ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 368,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 174

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.87% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 862 次浏览,首日通常累积 2 620 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 537
订阅者
-624 小时
-207
+1030
帖子存档
photo content
+9

ተቋሙ ከሩብ ቢሊየን ብር በሚበልጥ በጀት ከ1 መቶ 40 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ አደረገ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኦሞ ዞን በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለተከሰተው የምግብ እጥረት ከሩብ ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ አደረገ። በዞኑ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የተከሰተውን የምግብ እጥረት በጊዜያዊነት ይቀርፋል የተባለ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ተካሒዷል። በሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ክልል አርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ እና የርዕሰ መስተዳድሩ ተወካይ አቶ ሎሬ ካኩታ እንደገለፁት በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የአየር ንብረት ለውጥ በዜጎች ላይ የምግብ እጥረት አስከትሏል። ችግሩ በተከሰተባቸው የአርብቶ አደር አካባቢዎች በእንስሳት መኖ አቅርቦት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩንም ነው የተናገሩት። እንደ አቶ ሎሬ ገለፃ የኦሞን ወንዝ መነሻ በማድረግ የመስኖ ልማት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በምግብ እጥረት ለተጎዱ የደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ማድረጉ ምስጋና የሚቸረው ነው ያሉት ኃላፊው የሥርጭት ሥራውን በፍትሐዊነት ተደራሽ ለማድረግ የክልሉ ሁሉም አመራሮች በቅንጅት መሥራት እንደሚጠቅባቸው አሳስበዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ በበኩላቸው በዞኑ ቆላማ ወረዳዎች ለተከታታይ 3 ዓመታት የዝናብ እጥረት ማጋጠሙን ተናግረዋል። በዞኖቹ የተከሰተው የዝናብ እጥረት ያስከተለውን የምግብ  እጥረት ለመቅረፍ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። ከመስኖ ሥራ እና ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን በመቅረፍ ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸት የዞኑ ቀጣይ አቅጣጫዎች መሆናቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ተቋሙ በደቡብ ኦሞ ዞን በሐመር፣ ዳሰነች፣ ኛንጋቶም እና ሰላማጎ ወረዳዎች የተከሰተውን የምግብ እጥረት ለመከላከል ከሩብ ቢሊዮን ብር በላይ በመመደብ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ አገልግሎት ሥራዎች ማስጀመሩን ተናግረዋል። ተቋሙ ከተቋቋመበት ተልዕኮ ባሻገር በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። እንደ አቶ አሸብር ገለፃ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ በዘርፉ ለበርካታ ዓመታት ከሰራው ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በትብብር ይከናወናል። የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ በዞኑ በሚገኙ  ከ1 መቶ 40 ሺህ በላይ የሐመር፣ ዳሰነች፣ ኛንጋቶም እና ሳላማጎ ወረዳ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰብዓዊ ድጋፉን በአግባቡ ማሰራጨት እንዲችል የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ አስተዳደሮች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የቦርድ ፕሬዝደንት አቶ አበራ ቶላ በበኩላቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት በአብዛኛው የሀገሪቱ ቆላማ አካባቢዎች ላይ በተከሰተ የአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውን ተናግረዋል። ማህበሩ በየጊዜው በድርቅ የሚጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት በማቋቋም አምራች ዜጋ የሚፈጠርበትን አቅም ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ምስጋናቸውን የገለፁት አቶ አበራ በቀጣይም በርካታ ሥራዎችን በጋራ ለመስራት ማህበራቸው ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው የወረዳዎቹ አመራሮች፣ የማህበረሰብ ተወካዮች እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አመራሮችና በጎ ፍቃደኞች ተሳትፈዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+5

ተቋሙ በደቡብ ኦሞ ዞን ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ለማድረግ ቱርሚ ከተማ ገባ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኦሞ ዞን በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለተከሰተው የምግብ እጥረት ከሩብ ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሊያደርግ ነው። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ቶላ የተመራ የልዑካን ቡድን ጂንካ አየር ማረፊያ እና ቱርሚ ከተማ ሲደርስ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳን ጨምሮ በዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ተቋሙ በዞኑ የሚያካሒደው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ  ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ዓላማ ያደረገ መሆኑም ተጠቅሷል። የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ የሚደረገው በዞኑ ውስጥ በሚገኙት በሐመር፣ ዳሰነች፣ ኛንጋቶም እንዲሁም ሳላማጎ ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ወገኖች እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። በነገው ዕለትም ተቋሙ በሚያደርገው ሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ እና በስርጭቱ ዙሪያ ከደቡብ ኦሞ ዞን አስተዳደር እና ከአራቱ ወረዳዎች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 21 ቀን 2015 ዓ.ም.

✍️ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444 ኛው የኢድ አል አድሃ / አረፋ / በዓል በሠላም አደረሳችሁ ❤‼️
✍️ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444 ኛው የኢድ አል አድሃ / አረፋ / በዓል በሠላም አደረሳችሁ ❤‼️

photo content

photo content
+2

በማመንጫ ጣቢያዎቹ ላይ የመልሶ ጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ ጥናቶች ተጀምረዋል ……..///……. በአዋሽ 2ኛ እና 3ኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የመልሶ ጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ ጥናቶች መጀመራቸውን የጣቢያዎቹ የጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሮቤል አበበ እንዳስታወቁት ማመንጫ ጣቢያዎቹ ከተገነቡ ረጅም ጊዜ በማስቆጠራቸው፣ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት የውጪ ግዥ የሚፈልግ በመሆኑና ሲስተሞቹ ዘመኑን የዋጁ እንዲሆኑ ለማድረግ በጣቢያው ላይ የማሻሻያ ሥራ ማከናወን አስፈልጓል፡፡ የመልሶ ጥገና ሥራውን ለማከናወን በቻይና ኩባንያዎች እና በተቋሙ የኢንጂነሪንግ የሥራ ዘርፍ የተለያዩ ጥናቶች መከናወናቸውን የመልሶ ጥገና ሥራ የሚከናወንባቸው የጣቢያዎቹ አካባቢዎች እና አካላት በጥናት መለየታቸውንም አቶ ሮቤል አመልክተዋል፡፡ የጥናት ሥራው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት ኃላፊው የመልሶ ጥገና ሥራው ጥናቱን መሰረት በማድረግ ወደ ትግበራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡ ምንም እንኳን ማመንጫ ጣቢያዎቹ ከተገነቡ ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በሙሉ አቅም በሚያስብል ደረጃ የሚጠበቅባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጩ ይገኛሉ፡፡ በ2015 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ከአዋሽ 2ኛ ማመንጫ ጣቢያ በአንዱ ዩኒት ብቻ 85 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት ታቅዶ 82 ጊጋ ዋት በማመንጨት የዕቅዱን 96 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት የተቻለ ሲሆን ከአዋሽ 3ኛ ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ 120 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጫት ታቅዶ 118 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት የዕቅዱን 98 ነጥብ 97 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡ የአዋሽ 2ኛ ማመንጫ ጣቢያ በ1958 ዓ.ም እንዲሁም የአዋሽ 3ኛ ማመንጫ ጣቢያ በ1963 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን እያንዳንዳቸው 16 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሁለት ሁለት ዩኒቶች አላቸው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 19 ቀን 2015 ዓ.ም

በማመንጫ ጣቢያዎቹ ላይ የመልሶ ጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ ጥናቶች ተጀምረዋል ……..///……. በአዋሽ 2ኛ እና 3ኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የመልሶ ጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ ጥናቶች መጀመራቸውን የጣቢያዎቹ የጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሮቤል አበበ እንዳስታወቁት ማመንጫ ጣቢያዎቹ ከተገነቡ ረጅም ጊዜ በማስቆጠራቸው፣ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት የውጪ ግዥ የሚፈልግ በመሆኑና ሲስተሞቹ ዘመኑን የዋጁ እንዲሆኑ ለማድረግ በጣቢያው ላይ የማሻሻያ ሥራ ማከናወን አስፈልጓል፡፡ የመልሶ ጥገና ሥራውን ለማከናወን በቻይና ኩባንያዎች እና በተቋሙ የኢንጂነሪንግ የሥራ ዘርፍ የተለያዩ ጥናቶች መከናወናቸውን የመልሶ ጥገና ሥራ የሚከናወንባቸው የጣቢያዎቹ አካባቢዎች እና አካላት በጥናት መለየታቸውንም አቶ ሮቤል አመልክተዋል፡፡ የጥናት ሥራው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት ኃላፊው የመልሶ ጥገና ሥራው ጥናቱን መሰረት በማድረግ ወደ ትግበራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡ ምንም እንኳን ማመንጫ ጣቢያዎቹ ከተገነቡ ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በሙሉ አቅም በሚያስብል ደረጃ የሚጠበቅባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጩ ይገኛሉ፡፡ በ2015 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ከአዋሽ 2ኛ ማመንጫ ጣቢያ በአንዱ ዩኒት ብቻ 85 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት ታቅዶ 82 ጊጋ ዋት በማመንጨት የዕቅዱን 96 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት የተቻለ ሲሆን ከአዋሽ 3ኛ ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ 120 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጫት ታቅዶ 118 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት የዕቅዱን 98 ነጥብ 97 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡ የአዋሽ 2ኛ ማመንጫ ጣቢያ በ1958 ዓ.ም እንዲሁም የአዋሽ 3ኛ ማመንጫ ጣቢያ በ1963 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን እያንዳንዳቸው 16 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሁለት ሁለት ዩኒቶች አላቸው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 19 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የተቋሙ ሴት ሠራተኞች ሥራቸውን በኃላፊነት እንዲወጡና የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ተግተው እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ ....///.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቴክኒክ ዘርፎች ላይ የሚታየውን አነስተኛ የሴቶች ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችሉ በጎ ጅምሮች መኖራቸውን በተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው ከተለያዩ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለተውጣጡ ጀማሪ ሴት መሐንዲሶች ሥልጠና ሰጥቷል። የመምሪያው ዳይሬክተር ወይዘሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለፁት ሥልጠናው በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚገኙ ሴት ሠራተኞች በቂ ግንዛቤ በማግኘት በሥራ ላይ የሚያጋጥሟቸውን ጫናዎች መቋቋም የሚያስችላቸውን አቅም ለመፍጠር ያለመ ነው። ሥልጠናው ሠራተኞቹ የተቋሙን መተዳደሪያ ደንብ አውቀው መብትና ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለማስቻል እንደሚያግዝ ነው ዳይሬክተሯ የገለፁት። በሥልጠናው ማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደተናገሩት ሠራተኞቹ በትምህርት ያገኙትን ዕውቀት ተግባር ላይ በማዋል ተቋሙን ተጠቃሚ ማድረግ አለባቸው። ተቋሙ ለሴት ሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ በመፍጠር የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣም የተናገሩት ወ/ሮ ስመኝ ሠራተኞቹ ሙያቸውን በሚገባ ተጠቅመው ሥራቸውን በኃላፊነት እንዲወጡና የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ተግተው እንዲሰሩ አሳስበዋል። የሥልጠናው ተሳታፊዎችም ሥልጠናውን መውሰዳቸው በሥራቸው ላይ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content

ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በአግባቡ እየመለሰ እንደሚገኝ ሪጅኑ አስታወቀ ……….///……… በሰኮሩ የማከፋፈያ ጣቢያ ዙሪያ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች እየመለሰ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን እና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው ዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎች የውሃ፣የመብራትና የመንገድ አገልገሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሪጅኑ ጥረት እያደረገ ነው። በህብረተሰቡ ፍላጎት እንዲገነቡ የተለዩ የማህበራዊ አገልግሎት መስጫዎችን በፍጥነት ተደራሽ ለማድረግ የሶኮሩ ወረዳ አጥንቶ ባቀረበው ረቂቅ መሠረት ሪጅኑ ከ3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ በጅማ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ስምምነት መደረጉን አስታውቀዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በስምምነቱ መሰረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኃላፊነቱን ወስዶ ሥራውን እንዲያከናውን ገንዘቡ ገቢ ተደርጎለት ዝርጋታውን ቢያገባድድም በትራንስፎርመር እጥረት መዘግየቱን አቶ ጌታሁን ጠቁመዋል። በመሆኑም ሥራውን የሚያከናውነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጅማ ዲስትሪክት ችግሩን እንዲፈታና ሥራውን በፍጥነት አጠናቆ ለአካባቢው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲያደርግ ከዲስትሪክቱ ጋር በቅርበት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ሪጅኑ በመደበኛነት ከሚያከናው የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ በተጨማሪ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ቅሬታዎችና ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 16 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

በተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ አፈፃፀም ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶች እንዳይደገሙ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ........///....... በተቋሙ ስትራቴጂክ ዕቅድ አተገባበር ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች አሳሰቡ። ተቋሙ እያያዘጋጀው ባለው የሦስት ዓመታት ስትራቴጂክ ዕቅድ ቀረፃ ላይ ግብዓት ለመሰብሰብ የዘርፉ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ የተቋሙና የሥራ ዘርፉ ያለፉት ሦስት ዓመታት የስትራቴጂክ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የትኩረት አቅጣጫዎች ቀርበዋል። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደተናገሩት ውይይቱ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተቋሙና በሥራ ክፍሉ አፈፃፀም ላይ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች እንዲሁም መልካም አጋጣሚዎችንና ስጋቶችን በመገምገም ክፍተቶቹ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት እንዳይደገሙ ለማድረግ ያግዛል። ከዚህ በፊት የተቋሙ ስትራቴጂክ ዕቅድ ቀረፃ ላይ ሠራተኛውን በማሳተፍ በኩል ክፍተቶች እንደነበሩ አስታውሰው የአሁኑ ውይይት ግን ከሠራተኞች ግብዓት በመሰብሰብ በዕቅዱ ላይ ለማካተት እንደሚያግዝ አቶ ክብሮም ተናግረዋል። ተቋሙ በቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚተገብረው ዕቅድ ሁሉን አካታችና ግልፅነት ባለው መልኩ እንዲቀረፅ ለማድረግ የሠራተኞች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑንም ሥራ አስፈፃሚው አመለክተዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በበኩላቸው የዕቅድ ዝግጅቱ ሁሉን አካታች እንዲሆን መደረጉ ተቋሙን ውጤታማ እንደሚያደርገው ጠቅሰዋል። የውጭ ምንዛሪ እጥረት፣ በማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀም ስርቆት፣ የፀጥታና የወሰን ማስከበር ችግሮች እንዲሁም የግንባታ ግብዓቶች እጥረት በስትራቴጂክ ዕቅድ አፈፃፀሙ ላይ ተግዳሮት እንደነበሩም ተሳታፊዎቹ አንስተዋል፡፡ ግንባታቸው የተጠናቀቁ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በወቅቱ ወደ አገልግሎት ያለማስገባት፣ የሠራተኞች ቅሬታ የሚፈታበት አሰራር ግልፅ አለመሆን፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ግንኙነት የተጠናከረ አለመጠናከር እና በፕሮጀክት ኮንትራት አስተዳደር ላይ ክፍተቶች መስተዋላቸውን የውይይቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል። የቀጣዮቹን ሦስት ዓመታት የሚተገበረው ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የወሰን ማስከበር ችግሮችና የመሠረተ ልማት ሥርቆቶች መፍትሔ የሚያገኙበት፣ የስትራቴጂክ አስተሳሰብ ያለው አመራር የሚፈጠርበት፣ የሠራተኞች አቅም ግንባታ፣ በተቋሙ ውስጥ ተጨማሪ ሥራ ተቋራጮችን የሚፈሩበት፣ ለሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ የሚፈጠርበት፣ ተቋማዊ የሥራ ባህል የሚያድግበት፣ ለሥራ የሚያስፈልጉ መሣሪያዎች የሚሟሉበት ሁኔታ እና የገቢ ምንጮችን ማስፋት ላይ ትኩረት ያደረጉ ጉዳዮች በዕቅዱ ላይ እንዲካተቱ ተወያዮቹ ሰጥተዋል። ሥራ አስፈፃሚውም ከውይይቱ የተገኙ ግብዓቶችን በመውሰድ አካታች የሆነ ስትራቴጂክ ዕቅድ እንደሚዘጋጅ እና ከትግበራ በፊት  ዳግም ውይይት እንደሚደረግበትም ነው የጠቆሙት። በተቋሙ የሦስት ዓመታት የዕቅድ ዝግጅት ላይ ግብዓት ለመሰብሰብ የኮርፖሬት ፕላኒንግ እና የሠው ኃይል የሥራ ዘርፍ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ውይይት ያካሄዱ ሲሆን በቀጣይም ሌሎች የሥራ ዘርፎች ውይይት ያካሂዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+5

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚታየው የወሰን ማስከበር ችግር ተቋሙ ብድርና ድጋፍ እንዳያገኝ ያደርጋል ……..///……… በኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የሚስተዋለው የወሰን ማስከበር ችግር ተቋሙ ለፕሮጀክቶች ግንባታ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት የሚያገኘውን ብድርና ድጋፍ እንዳያገኝ እንደሚያደርገው የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለፁት ለፕሮጀክቱ ግንባታ ፋይናንስ ያደረጉ አካላት ፕሮጀክቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ ጥናት በማድረግ የማረጋገጫ ሠርተፊኬት ይሰጣሉ። በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ ላይ የሚስተዋለው የወሰን ማስከበር ችግር ከአካባቢያዊ ተፅዕኖ ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሠርተፊኬት ሊያሰጠው እንደማይችል እና በቀጣይ ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚሆን ብድርና ድጋፍ ለማግኘት እንቅፋት እንደሚሆንም ነው አቶ ክብሮም የተናገሩት። መስመሩ በሚያልፍባቸው ቦታዎች ላይ የሠፈሩ ነዋሪዎች በወቅቱ ካልተነሱ መስመሩ በህብረተሰቡ ላይ አደጋ ሊያደርስ እንደሚችል ሥራ አስፈፃሚው አመልክተዋል። በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የሚስተዋለው የወሰን ማስከበር ችግር ለኃይል ማስተላለፍ ሥራው እንቅፋት እንደሚሆን የጠቆሙት አቶ ክብሮም ሀገሪቱን ከተጨማሪ ወጪ ለመታደግ የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት ለችግሩ መፍትሔ እንዲሰጡም አሳስበዋል። የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው በበኩላቸው መስመሩ ከሚያልፍባቸው አራት ዞኖች መካከል በጋሞ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች የወሰን ማስከበር ችግሩ በስፋት እንደሚስተዋል ገልፀዋል። የተቋሙ ባለሙያዎች የፍተሻ እና የአስቸኳይ ጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ወደ ስፍራው ሲገቡ የወሰን ማስከበር ችግሩ በሚስተዋልባቸው አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ሠራተኞቹ እንዳይገቡ የመከልከልና የማንገላታት ሁኔታ ስለሚፈጽሙ ችግሩን በወቅቱ ለመፍታት አዳጋች መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ የካሳ ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ ይዘዲን ሽምሱ እንደተናገሩት ደግሞ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ከመጀመሩ በፊት መስመሩ በሚያልፍበት በ65 ሜትር ስፋት ላይ ለነበሩ ንብረቶች ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ ካሳ ተከፍሎ ነበር ወደ ሥራ የተገባው። የፕሮጀክቱ ሥራ ሲጀመር መስመሩ የሚያልፍበት ቦታ ከወሰን ማስከበር ችግር ነፃ እንደነበር የጠቆሙት አቶ ይዘዲን የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ከተጀመረና ከተጠናቀቀ በኋላ በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጋንታ መጬ እና ቆላ ሻራ ቀበሌዎች ላይ በርካታ ቤቶች ተገንብተዋል። የግንባታ ሥራዎች በወቅቱ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ለአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ እና ለከተማ አስተዳደደሩ የማሳወቅ ሥራ ቢሰራም በወቅቱ መቆጣጠር እንዳልተቻለ ነው አስተባባሪው የተናገሩት። መስመሩ በተዘረጋባቸው ቦታዎች ላይ የሚገኙ የቤት ግንባታዎች መፍትሔ እንዲሰጣቸው በየደረጃው ለሚገኙ የክልል መስተዳድር አካላት የማሳወቅ እና በሚነሱበት መንገድ ላይ ተደጋጋሚ ውይይቶች ቢደረጉም እስከ አሁን ድረስ ግንባታዎች ሊቆሙ እንዳልቻሉ የሥራ ኃላፊዎች አስታውቀዋል። የወሠን ማስከበር ችግሩን ለመፍታት በየደረጃው የሚገኙ የክልል መስተዳድር አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም ነው የሥራ ኃላፊዎቹ ያስገነዘቡት። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2015 ዓ.ም.

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በምግብ አብሳይ ( ሼፍ) የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ/ም ባወጣው የዉጪ ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገ
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በምግብ አብሳይ ( ሼፍ) የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ/ም ባወጣው የዉጪ ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ሜክሲኮ ኬ ኬር በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት 20ኛ ፎቅ የጽሑፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን።

photo content
+8