403
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
#ዶክተር፡ ሄሎ ትላንት ሰርጀሪ የሰራውክ ታማሚ ነህ
#ታማሚ፡ አው ምነው
#ዶክተር፡ ሆድህ ውስጥ መቀስ ስለረሳው ነገ ናና አወጣልሀለው
#ታማሚ፡ እንዴ አሁኑኑ ልምጣ እንጂ
#ዶክተር ፡ አይ ምንም ሚያቻኩል ነገር የለም ለጊዜው ምሰራበት ትርፍ መቀስ አለኝ 😂😂
እኔ ማለት ከቺኬ ጋር እየተሳሳምን💋 ሱሬዬን ልትፈታ ስትል ኖ ኖ ከዚህ በላይ መሄድ የለብንም ብዬ ያስቆምኳት ወንድ ነኝ።
#ብሎ_ነገረኝ ልመነው እንዴ 🤔🤔
#ተ_ረ_ት___#ተ_ረ_ት
ተረት ተረት
የላም በረት
አንድ ሰው ነበረ
በሀብቱ የከበረ
ውልደቱም እድገቱም የሆነ አሜሪካ
ባለው ነገር ሁሉ ጭራሽ የማይረካ
ሲሞላለት ሆዱ 'ሀምበርገሩን' በልቶ
'ጋዴሚት' ይለዋል አልጋው ላይ ተኝቶ።
ተረት ተረት ...
አንድ ሰው ነበረ
በጣም የተማረ
በቃኝን የማያውቅ የጣልያን ተወላጅ
ሁሌም ለአዲስ ነገር ጠዋት ማታ 'ሚባጅ
'ፒዛና ፓስታውን' ጥርግርግ አድርጎ
ይተኛል ጥሩ እንቅልፍ 'ባፋንኩሎ' ብሎ።
ተረት ተረት ...
አንድ ሰው ነበረ
ህልሙ የሰመረ
ጀርመን ነው ሀገሩ
'ምርጥ ዘር' ነው ዘሩ
'ቮግ ቮረስቱን' በልቶ ሞልቶለት አዱኛ
'ሻይሰ' ብሎ ነው ሁሌም የሚተኛ።
ተረት ተረት ...
አንድ ሰው ነበረ
የተመራመረ
ጃፓን ተወለደ
በሮቦት አደገ
ቀን ሲሰራ ውሎ
ሩዙን ቀቅሎ
'ሱሺ' ጠግቦ በልቶ
'ባጋይሮ' ብሎ ያነጋል ተኝቶ።
ተረት ተረት ...
አንድ ሰው ነበረ
አጥቶ የተቸገረ
ኢትዮጵያ ተወልዶ ኢትዮጵያ ያደገ ኩራት ነው 'ራቱ ዛሬም ሆነ ነገ
ቢጠግብም ባይጠግብም ቆሎውን ቆርጥሞ
'ተመስገን' ይለዋል መደብ ላይ ተጋድሞ።
ተረት ተረት ...
እግዜር ከመንበሩ ወደ ምድር ወርዶ
ይጎበኝ ነበረ በየቤቱ ሄዶ
ከእነኚያ ከአራቱ ቆዳቸው ከነጣ
ከየአንደበታቸው መልካም ነገር ቢያጣ
ጥቁሩ ሲያመሰግን የፈለገው ሞልቶ
ያጎደለባቸው አንድ የሆነ ነገር እንዳለ ገምቶ
ሊጨምርላቸው ነጮቹጋ ሄደ አበሻውን ትቶ።
ተረቴን መልሱ
አፌን በዳቦ አብሱ።
© ✍ በሜሮን_ጌትነት
@Hayitiye 🦋
@Hayitiye 🦋🦋
@Hayitiye 🦋🦋🦋
ቃላት አጣውላት
ከእስክሪብቶ ጫፍ ላይ ፤ በሚወጣው ቀለም
ብሶቴን ልወጣ ፤ ህመሜን ለማከም
በነጩ ወረቀት ፤ ከሸንጎ ገትሬያት
በብእሬ ቀለም ፤ ሄዋንን ከስሻት
በቃላት ካቴና ፤ በግጥሜ ላስራት
ከኦረት ዘፊጥረት ፤ እስከ ራዕይ ድረስ
ወንጀሏን ለቅሜ፤ ከመፅሀፍ ቅዱስ
በገላዋ በውበቷ
በቀጭኑ አንደበቷ
የሄዋን ልጅ የሲፖራ
የአዳምን ልጅ ልብ አውራ
ያመጣችበትን አበሳ
በብእሬ ላወሳ
የግጥሜን እስር ቤት ፤ በፊደል ልቆልፈፍ
መያዙአን ሳስታውስ ፤ እናት የሚባል ቁልፍ
ድካሜ ልፋቴም ፤ ሆነብኝ ስንፍና
ቤት የሚመታልኝ ፤ የቃላት ካቴና
እናት በሚባል ፤ ቁልፍ ይከፈታልና
አቤል ታደለ
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 20
✍ እድል
"
"
ዲና ፈጠን ፈጠን እያለች ወደ ሄዋን ክፍል ሄደች። ስትደርስ
ሄዋን አልጋዋ ላይ ተኝታለች የተተከለላት ጉልኮስ ወደ እሷ
ሰውነት ጠብ ጠብ ጠብ እያለ በእርጋታ እየገባ ነው። ዲና ሄዋን
ወደተኛችበት ጠጋ ብላ በአትኩሮት ፍጥጥ ብላ እያየቻት በሀሳብ
ጭልጥ አለች።
ወደ ሀባብ እየተጓዘች ነው። ማን ጋር ለመድርስ ወይም ማንን
ይዛ ለመትመም እንደሆነ አታውቅም የሆነ ሰው ጋር በሀሳብ
ሄዳለች። "እኔስ መቼ ነው ፍቅር ይዞኝ ልክ እንደ አዳም እና ሄዋን
አይነት የፍቅር ህይወት የማሳልፈው?" ብላ እራሷን ጠየቀች
እናም ጓጓች። ፍቅርን በተመለከተ ብዙ ነገሮች አሰበች። እኔስ
እንደ አዳም አይነት አፍቃሪ አገኝ ይሆን? ፤የወደፊት የፍቅር አጋሬ
እንደ አዳም አይነት ፍቅርን ከምላስ ባሻገር በተግባር የሚያሳይ
ይሆንልኝ ይሆን? ወይስ ምን አይነት ሰው ይሆን? አሁንስ የት ምን
እየሰራ ይሆን? እያለች በሀሳብ ክንፍፍ አለች።
በድንገት ሄዋን ከእንቅልፏ ተነስታ መብርቃዊ ድምፆን "ምነው
ተከዝሽ?" በማለት ለቀቀችባት። ዲና ያኔ የቆመችበት መሬት
ከድቷት በድንጋጤ በሩ ጋር ደርሳ ወደነበርችበት ተመለሰች።ሄዋን
ግራ ገብቷት "ምን ሆነሽ ነው?" አለቻት ዲና አይ አይ ዝም ብዬ
ነው። በቃ ተኚ ብላት ውልቅ ብላ ወጣች።
በጥድፊያ አዳም ወደተኛበት ክፍል ሄደች። ክፍሉ ስትደርስ
አዳም አንድ ወርቀት እና ብእር ይዞ አገችው። ብእሩን አፉ ላይ
አድርጎ ለግጥም የሚሆን ቃላት እያሳደደ ነበር። ዲና ድንገት በሩን
በሀይል ከፍታ ገባች አዳም ምን እንደሚሰራ አላስተዋለችም
"ኡፍፍፍ" አለች። አዳም "ምነው?"አላት ዲና በድንጋጤ መንፈስ
ተወኝ ባክህ ቆይ እንዴት ነው የሄዋንን ጩከት የምለምደው?
ዛሬምአስበርገገችኝ"።
"የሆነ ሀስብ ውስጥ ነበርኩኝ። በተናገርችው አንድ ቃል
ምክንያት ልቤ በአፌ ሊወጣ ነበር"።አለችው።አዳም አሁን በጣም
ሳቀ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲ ድምፅ አውጥቶ ሲስቅ ፊቱን
አየችው። ሲስቅ የሚያወጣውን ድምፅ እንኳን ያኔ ጊድዮንን
ለማብሽቅ ሲስቅ ሰምታዋለች። ይሄን ሳቁን አይታ ዲና ፈዛ ቀርች።
ሄዋን በጩከቷ አዳም በፍገግታው አስደንግጠው ልቧንን ቀጥ
ሊያደጉ የተባበሩ መስላት።
አሁን እጁ ላይ የያዘውን ወርቀት እና ብእር አየችው። ዲና ሰፍ
ብላ "ምንድነው?" አለችው አይነኖን ወደ ወርቀቱ ወርዉራ ።
አዳም አሁንም ሳቁን አልጨረሰም ዲና የአዳምን ሳቅ አለመጨረስ
አይታ ፍገግ ብላ "ሳቅ አንተ ምን አለብክ የእሷ ድምፅ እንኳን
በሀሳብ የተዋጠን ሰው ሀሳብ ላልገባውም ስው ስታወራ ልብ
ቀጥ ነው የምታደርገው። በል አሁን ምን እየፃፍክ ነው? እስቲ
አንብብልኝ" አለችው።
አዳም በፍገግታ እና በበራ ፊት "ለሄዋኔ እና ላንቺ ነው ግጥም
የፆፍኩት ብእር እና ሉክ አንድ ዶክተር ሰቶኝ ነው" አላት። ዲና
እስቲ አንብብልኝ ግን ቆይ ከእሱ በፊት የምትነግርኝ ነገሮች አሉ።
ከዛ ግጥሙን ታነብልኛለክ።የምጠይቅህን ጥያቄዊች ሳታንዛዛ
መልስ ስትለው አዳም በአግራሞት እያያት እሺ እመልሳለው
አላንዛዛም ብሎ ፈገግ አለ ዲና እ ጥሩ ስማኝ በደንብ በመጀመሪያ
የምጠይቅህ"
"የበደሉክን ይቅርታ ለመጠየቅ ለምንድነው እንደዛ የምትሆነው
ቆይ ያጠፋው እራሱ ይቅርታ ያለክ እንዲ እንዳንተ ተንበርክኮ
አደለም እኮ። በል ይህንን አስርዳኝ " አለችው። አዳምም
"እይውልሽ ዲና አንቺ ገና ስለ ህይወት አልገሽም"።ሲላት ዲና
"እንዴት?" አለችው በተራዋ እሷ አዳምን ቁልቁል እያየችው።
አዳም ንግግሩን ቀጠለ "የምንኖረው በጣም ጥቂት ጊዜ ነው
ረዥሙን ዘመናችንን የምናሳልፈው በምድር ላይ በኖርናት ጥቂት
ጊዜያት ስለ ሰራነው ፅድቅ ወይም ኩነኔ ስንከፈል ነው የምንኖርው
ታዲያ ለእዚህ አጭር ጊዜ ብዬ ለምን ረዥሙን ህይወቴን ሲኦል
አረገዋለው? ይቅርታ መጠየቅ የትልቅነት እንጂ የትንሽነት
ምልክት አደለም" አላት።
ዲና አዳም በተናገርው ንግግር ድንገት ከሰማይ የወርደ
መላእክት መስላት ምን እንደምትለውም ጠፋባት የእራሷን አስተሳሰብ ጠላችው።
ዲና ቀጠል አድርጋ እሺ በቃ ተወው የፃፍከውን ግጥም
አንብብልኝ ስትለው መጀመሪያ ሄዋን እንዴት እንደሆነች ንገሪኝ ስለ
ጤንነቷ ሲላት ዲና "ኧረ ደና ናት ምን ትሆናለች? እኛን
እያስደነጠች በሽተኛ ታርገን እንጂ" አለችና አዳምን ጠቀሰችው
አዳም ጥቅሻው የቀልድ ነው ምልክት አንደሆነ ገብቶት ፈገግ
አለ።
ዲና "በል ግጥሙን አንብብልኝ" ብላ ለመስማት አኮበኮበች።
አዳምም ግጥም የፀፈበትን ወርቀት አስተካክሎ ማንበብ ጀመረ።
"ነቃችልኝ ፍቅሬ አፅናኝም አገኘው
በፍቅር ስቃጠል ማቀዝቀዣ አገኘው
ነቃችልኝ ፍቅሬ የአይኔ እርሀብ
ስለሜ የሆነች ልክ እንደ ነጭ እርግብ
ውስጤ ተደስተ በሩቡም ተከፋ
ሰምቼ ስለ እሷ ትዝታዋ ሁሉ ባንዴ እንደተደፋ
ኮማ ውስጥ ሆና መንቃቷን ጠቀኩኝ
እስክትነቃ ድርስ በሀሳብ እያለኩኝ
ዛሬ ትነቃለች ነገ ነው እያልኩኝ
በስተመጨርሻ ሄዋኔ ስትነቃ
ጭንቀቴ ናፍቆቴ መሰለኝ ሊያበቃ
ግን ጭራሽ አልሆነም ሀኪሙ አርዳኝ
ከኮማ ስትወጣ ጭራሹን ብትረሳኝ
ግን ደሞ ሳይከፋኝ መንቃቷ ደስ አለኝ
ለማፅናኛ ብሎ አንድ ጀርባ መቺ ፈጣሪ ጣለልኝ
ጀርባዬን መታ አርጋ ካሳብ ያነቃችኝ
ይህቺ ሴት ዲና ነች እንደነገርችኝ
የውስጤን ቁስል ያለብኝን ህመም
ልቤ ለመናገር ጭራሽ አላቅማማም
የሄዋኔን ጩከት መልመድ ቢያቅታትም
ዲና ጓደኛዬ ከእኔ አራቀችም
፨ብሎ ግጥሙን ጨርስ "ይህንን ይመስላል" አላት። ከዛም
አዳምን ዲና ደስስስ ብሏት እቅፍ አርገችና አመስገችው።
በድንገት በር ተንኳኳ "ይግቡ" አለ አዳም ዶክተር ነበሩ አዳም
ሲያያቸው ደስስስ አለው። ስለ ጤንነቱ ከጠየቁት እና ካረጋገጡ
በኋላ ዲናንም ሰላም ብለዋት ወደ አዳም ዞረው ። "አንድ ላንተ
የሚሆን አስደሳች ዜና አለኝ" አሉት። አዳም "ምንድነው ዶክተር"
ብሎ ሰፍ አለ።ዲናም ለመስማት ጓጓች ዶክተሩም ለመናገር
አኮበኮብ ለመናገር የቸኩሉ ይመስላሉ
✨ይቀጥላል......
@Hayitiye 🦋🦋
❤️እወድሀለሁ❤️
ዘመኑ ቢራቀቅ እሳቱ ቢጨመር
ፈታኞች ቢበዙም ቃልኪዳን ቢሰበር
ትውልድ ቢዘምን ቢጨልምም ፍቅር
ሁሉም ነገር ረክሶ ቢቀዬር ወደ አፈር
ቆርቤያለው ባንተ በውስጥህ ልቀበር
❤️እወድሀለሁ❤️
ሰው እኮ ማለት የትውስታና የትዝታ ድምር ነው። ሂወት የመርሳትና የማስታወስ ሚዛን ናት። መርሳት ያለብንን መርሳት ሲያቅተን ሂዎታችን ይመሰቃቀላል። ደግሞ ማስታወስ ያለብንን የሂወት ልምዶች፣ ሰዎችና ነገሮችን ከረሳን የኛነታችን መለያ፣ የስብዕናችን ድንበር ይጠፋና እንዳልሽው ሌላ ሰው እንሆናለን።
@Hayitiye 🦋🦋🦋
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 19
✍ እድል
"
"
አዳም በድንጋጤ ሲጮህ የሰሙት ነርሶች ፣ሃኪሞች፣ መንቀሳቀስ የሚችሉ ታካሚዎች ፣አስታማሚዎች በሙሉ
ተከታትለው ወጡ። ነርሶች ተሯሩጠው ወደ ሄዋን ገቡ። ከዛም በፍጥነት የክፍሉን በር ዘጉት። ለታካሚዎች ፣አስታማሚዎች እና ዘበኞች አዳምን ውርር አደረጉት። ከሩቅ ላያቸው ስኳር ያዩ ቁጫጮች ይመስላሉ። ዘበኞች አዳምን ደጋግፈው ወደ ውጭ ወሰዱት ። አዳም አቅሉን ሳተ "ሰዎች በብዙ ነገሮች ይፈተናሉ ፈተናውን ሊያልፉ አልያም ሊወድቁ ይችላሉ። በፍቅር በሚያፈቅሩት ሰው መፈተን ግን እጅግ በጣም ከባድ ነው። በተለይ ደሞ በከባድ ፍቅር የፍቅር ፈተና በጣም ከባድ ነው"። ጠንካራ፣ ብርቱ፣ አልበገር ባይ ፣ ቻይ የሆነ ስው በፍቅር ሲፈተን ልፍስፍስ ነው።ፍቅር እንኳን ፈተናውን ደስታውን መቋቋም ከባድ ነው። ይህንን ደሞ ሁሉም ተገንዝበዋል የተገነዘቡት ከአዳም ነው። አዳም ሁሉም ነገር አቅቶታል ግን አልሰለቸውም። ጉልበቱ ከድቶት ወደቀ ዘበኞች በፍጥነት ወደ ድንገተኛ ክፍል ወሰዱት የቀሩትም ተከተሏቸው ። ስልኩ ላይ በመጨርሻ የተደዋወለበትን ቁጥር ሊያወጡ ሲሉ ስልኩ የይለፍ ቃል አለው።
ሁሉም ምን እንደሚያድጉ ግራ ተጋቡ አዳም አንገት ላይ ሄዋኔ ብሎ በሚያምር ኢንግሊዘኛ አፆፆፍ የተፃፈ ንቅሳት ከሆስፕታሉ የስነልቦና ሀኪም ውጥ አንዷ የሆነችው ዶክተር ትርሲት "ቆይ ቆይ ምን አልባት አንገቱ ላይ የተነቀሰው ፁሁፍ የይለፍ ቃሉ ሊሆን ይችላል"። ብላ ስልኩን ተቀብላ ስትሞክርው አልሰራላትም። አሁን ክንዱ ላይ በደማቁ ልክ አንገቱ ላይ ባለው የአፃፃፍ ስልት የተፃፈ ንቅሳት አየች። "ይሄ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለው"። ብላ እጁን በአትኩሮት አየችው ቅጥልጥል ፅሁፍ ነው። ቢሆንም ግን ዶክተሮች ይህንን ማንበብ በጭራሽ አያቅታቸውም ሄአድ ኤንድ አድሄ ይላል። ዶክተር ትርሲት የሳይኮሎጂ ሁነኛ ምሩቅ በመሆኗ ስዎች የሚወዱትን ነገር ወይም በውስጣቸው ያለውን የሚገልፅልቻለውን ነገር ከመነቀስ አልፎ የስልካቸው አልያም
የሊላ ይለፍ ቃላቸው እንደሚያደርጉ ታውቃለች። ወዲያው ስልኩ ላይ ያለውን ቃላት አዳም ስልክ ላይ አስፈርችው። ወዲያው ነበር ስልኩ የከፈተው። "ከፈተ" አለች። ፈገግ ብላ ሁሉም በዶክተሯ ጥበብ እና እውቀት ተደመው እርስ በእርሳቸው ይንሾካሾኩ ጀመር። ስልኩን ከከፈተተችው በኋላ ወዲያው መጨርሻ ላይ የተደወለበት ላይ ለመደወል ልትጫን ስትል ስልኩ ጠራ ፈጠን ብላ አነሳችው። "ሄሎ አንተ ገራገር በጣም ነው እሺ ያናደድከኝ ግን በአንተ ስለማልጨክን ምግብ ይዜልክ መጥቻለው ለማንኛውም ሆስፒታል በር ላይ ነኝ ና" አለች። ዲና ነበርች የደወለችው ዶክተሯ ፈጠን ብላ "ይቅርታ የኔ እህት የእዚህ ስልክ ባለቤት እራሱን ስቶ አሁን ድንገተኛ ክፍል ነው" ስትላት ዲና "ዶክተር ትርሲት ነሽ አደል እባክሽ ተንከባካቢው በር ላይ ነኝ
መጣው እኔ ዲና ነኝ ተማሪሽ" አለች።ዲና ዶክተር ትርሲትን ያወቀቻት በድምጿ ነው ድምጿ በጣም ተስረቅራቄ እና የተርጋጋ ነው። እና ስልኩን ዘጋችው። ዶክተር ትርሲት ወዲያው ስልኩን ከዘጋች በኋላ ክፍሉ ውስጥ በግርግር ፣ በድንጋጤ እና ለወሬ የገቡትን ስዎች ከአካሚ ነርስ
እና ዶክተር በቀር ከእነ እራሷ አክተልትላ አስወጣች።
ትንሽ ከክፍሉ እንደራቀች ወፈር ያለ የሴት ድምፅ በሚሮጥ ኮቴ እና በተቆራርጠ ትንፋሽ ታጅቦ ዶክተር ዶክተር ዶክተር ትርሲት ብሎ ጠራት ስትዞር ዲና እየተሯሯጠች ስትመጣ ፍጥነቷ ከእጥረቷ ጋር ተደምሮ የሚንከባለል በርሜል አልያም አንዳች ድቡልብል ነገር ይመስላል። ዲና በመከራ ዶክተር ትርሲት ጋር ደርስችባት እና ዶ ዶ ዶ ዶክተር ትርሲት አዳም ደና ነው? አለች። ዶክተር ትርሲት በአግራሞት እያየቻት ደ ና ነው።አለቻት ዶክተር በዲና እንዲ
መሆን የተገርመች ከመገርምም አልፋ የተደመመች ትመስላለች። ዲና ኩምሽሽ ባለ ፊት እየያየቻት ምን ሆኖ ነው አለቻት ። ተርጋጊ ድንጋጤ እና ሀዘን ተደራርቦበት ነው ። ምንሽ ነው ግን አለቻት። ዲና ፍጠን ብላ የህይወት መምህሬ እና ጓደኛዬ አለቻት። ዶክተር በድጋሜ ግራ በመጋባት ስሜት ውስጥ ሆና ማለት ፍቅርኛሽ? አለቻት። ዲና ኮስተር ፈገግ እያለች "አይ አይ ምነው ስለ አዳም አልስማሽም እንዴ?" አለቻት። ዳክተሯ" ምኑን?" አለች ፈጠን ረጋ ብላ። አዳም ማለት እኮ በፍቅር እየተስቃየ ያለ ስው ነው። "ግን ለምን ይሆን እንዲ የሆነው? ብላ ዲናን ጠየቀቻት የዲናን መልስ
ሳትጠብቅ ቀጠል አድጋ ነገሩ በፍቅር እንደተነደፈ ያስታውቃል" አለች። "ምን እንደተፈጠር ንገሪኝ" አለች ዲና ወደ ዶክተሯ ሽቅብ እያየች ዶክተሯም ዲናን አዘቅዝቃ እያየቻት "ብዙም ባይገባኝም
ልንገርሽ" ብላ የተፈጠርውን አጠር አድርጋ በተርጋጋ አንደበት አስርዳቻት። ዲና ድርቅ ብላ ቀርች በዶክትር ብልሀት ተገርመች በአዳም ስቃይ ውስጦ ታመመ ዲናም በተራዋ ስለ አዳም ነገርቻት ዶክተሯ እዚህ ባልነበረችበት ጊዜ ስለተፈጠርው ነገር ዲና ስትነግራት እጅግ አዘነች። ዲና ቀጠል አድርጋ "ዶክተር ትርሲት ግን ወዴት ሄደሽ ነው የጠፋሽው?" ስትል ጠየቀቻት። ዶክተርም
"አንድ ህንድ ውስጥ ስራዬን በተመለከተ የምወስደው ኮርስ ነበር። ዛሬ ከስአት ነው ስራ የጀመርኩት። ዶክተር ግሩምንም አላገኘዋቸውም ስትል" ዲና ፈጠን ብላ "እይ አሉ ለሶስት ቀናት
ግን አልመጡም" ስትላት። አዎ አዎ ልክ ነሽ እሳቸውም ወዴት እንደሆነ ባላቅም በረራ አድርገዋል አለቻት። "ዲና እ በጣም ጥሩ ሰው ናቸው። የሄዋን የስነልቦና ሀኪም ናቸው"። አለቻት ዶክተሯም እውነት በጣም ደስ ይላል ሜንታል ዶክተሯ መሆናቸው ምርጥ ነው። እና ፊዚካል ዳክተሯስ ማነው ስትላት ዲና "ለጊዜው እየተፈራርቁ ነው የሚያክሟት። ግን ዶክተር በሜንታል እና ፊዝካልነት ስለሚስሩ እሳቸው ባሉበት ስአት ሄዋንን
ያግዟታል እና ደሞ ያክሟታል" አለቻት።
ዶክተር ትርሲትም በስማችው የአዳም ስቃይ እጅግ አዘነች። እዛ ሆስፒታል ውስጥ ያሉ ሁሉ ይተዋወቃሉ አፓርንት የወጡት፣ ዶክተሮች ፣ዘበኞች ፣የሆስፒታሉ የምግብ ሰራተኞች ልክ እንደ ጓደኛ ናቸው። በጭንቅላት እንጂ በስልጣን የማያምኑ ለእዛም ነው። ዲናና ዶክተሯ እንዲ ቁጭ ብለው እንደ ስራ ባልደርባ ሊያወሩ የበቁት።
እንደውም ያ ባለጌ ዶክተር ከሁሉም የተለየ ስርአት ያለው ስለእሱም ዲና ለዶክተሯ ነገርቻት። አዳም ባላጠፋው ጥፋት ይቅርታ እንደጠየው እና ይቅርታ ለምን ትለዋለክ ብላ ስትጠይቀው ይቅርታ የጠየቀበትን ምክንያት እንዴት እንዳብራራላት። ስለ ሄዋን ጩከት ባጭር ባጭሩ ነገረቻት እጅግ አስደመመቻት።
ዶክተር ትርሲት አዳም ሲያገገም ልታናግርው እንደምትፈልግ ነገርቻት ቀጥላም ለዲና እንዲ አለቻት እንደ ነገርሽኝ ከሆነ እሱ የስነ ልቦና ሀኪም ሳያስፈልገው እርሱን ስላጠነከር ሜንታል
ዶክተር ባያስፈልገውም ስለ አለባበሱ እና ሄዋንን እንዴት መቅርብ እንዳለበት እንዲያውቅ እርዳዋለው" አለቻት። ዲና ደስስስ አለት። እኔን ቤቱን አምኖ እንድኖር ላርገኝ እና ለውስጤ ጥንካሬን ስጥቶ ፍቅርን እና መውደድን ኑሮ እና ህይወትን ላስተማርኝ ምንም አደርግለታለው ስትል ዶክተርም አዎ እየተጋገዝን ከእዚህ ችግር እናወጣዋለን ተባባሉ።
✨ይቀጥላል.......
@Hayitiye 🦋🦋
ዛሬ ቅዳሜ ነው ፣ ይሄን ሁሉ ያውቃል
"አደረች አራዳ" ፣ ዘፈን ይለቀቃል
አሳዳሪ አራዳ ፣ አልጋቤቱ ያልቃል
ነይና ላሳይሽ
ቅዳሜ ብቻውን ፣ ለሳምንት ያስቃል
።።።
ዛሬ ቅዳሜ ነው
በየ መጠጡ ቤት ፣ ገርበብ ያሉ ጭኖች
በየ ጎዳናው ላይ
ቆንጆ ሴት የጫኑ ፣ ዘመናይ መኪኖች
በየ ፋርማሲው ቤት
ፅንስን የሚያመክኑ ፣ እንክብል ኪኖኖች
የሚቸረችረው
እሽግ እሽግ ብሮች ፣ የሚዘረዝረው
አደንዛዥ እፆችን ፣ የሚያዘዋውረው
ከባለትዳር ጋር ፣ የሚያመነዝረው
እንደ አሸን ይፈላል ፣ እንደጉድ ይበዛል
ፌስቡክ ላይ ምታውቂው
አውቀሽ ምታደንቂው
ባልኮል አቅሉን ስቶ
ፓስት የሚያደርገውን ፣ ሚሪንዳ ይገዛል
ሰክሮ ሚንገዳገድ
"ይህች ሀገር ወዴት ነው
ምትሔደው ?" እያለ ፣ መጠየቅ ያበዛል
።።።
ነይና ላሳይሽ
ሁሉ በመሐላ ፣ እውነትን ይገድላል
አንዳንዱ ሀገር ወዳጅ
የራሱ እያረረ ፣ የሰው ያማስላል
"እስራኤል ፍልስጤም"
የሚል ጎራ ከፍሎ ፣ እርስ በርስ ይጣላል
ነይና ላሳይሽ
ቅዳሜ ብቻውን ፣ አንድ ሀገር ያክላል።
።።።
ነይና ላሳይሽ
"ጨዋ የሚባል ህዝብ ፣ ጠፍቶት ትርጓሜ
"ቀሚስ" የሚባለው
የት እንደደረሰ ፣ አጥሮ እንደጷግሜ
የዚች ሀገር ጉዞ ፣
ወዴት እንደሆነ ፣ መልስ አለው ቅዳሜ።
።።።
ነይና ላሳይሽ
በአልኮል ባህር ላይ ፣ የመረብ አጣጣል
መንግስት አልወርድ ያለው
ውስኪ እያወረደ ፣ ሴት ከቦት ይጠጣል
ጨፋሪው ብዙ ነው ፣ አያስጥልም ጠጠር
ጎንበስ ላሉት ጡት ፣ ቀና ላሉት ከንፈር
ያለአንዳች ክፍያ ፣ ነፃ ይታደላል
ሰክሮ ሚንገዳገድ
"ይህች ሀገር ወዴት ነው ፣ የምትሔደው ይላል?
።።።
ሁሉ እየተነሳ
ከመስከሩ ብዛት ፣ መንገድ እየረሳ
"ይህች ሀገር ወዴት ነው
የምትሔደው?" ብሎ ፣ መጠየቅ ቢወድም
ነይ መልሱን ላሳይሽ
ወደ አልጋ ቤት እንጂ ፣ ወዴትም አትሔድም!
።።።።
ዛሬ ቅዳሜ ነው!
አደረች አራዳ ፣ ዘፈን ይለቀቃል
አሳዳሪ አራዳ ፣ አልጋ ቤቱ ያልቃል
አካሔድ የጠፋው
ይች ሀገር ወዴት ነው ፣ የምትሔደው ብሎ ፣ ሁሉን ይጠይቃል
ይወደሳል ጋባዥ ፣ ያወድሳል ጠጪ
ነይና ላሳይሽ
ቅዳሜ ከቀረሽ ፣ ዘልአለም አትምጪ!
#እድል
@Hayitiye 🦋🦋
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፋል 18
✍ እድል
"
"
አዳም ካሸለበበት የነቃው የትናትናዋ ነርስ የሄዋንን ግሉኮስ ማለቅ እና አለማለቁን ለማጣራት ስት መጣ ነው። ያኔ አዳም ነርሷን ሲያያት የትናንቱ ትዝ ብሎት ሳቅ ፈገግ አለ።
ነርሷም ፊቱን ስታየው ገብቷት ፈገግ አለች። ነርሷ የሄዋንን ግሉኮስ ቀይራላት በፍጥነት ወጣች። አወጣጧ በድጋሜ የሄዋንን ድምጽ ላለመስማት ይመስላል። ነርሷ ለመውጣት ስትጣደፍ በሩን በሀይል ጓ ስታደርገው ሄዋን በርግጋ
ተነሳች ከዛ ምንም ሳትናገር መልሳ ተኛች። ነርሷም ውልቅ ብላ
ሄደች።
ሄዋን በድንገት ማቃሰት ጀመርች እእ እህምምምም እምምምም
ወይኔ ኧረ ወይኔ ማለት ጀመርች። አዳም ወደ እሷ ጠጋ ብሎ "ሄዋን ሄዋን ሄዋን ደና ነሽ ሄዋን ምን ሆንሽ እእእ" አላት
በድንጋጤ ሄዋን ቆይ ቆይ ቆይ ቆይ ቆይ ኡፍፍፍፍ አለች። ልክ እንደ መገላገል ብላ አዳም ደንግጦ "ምንድነው?" አላት። "ደና ነኝ ዶክተሩ አንዳንዴ እንዲህ ሊያደርገኝ እንደሚችል ነግሮኛል" አለች።
አዳም ክው ብሎ "መቼ?" አላት። ሄዋንም ከተኛችበት ለመቃናት እየሞከረች "ለሊት መጥቶ ነበር አንተ አልስማከውም" አለችው። አዳም "እእእ የትኛው የባለፈው?" ሲላት ሄዋን ኮስተርም ፍገግም እያለች "አይ አይ የሆነ ትልቅ
ዶክተር ነው ከ እዛ ባለጌ በፊት አንዴ አክመውኛል" ስትለው የአዳም ፊት አበራ ልክ እንደ ነፀብራቅ። "ዶክተር ወደ ስራ
ተመለሱ ማለት ነው?"ብሎ በውስጡ ደስስስ አለው። በደስታ ፈነደቀ ።
የክፍሉ በር ተንኳኳ አዳም "ይግቡ" አለ። በሩን ገፋ አድርገው ዶክተር ያንን ባለጌ ዶክተር ይዘውት ገቡ ያባለጌ አንገቱን ደፍቶ እንዳቀረቀረ ዶክተር "ሰላም አዳም እና ሄዋን ዛሬ ይህንን ዶክተር ይዤው የመጣውት ይቅርታ እንዲጠይቃቹ ነው"። አሉና ወደ ዶክተሩ ዞር ብለው በል ጀምራ አለት። እየተንቀጠቀጠ እኔ እኔ ማለቴ እኔ ያው ባለማወቅ ነው ያደርኩት ይቅር በሉኝ ባለማወቅ ነው። አለና ረዥም ትንፍሽ ተነፈሰና አይን አይናቸውን እያፈራረቀ
ይቅርታቸውን ይለምን ጀመር። ሄዋን ሳቅ ብላ "የሰው ልጅ ያጠፋል ያጠፋውን ካመነ ደሞ ትልቅ ነገር ነው ከእዛም አልፎ ይቅርታ ካለ ደሞ እጅግ በጣም ጥሩ ነገር ነው። እኔ በበኩሌ ይቅር ብዬካለው" አለች። ሄዋን ነገሮችን አለማከበዷ ሁለቱንም ዶክተሮች አስገርሞል። አዳም ግን ምንም አልተገርመም ምክንያቱም ድሮም ፀባይዋን ያውቀዋል። እሺ አንተስ አዳም አሉ ዶክተር። አዳምም እኔም ይቅር ብዬዋለው እንደውም የስራው ስራ ባለማወቅ ሆኖ እኔ ግን ስህተት መሆኑን ሳለናግርው ሰለ ደበደብኩት ይቅር ይበለኝ ብሎ ተንበርከከ
እንዲ እያወሩ ዲና ቁርስ ቋጥራ በእጇ ይዛ ገባች ዲና ያየችውን ማመን ተሳናት።
አዳም ተንበርክኮ የበደለውን ዶክተር ይቅርታ እየጠየቀ ነው። ዲና ሳታስበው ንዴት ቦግ አለባት። "አዳም" አለች ጮክ ብላ አዳምም እንደተንበርከከ ሽቅብ ዲናን እያያት ወዬ አላት በተረጋጋ አንደበት። ዲና ንዴቷ እንደጦፈ ለምን
እንደተንበርከከ ጠየቀችው አዳምም ከእንብርክኩ ሳይነሳ ረጋ ባለ ድምፅ "ዛሬ ወንድሜ ተፀፅቻለው ፤ላጠፋውት ነገር ይቅር በለኝ" ሲለኝ ፊቱ ላይ ያየውት የልመና ገፅታ በጣም አሳዛኝ ነው። ከዛም
እኔ ውስጤን አመመኝ ባልመታውት ኖሮ ብዬ ምክንያቱም ይህ ሰው ያጠፋው ባለማወቅ እንደሆነ ስላወኩኝ ባለ ማወቅ የሰራውን ስራ እኔ በመንገር ፈንታ ስለመታውት ይቅርታ እየጠየኩት ነው"አለ።
ዲና አይን እና ጆሮወዋን ማመን ተሳናት። "አንተ ቆይ ምን አይነት
ሰው ነክ እእእ የምር መላክ ነክ? ወይስ ሰው ። እንደዛ አናዶክ ባደርክበት ነገር እንዴት ይቅርታ ትለዋለክ? እ መልስልኛ" አለች ፍጥጥ ብላ። አዳምም "አትናደጂብኝ ዲናዬ ይቅርታ መጠየቅ የትልቅነት እንጂ የትንሽነት ምልክት አደለም። ቢሆንም ደሞ ትንሽ ልሁን ተመልከች እስቲ እንዴት ፊቱን እንዳበላሸውት አይተሽዋል? እኔ ስለደበደብኩት በፊቱ ህመም ምክንያት አይተኛም ሰላም አይሰማውም በመንገድ ሲሄድም በፊቱ ምክያት ይሸማቀቃል።
እኔን ግን ተመልከች ፊቴ ላይ ምንም የለም አሁን ላይ እንኳን ከፍተን ደግ ሆነንም አለም ከንቱ ናት። ስለዚህ ዲናዬ እንደዛ ስለማይሻል እንደዚህ ይሻላል ብለን መኖርን እንቀጥል" አለ።
"ትስማኛለክ አሁኑኑ አሁን" አለች ዲና በጩከት ደንገጥ ብሎ ዶክተሩን ሽቅብ ሲያየው እንዲነሳ ነገረው። አዳምም ተመስገን ብሎ ተነስቶ አቅፈው ተቃቀፉ
ሄዋን ተኝታለች። ከዛም ሁለቱ ዶክተሮች ተከታትለው ወጡ። ዲና ምንም ሳትለው ቁርሱን ስታው ወጣች። አዳምም ወዲያው እጁን ታጥቦ ዲና
ያመጣችለትን ፍርፍር በላ። "ኣ የሆነ የዘነጋውት ነገር አለ"። አሁን አስታወሰ ለሄዋን ስለ ታሪካቸው መናገርን ነበር እንዴት ይህ ይረሳል ብሎ እራሱን ጮክ
ብሎ ሄዋንም ከተኛችበት ተነሳች።
አዳምም ረጋ ባለ ድምፅ ዛሬ ነው እነግርሻለሁ ያልኩሽን የምነግርሽ ዝግጁ አላት። አዎ ንገርኝ አለችው። እሺ ብሎ
መናገሩን ለመጀመር ኡፍፍፍፍፍ አለ።
ሄዋን በጉጉት መተንፈስ ፍጥጥ ብላ አይኑን ማየት ጀመርች።
የአዳም ስልክ ጠራ ዲና ነበርች። "ሄሎ" ሲላት ነገ ትምህርት ስለምጀምር እርፍት ያስፍልገኛል ስለዚህ አልመጣም ብላ ጆሮው ላይ ዘጋችው። አዳም ርብሽ ስላለኩ ፊልም እንይ ከዛ እነግርሻለው" አላት። ከዛም በአዳም ስልክ ለ4 ስአታት ሙሉ ፊልም ሲያዩ ቆዩ። ከዛም ንገረኝ ብላ ስታስጨንው መናገር ጀመር። የምነግሽ የፍቅር ታሪክ ነው።
እኔና ይህቺ ሴት የተዋወቅነው ካንፓስ ነው። እንዳየዋት ነው የወደድኳት ብሎ አይኑን ጣራ ላይ ጠመደው ሄዋንም እንደ ዲና ጉጉ ናት እ ከዛስ አለችው። የወደድኳት በእዚህ ምክንያት ነው ብዬ አልነግርሽም ምክንያቱም እንዳቀለልኳት ይስማኛል። ሳያት አለም ሙሉ ትሆናለች፣ሁሉም ሰው ጥሩ ይሆናል፣ ደስተኛ እሆናለው ብዬ ለእራሴ ሳላሳምነው ደስተኛ ሆንኩኝ እያለ አጠር አጠር ባለ መልኩ እስከ መኪና አደጋው ነገራት ልዩ ሴት ናት ብሎ ዝም አለ። ስለ እርሷ መናገር ተሳነው ሄዋንን አያት በጣም ደነገጠ የተሰካላት ጉሉኮስ አየር ስቦ ደሟ ወደ ላይ ወደ ግሉኮስ ቀርጢቱ እየተዘዋወር በቀርጢቱ እሩብ ሆኖል አዳም ነርስ ዳክተር ነርስ እር ድርሱልኝ ሄዋኔን አትርፉልኝ ፍቅሬሬሬሬ ህይወቴ እያለ ቀወጠው።
✨ይቀጥላል.....
@Hayitiye
ትቆያለች ሃይሏ ተማጦ" አለች።
አዳም ዲናን "ውይ አንቺ ገና በደንብ ሳታውቂያት ሰለቸችሽ?"
ሲላት ፈገግ ብላ "ኧረ በጭራሽ እንደውም ከእሷ ከጩከቷ
በስተቀር የፍቅር እመቤት ስለመሆን እና ስለ ጥሩነቷ ቀርቤ
መማር እፍልጋለው ጩከቷንም በመጠኑ እንድታርግ እርዳታለው"
አለች። አዳም በለው በለው በይ አሁን ቤት ሂጂ እና እርፍ በይ
ጠዋት ስተመጪ ቁርስ ይዘሽልኝ ነይ አላት ዲና ግን አይይ ብላ
ደርቀች አዳም ደሞ ከእሷ የባስ ደርቅ ስለሆነ እንድትሄድ አደርገ።
እሱም የአስታማሚ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ ሄዋንን ሊስላት
በሚመስል መልኩ ረዥም ስአት ሲያያት ቆይቶ ሳያስበው
እንቅልፍን አሸለበው።
✨ይቀጥላል......
@Hayitiye 🦋🦋
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 17
✍️ እድል
""
""
አዳም" ያስብኩት እንዳይሆን አምላኬ" ሲል ዲና በጭንቀት ፊት
እያየችው "ምንድነው ያሰብከው?" አለችው አይኗን ፍጥጥ አርጋ
አዳም በንዴት እየተንቦገቦገ በተቆራርጠ ድምፅ ጌ ዲ ዮ ንንንን አለ።ዲና በድንጋጤ "ምን?" አለች።
አዳም አዎ ልክ እንዲ የምትደሰችበት ቀን መጥቶ ሲያጠቃሽ ነው
ደስ የሚለው አለ።ዲና ክው ብላ ቀርች። አዳም ድምፅ አውጥቶ
ማልቀስ ጀመር። ጊዲዮንን በሀዘኔ ጊዜ አልፈራውም የምፈራው
ጊዜ በደስታዬ ነው። ለእኔ አደለም የምፈራው ለምወዳቸው ነው።
እያለ በጣም ከፍ ባለ ድምፅ ተንሰቀስቀ።
ዲና አዳምን ጠራችው እና ተመልከት እዛ ጋር አለችው። አዳም
የሚያየውን ማመን ተሳነው። ሄዋን በእግሯ ቆማ መሄድ
ጀምራለች አጠገቧ አንድ እንዳትወድቅ የደገፍቻት ነርስ አለች።
የሄዋን ቅላት ከበፊቱ በልጧል ከስታለች ፀጉሯም እንደተለመደው
ዝብርቅርቁ በወጣ መልኩ እንደ ወጉ ተይዞአል። አዳም ኡፍፍፍፍ
ተመስገን አምላኬ አለ ድምፁን ለስለስ አድርጎ።
ሄዋን ወደነሱ በቀርበች ቁጥር ፈገግ እያለች ነበር። ልክ እነሱ ጋር
ስደርስ ደሞ ባሰባት ወደ ዲና እያየች "እህቴ አለቻት" ዲናም
"ወዬ ማሬ በእግርሽ መቼ መሄድ ጀመርሽ?" አለቻት። ሄዋንም
አገጯን ወደ አዳም እየጠቆመች "ይሄ ሰውዬ ጥሎኝ ሲሄድ ውሀ
ፈልጌ ነበር ልነሳ ስጣጣር ነርሷ መጣች ከዛም እንድነሳ እርዳችኝ
እና ውሀ ከስጠችኝ በኋላ ዳክተርን አስፈቅዳ ወክ እንዳርግ
እርዳችኝ" አለቻት።
ዲና ወደ አዳም ዞራ በቀስታ "አንተ ዛሬ ደሞ ፈታ ብላልካለች"
አለችው። አዳም "አዎ ደስ ብሎኛል በጣም ግን ከስታለች" አላት።
ዲናም "አይ አንተ ደሞ ህክምና ላይ ነው እንጂ አራስ ሆና
ለመታርስ አደም እኮ እዚህ ያለችው" ብላ ፈገግ አስባለችው
እሷም ፍገግ አለች።
ሄዋን በእጇ የያዘችውን የግሉኮስ ማንጠልጠያ ብርት ከእነ
ግሉኮሷ እየገፋች ወደ እነሱ ጠጋ ብላ በሉ አሁኑኑ ተንሾካሽኮቹ
የሳቃችውበትን ንገሩኝ አለች። ፍጥጥ ብላ አዳም ይህንን
ፀባይዋን ያቀዋል ሄዋን መንሾካሾክ በጭራሽ አትወድም
እንደውም የሆነ ጊዜ "ሰው ለምን ድምፁን ቀንሶ ይንሾካሾካል
የሚንሾካሾከው ለማውራት የማይመች ወይም ያልተፈቀደለት ባታ
ስለሆነ ነው መቼስ ስለዚህ አለማውራት ነው በቃ" ያለችው ትዝ
አለው። ይህንን ያለችው ላይብረሪ ገብተው በሹክሹታ እንውጣ
ስላላት ነው። አዳም ይህንን ቀን አስታውሶ ፈገግ አለ።
ሄዋን ዲናንን ለምን እንደሳቃቹ ንገሩኝ እያለች እየጎተጎተቻት ነው።
ዲናም "እሺ በቃ" ብላ የተሳሳቁበትን ብቻ ነገርቻት ሄዋን ያኔ
የማያባራ ልክ እንደ መብርቅ የተንቦገቦገ ሳቋን ለቀቀችው። ነርሷ
በድንጋጤ ደርቃ ቀርች ከድንጋጤዋ ስትነቃ ልትሮጥ ምንም
የማይቀራት ደርጃ ላይ ናት ። ዲናም ደንግጣለች አዳም ስለ ሄዋን
መብርቃዊ ሳቅ መናፈሻ ቦታ ሄደው ግጥም ከገጠመላት በኋላ
ተኮሳትራበት ከዛም ሲደነግጥ የሳቀችበት እለት መናፈሻ ቦታ
ያሉትን ሰዎችን ቀልብ እንደሳበ ቢነግራትም እንዲ ነው ብላ ግን
እንኳን ማሰብ አለጠርጠርችም። ዲናና ነርሷ ተያይዘው ቢሮጡ
ደስታቸው እጥፍ ድርብ ነው።
አዳም ይህንን ጩከት ስለለመደው ምንም አልመስለውም
እንደውም ዲናና ነርሷ ላይ ባየው የፊት ሁኔታ ሳቅ ተናነቀው።
እጁን በአፉ ጭኖ ሽቅብ እያየ ሳቁን ለመቆጣጠር ጣረ ሄዋን
የሁሉንም ፊት እያፍራረቀች አየች ዲናና ነርሷ እንደዛ ኩምሽሽ
ብለው ሳለ የአዳም ፊት ለፈገግታ እንዴት እንደዳዳው ግራ ገባት።
"ምነው እእእ ችግር አለ?" አለች አንገቷን ወደ ዲና ጃሮ አስጠግታ
በጩከት በእሷ ቤት ግን ድምፆን ቀንሳ ማውራቷ ነው። ዲና
ጃሮዋን ያዘችው።
አዳም ሳቁን እንዳፈነ ጨርሰው ዲናና ነርሷ ግን ድንጋጤያቸውን
የጨርሱ አይመስልም። ሄዋን ለምን እንዲ እንደሆኑ ብጠይቅም
መልስ አጣች ከዛም ነርሷ "አይ ምንም አደለም ነይ ክፍልሽ
ላስገባሽ" ብላ ይዛት ገባች። አዳም ዲናን አያት አሁንም ክው
እንዳለች ነው። ፊቷ ላይ እጁን እያውለበለበ ንቂንቂ አላት እና
ፈገግ አለ። ዲና "አንተ ቆይ ምንድነው ድምጿ በስመአም ኧረረረ
መቼም አለምደውም እና ደሞ ስታወራስ ጩከቷ መች ይለመዳል
በድንጋጤ ልቤን ቀጥ አድርጋ ልደፋኝ ነበር እኮ" አለች አዳምም
"በይ ልመጃት እኔም ለምጄው ነው" አላት። ዲና በአግራሞት
"ወይ የፍቅር ሀይል ይገርማል ስንቱን ያስለምደናል አሁን ይሄ
የሚለመድ ድምፅ ነው እውነት?" አለች። አዳም "ኧር በቃ
አካበድሽው እንደውም ሳቋ ነው እንጂ ድምፆን ቀንሳው ነው"
አላት። ዲና "ምን ጭራሽ ተቀንሶ ነው ውይ በስመአም አሁን
መብርቅም ጮከ ይባላል?። እኔ ደሞ ምን መአት መጣ ብዬ
ድምጿ የሞተን ያስነሳል ያውም አስበርግጎ ተመልከት እስቲ
እነዚህን አስታማሚ እና ታካሚዎች በርግገው እንዴት እንደወጡ"
ብላ ክፍሎቹን እየጠቆመች አሳየችው አዳም አላስተዋለም ነበር።
ሁሉም ምን መጣ ብለው በር በራቸውን ከፍተው ለወሬ
ተስገብግበው ተኮልኩለዋል። አዳምም የፈጣሪ ያለ ውይ ብሎ
ይቅርታ ይቅርታ በእየ ክፍላቹ ግቡ በስህተት እና ባለማወቅ ነው
ብሎ ሁሉንም በጅምላ ይቅርታ ጠየቃቸው። ሰዎችም
እየተነጫነጩ ወደእየ ክፍሎቻቸው ገቡ።
አዳምና ዲናም ወደ ሄዋን ክፍል ገቡ። ሄዋን አልጋዋ ላይ
ተመቻችታ ተኝታለች። ነርሷም የሄዋንን ብርድ ልብስ በማስተካከል
ላይ ናት። አዳም እና ዲናም ነርሷን ትክ ብለው እያዩዋት ነው።
አስበውበት ሳይሆን እንዳጋጣሚ ነርሷ አልጋ ለማስተካከል
ካቀርቀርችበት ቀና ስትል አፍጥጠውበታል ክው ብላ "ምነው"
አለች። ዲናም ምንም ሳሪዬ በድንገት ነው ብላ ሳቀች። ነርሷም
እሺ ብላ ከክፍሉ ውልቅ አለች።
አዳምም ዲናን "ታቂያታለሽ እንዴ?" አላት ዲናም አዎ "እንዴት
አላውቃትም አንድ ጊቢ እየዋልን" ስትል። አዳም ቀጠል አድርጎ
"እና ቅድም ለምን ስላም አላልሻትም ቆይ" አላት። ዲና
እንደመሳቅ ብላ "አይ አንተ የደላክ በየት በኩል ሰላም እላታለው
መች ጊዜ አገኘው"አለችው አዳም ሀሀሀሀሀ ለነገሩ ልክ ነሽ
አላት።
ሄዋን "ምኑን ነው ልክ የሆነችው" ስትል ዲና በድጋሜ በርገገች።
አዳምም "አይ ምንም በድምፅሽ ጩከት ማለቴ በሳቅሽ
ደንግጠው" ነው አላት። ሄዋን በአግራሞት አሀ ለእዛ ነዋ ብላ
በድጋሜ ያንን ሳቋን በትንሹ ደገመችው። አዳም ሄዋን ማለት
1+1=2 ብትባል ሁላ ከልቧ እንቦዋ እስኪርግፍ የምስቅ
እንደሆነች ስለሚያውቅ አልገርመውም። ዲና ግን አግራሞት ላይ
ናት።
አዳም ወደ ሄዋን ጠጋ ብሎ ነርሷ ያስተካከለችላት ብርድ ልብስ
በድጋሚ እያስተካከለላት "በቃ ተኚ ነገ የሆነ ደስ የሚል ታሪክ
እነግርሻለው እሺ እና ደሞ ውሀም ከጠማሽ ከአሁን በኋላ እኔ ነኝ
የምሰጥሽ እሺ" ብሎ ፈገግ አለላት ዲና አሁንም ሄዋን ሳቋ
እንዳይመጣ ፈጣሪዋን በመለመን ላይ ናት። ሄዋንም "እሺ ደስ
ይለኛል እስቲ አሁን ትንሽ ንገረኝ" አለችው ጉጉ እንደሆነችም
ያውቃል ግን እንደምንም ነገ እነግርሻለው ብሎ አሳምኗት ተኛች
ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰዳት።
አዳም "ተኛች" ሲል ዲና "እና ድሮስ እንደዛ እንደመፈክር
እየጮከች እያወራች እና እየሳቀች ምን አቅም ኖሯት ሳትተኛ
