EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 537
ሠላም ለሁላችሁ!
ደም ለሚፈልጉ ወገኖቻችን ያዘጋጀነው የደም ልገሳ ስለተጀመረ ሠራተኞቻችሁን አስተባብራችሁ ግራውንድ ፍሎር ላይ እንድንገናኝ መልዕክቱን እንድታስተላልፉልን እንጠይቃለን!!
ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችንና ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን የጀመርነው የገንዘብ፣ የአልባሳት እንዲሁም የንፅህና መጠበቅያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የተሳተፋችሁትን እንዲሁም በቀጣይ የምታደርጉትን ተሳትፎ ታሳቢ አድርገን እናመሰግናለን።
ደማችን ለወገናችን!!
ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!!!!
15 537
የኮምቦልቻ ሠመራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና በመገባደድ ላይ ይገኛል
…..///……
የኮምቦልቻ ሠመራ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ከ80 በመቶ በላይ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሃብታሙ ውቤ ገለፁ፡፡
አቶ ሀብታሙ እንደገለፁት በሽብርተኛው የህወሓት ቡድን ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መካከል የኮምቦልቻ ሠመራ መስመር አንዱ ነው።
አካባቢው ከሽብርተኛው ቡድን ነፃ ከወጣ ጀምሮ ጉዳት የደረሰባቸውን መስመሮችና ምሶሶዎች በከፍተኛ ርብርብ የጥገና ስራው እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በመሳሪያ ተመተው ወድቀው የነበሩ ምሶሶዎች ተከላ መጠናቀቁን እና የተበጣጠሱ መስመሮች ጥገና በርብርብ እየተከናወነ መከናወኑንገልፀዋል።
እስካሁንም በተከናወነው የጥገና ሥራ ከ 80 በመቶ በላይ መጠናቀቁን የጠቆሙት አቶ ሀብታሙ በቅርቡም ቀሪውን ሥራ በማጠናቀቅ አገልግሎት ለማስጀመር ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 07 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
ከጃማ ደጎሎ እስከ አለም ከተማ ያሉ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ አግኝተዋል
…..///……
በካራምሽግ አካባቢ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት የነበረው ከጃማ ደጎሎ እስከ ዓለም ከተማ ያለው ከፍተኛ ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ አካባቢዎቹ ኃይል አግኝተዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደተናገሩት ከአንድ ወር በላይ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩት የሚዳ መራኛ፣ ዓለም ከተማ፣ ፌጥራ፣ ሬማ፣ ደራ ጉንዶመስቀል እና ለሚ ከተሞች ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ኃይል አግኝተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 07 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
ከጃማ ደጎሎ እስከ አለም ከተማ ያለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቀቀ
…..///……
ሽብርተኛው የህወሓት ቡድን ከጃማ ደጎሎ እስከ ዓለም ከተማ ባለው ማስተላለፊያ መስመር ያደረሰውን ጉዳት የመጠገን ሥራ ተጠናቆ ለሙከራ ሥራ ዝግጁ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ፡፡
ሥራ አስ ፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደተናገሩት በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ቢሆንም የጥገና ቡድኑ ከፍተኛ ርብርብ በማድረጉ መስመሮቹ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ከአንድ ወር በላይ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ የሚዳ መራኛ፣ ዓለም ከተማ፣ ደራ ጉንዶ መስቀል እና ለሚ ከተሞች በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ኃይል የሚያገኙ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 07 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
ከኮምቦልቻ እስከ ሰመራ ያለው ጥገና ከ60 በመቶ በላይ ተጠናቋል
…..///……
አሸባሪው ህወሓት ከኮምቦልቻ እስከ ሰመራ ባለው ማስተላለፊያ መስመር ያደረሰውን ጉዳት የመጠገን ሥራው ከ60 በመቶ በላይ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ፡፡
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንዳስታወቁት በመስመሩ ላይ እስካሁን 52 ሚሊየን ብር የሚገመት ውድመት መድረሱ ተረጋግጧል።
ይህም በሰመራና በአፋር ክልል የተለያዩ ከተሞች በሚኖሩ ዜጎች የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ለወራት የዘለቀ አሉታዊ ጫና አሳድሮ ቆይቷል ብለዋል፡፡
ሁለት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች እና ኃይል ማስተላለፊያ ሽቦዎች በአብዛኛው ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን አሁን ላይ ከኮምቦልቻ ሰመራ ያለው መስመር ጥገና ከ60 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡
በተያያዘ ዜና በሰሜን ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ እና በደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ደጎሎ ወረዳ መካከል ካራ ምሽግ ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መሰረተልማት ውድመት መድረሱን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመር ጥገና የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አስታውቀዋል፡፡
ኃላፊው አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንዳስታወቁት በካራ ምሽግ አካባቢ የሚያልፈው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከባድ ጉዳት ደርሶበታል፡፡
መስመሩን በመጠገን አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 06 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
በካሳጊታ በከባድ መሳሪያ ተመተው የወደቁ ምሰሶዎችን መልሶ የመትከል ሥራ ተጠናቋል
……///……..
በአሸባሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመጠገን መልሶ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ መቀጠሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር ጥገና የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ ገለፁ፡፡
ኃላፊው አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት የደረሱ ጉዳቶችን በመለየትና በፍጥነት መልሶ በመጠገን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በተቋሙ ዘጠኙም ሪጅኖች ያሉ የጥገና ባለሙያዎች በቅንጅት በመሥራት ላይ ናቸው፡፡
የጥገና ቡድኑ ሥራውን ለማቀላጠፍ በሦስት አቅጣጫዎች - በጋሸና፣ በኮምቦልቻና በሚሌ መስመሮች ተከፋፍሎ እየሰራ መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
በኮምቦልቻ መስመር ጥገናውን እያከናወነ ያለው ቡድን ባከናወናቸው የመልሶ ጥገና ሥራዎች ከሸዋ ሮቢት እስከ ደሴ ያሉ ከተሞች እንዲሁም ወደ አቀስታ መስመር ያሉ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡
በሚሌ በኩል ያለውን የጥገና ሥራ የሚያስተባብሩት የምሥራቅ ሪጅን ትራንስሚሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ በበኩላቸው የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነና ከጠበቁት በላይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ከካሳጊታ እስከ ኤሊውሃ 20 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው መስመር ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንና መስመሩን በአብዛኛው እንደአዲስ የመዘርጋት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በካሳጊታ በከባድ መሳሪያ ተመተው የወደቁ ሶስት ምሰሶዎችን መልሶ የመትከል ሥራ መጠናቀቁንም ገልፀዋል፡፡
ከኮምቦልቻ ሠመራ የሚሔደውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በአራት ቡድኖች ተከፋፍሎ ሁሉም ተናቦ እየሠራ ነው ብለዋል፡፡
የጥገና ቡድኑ ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅና በበርካታ የአፋር ከተሞች የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማስጀመር በትጋት እየተሰራ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 05 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
የተቋሙ ሠራተኞች የደም ልገሳ እንደቀጠለ ነው
........./////............
የድሬዳዋ ተጠባባቂ ዲዝል ኃይል ማመንጫ ሰራተኞች በዛሬው እለት 20 ዩኒት ደም እና የ30 ሺ ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የጣቢያው ኃላፊ ገለጹ፡፡
ኃላፊው አቶ ጌትነት ዓለሙ እንደተናገሩት ደሜን ለወገኔ በሚል መሪ ቃል የጣቢያው ሠራተኞች የድሬዳዋ ደም ባንክ በመከለከያ ሠራዊት ሆስፒታል ባዘጋጀው የደም ልገሳ በመገኘት 20 ዩኒት ደም ለግሰዋል።
ሠራተኞቹ ከመስከረም እስከ ጷጉሜ 2013 ዓ/ም ድረስ በየ 3 ወሩ ሳያቋርጡ ደም መለገሳቸውንም ኃላፊው ገልፀዋል።
ሠራተኞቹ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ከመደበኛ ሥራቸው በተጓዳኝ ጉዳት ለደረሰባቸው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ያላቸውን ክብር በተግባር ያሳዩበት መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡
የዲዚል ማመንጫ ሠራተኞቹ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመርዳት በተቋሙ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል 30 ሺ ብር አሰባስበው ለዚሁ ሲባል በተከፈተው የባንክ አካውንት ማስገባታቸውን አቶ ጌትንት ተናግረዋል፡፡
የጀመሩትንም ድጋፍ በድሬደዋ ለሚገኙ ጉዳት ለደረሰባቸው የሠራዊቱ አባላት እስከ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ለመቀጠል መወሰናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
ጣቢያው በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች የንጽህና መጠበቂያ ቁሶችእና አልባሳት በማሰባሰብ ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 04 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ሠራተኞች ደም ለገሱ
…..…///……
የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አመራሮችና ሠራተኞች 44 ዩኒት ደም ለግሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የአልባሳት፣ የደረቅ ምግቦችና የገንዘብ ማሰባሰብ የበጎ አድራጎት ሥራ እያከናወኑ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነው የደም ልገሳም በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና በትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሪጅን ቢሮዎች እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በጊቤ 3 ባለፈው አርብ የተካሄደው የደም ልገሳ መርሃግብር የዚሁ አካል ሲሆን ከዚህ ቀደም የአዳማ አንድ ንፋስና የደቡብ ሪጅን ሠራተኞች ደም መለገሳቸውን መግለፃችን ይታወሳል፡፡
ዛሬ የድሬዳዋ የዲዝም መጠባበቂያ ጣቢያ አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም የፊታችን አርብ የዋና መሥሪያቤት አመራርና ሠራተኞች ደም ለመለገስ ቀጠሮ ይዘዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 04 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
በወረኢሉ መስመር አቀስታ ከተማ በኮምቦልቻ መስመር ደግሞ ባቲ ከተሞች ዛሬ መብራት አግኝተዋል
......////......
ከደሴ ለጋምቦ ወረ ኢሉ የሚሄደው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ እስከ አቀስታ ድረስ ኃይል ማገናኘት ተችሏል።
የተቋረጡ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ከማከፋፈያ ጣቢያዎች ጋር ለማገናኘት በተከናወነው ሥራ ዛሬ ባቲ፣ አቀስታ፣ መሐል ሳይንትና ሳይንት አጅባር ከተሞች ኤሌክትሪክ ኃይል አግኝተዋል።
በስራ ኃላፊዎችና በባለሙያዎች ርብርብና መናበብ መብራት የተቋረጠባቸውን አካባቢዎች ብርሃን እንዲያገኙ ለማድረግ ያለእረፍት ረጅም ሰዓት እየተሰራ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 02 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
# News Update
ወደ ደሴ ከተማ የሚገባው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርን ከደሴ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር አሁን ማገናኘት ተችሏል።
15 537
ኮምቦልቻ ከተማ ኤሌክትሪክ አግኝታለች፣ ደሴም ኤሌክትሪክ እንድታገኝ በምሽት ርብርቡ ቀጥሏል
…….///……
የጥገና ባለሙያዎቻችን የገቡትን ቃል በተግባር ለውጠዋል፡፡
ቃል በገቡት መሰረት ከከሚሴ ኮምቦልቻና ደሴ የሚሄደውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጠግነው አጠናቀዋል።
የመስመር ጥገናው መጠናቀቅን ተከትሎ የፍተሻና የሙከራ ሥራ የተሰራ ሲሆን ኮምቦልቻ ከተማ ኤሌክትሪክ አግኝታለች። ደሴ ከተማም ኤሌክትሪክ እንድታገኝ ከመሸም ርብርቡ ቀጥላል።
በአሸባሪው ቡድን የተጎዱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለመጠገን ርብርብ ላደረጉ ባለሙያዎች የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 01 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
ኮምቦልቻና ደሴ ኤሌክትሪክ ዛሬ ማግኘት እንዲችሉ በርብርብ እንሰራለን - የኢ.ኤ.ኃ. የጥገና ባለሙያዎች
……..////……..
በሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ መስመር የተጎዳውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት የሚጠግነው የጥገና ቡድን አባላት የኮምቦልቻና ደሴ ከተሞች ዛሬ ኤሌክትሪክ ማግኘት እንዲችሉ በርብርብ እንሰራለን አሉ፡፡
የጥገና ቡድኑ ትናንት ምሽት የጥገና ሂደቱን፣ በየከተሞቹ የደረሰውን ጉዳትና የህብረተሰቡን ስሜት የተመለከተ አጠቃላይ ግምገማ ካደረገ በኋላ ዛሬ የኮምቦልቻና ደሴ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ የቻለውን ያህል ጥረት እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል፡፡
የጥገና ቡድኑ ትናንት ከካራቆሬ - ከሜሴ ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ አድርጓል።
የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ የቴክኒክ ቡድኑ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከሸዋሮቢት እስከ ከሚሴ ያለውን መስመር ጠግኖ ለአገልግሎት ለማብቃት ያደረገውን ጥረት አድንቀዋል፡፡
ከባድ መስዋዕትነት በመክፈል የህዝቡን ችግር ለመፍታት ያደረጋችሁትን ርብርብ ተቋማችንና ህብረተሰቡ ሁሌም ሲያስታውሰው ይኖራል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 1 ቀን 2014 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
