EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 688 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 024,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 156 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 688 名订阅者。
根据 28 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 137,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 17.40% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 528 次浏览,首日通常累积 2 730 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 12。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 29 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 688
订阅者
-524 小时
-17 天
+13730 天
帖子存档
15 688
#COP32
የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን የጋራ ኃላፊነታችን ነው፡፡ በCOP 32 የጋራ ድምፃችንን እናሰማለን! #ClimateAction #COP32
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
+3
ዘርፉ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታ በማጠናቀቅ ላይ ነው
…..///……
ተቋሙ የማህበራዊ አገልግሎት ተልዕኮውን ለመወጣት በደሴ ከተማ እያስገነባ የሚገኘውን የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ግንባታ በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደገለፁት ተቋሙ ለስድስት አቅመ ደካማ አባዎራዎች መኖሪያ የሚውሉ እያንዳንዳቸው 42 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ስድስት ባለ አንድ መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየገነባ ነው፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ተቋሙ በ28.2 ሚሊዮን ብር ወጪ እያስገነባ ያለው ባለ አንድ ፎቅ (ጂ+1) ህንፃ የመኖሪያ ቤት ግንባታ 98 በመቶ ደርሷል፡፡
ግንባታቸው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የደሴ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት ለተጠቃሚዎች እንደሚተላለፉ አቶ ቴዎድሮስ አስረድተዋል፡፡
ተቋሙ በኃይል ዘርፍ እያከናወነ ከሚገኘው ዋና ተልዕኮ ባሻገር የማህበራዊ ኃላፊነት ማስፈፀሚያ ፖሊሲ በማዘጋጀት በመላ ሀገሪቱ የማህበራዊ አገልግሎት ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
የቀድሞ ተመራቂዎች ቀጣይነት ላለው የኃይል ዘርፉ እድገት አሻራቸውን ማሳረፍ አለባቸው፤
.........///.........
የቀድሞ የኢትዮጵያ መብራትና ኃይል ባለስልጣን የሥልጠና ኢንስቲትዩት ተመራቂዎች የረጅም ጊዜ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን በመጠቀም በኃይል ዘርፉ ቀጣይነት ያለው መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ላይ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አማካሪ ዶ/ር ምህረት ደበብ ቀድሞ የኢትዮጵያ መብራትና ኃይል ባለስልጣን የሥልጠና ኢንስቲትዩት 762 ባች 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት የባቹ አባላት ባለፉት 40 ዓመታት በኃይል ዘርፉ ለተመዘገበው እድገት እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ልምዳቸውን በመጠቀም ታሪካዊ አሻራ አሳርፈዋል፡፡
እንደሀገር በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ እድገቶችን ለማስመዝገብ የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ተቋማቱ የባለሙያዎችን የውስጥ አቅም በማሳደግ በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እየሰሩ መሆኑን ያብራሩት ዶ/ር ምህረት ለዚህም በመንግሥት እና በግል አልሚዎች በቀጣይ ዓመታት በኃይል ዘርፉ የሚተገበሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ የቀድሞ ተመራቂዎች ልምድና እውቀት ወሳኝ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡
የባቹ አባላት ባለፉት 40 ዓመታት ያካበቱትን እውቀትና ልምድ በጡረታ እድሚያቸውም በተደራጀ መንገድ ለሀገራቸውና ለሁለቱ ተቋማት ሁሉን አቀፍ እድገት ለማዋል ከመቸውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የባች 762 አባላት ቀድሞ ተመራቂዎች በበኩላቸው ተቋማቱ በቀጣይ በዘርፉ ለሚከናውኗቸው የልማት ሥራዎች የበኩላቸውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
የ762 ባች ተመራቂዎች 40ኛ ዓመት የምርቃት በዓላቸውን በተለያዩ ዝግጅቶች አከበሩ፤
…///…
የቀድሞ የኢትዮጵያ መብራትና ኃይል ባለስልጣን የሥልጠና ኢንስቲትዩት የ762 ባች የ1978 ዓ.ም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ተመራቂዎች የተመረቁበትን 40ኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በተለያዩ ዝግጅቶች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት አክብረዋል፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ የቀድሞው የኢትዮጵያ መብራትና ኃይል ባለስልጣን ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ምህረት ደበበን ጨምሮ የመብራት ኃይል ጡረተኞች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ተሾመ መርድ እንዲሁም መምህራንና የባቹ ተመራቂዎች ተገኝተዋል።
የማህበሩ የቦርድ አባልና የዝግጅት ኮሚቴው አስተባባሪ አቶ መኮንን ብርሃኔ እንደገለጹት በወቅቱ ከኢንስቲቲዩቱ 122 የባቹ አባላት በኤሌክትሮ ሜካኒካል ተመርቀው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተመድበው ባለፉት አራት አስርት ዓመታት በኃይል ዘርፉ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
የባቹ አባላት ከኢንስቲቲዩቱ ያገኙትን የንድፈ-ኃሳብ እውቀት መነሻ በማድረግ ከዲዝል ኃይል ማመንጫዎች ጀምሮ በተመደቡባቸው የሥራ ቦታዎች ሁሉ በብዙ ፈታኝ አጋጣሚዎች ውስጥ አልፈው ውጤታማ ሥራ ማከናወናቸውን አብራርተዋል።
ክበረ በዓሉ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ የባቹን አባላት በጡረታና በሌሎች ምክንያቶች ከተቋማቶቹ ቢወጡም ማህበራዊ ግንኙነታቸውን በማጠናከር በዘርፉ የእውቀትና የሙያ ሽግግር እንዲኖር ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የቀድሞ ተመራቂዎች በሥራ ቆይታቸው ያካበቱትን የረጅም ጊዜ ልምድና እውቀት በመጠቀም እንዲሁም ከሌሎች መሰል ማህበራት ጋር ጠንካራ ግንኙነት በመመስረት በቀጣይ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በአቅም ግንባታ፣ በቴክኒክ ድጋፍና በሌሎችም ጉዳዮች በትብብር ለመስራትና ዘርፉን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም አቶ መኮንን ገልጸዋል።
በበዓሉ ላይ የተገኙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የቀድሞ መምህራን የባቹ አባላት ያሳዩት አንድነትና ለኃይል ዘርፉ እድገት ያበረከቱት አስተዋጽኦ የሚያስመሰግንና ለሌሎች ባቾችም አርአያ የሚሆን ነው ብለዋል።
የቀድሞ ተመራቂዎች ባለፉት 40 ዓመታት ለደረሱበት የሙያ ደረጃ፣ ላገኙት እውቀትና ልምድ ኢንስቲትዩቱን፣ መምህራኖቻቸውን እና ተቋማቱን አመስግነዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
በሚቀጥሉት አራት ዓመታት በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ኤሌክትሪክ ኃይል ለማዳረስ ሰፊ እቅድ ተይዟል።
......///........
በመጪዎቹ አራት ዓመታት አብዛኛውን የሀገሪቱን ክፍል የኤሌክትሪክ ኃይል ለማዳረስ የሚያስችል ሰፊ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ።
ሥራ አስፈጻሚው ተቋሙ በጂንካ ከተማ ባካሄደው የ2018 ክረምት በጎ ፈቃድ እና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ጎን ለጎን በኤሌክትሪክ ተደራሽነት ዙሪያ ከዞኑ አመራሮች እና ከማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ ወቅት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአሪ ዞን ተወካዮች እንደገለፁት በዞኑ ከሚገኙ 101 ቀበሌዎች መካከል ኤሌክትሪክ የሚያገኙት 20 ያህሉ ብቻ ሲሆኑ በጂንካ ከተማ ከሚገኙ አምስት ቀበሌዎች ውስጥም ሁለቱ አገልግሎቱ አልደረሳቸውም።
በተጨማሪም በዞኑ በቂ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ባለመኖሩ ምክንያት የስርጭት እጥረት እና የአገልግሎት መቆራረጥ እያጋጠመ መሆኑን በመጥቀስ በቅርብ ጊዜያት የታዩ የጥገና መሻሻሎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ከተወያዮቹ ለተነሱት ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ተልዕኮ የኃይል ማመንጫዎችን፣ የከፍተኛ ማስተላለፊያ መስመሮችን እና የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ኃይልን ከማመንጫ ወደ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ የማጓጓዝ፣ ኃይልን በጀምላ የማቅረብ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ኃይልን ለእያንዳንዱ ቀበሌና ተጠቃሚ ማህበረሰብ የማዳረስ፣ የመስመር ዝርጋታ የማካሄድና የደንበኞች አገልግሎት የመስጠት ኃላፊነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም ከተወካዮቹ የቀረቡት አብዛኞቹ ጥያቄዎች ቀጥታ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስሪያ ቤትን ድርሻ የሚመለከቱ ቢሆኑም አካባቢው በጅምላ የሚያስፈልገውን የኃይል መሰረተ-ልማት ለማሟላት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጥናት ላይ ተመስርቶ ተጨማሪ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመገንባት እና ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ሁለቱ ተቋማት ተቀናጅተው የሚሰሯቸው ስራዎች መኖራቸውን ጠቁመው የቀረቡትን የህዝብ ጥያቄዎች ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚያደርሱና ከሚመለከተው አካል ጋር በቅንጅት በመስራት መፍትሔ ለመስጠት የሚሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ ተደራሽነት 50 በመቶ ገደማ ነው። በመሆኑም በቅርቡ በተሻሻለው የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ማስተር ፕላን መሠረት በሚቀጥሉት አራት ዓመታት ውስጥ አብዛኛውን የሀገሪቱን ክፍል ኤሌክትሪክ ለማዳረስ የሚያስችል ሰፊ እቅድ ተይዞ የውጭ ምንዛሬ የማፈላለግና የኢንቨስትመንትን የማስፋፋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ኢንጂነር አሸብር አብራርተዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
ከትምህርቱ ያገኙትን ዕውቀት ለተቋሙ አገልግሎት ለማዋል ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂዎች ተናገሩ
...///...
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያሰለጠናቸውን የጊቤ 1 እና 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞችን በትናንትናው ዕለት አስመርቋል።
ከተመራቂዎች መካከል በግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽን ባለሙያው አቶ ሳሙኤል ንጉሴ ላለፉት 5 ዓመታት ከሥራ ጎን ለጎን ትምህርቱን በትጋት ሲከታተል መቆየቱን ገልጿል።
በዚህም 3 ነጥብ 84 በማምጣት ከዩኒቨርሲቲው የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የምስክር ወረቀትና የሜዳሊያ ሽልማት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ ዶ/ር አዳነ ወልደመድህን ተቀብሏል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ባመቻቹት የትምህርት ዕድል ንድፈ-ሐሳብን ከተግባር ያቀናጀ ለወደፊት ሥራውም የሚጠቅም በቂ ዕውቀትና ክህሎት ማግኘቱን ገልጿል።
በዕለቱ ከተመረቁ 11 ሴት ሠራተኞች መካከል የሶኮሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬተሯ ወ/ሮ ፋናዬ አዱኛ ባለፉት 5 ዓመታት በንድፈ-ሐሳብ የቀሰመችው ዕውቀት የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራ ለማቀላጠፍ እንደሚያግዛት ተናግራለች።
በትምህርት ቆይታዋ አጋጥሟት የነበረው የእርግዝና ሁኔታ በትምህርቷ ላይ ተፅዕኖ ፈጥሮባት እንደነበር ያወሳችው ወ/ሮ ፋናዬ በመምህራንና በሥራ ባልደረቦቿ ድጋፍ ትምህርቷን በስኬት ማጠናቀቋን ገልጻለች።
የግልገል ጊቤ 1 የጥገና ባለሙያው አቶ የሸዋቀና መልካሙ በበኩላቸው በትምህርት ቆይታቸው ያጋጠሟቸውን ተፅዕኖዎች ወደ ስኬት መቀየር መቻላቸውን ጠቁመዋል።
ከትምህርቱ "ችግር ጠቋሚ ሳይሆን ችግር ፈች ለመሆን፤ በጣቢያው ያሉ ችግሮችን ተናጋሪ ብቻ ሳይሆን አሠራሮችን በአዲስ ቴክኖሎጂ ለመተካት" የሚያስችል ዕውቀት ማግኘታቸውንም ነው ያብራሩት።
የመማር ማስተማር ሂደቱ ከዕለት ተዕለት ሥራቸው ጋር የተገናኘ መሆኑ የቀደመ የሥራ ልምዳቸው በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
ከትምህርት ቆይታቸው ያገኟቸው የንድፈ ሀሳብ ዕውቀቶች በዕለት ተዕለት ሥራቸው ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸውም ተመራቂዎቹ አብራርተዋል።
በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርቱን እንዲከታተሉ እገዛ ላደረጉላቸው አካላት ሁሉ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ተመራቂዎቹ የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ተቋማዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
+7
#2
የድካም ፍሬ፣ የዕውቀት አክሊል!
.....///.....
የጊቤ ማመንጫዎች እና የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የ2018 ምረቃ ስርዓት በምስል
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
+9
#1
የድካም ፍሬ፣ የዕውቀት አክሊል!
የጊቤ ማመንጫዎች እና የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የ2018 ምረቃ ስርዓት በምስል
.....///......
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
ተመራቂዎች ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ የሚቆሙ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ
ተመራቂዎች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እና ለችግሮች በጋራ መፍትሔ በማስቀመጥ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳሰቡ።
ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የኃይል ማመንጫዎች ማስተባበሪያ አንድ ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም ናቸው።
ዳይሬክተሩ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ለተመረቁ የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በወቅቱም ተቋሙ የያዘውን ርዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል እንደሚያስፈልገው ጠቁመው ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ሆነው እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ መቻሉን አቶ አብዱ ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላለው ጥረት እና ለተመራቂዎች ስኬት ላበረከተው አስተዋፅኦም ምስጋና አቅርበዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም በቀጣይ ሠራተኞችን ከማስተማር ባለፈ የኃይል ማመንጫዎችን የምርምር ማዕከል ለማድረግ የሚደረገው የጋራ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ተመራቂዎቹም ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ በጋራ በመቆም እና ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለተሻለ የኃይል አቅርቦት ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተወካይ እና የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር አዳነ ወልደመድህን በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ሀገሪቱ የምትከተለውን የአረንጓዴና ዘላቂ ልማት ግብ እውን ለማድረግ የታዳሽ ኃይልን የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ እየሠራ ይገኛል።
ይህንን ስትራቴጂ መነሻ በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነት ያህልም ላለፉት አምስት ዓመታት ከሥራቸው ጎን ለጎን በፅናትና በቁርጠኝነት በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ መስክ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው የተመረቁትን የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞችን ጠቅሰዋል።
ምርቃት የትምህርት ማብቂያ ሳይሆን የምርምር መጀመሪያ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር አዳነ ተመራቂዎች በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂዎች ላይ የፈጠራና የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን በማምጣት የሀገሪቱን የኃይል ሽፋን ማሳደግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
የተፈጥሮ ታዳሽ ሀብት ወደ ኤሌክትሪክ ተቀይሮ ሀገር እንደሚያበራ ሁሉ ተመራቂዎችም ንድፈ-ሐሳባዊ እውቀቸውን ከሥራ ልምዳቸው ጋር በማቀናጀት ለሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ብርሃን ሰጪ መሆን እንዳለባቸው ዶ/ር አዳነ ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከዩኒቨርሲቲው የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 3.84 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው የተቋሙ ሠራተኛ ሳሙኤል ንጉሴ የሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ ተቀብሏል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
ተመራቂዎች ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ የሚቆሙ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ
ተመራቂዎች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እና ለችግሮች በጋራ መፍትሔ በማስቀመጥ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳሰቡ።
ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የኃይል ማመንጫዎች ማስተባበሪያ አንድ ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም ናቸው።
ዳይሬክተሩ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ለተመረቁ የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በወቅቱም ተቋሙ የያዘውን ርዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል እንደሚያስፈልገው ጠቁመው ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ሆነው እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ መቻሉን አቶ አብዱ ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላለው ጥረት እና ለተመራቂዎች ስኬት ላበረከተው አስተዋፅኦም ምስጋና አቅርበዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም በቀጣይ ሠራተኞችን ከማስተማር ባለፈ የኃይል ማመንጫዎችን የምርምር ማዕከል ለማድረግ የሚደረገው የጋራ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ተመራቂዎቹም ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ በጋራ በመቆም እና ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለተሻለ የኃይል አቅርቦት ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተወካይ እና የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር አዳነ ወልደመድህን በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ሀገሪቱ የምትከተለውን የአረንጓዴና ዘላቂ ልማት ግብ እውን ለማድረግ የታዳሽ ኃይልን የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ እየሠራ ይገኛል።
ይህንን ስትራቴጂ መነሻ በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነት ያህልም ላለፉት አምስት ዓመታት ከሥራቸው ጎን ለጎን በፅናትና በቁርጠኝነት በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ መስክ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው የተመረቁትን የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞችን ጠቅሰዋል።
ምርቃት የትምህርት ማብቂያ ሳይሆን የምርምር መጀመሪያ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር አዳነ ተመራቂዎች በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂዎች ላይ የፈጠራና የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን በማምጣት የሀገሪቱን የኃይል ሽፋን ማሳደግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
የተፈጥሮ ታዳሽ ሀብት ወደ ኤሌክትሪክ ተቀይሮ ሀገር እንደሚያበራ ሁሉ ተመራቂዎችም ንድፈ-ሐሳባዊ እውቀቸውን ከሥራ ልምዳቸው ጋር በማቀናጀት ለሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ብርሃን ሰጪ መሆን እንዳለባቸው ዶ/ር አዳነ ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከዩኒቨርሲቲው የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 3.84 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው የተቋሙ ሠራተኛ ሳሙኤል ንጉሴ የሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ ተቀብሏል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 688
በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የተቋሙ ሠራተኞች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው።
......///......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በመጀመሪያ ዲግሪ ያስተማራቸውን 47 የጊቤ አንድ እና ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በጊቤ አንድ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግቢ ውስጥ እየተከናወነ ይገኛል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 29 የሚሆኑት ከጊቤ አንድ፣ ዘጠኝ ከጊቤ ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እንዲሁም 9 ደግሞ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን የተውጣጡ ሲሆኑ ከአጠቃላይ ተመራቂዎች ውስጥ 11 ሴቶች ናቸው።
ዩኒቨርሲቲው ሠራተኞችን ሲያስመርቅ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን የዛሬ ተመራቂ ሠራተኞች በኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርታቸውን በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራም ለአምስት ዓመታት ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ የኃይል ማመንጫዎች ማስተባበሪያ አንድ ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም፣ የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተወካይ እና የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር አዳነ ወ/መድህን (ዶ/ር)፣ የጣቢያዎቹና የሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ በቦታው ተገኝቶ የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን እየተከታተለ የሚገኝ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን በቀጣይ የሚያደርስ ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
