EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 538 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 538 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 538
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 533
Mygerd.com ይፋ በተደረገ በደቂቃዎች ውስጥ 36 ሰዎች ባደረጉት ልገሳ 1899 ዶላር ተሰብስቧል፡፡ 5 ሰዎች ደግሞ ለሌሎች በማስተዋወቅ ዘመቻውን ተቀላቅለዋል፡፡ ድጋፉ ተጀምሯል፡፡
15 533
ዳያስፖራው ለህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚያደርግበት ድረገፅ ይፋ ሆነ
www.mygerd.com
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
15 533
የአይኤስኦ የጥራት ሥራ አመራር (ISO Quality Management) ሥልጠና እየተሰጠ ነው
………/////……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የአይኤስኦ የጥራት ሥራ አመራር (ISO Quality Management) ሥልጠና በመውሰድ ላይ ይገኛል፡፡
ሥልጠናው ሥራ አመራሩ ከጥራት ማኔጅመንት ጽንሰሐሳብ ጋር እንዲተዋወቅ፤ ዓለምአቀፍ አሰራሮችን እንዲረዳና የኦፕሬሽን ቅልጥፍና እንዲያመጣ እንዲሁም የደንበኞችን እርካታ እንዲያሳድግና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲያመጣ ያግዛል ተብሏል፡፡
በስልጠናው ላይ የአይኤስኦ የጥራት ሥራ አመራር ጽንሰሐሳብ፣ መርሆዎችና ጥቅም፣ ሂደትና ስጋት ሥራ አመራር ላይ ትኩረት ያደረጉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተደርጓል፡፡ ሥልጠናውን በመስጠት ላይ የሚገኘው በዓለም አቀፍ ደረጃ የኦዲት፣ የታክስና የማማከር አገልግሎት የሚሰጠው KPMG ዓለምአቀፍ ነው፡፡
ሐምሌ 16 ቀን 2013 ዓ.ም.
15 533
ከቃሊቲ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ወደ መካኒሣ እና ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚመጣው ኃይል ትናንት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ከ2፡15 ጀምሮ ኃይል ተቋርጦ አድሯል፡፡
የጥገና ባለሙያዎቻችንም በዋናው መስመር ላይ ያጋጠመውን የኮንዳክተር መበጠስ ለማስተካከል ሲሰሩ ቆይተው ከቀኑ 7፡30 ላይ መብራት የተቋረጠባቸውን ሁሉንም አካባቢዎች መብራት እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡
ለሰዓታት በትዕግስት የጠበቃችሁንን የኤሌክትሪክ ተቃሚዎች እናመሰግናለን፡፡
የጥገና ባለሙያዎቻችንም ህብረተሰቡ መብራት እንዲያገኝ ያደረጋችሁት ርብርብ ሊመሰገን ይገባል፡፡
ከቃሊቲ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ወደ መካኒሣ እና ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚመጣው ኃይል ትናንት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ከ2፡15 ጀምሮ ኃይል ተቋርጦ አድሯል፡፡
የጥገና ባለሙያዎቻችንም በዋናው መስመር ላይ ያጋጠመውን የኮንዳክተር መበጠስ ለማስተካከል ሲሰሩ ቆይተው ከቀኑ 7፡30 ላይ መብራት የተቋረጠባቸውን ሁሉንም አካባቢዎች መብራት እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡
ለሰዓታት በትዕግስት የጠበቃችሁንን የኤሌክትሪክ ተቃሚዎች እናመሰግናለን፡፡
የጥገና ባለሙያዎቻችንም ህብረተሰቡ መብራት እንዲያገኝ ያደረጋችሁት ርብርብ ሊመሰገን ይገባል፡፡
ሐምሌ 15 ቀን 2013 ዓ/ም
15 533
ከቃሊቲ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ወደ መካኒሣ እና ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚመጣው ኃይል ትናንት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ከ2፡15 ጀምሮ ኃይል ተቋርጦ አድሯል፡፡
የጥገና ባለሙያዎቻችን ችግሩን ለማስተካከል ሲሰሩ ቢያድሩም በአፋጣኝ ለማስተካከል ባለመቻሉ በመካኒሳ፣ በጀሞ፣ በኃይሌ ጋርመንት አካባቢ የሚኖረው ህብረተሰብ በጨለማ ለማደር ተገዷል፡፡ ለዚህም ህብረተሰቡን ይቅርታ እየጠየቅን በጥቅት ሰዓት ውስጥ ኃይል እንደሚያገኙ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
15 533
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ
........./////......
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል::
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው "ሁለተኛው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሙሌት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ ያለን!"ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በጽናት ትገሰግሳለችም ሲሉ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡
15 533
ዋና ሥራ አስፈፃሚው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል
............/////..........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ ለመላው የድርጅቱ ሠራተኞችና አመራሮች የእንኳነ ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው በመልዕክታቸው የግድቡን ቀሪ ስራ ለማጠናቀቅ በቀጣይ ፈታኝ ሥራዎች የሚጠበቁ በመሆኑ ሥራው በታላቅ ቁርጠ ነት እና ትጋት እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የፕሮጀክቱን ማኔጅመንት፣ ተቋራጮችና አማካሪዎች እንዲሁም ከሁሉም በላይ ሳምንቱን ሙሉ ቀንና ለሊት 24 ሰዓት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እየሰሩ ፕሮጀክቱን ለዚህ ስኬት ያበቁ ሰራተኞችን አመስግነዋል።
ለፕሮጀክቱ እውን መሆን ህይወታቸውን መስዋዕት ያደረጉ ሰራተኞችንም ተቋሙና ህዝብ ከፕሮጀክቱ ጋር ሲያስታውሳቸው እንደሚኖር ጠቅሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለፕሮጀክቱ ስኬት ለሰጡት አመራር፣ ክትትልና ድጋፍ ምስጋና ይገባቸዋል ያሉት ሥራ አስፈፃሚው ለውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ እና ለመከላከያ ሠራዊትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ሐምሌ 12 ቀን 2013 ዓ/ም
15 533
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቀቀ
.................///..................
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት ስራ በስኬት ተጠናቋል።
የሁለተኛው ዙር ውሃ ሙሌት በቅርቡ ኃይል የማመንጨት ስራ ይጀምራሉ ተብለው የሚጠበቁትን ሁለቱን ዩኒቶች ለማንቀሳቀስ በቂ ውሃ እንዲይዝ ያስችሏል።
ይህም ባለፈው ዓመት ከተያዘው የመጀመሪያው የውሃ መጠን ጋር ተደምሮ ሁለቱንም ዩኒቶች ዓመቱን ሙሉ ኃይል እንዲያመነጩ የሚያስችል ነው።
በአሁኑ ወቅትም ቀድመው ኃይል ለሚያመነጩት ዩኒት 9 እና 10 ኃይል ማመንጫዎች የተርባይንና ጀነኔተር ተከላ ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ።
በዘንድሮ ክረምት ወቅትም ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ወደ ግድቡ ሲገባ የነበረ በመሆኑ ሙሊቱ ከታሰበው ጊዜ ቀድሞ እንዲጠናቀቅ አድርጎታል።
የመጀመሪያው ዓመት የውሃ ሙሊት ልክ በዛሬው ዕለት እንደተከናወነ ይታወሳል።
15 533
ማከፋፈያ ጣቢያው ለሀገር አቀፍ የኃይል ስርጭት አስተማማኝነት የጎላ ሚና አለው
……….///………..
የገላን ባለ 400/230/132/33/15 ኪ.ቮ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአዲስ አበባን ብሎም የሀገር አቀፉን የኃይል ስርጭት አስተማማኝ እንዲሆን በማድረግ በኩል ከፍተኛ ሚና እንዳለው የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡
ኃላፊው አቶ ዓለሙ ዳኛቸው እንደተናገሩት በሀገሪቱ ካሉ ግዙፍ ጣቢያዎች አንዱ የሆነው የገላን ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአማካኝ እስከ 2 ሺህ ሜጋ ዋት ኢነርጂ የመሸከምና የማስተላለፍ አቅም አለው፡፡
በፊንፊኔ ልዩ ዞን በገላን ከተማ አስተዳደር በመኑሮ ቀበሌ ማህበር የሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያው 2075 ሜጋ ቮልት አምፒር (M.V.A.) የመሸከም አቅም ያለቸው 10 ትራንስፈርመሮች አሉት፡፡
ከመጋቢት 2006 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ጣቢያው ስድስት ባለ 230 ኪ.ቮ.፣ስምንት ባለ 132 ኪ.ቮ እና 14 ባለ 15 ኪ.ቮ እንዲሁም ሁለት ገቢ እና ሰባት ባለ 400 ኪ.ቮ ወጪ መስመሮች አሉት ፡፡
ከእነዚህ ወጪ መስመሮች ውስጥ ሁለት ባለ 230 ኪ.ቮ፣ ሁለት ባለ 132 ኪ.ቮ እና 5 ባለ 15 ኪ ቮ. ወጪ መስመሮች አገልግሎት ዝግጁ ሆነው ደንበኞችን እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ወቅትም አራት አዲስ ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች የግንባታ፣ የሙከራና የፍተሻ ስራቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እየሆኑ እንደሚገኙ አቶ ዓለሙ ጠቁመዋል፡፡
ወጪ መስመሮቹ በቀለበት ሲስተም (ring systyem) ከሌሎች ማከፋፋያ ጣቢያዎች ጋር ስለተገኛኙ ኃይል የመስጠትም ሆነ ኃይል የመቀበል አገልግሎት ይሰጣሉ ብለዋል፡፡
በ250 ሺህ ካሬ የመሬት ስፋት ላይ የተገነባው ይህ ማከፋፋያ ጣቢያ የአዲስ አበባ እና የሀገር አቀፍ የኃይል ስርጭት በማሳለጥ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አውታሮችን በማንቀሳቀስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 09 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
በገላን ማከፋፈያ ጣቢያ የአረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተካሄደ
………….///…………..
“ኑ ኢትዮጵያን እናልብሳት” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ3ኛው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐግብር በገላን ባለ 400/230/132/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተካሄደ፡፡
በፊንፊኔ ልዩ ዞን በገላን ከተማ አስተዳደር በመኑሮ ቀበሌ ማህበር በሚገኘው የገላን ማከፋፈያ ጣቢያ ግቢ ውስጥ በተካሄደው የአረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዲስ አበባ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ቢሮ ዳሬክተር አቶ ወንደሰን ወ/ማሪያም እንደተናገሩት ለአረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ ጥሪው የገላንን ጨምሮ እስከ አሁን በሰበታ አንድ እና በቃሊቲ ጂ.አይ .ኤስ ማከፋፈያ ጣቢያ የአንረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
በቀጣይም በሪጅኑ በሚገኙ በሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች መርሃ ግብሩን የማስቀጥል እቅድ እንደተያዘ ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ከችግኝ ባሻገር የተለያዩ አበባዎችን በመትከል ማከፋፈያ ጣቢያዎቹን ውብ ፣ ጽዱ እና ምቹ የስራ ቦታ ለማድረግ በሪጅኑ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው ኃላፊ አቶ ዓለሙ ዳኛቸው በበኩላቸው 25 ሄክታር ስፋት ባለው የኃይል ማከፋፋያ ጣቢያ ውስጥ ለማስፋፈያ የማይውለውን የውጪኛውን አጥር ተጠግቶ ያለውን ቦታ አረንጓዴ፣ ውብ እና ነፋሻ ለማድረግ መታሰቡን ተናገረዋል፡፡
እንደ ኃላፊው ገለፃ ከ10 ሺህ በላይ ችግኞችን በማቅረብ ፣ የአካባቢውን ህብረተሰብ አስተባብሮ ጉድጓድ በመቆፈር እና ችግኞቹን በመትከል የገላን ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ እገዛ እና ትብብር አድርጓል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ ችግኞችን ከመትከል ባሻገር እንዲጸድቁ ተገቢው እንክብካቤ በጣቢያው ሠራተኞች እንደሚደረግ አቶ ዓለሙ አረጋግጠል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 06 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
"እየገነባን ያለነው የውሀ ግድብ እንጂ የኒውክሊየር ማብለያ አይደለም"
"ግብጽና ሱዳን ጉርብትናን፣ አብሮ መልማትን ሊማሩ ይገባል"
"ምክር ቤቱ በህዳሴው ግድብ ላይ የሚያደርገው የመጨረሻው ስብሰባ እንደሚሆን ተስፋ አለኝ"
ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ - የውሃ እና መስኖ ኢነርጂ ሚኒስትር
የጸጥታው ምክር ም/ቤት በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያሉ ልዩነቶች በአፍሪክ ህብረት እንዲታዩ ወስኗል።
15 533
“ህዳሴ ግድብን በተመለከተ የኢትዮጵያ ፍላጎት፣ የኢትዮጵያን የመብራት ጥያቄ የሚመልስ፣ የሱዳንን ስጋት የሚቀንስ፣ የግብጽን ስጋት የሚቀንስ፣ በቀጠናው ሰላምና ብልጽግናን የሚያመጣ፣ ኃይል ሲመረት በጋራ የምንጠቀምበት፣ የውሃም ችግር ካለ እየተወያየን የምንፈታበት፣ ሰላማዊ የልማት ጉዞ እንዲሆን እንፈልጋለን፤ ለዚህም እየሰራን እንገኛለን፡፡ ”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ምላሽ
15 533
ሚኒስቴር መ/ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ በአዲስ አበባ የአረጋውያንና የአቅመ ደካሞችን ቤት እድሳት አስጀመሩ
.............////.........
የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት ጋር በቦሌ ክፍለ ከተማ የአረጋውያንና የአቅመ ደካሞችን ቤት እድሳት በይፋ አስጀምረዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዚህ ዓመት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ 20 የአቅም ደካሞችን ቤቶች ለማሳደስ ሥራ መጀመራቸውን ገልፀዋል።
አምስት መቶ ለሚሆኑ ቤተሰቦም ማዕድ ማጋራታቸውን ተናግረዋል።
አመራሮቹ በሐዲስ ዓለማየሁ መታሰቢያ ትምህርት ቤትም ከተማሪዎች እና ከትምህርት ቤቱ ማኅበረሰብ ጋር ችግኝ ተክለዋል።
ተቋማትና የተሻለ ኑሮ ያላቸው ዜጎች ከጎናቸው ያለውን በመደገፍ ስር የሰደደ ድህነትን ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት እንዲያግዙም ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 27 ቀን 2013 ዓ.ም
15 533
የሀዘን መግለጫ
..........///........
የብዙዎች እናት በሚል ቅፅል ስም የሚታወቁት አበበች ጎበና ዛሬ ጠዋት ህክምና ሲከታተሉ በቆዩበት የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አርፈዋል።
አበበች ጎበና (እዳዬ) በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል በጽኑ ህክምና ክፍል የኮቪድ ሕክምና ሲከታተሉ ቆይተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወ/ሮ አበበች ጎበና ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ፤ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል፡፡
ሰኔ 27 ቀን 2013 ዓ/ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
