EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 545 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 545 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 545
订阅者
+824 小时
-227 天
+2730 天
帖子存档
15 546
በተቋሙ በሙከራ ደረጃ የተተገበረው የካይዘን ፍልስፍና አበረታች ለውጥ አምጥቷል
………////……..
በኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት በሙከራ ደረጃ በተተገበረው የካይዘን ፍልስፍና አበረታች ለውጥ መምጣቱን የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ስራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ እንደገለፁት ስለተቋሙን ነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳ በማድረግ በሦስት ዙር ከ40 በላይ ባለሙያዎች የቴክኒካል ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ በተመረጡ አካባቢዎች ካይዘን በሙከራ ደረጃ ተተግብሯል፡፡
ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ የንብረት ማከማቻ መጋዘን በኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት አማካሪዎችና በተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ ባለሙያዎች ድጋፍ የካይዘን አሰራር መጀመሩን ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ በመጋዘኖቹ ኃላፊና ባለሙያዎች ርብርብ ትግበራውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማስፋት አመርቂ ውጤት መምጣቱን ገልፀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በተቋሙ ካሉት ሰባት የንብረት ማከማቻ መጋዘኖች መካከል ካይዘን ተግባራዊ በሆነባቸው በአምስቱ ውስጥ በተደረገ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣራት ብቻ የሥራ አካባቢ ሁኔታ ከነበረበት 26 ነጥብ 3 በመቶ ወደ 35 ነጥብ 5 በመቶ ተሻሽሏል፡፡
በመጋዘኖች ተከማችተው ከነበሩ ንብረቶች መካከል ሊወገዱ የሚችሉ ከ70 ሺህ በላይ ቁሳቁሶችን በመለየት ሌሎች ንብረቶችን ለመያዝና ለእንቅስቃሴ የሚያግዝ ነፃ ቦታ ማግኘት መቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ይሁንና ቀጣይ ትግበራዎች በቋሚ መጋዘኖች ላይ መከናወን የሚገባቸው በመሆኑና አዲስ የሚገነቡት ማከማቻ ህንፃዎች ባለመጠናቀቃቸው ለጊዜው ትግበራው በኮተቤ መጋዘን ብቻ መገደቡን ተናግረዋል፡፡
በጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ ካይዘንን ለመተግበር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁንና የተገኙ ውጤቶችን መሰረት በማድረግ በቀጣይ በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለመተግበር መታቀዱን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 05 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 4 ሺህ 100 ጊጋ ዋት ሰዓት የሚጠጋ ኃይል ማመንጨት ተችሏል
………/////………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት 4 ሺህ 98 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
በጽ/ቤቱ የዕቅድ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 4 ሺህ 622 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ 4 ሺህ 98 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት የዕቅዱ 88 ነጥብ 7 በመቶ ተሳክቷል፡፡
በሩብ ዓመቱ ማመንጨት ከተቻለው ውስጥ 3 ሺህ 989 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት ከውሃ እንዲሁም 108 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከንፋስ የተገኘ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
በሩብ ዓመቱ ማመንጨት የተቻለው ከዕቅዱ አንጻር ሲታይ ቅናሽ የታየበት ቢሆንም ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነፃፀር ግን የ5 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ያለው መሆኑን ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገልፀዋል፡፡
ማመንጫ ጣቢያዎች በሩብ ዓመቱ የታቀደውን ኃይል ለማመንጨት ዝግጁ የነበሩ ቢሆንም በኃይል ተጠቃሚ ማነስ እና በሀገሪቱ በነበረው ግጭት ምክንያት የታቀደውን ኃይል ሙሉ በሙሉ ማምረት አለመቻሉ ለዕቅዱ አለመሳካት በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡
እንደ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገለጻ ገናሌ ዳዋ፣ አዳማ 2፣ ቆቃ እና ጢስ አባይ 2 ማመንጫ ጣቢያዎች ከታቀደላቸዉ በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የቻሉ ሲሆን የመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ የዕቅዱን 45 ነጥብ 9 በመቶ ብቻ ነው ማሳካት የቻለው፡፡
በአራቱ ማመንጫ ጣቢያዎች በክረምት ወቅት የነበረው የግድቡ ውሃ ጥቅም ላይ እንዲውል በመደረጉ ከዕቅድ በላይ ለማምረታቸው በምክንያትነት የተጠቀሰ ሲሆን በአንፃሩ በመልካ ዋከና ጣቢያ በክረምት ወቅት በግድቡ ውሃ ለመያዝ ሲባል የኃይል ጭነት በመቀነሱ አፈፃፀሙ መቀነሱን ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ ጥሩወርቅ እንዳሉት አዋሽ 3፣ አዳማ 1፣ አመርቲ ነሼ፣ ፊንጫ፣ ግልገል ጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች የዕቅዳቸውን ከ91 በመቶ በላይ ማሳካት የቻሉ ጣቢያዎች ናቸው፡፡
ማመንጫ ጣቢያዎቹ በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመንጩ ለማድረግ በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የፍተሻ እና የቅድመ መከላከል የጥገና ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሲከናወኑ እንደነበር ሥራ አስኪያጇ ገልፀዋል፡፡
በሩብ ዓመቱ ውስጥ በገናሌ ዳዋ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አንድ ዩኒት ላይ አጋጥሞ የነበረን "የMIV Hydrolic Piston" መሰበር ችግር በመጠገን ዩኒቱን ወደ ኦፕሬሽን መመለሱን አስታውቀዋል፡፡
በ2015 በጀት ዓመት ከተለያዩ የኃይል ምንጮች 18 ሺህ 994 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ እየተሰራ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 02 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ጥገናው ላይ ጥምር ጦሩና የአካባቢው ወጣቶች እየተሳተፉ ነው
.......///......
በሁመራ በኩል ከተከዜ እስከ ሽሬ እየተካሔደ ባለው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ላይ ጥምር ጦሩ እና የአካባቢው ወጣቶች እየተሳተፉ መሆኑን በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ የፀጥታ አካላት አስታወቁ።
የፀጥታ አካሉን በመወከል ኮንስታብል ምህረት ወርቅነህ እንደገለፁት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራው ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ጥምር ጦሩ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገና ሠራተኞቹ ጎን ሆኖ እየሰራ ነው።
የተቋሙ የማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሠራተኞች ለሀገር ልማት ዘብ የቆሙ ወታደሮች ናቸው ሲሉ የገለፁት ኮንስታብል ምህረት ከሁለት ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ብርሃን እንዲያጣ የተደረገውን ህብረተሰብ ለመታደግ እያደረጉት ያለው ርብርብ የሚያኮራ ነው ብለዋል።
የፀጥታ ኃይሉ የጥገና ሠራተኛው ደህንነቱ ተጠብቆ ሥራውን እንዲያከናውን ከማድረግ ባለፈ አስፈላጊ ሆኖ በተገኘው ሁሉ ለማገዝ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ጥምር ጦሩ የኤሌክትሪክ መስመሮች በሚያልፍባቸው አካባቢዎች ቀድሞ እየደረሰ የአካባቢውን ደህንነት የማረጋገጥ ሥራ እየሰራና ለጥገና ሥራው ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ ይገኛል ሲሉም ተናግረዋል።
ከአዲ-ጎሹ እስከ ሽሬ ያለው የፀጥታ ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን የጠቆሙት ኮንስታብል ምህረት ለጥገና ሠራተኞቹ በሚደረገው የተደራጀ ጥበቃ ጥገናው በአጭር ጊዜ እንደሚጠናቀቅ እምነቱ እንዳላቸው ገልጸዋል።
እንደ ኮንስታብል ምህረት ገለፃ የጥገና ሥራው እየተከናወነ ያለበት አካባቢ በጣም ሞቃትና ተራራማ ቢሆንም ሠራተኞቹ እያሳዩት ያለው ተጋድሎ ግን ታሪክ የማይረሳው ነው።
የሀገር ሰላምና ልማት በዘላቂነት የሚረጋገጠው ሁሉም በየመስኩ በአንድነት መረባረብ ሲችል ነው ያሉት ኮንስታብል ምህረት ከአዲ-ጎሹ እስከ ሽሬ የኤሌክትሪክ መስመር እየጠገኑ ያሉ ሠራተኞች ለዚህ ትልቅ ምሳሌ መሆን ይችላሉ ብለዋል።
ከአዲ-ጎሹ እስከ ሽሬ እየተካሔደ ባለው የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ ላይ ከፀጥታ አካላት በተጨማሪ የአካባቢው ወጣቶች እገዛ በማድረግ ላይ ናቸው።
ከሁመራ እስከ ተከዜ ያለው የጥገና ሥራ ተጠናቆ ከተከዜ እስከ ሽሬ ያለው መስመር በመጠገን ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 01 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ ዕሴቶች፣ ተግባርና ኃላፊነት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተሻሻው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 381/2008 መሰረት የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ሲሆን የተቋቋመባቸው ዓላማዎች የሚከተሉት ናቸው፡-
1. ከብሔራዊ ግሪድ ጋር የተያያዙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች፣ ከ66 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ሥራዎች የአዋጭነት ጥናት፣ የንድፍ እና የቅየሳ ሥራዎች ማከናወን፣ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በአማካሪ ማሠራት፤
2. ከብሔራዊ ግሪድ ጋር የተያያዙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች፣ ከ66 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታና የማሻሻያ ሥራዎችን ማከናወን፤ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በሥራ ተቋራጭ ማሠራት፤
3. ከብሔራዊ ግሪድ ጋር የተያያዙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጪያ ጣቢያዎችን፣ ከ66 ኪሎ ቮልት ኃይል በላይ የመሸከም አቅም ያላቸውን የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ማስተዳደር፣ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን ማከናወን፤
4. ከ66 ኪሎ ቮልት ደረጃ በላይ በሆኑ መስመሮች የኤሌክትሪክ ኃይልን በጅምላ መሸጥ እና መግዛት፤
5. ከ66 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ሊዝ ማድረግ፤
6. የሚሸጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል በተመለከተ የታሪፍ ማሻሻያ ሀሳብ ማቅረብ፣ ሲፈቀድም ተግባራዊ ማድረግ፤
7. የገንዘብ ሚኒስቴር የሚያወጣውን መመሪያና የፖሊሲ አቅጣጫ መሠረት በማድረግ ቦንድ መሸጥና በዋስትና ማስያዝ እና ከአገር ውስጥ፣ ከውጭ የገንዘብ ምንጮች ጋር የብድር ውል መደራደርና መፈራረም፤
8. ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ የሆኑ ሥራዎችን ማካሄድ፤
ራዕይ
ለሀገር ዕድገት አለኝታ የሆነና ለአህጉራዊ ትስስር መሠረት የሚጥል ዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋም ሆኖ ማየት፤
ተልዕኮ
ታዳሽ ኃይል ላይ ትኩረት በማድረግ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ መሠረተ ልማቶችን የአዋጭነት፣ የቅየሣ ዲዛይን፣ የመገንባት የማሻሻል የማስተዳደር ተግባራትን ማከናወን፣ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጅምላ በመሸጥና በመግዛት ለአገር ብልፅግናና ለአህጉራዊ ትስስር መሠረት የሚሆን አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ፤
እሴቶች
• ቀጣይነት ያለዉ ልህቀት
• የአገልግሎት አስተማማኝነትና ጥራት
• ፕሮፌሽናሊዝም
• ተጠያቂነት
• ማህበራዊ ኃላፊነት
• የሙያ ደህንነትና ጤንነት
• መደመር
ተቋማችንን የማይመለከቱ ተግባራት
• ከላይ በዝርዝር ከተገለፁት የመ/ቤቱ ዓላማዎች ውጭ ያሉ ተግባራት ማለትም፦
• ለደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት የመስጠት፤
• የኤሌክትሪክ ጥገና አገልግሎት ተግባራትን የማከናወን፤
• ደንበኞች የተገለገሉበትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ ስሌት የማንበብ፤
• ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሒሳብን የማስከፈል፤
• የኤሌክትሪክ ሥርጭት እና ተያያዥነት ያላቸው ተግባራትን የማከናወን መብቶችና
• ግዴታዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተግባርና ኃላፊነቶች መሆናቸውንም ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 01 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በማማከር አገልግሎት 50 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ ወጪ ማዳን ተችሏል
………//////……….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ የማማከር አገልግሎቶችን በተቋሙ የራስ አቅም በመስራት 50 ሚሊዮን የሚደርስ የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት ተቋሙ በርካታ የግንባታ ፕሮጀክቶችን በማማከር እየተሳተፈ ቢሆንም ከ2012 እስከ 2014 ባሉት ሶስት ዓመታት ብቻ በዘጠኝ ፕሮጀክቶች የማማከር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
ከእነዚህም መካከል የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት፣ የቡሬ ደብረማርቆስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር እና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት፣ የቡታጅራ ወራቤ የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት፣ የባህርዳር ወልዲያ ኮምቦልቻ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክትን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
ተቋሙ የተሳተፈበት የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራው በውጪ አማካሪ ድርጅት ቢሰራ ኖሮ ተቋሙን ከአስር ሚሊዮን ዩሮ በላይ እና ወደ 23 ሚሊዮን ብር ያስወጣ እንደነበር ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡
ይሁንና ሥራው በራስ አቅም በ48 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በመከናወኑ ተቋሙ ሊያወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሪ ማዳን እንደተቻለ አስረድተዋል፡፡
በአዳማ ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ በተመሳሳይ በውጪ አማካሪ ቢሰራ ኖሮ 7 መቶ ሺህ የአሜሪካ ዶላር እና 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ያስወጣ እንደነበር የገለፁት ሥራ አስፈፃሚው የማማከር ሥራው በራስ አቅም በ6 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በመሰራቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማዳን መቻሉን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ከ 652 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላር እና 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የቡታጅራ - ወራቤ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክትን የማማከር አገልግሎት በአምስት ሚሊየን ብር በራስ አቅም በመሰራቱ የተቋሙን ወጪ መቀነስ እንዳስቻለም አስረድተዋል፡፡
ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት ከ2012 እስከ 2014 ባሉት ሶስት ዓመታት ብቻ በራስ ኃይል የማማከር አገልግሎት በመስጠት ተቋሙ 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የውጪ ምንዛሪ ማዳን ችሏል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መልሶ በመጠገን የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የተቋሙ ሠራተኞች ገለፁ
……....///…….....
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በመጠገን የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ የጥገና ሠራተኞች ገለፁ።
የባህርዳር- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ጥገና ላይ የተሳተፉት የደቡብ ምዕራብ ሪጅን የጥገና ሠራተኛ አቶ ከሊፋ ረዲል እንደተናገሩት ለበርካታ ወራት በጨለማ ውስጥ ለቆየው ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ ማድረግ የሚፈጥረው ስሜት ልዩ ነው፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ በአጭር ጊዜ የጥገና ሥራቸውን አጠናቆ ለማገናኘት የነበረው ርብርብ የሚደነቅ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከማዕከላዊ ሪጅን የመጡት ባለሙያ አቶ ሞገስ በላይ በበኩላቸው ከኮምቦልቻ - አላማጣ አንድ ወር ይፈጃል የተባለውን የጥገና ሥራ በ7 ቀን ማጠናቀቅ መቻላችን ያለንን የሥራ ላይ መናበብና ቅንጅት ያሳየ ነው ብለዋል።
ከአንዳንድ የሴፍቲ ዕቃዎችና ጫማዎች እጥረት በስተቀር አጠቃላይ የጥገና ሥራው በጥሩ ደረጃ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ሞገስ በአሁኑ ሰዓት ተቋሙ በማህበረሰቡ ውስጥ ያለው ተቀባይነት እየጨመረ በመምጣቱ መደሰታቸውን ገልፀዋል።
ከሰሜን ምስራቅ ሪጅን የመጡት አቶ ያረጋል ታዬ እንደተናገሩት ጥገናው እየተከናወነ የሚገኝባቸው ቦታዎች ገደላማ እና ጫካ የሚበዛባቸው በመሆናቸው ሥራውን ፈታኝአድርጎታል፡፡
ከተለያዩ ሪጅኖች ከተውጣጡ ሠራተኞች ጋር በጋራ በመስራታቸው የሙያና ልምድ ልውውጥ ለማድረግ እንዳገዛቸው የተናገሩት አቶ ያረጋል ሁሉም ሪጅኖች ለሥራው የሚያስፈልጉ መለዋወጫና ግብዓቶችን ይዘው በመምጣታቸው ጥገናው እንዳይስተጓጎል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጉን ጠቁመዋል።
ተቋሙ የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የጠቆሙት ባለሙያዎቹ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በከፍተኛ ወጪ የሚገነቡ በመሆናቸው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል እንደ ዓይኑ ብሌን ሊጠብቃቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በኢትዮ- ኬንያ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ በስኬት ተከናወነ
………/////………..
በኢትዮ- ኬንያ የኮንቨርተር ስቴሽንና የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ በዛሬው ዕለት በስኬት መጀመሩን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው እንገደለፁት በኢትዮ ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ በይፋ ተጀምሯል፡፡
በፕሮጀክቱ ላይ የተተከሉ የተለያዩ የኤሌክትሮ ሜካኒካል መሳሪያዎችንና ዕቃዎችን እንዲሁም የኮሙዩኒኬሽን ዳታ ሲግናሉን በተለያየ ጊዜ የመፈተሸ እና የመሞከር ሥራ ሲሰራ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ቴዎድሮስ በዛሬው ዕለት ደግሞ ኃይል በማስተላለፍ (energize በማድረግ) ከኬንያ ጋር ያለውን ግንኙነት ያለምንም ችግር መሞከር ተችሏል ብለዋል፡፡
የሙከራ ሥራው መሳካቱ በቅርቡ ከኬንያ ጋር የሚጀመረው የኃይል ትስስር ሥራ በአስተማማኝ ሁኔታ እንደሚከናወን አመላካች መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ከቀናት በፊት የኮሙዩኒኬሽን ሲግናል በመላክ ሲግናሉን ከኬኒያ ኔትወርክ ጋር ማገናኘት መቻሉን አቶ ቴዎድሮስ ጠቁመዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ኃይል ማስተላለፍ ሲጀምር በህብረተሰቡ ላይ አደጋ እንዳያደርስ መስመሩ ከሚያልፋባቸው ዞኖች በየደረጃው ከሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ከወረዳና ከቀበሌ ተወካዮች ጋር የውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች መካሄዳቸውን አስታውሰዋል፡፡
በተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ምክንያት የሙከራ ሥራ እየተከናወነ ባለበት ወቅት ምንም አደጋ አለማድረሱንም አቶ ቴዎድሮስ አረጋግጠዋል፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ስቴሽን ፕሮጀክት በ334 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተገነባ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 214 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላሩ ለኮንቨርተር ስቴሽኑና ለግራውንድ ኤሌክትሮድ መስመር የግንባታ ሥራ እንዲሁም 120 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ ለማስተላለፊያ መስመሩ የዋለ ነው፡፡
የግንባታ ሥራው በ2008 የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት እስከ 2000 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፍ አቅም እንዳለው በፕሮጀክቱ ሲነየር ፕሮጀክት ኢንጂነር ኃይለማርያም ሞገስ ገልፀዋል፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ የግንባታ ሥራ እንደ አዉሮፓዉያኖች አቆጣጠር በ2018 እንዲሁም የኮንቨርተር ስቴሽኑ በታህሳስ 2021 እኤ.አ መጠናቀቁን ኃይለማሪያም ጠቁመዋል፡፡
ይሁን እንጅ የፕሮጀክቱ አካል የሆነውና በኬኒያ በኩል ሲገነባ የነበረው በወቅቱ መጠናቀቅ ባለመቻሉ ኢነርጃይዝ ሳይደረግ ቆይቷል፡፡
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ "CET" በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን የኮንቨርተር ስቴሽኑና የግራውንድ ኤሌክትሮድ መስመሩ ደግሞ ሲመንስ በተሰኘ ኩባንያ ተከናውኗል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል በተገነባው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ላይ 994 የመስመር ተሸካሚ ታወሮች የተተከሉ ሲሆን 440 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የዳታ ሲግናል ማስተላለፊያ ኬብሎችም ተዘርግተውለታል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በኢትዮ- ኬኒያ ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀሙ ስርቆቶች ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ ዳርገውታል
......../////.......
በኢትዮ - ኬኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ላይ የተፈፀሙ ስርቆቶች ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ እንደዳረገው የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው እንደገለጹት በፕሮጀክቱ የማስተላለፊያ መስመር ሽቦዎች፣ የመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች፣ የዳታ ሲግናል ማስተላለፊያ ኦፕቲካል ፋይበር (OPGW) ኬብሎች እና የዳታ ገመዶችን የማገናኛ ሳጥኖች (joint boxes) ስርቆት ተፈጽምባቸዋል።
የተሰበሩትን ኢንሱሌተሮች ጨምሮ ስርቆት የተፈጸመባቸውን ዕቃዎች ለመተካትና ለመጠገን ተቋሙ ተጨማሪ 16 ሚሊዮን በላይ የቻይና ዩዋን እና 20 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉንም ገልፀዋል።
የስርቆት ወንጀሉ በደቡብ ክልል ወላይታና ጋሞ ዞኖች ላይ በስፋት እንደሚስተዋል ያነሱት አቶ ቴዎድሮስ በሁለቱ ዞኖች ብቻ 105 ቶን የሚሆን የተለያየ ብረት፣ 6 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ሽቦዎች፣ 12 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር የዳታ ሲግናል ማስተላለፊያ ኬብል እንዲሁም 13 የኦፕቲካል ፋይበር ማገናኛ ሳጥኖች መሰረቃቸውን ተናግረዋል።
ከጋሞና ከወላይታ ዞኖች በተጨማሪ መስመሩ በሚያልፍበት የኮንሶ ዞን 0 ነጥብ 21 ቶን ብረት እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን 24 የዳታ ሲግናል ማስተላለፊያ ኬብል ማገናኛ ሳጥኖች ስርቆት ተፈጽሞባቸው እንደነበር አስታውሰዋል።
ከዚህ በፊት በመስመሩ ሽቦዎች እና በመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ ይፈጸፀም የነበረው ስርቆት በአሁኑ ወቅት መቀነሱን የጠቆሙት የሳይት ሥራ አስኪያጁ በዳታ ሲግናል ማስተላለፊያ ማገናኛ ሳጥኖች ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆት እና በኢንሱሌተሮች ላይ እየደረሰ ያለው ውድመት አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ሁሉም በኃላፊነት ስሜት ጥበቃ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።
በኢትዮጵያ በኩል በተገነባው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ላይ 994 የመስመር ተሸካሚ ታወሮች የተተከሉ ሲሆን 440 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የዳታ ሲግናል ማስተላለፊያ ኬብል ተዘርግቶለታል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
አንጋፋው አርቲስት አሊ መሐመድ ቢራ
ከ1940 ዓ.ም -2015 ዓ.ም
ከ 50 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ አሻራውን ያሳረፈው አርቲስት አሊ ቢራ የአፋን ኦሮሞ ሙዚቃዎቹ በሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች ጭምር ተወዳጅ ነበሩ፡፡
የአርቲስቱ አስከሬን በወዳጅነት አደባባይ የክብር ስንብት ከተደረገለት በኋላ በድሬዳዋ በክብር እንደሚያርፍ ይጠበቃል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በክብር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለአድናቂዎቹና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል::
15 546
ክለቡ የተመሠረተበትን 60ኛ ዓመት ለመዘከር መዘጋጀቱን አስታወቀ
.........../////..........
አንጋፋው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የተመሠረተበትን 60ኛ ዓመት አስመልክቶ በተለያዩ ስፖርታዊ ሁነቶች እንደሚያከበር የክለቡ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ መንግሥቱ ገለፁ።
ክለቡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ የሚያስተዳድሩት መሆኑን የገለፁት አቶ አለማየሁ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የለውጥ ስራዎች መከናወናቸውንና በዚህም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።
እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ ከዛሬ ጥቅምት 27 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች መካከል የእግር ኳስ፣ የገመድ ጉተታ እና በሌሎች ስፖርታዊ ዘርፎች ውድድር ይካሄዳል።
60ኛ ዓመቱን ከመዘከር ባሻገር ይህ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲዳብር እና ጤናማ የሰው ኃይል ለማፍራት ያለመ መሆኑን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
የክለቡን የፋይናንስ አቅም ለማጎልበት እንዲረዳው የደጋፊ ማህበር እንደአዲስ በመቋቋም ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ አለማየሁ በአሁኑ ጊዜ በህጋዊነት የተመዘገቡ ከ1 ሽህ 4 መቶ በላይ ደጋፊዎች እንዳሉት አስታውቀዋል።
የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች የሚሳተፉበት የስፖርታዊ ውድድር ዛሬ ጥቅምት 27 ቀን2015 ዓ.ም የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች ከዋናው መስሪያ ቤት ሠራተኞች በአበበ ቢቄላ ስታዲየም ከረፋዱ 5 ሰዓት በሚያደርጉት የእግር ኳስ ጨዋታ ተጀምሯል።
በመጨረሻም በአሠልጣኝነት፣ በተጫዋችነት፣ በአመራርነት እና በተለያዩ ዘርፎች ክለቡን ያገለገሉ የስፖርት ቤተሰቦች ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም በሚከናወነው የመዝጊያ ሥነስርዓት ላይ እንዲገኙ አቶ አለማየሁ ጥሪ አቅርበዋል።
በእግር ኳስ፣ በአትሌቲክስ፣ በብስክሌት እና በጠረጴዛ ቴኒስ የስፖርት ዘርፎች በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ለሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ስመጥር ስፖርተኞችን አፍርቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 27 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
