EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 567 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 356,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 567 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 24,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.83% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 035 次浏览,首日通常累积 2 465 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 567
订阅者
+1924 小时
+197 天
+2430 天
帖子存档
15 560
ለፕሮጀክቱ የሚውሉ ግብዓቶች በሳይቱ በራስ አቅም እየተመረቱ ነው
………///……..
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በመገንባት ላይ ለሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግብዓቶች በራስ አቅም በሳይቱ ላይ እየተመረቱ መሆኑን በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል የሳይት መሐንዲስ ገለፁ፡፡
መሐንዲሱ አቶ ቢኒያም ሀብታሙ እንደተናገሩት በሳይቱ ለአንከር ቦልት ስራ የሚውል ቴምፕሌት እየተዘጋጀ ነው፡፡
በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሠራተኛ ብርቱካን አብዱ በበኩሏ በሳይቱ በራስ አቅም በሚሰራው የአንከር ቮልት ተከላ ሥራ ላይ እየተሳተፈች መሆኗን ገልፃለች፡፡
ከአሁን ቀደም በውጭ ባለሙያዎች ይከናወኑ የነበሩ ሥራዎችን በሳይቱ በራስ አቅም መስራት መቻሉ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪና የጊዜ ብክነት እንዳዳነው ተናግራለች፡፡
እንደ ብርቱካን ገለጻ በሳይቱ በራስ አቅም የሚከናወኑ ሥራዎች ባለሙያዎች ዕውቀታቸውን እንዲያዳብሩ እድል ከመፍጠሩ በሻገር ተቋሙ ያሉትን ባለሙያዎች በመጠቀም ትልልቅ ዕቃዎችን እንዲሰራ መተማመንን የሚፈጥር ነው፡፡
የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው በበኩላቸው በሳይቱ ለፕሮጀክቱ አስፈላጊ የሆኑ የግንባታ ግብዓቶችን በራስ አቅም ማምረት መጀመሩ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተናግረዋል።
የተጀመሩት ሥራዎች ፕሮጀክቱ በግብዓት አቅርቦት ችግር ምክንያት እንዳይጓተት ሚናቸው የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ቴዎድሮስ በቀጣይ የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት ሌሎች የግንባታ ግብዓቶችን ለመስራት ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በፕሮጀክቱ ላይ በራስ አቅም እየተሰሩ ላሉት ሲቪል ሥራዎች የሚያግዙ ከ50 ሺ በላይ ብሎኬቶች በራስ አቅም በሳይቱ ማምረት መቻሉን ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወሳል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 02 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል
………///……..
በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው 11ኛው የኢትዮጵያ የ30 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሁለቱም ፆታ አሸናፊ ሆኗል።
በወንዶች በተካሄደው ውድድር የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌት ኃይለ ማርያም ኪሮስ 1ኛ በመውጣት የወርቅ ተሸላሚ ሲሆን የቡድን አጋሩ አትሌት ባየልኝ ተሻገር ውድድሩን በሶስተኛነት አጠናቋል፡፡
በተመሳሳይ የሴቶች የሩጫ ውድድር አትሌት ጽጌ ኃይለ ሥላሴ 2ኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች፡፡
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጠቃላይ ነጥብ አንደኛ በመሆን የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።
በዚህ ውድድር ከሶስት ክልሎች፣ከአንድ ከተማ አስተዳደር እና ከ15 ክለቦች የተውጣጡ 522 አትሌቶች ተሳትፊ ሆነዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 01 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ሽንፈት ገጥሞታል
……..///……….
በ2ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂው ጨዋታ በሐዋሳ ከነማ አሸናፊነት ተጠናቋል።
ከረፋዱ 4 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተከናወነው የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እና ሐዋሳ ከነማ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አንድ ለባዶ ተረቷል።
የሐዋሳን ብቸኛ የማሸነፊያ ጎል እፀገነት ግርማ በ26ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፋለች።
ከጎሉ መቆጠር በኋላ ተጭኖ የተጫወተው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ያገኛቸውን በርካታ የጎል ዕድሎች አባክኗል።
በአንፃሩ ሐዋሳ ከነማ ውጤቱን ለማስጠበቅ በመከላከል ላይ የተመሰረተ የአጨዋወት ስልት ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን ተጫዋጮቹ ሰዓት ለማባከንም በርካታ ጊዜ ሜዳ ላይ ሲወድቁ ተስተውሏል።
በ3ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከልደታ ክፍለ ከተማ በመጪው አርብ ህዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ጨዋታቸውን የሚያከናውኑ ይሆናል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከላይ ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች ሥራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች ከታች በተገለፁት አማራጭ ሊንኮች በመጠቀም የተዘጋጀው ቅጽ የሚጠይቀውን መረጃዎች በሙሉ ሞልቶ በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
Link 1: https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSf2CT-PMEIAJS7eb2e-4UcDvlUFTTmkaMpQ9RFIJgTqyqgeyw/viewform?usp=sf_link
Link 1: https://forms.gle/brmiQnKWc8wQChH38
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ማህበሩ ከ48 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ አግኝቷል
.......///.........
በ2016 የበጀት ዓመት ከ48 ነጥብ 21 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/የህ/ሥራ ማህበር አስታወቀ።
የህብረት ሥራ ማህበሩ የጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስብሰባ አዳራሽ አካሂዷል።
የማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ሠብሳቢ አቶ አንበሴ ግዛቸው እንደገለፁት ማህበሩ በ2016 በጀት ዓመት 49 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ለማግኘት አቅዶ ከ48 ነጥብ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማግኘት የዕቅዱን 98 በመቶ ማሳካት ችሏል።
በበጀት ዓመቱ የተገኘው ትርፍ ከቀዳሚው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ወይም የ6 በመቶ ብልጫ እንዳለውም ጠቁመዋል።
እንደ አቶ አንበሴ ገለፃ ማህበሩ በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ ምንጮች ከ129 ነጥብ 46 ሚሊዮን በላይ ብር ገቢ ማግኘቱንና ይህም ከ2015 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው ነው።
የማህበሩ አጠቃላይ ካፒታል ከ1 ነጥብ 53 ቢሊዮን ብር በላይ እንደደረሰ እና ከ2015 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ21 በመቶ እድገት እንዳለውም አመልክተዋል።
ማህበሩ ለአባላቱ እስከ አሁን 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ብድር መስጠቱንም ሠብሳቢው አስታውሰዋል።
በ2017 በጀት ዓመት አባላቱ በማህበሩ ላይ ያላቸውን የገንዘብ እንቅስቃሴና የብድር መረጃዎችን በቀላሉ በስልካቸው የሚያገኙበትን አሰራር ለመዘርጋት፣ ተጨማሪ የሠው ኃይል ቅጥር ለመፈፀም፣ የህንፃና ተሽከርካሪ ግዥ ለመፈፀም ማቀዱንም አቶ አንበሴ አስረድተዋል።
የማህበሩ የቁጥጥር ኮሚቴ ሠብሳቢ አቶ ደረጀ አጥናፌ በበኩላቸው የቁጥጥር ኮሚቴው በጠቅላላ ጉባኤው ላይ የሚሰጡ ውሳኔዎች ተፈፃሚ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
ኮሚቴው ከአባላቱ የሚነሱ ጥያቄዎች እልባት እንዲሰጣቸው በቅርበት እየተከታተለ እንደሆነ አንስተው የአባላቱን እርካታ ለማሳደግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
የማህበሩን የ2016 የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት ያቀረቡት ወ/ሮ አስናቀች መንገሻ በበኩላቸው የኦዲት ሪፖርቱ በማህበሩ የሚቀርቡ የተለያዩ ማስረጃዎችን በማረጋገጥ እንደተከናወነ ተናግረዋል።
ማህበሩ በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ ምንጮች ከ129 ነጥብ 46 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን እና ከዚህ ውስጥ ከ77 ነጥብ 46 ሚሊዮን ብር በላዩ ለተለያዩ አገልግሎቶች ወጪ መደረጉን በሂሳብ ሪፖርቱ ላይ ቀርቧል።
በበጀት ዓመቱ ከተገኘው የተጣራ ትርፍ ውስጥ 33 ነጥብ 75 ሚሊዮኑ ለትርፍ ክፍፍል ድልድል የሚውል ሲሆን ቀሪው 14 ነጥብ 46 ሚሊዮን ብሩ ደግሞ ለመጠባበቂያነት እንደሚቀመጥ ተመላክቷል።
በጉባኤው ላይ የተገኙት በአራዳ ክፍለ ከተማ የህብረት ሥራ ማህበራት ማደራጃ ቢሮ የኢንስፔክሽን ቡድን መሪ አቶ ዳኜ ከበደ እና የማህበራት አስተባባሪ አቶ አስናቀ ጫላ በበኩላቸው ማህበሩ በክፍለ ከተማው ሥር ከሚገኙ አራት ማህበራት መካከል በአባላት ብዛትና የካፒታል መጠን ቀደሚ ነው ብለዋል።
ህብረት ሥራ ማህበሩ ያለውን ዝና ለማስቀጠል የማህበሩ አባላት ከሥራ አመራር ቦርዱ ጋር በትብብር መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
ክፍለ ከተማው በማህበሩ ላይ ከዚህ በፊት ያጋጠመው ችግር መፍትሔ እንዲሠጠው በትኩረት እየሠራ እንደነበር አውስተው በቀጣይ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በጉባኤው ላይ የማህበሩ የ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም፣ የቁጥጥር ኮሚቴና የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና በጀት ጨምሮ ከማህበሩ አባላት መተዳደሪያ ደንብ ጋር በተያያዘ መሻሻል የሚገባቸው የተለያዩ ድንጋጌዎች ቀርበው በጠቅላላ ጉባኤው አባላት ፀድቀዋል።
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበሩ ከ13 ሺ 300 በላይ አባላት አሉት።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቁጥር ኢኤ.ኃ/8.4/23/16 ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሹፌር 2ኛ የስራ መደብ ለውጭ አመልካቾች ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም ከዚህ በላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡- ለፈተና በምትመጡበት ወቅት ስማችሁ የተገለጸበትን ተራ ቁጥር ማወቅ አስፈላጊ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
የማከፋፈያ ጣቢያው የመንገድ ኮንክሪት ሙሌት ስራ ተጠናቀቀ
........///.......
ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ ለሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት የውስጥ ለውስጥ መንገድ የኮንክሪት ሙሌት ሥራን ዛሬ መከናወኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሠራተኞች የመኖሪያ ቤት የውስጥ ለውስጥ መንገዱ ለተሸከርካሪ አራት ሜትር እንዲሁም ለእግረኛ ሁለት ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡
የውስጥ ለውስጥ መንገዱ ከ100 ሜትር በላይ ርዝመት ሲኖረው ለግንባታው የሚያስፈልገውን 140 ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት እና ሥራውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን ፓምፕ የመከላክያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት እንዳቀረበ ተናግረዋል፡፡
አቶ ቴዎድሮስ እንዳሉት የውስጥ ለውስጥ መንገዱ የኮንክሪት ሙሌት መጠናቀቅ ለፕሮጀክቱ አፈጻፀም ውጤታማነት የራሱ የሆነ አስተዋፅዖ ይኖረዋል፡፡
ከጥቂት ከማጠናቀቁያ ሥራዎች ውጪ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ መጠናቀቁን ያወሱት አቶ ቴዎድሮስ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለመትከል የሚያስፈልገው የመሠረት ሙሊት ሥራ 80 በመቶ መጠናቀቁንም ጠቁመዋል፡፡
ለኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች መትከያ ከሚያስፈልጉት 314 የመሰረት ሙሊት ሥራዎች መካከል የ243ቱ ሙሌት ሥራ መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡
የሁለት ትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ የኮንክሬት ሙሊት ሥራ ቀደም ብሎ መጠናቀቁን ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል፡፡
የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ አጠቃላይ አፈፃፀሙ 41 በመቶ መድረሱን አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ስርቆት የአፋር ክልል መገለጫ ባለመሆኑ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ሊታገሉት ይገባል
........///..........
በአፋር ክልል እየተፈፀመ ያለውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ለማስቆም የአካባቢውን የጎሳ መሪዎችና ወጣቶች በማሳተፍ እንደሚሰሩ የገቢረሱ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ።
የስርቆት ችግሩን ለመከላከል ከገቢረሱ ዞንና አዋሽ 7 ኪሎ ከተማ እንዲሁም ከፈንታሌ ወረዳ ከተውጣጡ አመራሮች፣ የፀጥታ ኃላፊዎች እና የጎሳ መሪዎች ጋር በተደረገ ውይይት ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱ አሊ እንደገለፁት ስርቆት የአፋር ክልል መገለጫ ባለመሆኑ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ሊታገሉት ይገባል።
ማህበረሰቡ ነውር ነው ብሎ የተጠየፈው የስርቆት ድርጊት ለምን እንደተስፋፋ በመለየት ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት መስራት ይገባል ብለዋል።
እንደ ዞን አስተዳዳሪው ገለፃ የስርቆት ወንጀሉ የተደራጀና በአቀባይና ተቀባይ ሰንሰለት የተሳሰረ በመሆኑ ድርጊቱን ለማስቆም አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት አለበት።
አመራሩና የፀጥታ አካሉ በኃላፊነት ስሜት ካልተንቀሳቀሰ በስተቀር በመሰረተ ልማቶቹ ላይ እየተፈፀመ የሚገኘውን የስርቆት ወንጀል ማስቆም አይቻልም ሲሉ ገልፀዋል።
የገቢረሱ ዞን ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባሃባ ሁሴን እንደተናገሩት ስርቆቱ በየትኛውም ወገን ይፈፀም በአፋር ክልል እስከተፈፀመ ጊዜ ድረስ የክልሉን ህዝብ ስም የሚነካ በመሆኑ እስከታችኛው የአስተዳደር መዋቅር ድረስ ግንዛቤ መፍጠርና በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቅ ማድረግ ያስፈልጋል።
በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በየደረጃው ያለው የመንግስት መዋቅር፣ ህብረተሰቡና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እጅና ጓንት ሆነው እንዲሰሩ አሳስበዋል።
የፈንታሌ ወረዳ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ባህሩ በበኩላቸው በየደረጃው የሚገኙ የዞንና የወረዳ አመራሮች የስርቆት ወንጀሉን ለማስቀረት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
ለህብረተሰቡ አገልግሎት በሚሰጡ የልማት አውታሮች ላይ የስርቆት ወንጀል የሚፈፅሙ አካላትን ለመከላከል የአጎራባች ወረዳዎች በትብብር እንዲሰሩ ነው ጥሪ ያቀረቡት።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በበኩላቸው በአፋር ክልል በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ለማስቀረት በዳጉ ባህላዊ የመረጃ ልውውጥ ስርዓት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ያስፈልጋል ።
በመሰረተ ልማቱ ላይ ዝርፊያ የሚፈፅሙ አካላት ብረቶቹን የፍተሻ ኬላዎች የሚያሳልፉት ቅርፃቸውን በመለውጥ በመሆኑ የፀጥታ አካላት የቁጥጥር ስርዓታቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።
በተቋሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው በመላ ሀገሪቱ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ እየተፈፀመ ያለው የስርቆት ወንጀል ወረርሽኝ አየሆነ መምጣቱን ገልፀዋል።
የዞንና የወረዳ አመራሮች ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጡ የኃይል መሰረተ ልማቶችን የመጠበቅ ግዴታ እንዳለባቸውም ነው ያሳሰቡት።
በተቋሙ የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት በዞኑና በከተማ አስተዳደሮቹ ስለተፈፀሙ የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ሞሰሶዎች ስርቆት መጠንና ስርቆቱ በየትኞቹ አካባቢዎች እንደሚፈፀም ለተወያዮቹ ገለፃ አድርገዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
