EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 538 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 538 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 538
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 533
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ለማድረግ የሚያገለግል የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ተደረገ
........... ////.............
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል Its My Dam የተሠኘ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ተደረገ።
የገቢ ማሰባሰቢያ መተግበሪያውን ወደ ሥራ ለማስገባት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም ከፍተኛውን ወጭ በመሸፈን አጋርነቱን አሳይቷል፡፡ ባንኩ እያደረገ ላለው ድጋፍም አመስግነዋል፡፡
መተግበሪያዉ ከ1 ዶላር ጀምሮ እስከ 10 ሺህ ዶላር ድረስ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ሲሆን ይፋ የተደረገው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነው።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዘዳንት አቶ አቤ ሳኖ በበኩላቸው የገቢ ማሰባሰቢያ መተግበሪያው ግድቡን ለመጨረስ በሚደረገው ጥረት ድጋፍ ማድረግ ለሚፈልጉ ዳያስፖራዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል፡፡
መተግበሪያዉ ይፋ የተደረገው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲሆን ይህም ለግድቡ ድጋፍ ማድረግ ለሚፈልጉ በውጭ በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በቀላሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያግዛል፡፡
ከዚህ በፊት በውጭ ሀገር የሚገኙ ሰዎች ለግድቡ ድጋፍ ለማድረግ ሲቸገሩ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን www.Itsmydam.et የተሰኘው መተግበሪያ ይሄን ችግር በቀላሉ ይፈታል ተብሏል፡፡
ዲያስፖራው ለታላቁ የኤትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ እንዲያደርግ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን ወደ ስራ የማስገባት ስራ እየተከናወነ ሲሆን ከቀናት በፊት www.mygerd.com የተሰኘ ድረገጽን መሰረት ያደረገ የድጋፍ ማሰባሰቢያ በይፋ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል፡፡
የሞባይል መተግበሪያው በይፋ ከመተዋወቁ አስቀድሞ በነበሩት 12 ቀናት 70 ሺህ ዶላር ለግድቡ ድጋፍ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በገቢ ማሰባሰቢያ መተግበሪያ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የሁለቱ ተቋማት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት፣ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሄ እና የሌሎች ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 28 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
በሪጅኑ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ እየጨመረ ቢመጣም እያስተናገድኩ ነው - ሪጅኑ
………….///…………
የከተሞች መስፋፋት፣ የህዝብ ቁጥር ዕድገትና የኢንዱስትሪ ፍሰት ያመጣውን የኃይል ፍላጎት እያስተናገደ መሆኑን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት በሪጅኑ የኃይል ፍላጎት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ቢመጣም አሁን ላይ ጥያቄውን ለመመለስ አስቸጋሪ አልሆነም፡፡
ይሁንና በወረታ፣ በእንጅባራና በቡሬ ከተሞችና አካባቢያቸው እየመጣ ያለውን ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ማስተናገድ የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ በወረታ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ በፈረቃ ማዳረስ ተጀምሯል ብለዋል፡፡
በቡሬና ደብረማርቆስ ግንባታቸው የተጀመሩት ማከፋፈያ ጣቢያዎችና በደብረታቦር ሊገነባ የታቀደው የማከፋፈያ ጣቢያ አሁን ያለውንና ወደፊት ሊመጣ የሚችለውን ጥያቄ ለመመለስ እንደሚያስችል አቶ ውበት ተስፋቸውን ገልፀዋል፡፡
የባህርዳር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ዕድሉ በበኩላቸው 45 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ካለውና እስከ 40 ሜጋ ዋት መሸከም ከሚችለው የደብረታቦር ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ከተማዋ፣ ዪኒቨርሲቲውና አካባቢው እየተጠቀመ ያለው 10 ሜጋ ዋት እንደማይደርስ አስታውቀዋል፡፡
በመሆኑም ቀደም ሲል በወረታ በኩል ደብረታቦር ኃይል ሲያገኝበት በነበረው የሥርጭት መስመር ወረታና አዲስ ዘመን ከተሞች ተጨማሪ ኃይል የሚያገኙበት ዕድል ስላለ ሊታሰብበት ይገባል፡፡
በባህርዳር 2 ካለው ማከፋፈያ ጣቢያ የመከላከያ ስርዓት መቆጣጠሪያ እና ዳታ ከመቆጣጠሪያው ወስዶ ትዕዛዝ በሚሰጠው (Relay) ላይ መጠነኛ ጥገና በማድረግ ለባህር ዳር ከተማ ተጨማሪ ኃይል መስጠት የሚችሉ 3 ባለ 15 ሺህ ቮልት መስመሮች ዝግጁ ማድረግ ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 28 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
ለዓመታት የቆመው የጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት በተቋሙ ባለሙያዎች ተጠግኖ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል
………..////…………
ከሰባት ዓመታት በላይ በብልሽት ምክንያት የቆመውን የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ጥገና በተቋሙ ባለሙያዎች እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ጉታ አስታወቁ፡፡
ዩኒቱ በደለል ስለተሞላና የተርባይን ሻፍት ዝንፈት ስላጋጠመው ተርባይኖቹ መንቀሳቀስ እንዳቆሙ በጥናት መታወቁን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ችግሩን አስተካክሎ ዩኒቱን ሥራ ለማስጀመር በተለያዩ የውጭ ድርጅቶች ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ መጠየቁን ተናግረዋል፡፡
ይሁንና የተቋሙ ባለሙያዎች በኃላፊነት ስሜት በመንቀሳቀሳቸው በበጋው ወራት ደለሉን የማስወገድና ተርባይኑን የማንቀሳቀስ ሥራ ተከናውኖ አሁን የጥገና ሥራው ተጀምሯል ብለዋል፡፡
የጥገና ቡድኑ መሪና የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሹመት በላቸው በበኩላቸው የጥገና ሥራው ከተጀመረ በኋላ የተርባይን ሻፍት ዝንፈትን የማስተካከል፣ ዩኒቱ እንዲሰራ ለማድረግ ተሸከርካሪ አካሉን ወይም ሮተር ከፍ የማድረግ (Lifting Pump)፣ የተርባይኑ ተሸከርካሪ አካል የማስተካከል ሥራዎች (Trust bearing) መሰራታቸውን ገልፀዋል፡፡
ለዓመታት የቆመውን ተርባይን ማሽከርከር መቻሉ ዩኒቱን ሥራ ለማስጀመር መቃረባችን ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ዩኒቱን ሥራ ለማስጀመር የሚቀረው ሥራ የተቃጠለውን የጀነሬተር ስቴተር ዋይንዲንግ በሌላ በመተካት የሙከራና ፍተሻ ሥራ ማከናወን ብቻ እንደሆነ አቶ ሹመት ተናግረዋል፤ ይህም ከአንድ ወር ያላነሰ ጊዜ እንደሚፈልግ ጠቁመዋል፡፡
ኃላፊዎቹ እንዳሉት እንዲህ ዓይነት ለረጅም ዓመታት ያልተንቀሳቀሰ ዩኒትን በተቋሙ ባለሙያዎች የመጠገን ሥራ ሲከናወን የአሁኑ የመጀመሪያው ነው፡፡
በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፈችው ብቸኛዋ ሴት የጣቢያው የጥገና ባለሙያ ኸደም መሐመድ ደግሞ ሥራው ብዙ ልምድ ያገኘችበት እንደሆነ ትገልፃለች፡፡
ዩኒቱን ወደ ሥራ ማስገባት ለርስዋም፣ ለጥገና ቡድኑም ለተቋሙም ትልቅ ስኬት ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው እንደሆነ ተናግራለች፡፡
ከደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ለተግባር ልምምድ ተመድበው ከመጡት ስድስት ተማሪዎች መካከል የአራተኛ ዓመት የኤሌክትሮ ሜካኒካል ተማሪ ይብለጥ በሪሁን እየተሳተፈበት ያለው የጥገና ሥራ ንድፈሐሳብን በተግባር የተረጎምንበት ነው ብሎታል፡፡
የጥገና ሥራው በስኬት ከተጠናቀቀ ዩኒቱ እስከ 33 ሜጋዋት ኃይል ማመንጨት ይችላል፡፡
የጢስ አባይ 2 የውኃ ኃይል ማመንጫ ሥራ የጀመረው በ1993 ሲሆን 72 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ተደርጎ ተገነባ ጣቢያ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 27 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
ቤትና ንብረታቸው ለተቃጠለባቸው የተቋሙ ሠራተኞች የቁልፍ ርክክብ ተደረገ
...............////.........
በአዋሽ 2 እና 3 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በሰራተኞች መኖሪያ ቤት በደረሰ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቤትና ንበረታቸው ለተቃጠለባቸው ሠራተኞች የቁልፍ ርክክብ ተደረገ፡፡
ተቋሙ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የቤት ግንባታ እና እድሳት ሥራ በማከናወን ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ለተጎጂ ሠራተኞች የቤት ቁልፍ አስረክቧል።
በውጭ ሀገር ከሚኖሩ እና ከአካባቢው ማህበረሰብ የተሰበሰበውን የገንዘብ ድጋፍም ርክክብ ተፈጽሟል፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ እያየሁ ሁንዴሳ እንደገለፁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በአዋሽ 2 እና 3 ጣቢያዎች የጎርፍ መጥለቅለቅና የእሳት አደጋ ያደረሱትን ጉዳት በመቋቋም ሠራተኛውና ተቋሙ አፋጣኝ ምላሽ ሰጥተዋል።
ይህም በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ የጎላ ተፅዕኖ ሳያሳድር ችግሩ እንዲወገድ መደረጉ ሊደነቅ ይገባል ብለዋል።
ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡
የአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ መጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ.ም እኩለ ለሊት ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ 13 ቤቶች እንደተቃጠሉ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በደረሰው አደጋም ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ሲወድም በሁለት ሰዎች ላይ የሞት አደጋ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 26 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
የተቋሙ የ2013 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2014 ዕቅድ ተገመገመ
..........////.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2013 በጀት ዓመት አፈፃፀሙንና የ2014 በጀት ዓመት ዕቅዱን በአዳማ ከተማ ለሶስት ቀናት ገምግሟል።
በግምገማው ላይ ሁሉም የስራ ሂደት ሥራ አስፈፃሚዎችና የዋና ስራ አስፈፃሚ ተጠሪ መምሪያ ዳይሬክተሮች ተገኝተዋል።
የ2013 በጀት ዓመት አፈፃፀም በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ ያለፈ ቢሆንም አበረታች ውጤት የተመዘገበበት እንደነበር ተጠቅሷል።
በሰሜን ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በተደጋጋሚ የደረሰውን ውድመት በማስተካከል ህብረተሰቡ አሌክትሪክ እንዲያገኝ የተሰራው ሥራ ለአብነት ተነስቷል።
በዚህም ተቋሙ ከ5 መቶ ሚሊየን ብር የሚበልጥ ጉዳት ቢያጋጥመውም በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በማለፍ አበረታች ስራ መስራቱ ተገልጿል።
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማከናወን የሚያስችሉና አስቀደመው ኃይል የሚያመነጩትን ሁለት ዩኒቶች ዝግጁ ለማድረግ የተሰሩት ስራዎችም ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷቸው የተከናወኑ እንደነበር ተመላክቷል።
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችም ኤሌክትሪክን በፍትሐዊነት ለማዳረስ የተጀመረውን ሀገራዊ ጥረት በሚያሳካ ደረጃ መከናወናቸው ተነስቷል።
ሌሎች የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችም በአብዛኛው ጥሩ አፈፃፀም እንደነበራቸው ተገምግሟል።
ለመጠናቀቅ የተቃረቡትንም በትኩረት በመስራት በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ወደስራ ለማስገባት አቅጣጫ ተቀምጧል።
የተቋሙ ገቢና የፋይናንስ ሁኔታ ከዓመት ዓመት እየተሻሻለና ጤናማ እየሆነ መምጣቱ የተጠቀሰ ሲሆን ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭም ሆነ ከኤክስፖርት የተሻለ ገቢ የተገኘበት ዓመት በመሆኑ ልምድ ሊወሰድበት ይገባል ተብሏል።
ለሀገር ወስጥ ኃይል ሽያጭ ገቢ ማደግ የስማርት ሜትሮች በሁሉም ኃይል ማመንጫዎችና የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በቀር በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች መተከሉ በምክንያትነት ተጠቅሷል።
የሲስተም ጥናት መደረጉ፣ የኤሌክትሪክ ዘርፍ የአስር ዓመት መሪ ዕቅድ መጠናቀቁ፣ የ25 ዓመት ማስተር ፕላን መዘጋጀቱና ለተመረጡ ፕሮጀክቶች የአዋጭነት ጥናት መዘጋጀቱ በአበረታች የተነሱ ጉዳዮች ናቸው።
የበጀት አፈፃፀሙን የገመገመው ማኔጅመንቱ አፈፃፀሙ አበረታች መሆኑን አንስቷል።
ማኔጅመንቱ የ2013 በጀት ዓመት ላይ የነበሩ የአፈፃፀም ክፍተትና ጥንካሬዎችን በመለየት የተዘጋጀውን የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ በጥልቀት ገምግሟል።
በሁሉም የስራ ክፍሎች የታቀደው ዕቅድ ከዘርፉ መሪ ዕቅድ ተመንዝሮ የቀረበ መሆኑን በማረጋገጥ ለተግባራዊነቱ ሁሉም ሠራተኛና አመራር በትጋት እንዲንቀሳቀስ አሳስቧል።
ከግምገማው በኋላ ማኔጅመነቱ የአዳማ አንድ እና ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 24 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሰራተኞች/ሥራ ኃላፊዎች ብቻ፤
የተቋሙን የሰው ኃይል ግንባታ ሥራ ፍላጎትን መሰረት ባደረገ መልኩ ለማከናወን እንዲቻል፤ የውጭ አማካሪ ተቀጥሮ ጥናት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሰራተኞች የተዘጋጀውን ቅፅ በአግባቡ በመሙላት ለጥናቱ ስኬት የተቻላችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን፡፡
መጠይቁን ለመሙላት፡-
- ኢንተርኔት አገናኝተው የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑት፤ወይም ኮፒ አድርገው ኢንተርኔት መፈለጊያዎ ላይ ይጫኑት፤
- መጠይቁን ከሞሉ በኋላ መላኪያውን(Send) መጫን እንዳይረሱ፤
https://ee.kobotoolbox.org/x/EH1v5NNc
የሰው ኃይል የስራ ሂደት
15 533
ለግድቡ በየደቂቃው በአማካይ 17 ዶላር እየተሰበሰበ ነው፤ በአምስት ቀን ውስጥ ከ111 ሺህ ዶላር በላይ ተሰብስቧል
…………///………..
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚደረግበት ድረ ገፅ www.mygerd.com ይፋ ከሆነ ዛሬ አምስተኛ ቀኑ ነው፡፡
እስካሁን ድረስ ከ874 ኢትዮጰያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ 111,390 ዶላር ተሠብስቧል ። 45 ሰዎች ደግሞ ለልገሳው የሚሆን ዘመቻ በማድረግ ላይ ናቸው።
በአማካይ በየሰዓቱ 1 ሺህ ዶላር ለግድቡ እየተለገሰ ሲሆን በየደቂቃው ደግሞ 17 ዶላር መሰብሰብ ተችሏል፡፡ እንዲህ ዓይነት የድጋፍ ማሰባሰቢያ ፕላትፎርም ሲዘጋጅ በኢትዮጵያ ይህ የመጀመሪያው እንደሚሆን እምነት አለን፡፡
www.mygerd.com ድረ-ገፅ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሉበት አካባቢ ሆነው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ለማድረግ እና አሻራቸውን ማሳረፍ ለሚፈልጉ የተዘጋጀ ድረ-ገፅ ነው ፡፡
የማይደበዝዝ አሻራዎን ያሳርፉ፤ ሌሎችንም እንዲሳተፉበት ይጋብዙ!!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 22 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
የአዋሽ 7 ኪሎ- አሰበ ተፈሪ የማስተላለፊያ መስመር ኢንሱሌተሮችን የመቀየር ሥራ እየተከናወነ ነው
……….////………..
የአዋሽ 7 ኪሎ - አሰበ ተፈሪ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኢንሱሌተሮችን የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳስታወቁት ኢንሱሌተሮቹን መቀየር ያስፈለገው የማስተላለፊያ መስመሩ ከተገነባ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ በመሆኑና ኢንሱሌተሮቹ በእርጅና ምክንያት በመሰባበራቸው ነው፡፡
ኢንሱሌተሮችን የመቀየር ስራው በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ከተተከሉ 3 መቶ 11 ምሰሶዎች (ታወሮች) መካከል በ2 መቶ 62 ምሰሶዎች ላይ እንደሚከናወን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ እስከ አሁን ድረስም በ107 የማስተላለፊያ መስመሩ ታወሮች ላይ 3 መቶ 30 ኢንሱሌተሮችን በአዲስ መተካቱን ገልጸዋል፡፡
በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የነበሩ 786 ፖርሲሊን (porceilin) ኢንሱሌተሮች በአዲስ የፕላስቲክ ኢንሱሌተሮች እንደሚቀየሩም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሪጅኑ የጥገና ሠራተኞች እየተከናወነ የሚገኘውን ኢንሱሌተሮችን የመቀየር ሥራ እስከ ጥር 2014 ዓ.ም ድረስ ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡
የአዋሽ 7 ኪሎ - አሰብ ተፈሪ ማስተላለፊያ መስመር 116 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ይህም ከቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጋር ተገንብቶ ከ1955 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በጣልያን ኩባንያ የተገነባ ነው፡፡
በተያያዘ ዜና የአዋሽ 7 ኪሎ - አሰበ ተፈሪ ማስተላለፊያ መስመር የመከላከያ ሲስተሙን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አቶ ጋሻው ተናግረዋል፡፡
የመስመሩ የመከላከያ ሲስተም የተጠናከረ ባለመሆኑ ችግር ሲያጋጥመው ሌሎች መስመሮችም አብረዉ ስለሚቋረጡ በችግር ወቅት መስመሩ ራሱን ችሎ የሚቋረጥበት ሁኔታ ለመፍጠር የመከላከያ ሲስተሙን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡
ለዚህም በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ እየተሰራ ያለውን የማሻሻያ ሥራ በማጠናቀቅ ወደ ሥራ ለማስገባት ጥረት ይደረጋል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 22 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
ለህዳሴ ግድቡ በ72 ሰዓታት ከዳያስፖራው 90 ሺህ ዶላር በላይ ተሰብስቧል
..........////........
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚደረግበት ድረ ገፅ www.mygerd.com ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ከ742 ኢትዮጰያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት እስከ 9:00 ሰዓት ድረስ 91 ሺህ 395 ዶላር ተሠብስቧል ። 39 ሰዎች ደግሞ ለልገሳው የሚሆን ዘመቻ በማድረግ ላይ ናቸው። ይቀጥልል........
ሐምሌ 20 ቀን 2013 ዓ/ም
15 533
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም www.mygerd.com ይፋ በተደረገ በ48 ሠዓት ውስጥ ወደ 70ሺህ ዶላር አካባቢ ድጋፍ ተደርጓል። 577 ሰዎችም ተሳትፈውበታል። ይህ በአማካይ በሰዓት 1500 ዶላር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ያሳያል። አስደናቂ የትብብር ና የድጋፍ ስሜት እየታየ ነው። የማይደበዝዝ አሻራን ማሳረፍ የሚለውን ከዚህ በላይ ምን የሚገልፀው ይሆን?
ባሉበት ቦታ ሆነው ለግድቡ ድጋፍ ለማድረግ: https://www.mygerd.com ይጠቀሙ።
15 533
ትናንት ይፋ በሆነው www.mygerd.com ድረ-ገፅ ላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ሲያደርጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ የተፈረመ ኢ-ሰርተፊኬት ወዲያውኑ ይደርሶታል፣ ለታሪክም ይቀመጣል!
"Your contribution is one your motherland will forever cherish." 🙏
አሁን $32,380 ደርሰናል፣ ድጋፍ ለማድረግ: https://www.mygerd.com ይጠቀሙ።
15 533
እንደምን አደራችሁ፣ Mygerd.com ይፋ መደረጉ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ያሉ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች #ህዳሴ ግድብን# በገንዘብ እንዲደግፉና አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ዕድል ፈጥሯል። እስካሁን 270 ሰዎች ባደረጉት ልገሳ 23,645 ዶላር ተሰብስቧል፡፡ 27 ሰዎች ደግሞ ለሌሎች በማስተዋወቅ ዘመቻውን ተቀላቅለዋል፡፡ ድጋፉ ቀጥሏል፡፡ ግድቡም ይጠናቀቃል።
ሐምሌ 18 ቀን 2013 ዓ/ም
15 533
Mygerd.com ይፋ በተደረገ በሰዓታት ውስጥ 124 ሰዎች ባደረጉት ልገሳ 9705 ዶላር ተሰብስቧል፡፡ 15 ሰዎች ደግሞ ለሌሎች በማስተዋወቅ ዘመቻውን ተቀላቅለዋል፡፡ ድጋፉ ቀጥሏል፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
