፔር አቅም ያለው ይህ ትራንስፎርመር በመበላሸቱ የተነሳ የምስራቅ ሐረርጌ የተወሰኑ አካባቢዎች የኃይል መቆራረጥ ገጥሟቸው እንደነበር አቶ ጋሻው ገልፀዋል። ትራንስፎርመሩ ከ24 ዓመታት በላይ በከፍተኛ ጭነት ያገለገለ በመሆኑ በቮልቴጅ ማስተካከያ አንቀሳቃሽ ባለ ጥርስ ማሽን ላይ በተከሰተ ችግር ምክንያት ለብልሽት መብቃቱ በፍተሻ ወቅት መታወቁን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ የቮልቴጅ ማስተካከያ አንቀሳቃሽ ባለ ጥርስ ማሽን ልዩ የጥገና ባለሙያዎች ከውጭ ሀገር እንደሚመጡ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ባለሙያዎቹ ሲመጡ ለተጨማሪ ጥገና ኃይል እንደሚቋረጥ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው የገጠመውን ችግር ተረድተው ለትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞችና በጥገና ሥራው ላይ ቀን ከሌሊት ለተሳተፉ ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 13 ቀን 2015 ዓ.ም