ch
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

前往频道在 Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

显示更多
637
订阅者
无数据24 小时
-37
-1230
帖子存档
❤ "በስመ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ኅዳር ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን #ለሰው_ወገን_ለሚያዝንና_ለሚራራ በእግዚአብሔር ጌትነት ፊት ሁልጊዜ በመቆም ለፍጥረት ሁሉ ለሚማልድ #ለመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ሚካኤል_እስራኤልን_ከግብፅ_ባርነት ሲወጡ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋር በሆነ ሕዝብ በመንገዳቸው ሁሉ እየመራ የኤርትራ ባሕር ለከፈለበት፣ #ለነዌ_ልጅ_ለነቢዩ_ለቅዱስ_ኢያሱ ለተገለጠለት፣ #ዱራታዎስና_ሚስቱን_ቴዎብስታ_ለረዳበት_ዓመታዊ_በዓልና #ለኢትዮያዊው_ንጉሥ #ለጻድቁ_ለዐፄ_በእደ_ማርያም_ለዕረፍቱ መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከመጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ ራሱ በደብረ ማህው ከታየችበት፣ ከእስክድርያ ስልሳ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳስ ከቅዱስ አባት #ከአባ_ፊላታዎስ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                  ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን #ለሰው_ወገን_የሚያዝንና_የሚራራ #በእግዚአብሔር_ጌትነት_ዙፋን_ፊት_ሁልጊዜ በመቆም #ለፍጥረቱ_ሁሉ_የሚማልድ_የመላእክት_አለቃ በሰማያትም ለሚኖሩ ኃይሎች ሁሉ አለቃቸው ለሆነ #ለቅዱስ_ሚካኤል_የበዓሉ መታሰቢያ ነው። ❤ ይህም በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በታላቅ ክብር ሁኖ የነዌ ልጅ ኢያሱ ያየው ነው "ከእኛ ሰዎች ወገን ነህን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ?" አለው። "እኔስ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ አሁንም ወዳንተ መጥቻለሁ" አለው። ኢያሱም ወደ ምድር በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደለትና "በእኔ በባሪያህ ዘንድ ምን አቁሞሃል?" አለው። የእግዚአብሔር የሠራዊቱም አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ኢያሱን "የቆምክባት ምድር የከበረች ቦታ ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅ" አለው ኢያሱም  እንዳለው አደረገ። እግዚአብሔርም ኢያሱን እንዲህ አለው "በውስጧ ያለውን ንጉሷን ከኃያላኑና ከአርበኞቹ ጋር በእጃችሁ ኢያሪኮን እነሆ አስገባታለሁ"። ❤ ይህም የከበረ መልአክ ከቅዱሳን ሰማዕታት ጋር በመሆን ገድላቸውን እስከ ሚፈጽሙ የሚያጽናቸውና የሚያስታግሣቸው ነው። ስለዚህም ስለ ልዕልናውና ስለ አማላጅነቱ በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን ለመታሰቢያው በዓል ተሠራለት እርሱ ስለ እኛ የምድሩን ፍሬ ይባልክልን ዘንድ ዝናሙንም በጊዜው እንዲወርድልን የወንዙንም ውኃ እንዲመላልን ነፋሱንም የምሕረት ነፋስ እንዲአደርግልን ሁሉንም የተስተካከለ እንዲአደርግልን ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ይማልድልናልና።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ሚካኤል_ያደረገው_ተአምር_ይህ_ነው፦ እንዲህም ሆነ እግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ የሚስቱም ስም ቴዎብስታ ነው እነርሱም ሁልጊዜ ያለ ማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢ ያደርጉ ነበር ከዚህም በኋላ በአገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ ለዚህም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉት አጡ ዱራታዎስም ሽጦ ለበዓሉ መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱን ልብስና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሔደ። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በታላቅ መኰንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለት ወደ ባለ በጎች ሒዶ በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ ሁለተኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሒዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ ግን መልአኩ ወደ ቤቱ ሳይደርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ ወደ ባለ ሥንዴም እንዲሔድና የሚሻውን እንዲሁ በርሱ ዋስትና እንዲወስድ አዘዘው ዱራታዎስም ቅዱስ ሚካኤል እንዳዘዘው አደረገ። ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ በረከትን ሁሉ ቤቱ ተመልቶ አገኘው። እጅግም አደነቀ የዚህንም የከበረ መልአክ የበዓሉን መታሰቢያ እንዳስለመደ አደረገ። የተራቡ ድኆችን ሁሉንም ጠርቶ መገባቸውና ወደየቤታቸው አሰናበታቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ሁለተኛ ተገለጠላቸው። ዱራታዎስንም የዓሣውን ሆድ እንዲሠነጥቅ አዘዘው። በሠነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሣው ሆድ ተገኘ። ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ቴዎብስታን እንዲህ አላቸው "ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ ለባለ ዓሣውና ለባለ ሥንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ እግዚአብሔር አስቧችኋልና በጎ ሥራችሁን መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን አስቦ በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ። በኋለኛውም መንግሥተ ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል" አላቸው። ❤ እነርሱም ሲሰሙ ስለዚህ ነገር ደነገጡ እርሱም "ከመከራችሁ ሁሉ ያዳንኳችሁ የመላእክት አለቃ እኔ ሚካኤል ነኝ መሥዋዕታችሁና ምጽዋታችሁን ወደ እግዚአብሔር ፊት ያሳረግሁ እኔ ነኝ አሁንም በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም" አላቸው። ይህንንም ብሎ ወደ ሰማያት ወጣ። እነርሱም ሰገዱለት ተአምራቱም የማይቈጠር ብዙ ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል ጸሎትና አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ፊላታዎስ፦ በእስክንድርያ ከተሾሙ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ስልሳ ሦስተኛ ነው። በሹመቱ ወራት የኢትዮጵያ ንጉሥ ወደ ኖባ ንጉሥ ወደ ጊዮርጊስ እንዲህ ብሎ የመልክት ደብዳቤ ጻፈ "ወንድሜ ሆይ ከሊቀ ጳጳሳት ቆዝሞስ ጊዜ ጀምሮ ለረጅም ጊዜ ጳጳስ ስለ ሌለን እኛ በታላቅ ችግር ውስጥ እንዳለን ዕወቅ። ይህም የሆነው ተንኰለኛው ሚናስ በተንኰልና በሐሰት ነገር የከበረ ጳጳሳችንን ጴጥሮስን ከሹመቱ ወንበር እንዲሰደድ ስለ አደረገው ነው። ስለዚህ አምስት ጳጳሳት እስቲአልፉ ለአገራችን ጳጳስ አልተላከም። አሁንም ስለ እግዚአብሔር ብለህ ስለ ቀናች ሃይማኖትም በድካም ከእኛ ጋር አንድ በመሆን ስለእኛ ወደ ግብጽ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቅዱስ ፊላታዎስ ጳጳስ ይልክልን ዘንድ ከራስህ ደብዳቤ እንድትጽፍለት እለምንሃለሁ" የሚል ነበር። ❤ በዚያንም ጊዜ የኖባ ንጉሥ ጊዮርጊስ ለኢትዮጵያ አገር ጳጳስን ይሾምላቸው ዘንድ የልመና ደብዳቤ ወደ አባ ፊላታዎስ ጻፈ ይህ ቅዱስ ፊላታዎስም ልመናውን ተቀብሎ ከአስቄጥስ ገዳም ስሙ ዳንኤል የሚባል አንድ ጻድቅ መነኰስ አስመጣ እርሱን ጵጵስና ሹሞ ወደ ኢትዮጵያ አገር ላከው ወደ እነርሱም በደረሰ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰዎች በታላቅ ደስታ ተቀበሉት። በዚህም አባት ፊላታዎስ ዘመን ብዙ ተአምራት ተገልጠዋል ኅዳር 12 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ፊላታዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 12 ስንክሳር።                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ ንጉሥ። ወብዙኀ ይትሐሠይ በአድኅኖትከ። ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ"። መዝ 20፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ19፥11-28።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዘነፈቃ ለባሕረ ኤርትራ ወከፈላ። እስመ ለዓለም ምሕረቱ። ወአውፆኦሙ ለእስራኤል እንተ ማዕከላ"። መዝ 135፥14-15 ወይም መዝ 33፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥17-24  ይሁ 1፥9-14 እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-21 ። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ነው። መልካም የቅዱስ ሚካኤል በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።          

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ኅዳር ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን #አምላክ_ለወለደች_ለእመቤታች #ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_እናት ለሆነች ለተመሰገነነች #ለቅድስት_ሐና ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሁለተኛው #ከአርኬላዖስ_ሰማዕት፣ #ከአበምኔት_ኤልሳዕ፣ #ከመነኰስ_ጳኵሚስና_ከሰማዕቱ_ሚናስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤  #ቅድስት_ሐና፦ ይችም ቅድስት ከኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነ ለማጣት ልጁ ናት። ለማጣትም ሦስት ልጆች አሉት የታላቂቱም ስሟ ማርያም ናት ሁለተኛዋም ስሟ ሶፍያ ሦስተኛዪቱም ስሟ ሐና ናት ታላቂቱ ማርያምም ለባል ተድራ አዋላጅ የሆነች ሰሎሜን ወለደቻት እርሷም መድኃኒታችንን ከወለደችበት ጊዜ ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ድንግል ማርያምን ያገለገለቻት ናት። ሶፍያም ለባል ተድራ ለመጥምቁ ዮሐንስ እናቱ የሆነች ቅድስት ኤልሳቤጥ ወለደቻት። ❤ ይችንም ቅድስት ሐናን ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙ ኢያቆም ለሚባል አጋቧትና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት እሊህም ሰሎሜና ኤልሳቤጥ ለቅድስት ሐና የእኅትማማች ልጆች ናቸው። ❤ የዚችንም የቅድስት ሐናን በሥውር የምትሠራውን ገድሏንና ትሩፋቷን እንዳናስታውሰው አናውቀውም ግን ከሴቶች ሁሉ እንደምትበልጥና እንደምትከብር እናውቃለን እንረዳለን እርሷ አምላክን በሥጋ ለወለደችው ወላጅዋ ትሆን ዘንድ የተገባት ሁናለችና ከሴች ሁሉ የሚበልጥና የሚበዛ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ታላቅ ጸጋ ባልተገባት ነበር። ❤ ይህችም ጻድቅት ሐና መካን በመሆንዋ ልጅን ይሰጣት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር በጸሎት ትማልድ ነበር እግዚአብሔርም በእርሷ ለዓለም ሁሉ ድኅነት የተደረገባትን ይቺን የተባረከችና የከበረች ልጅን ሰጣት እርሷም አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት። ስለዚህም ይህን ታላቅ ጸጋ ስለሰጣት የበዓሏን መታሰቢያ በደስታ ልናከብር ይገባል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በቅድስት ሐና በጸሎቷ የሚኝ በረከቷም ከእኛ ጋር ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 11 ስንክሳር።                           ✝️  ✝️ ✝️ ❤ "#ሰለም_ለኪ_ለጸሎተ_ኵሉ_ምዕራጋ። ከመ አስካለ ወይን ዲበ ሐረጋ። #ሐና_ብፅዕት ተፈሥሒ እንበለ ንትጋ። እስመ ረከብኪ ሞገሰ ወአድማዕኪ ጸጋ። እምሔውተ አምላክ ትኩኒ በሥጋ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር+11።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳት። ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን። እምኲሉ ተዒይኒሁ ለያዕቆብ"። መዝ 86፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 3፥23-ፍ.ም።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አዋልደ ንግሥት ለክብርከ። ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት"። መዝ 44፥9። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥5-11፣ 1ኛ ጴጥ 3፥5-7 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-19። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥1-9። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት ሐና የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።           

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ኅዳር ፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን #ለሠላሳ_ስድስቱ_ቅዱሳት_አንስት ለበዓላቸው መታሰቢያና #ለሃምሳ_ቅዱሳት_ንጹሐት #መነኰሳይያት_ደናግልና_ለእናታቸው ለነበረች #ለቅድስት_ሶፍያ በዑልያኖስ ዘመን ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ በእስክድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ድሜጥሮስ ዘመን ስለ ጾም ሥርዓት ቅዱሳት ሊቃነ ጳጳሳትና የኤጲስ ቆጶሳት የአንድነት ጉባኤ ከተደረገበት (#የቅዱስ_ድሜጥሮስን ቀመር አቡሻህርን በሁሉም ዘንድ እንዲጠቀሙበት በጉባኤ ወሰኑ)፣ #ከጳውሎስና_ከሦስት_ሰማዕታት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱሳት_ንጹሐት_መነኰሳይያት_ደናግል #እናታቸው_ቅድስት_ሶፍያ፦ እሊህም ቅዱሳት ከተለያዩ አገሮችና ቦታዎች ሲሆኑ መለኮታዊ ፍቅር በአንድነት ሰበሰባቸው የምንኲስናንም ልብስ ለበሱ ይኸውም የመላእክት ልብስ ነው። በሮሜ አገር ከአሉ ገዳማትም በአንዱ የሚኖሩ ሆኑ ቅድስት ሶፍያም በእነርሱ ላይ እመ ምኔት ሆነች። ❤ እርሷም ጸጋንና ዕውቀትን የተመላች ናት የቅዱሳን መነኰሳትን ገድል በማንበብ እየጾሙ እየጸለዩ በምድር ላይ እንደ መላእክት እስከ ሆኑ ድረስ መንፈሳዊ ዕድገትን አሳደገቻቸው ከእነርሱም በአንድ ገዳም ውስጥ ሰባ ዓመት ያህል የኖሩ አሉ ከውስጣቸውም ልጅ እግሮች የሆኑ አሉ። ❤ ከሀዲ ንጉሥ ዑልያኖስም ከፋርስ ንጉሥ ከሳቦር ጋር ሊዋጋ በሮሀ ሀገር በኩል በሚያልፍ ጊዜ እርሱ ሳቦር ሊወጋው ወደርሱ እንደሚመጣ ሰምቷልና አልፎ ሲሔድም በውስጡ እሊህ ደናግል ያሉበትን ገዳም አይቶ "ይህ ምንድን ነው" ብሎ ጠየቀ ሰዎችም "ይህ የደናግሎች ገዳም ነው" አሉት። ❤ በዚያንም ጊዜ ወደዚያ ገዳም ገብተው ደናግሎችን እንዲገድሏቸው በገዳሙ ውስጥም ያለ ገንዘባቸውን ሁሉ እንዲዘርፉ ወታደሮቹን አዘዘ ወታደሮችም ገብተው እሊያን ደናግል በሰይፍ ገደሏቸው ገዳሙንም አጠፉ የገዳሙን ገንዘብ ሁሉንም ዘረፉ። ❤ ከሀዲውን ንጉሥ ግን ስለ መንጋዎቹ በቀል እግዚአብሔር ተበቀለው ይህም እንዲህ ነው ያጠፋው ዘንድ ሰማዕት መርቆሬዎስን አዘዘው መርቆሬዎስም በአካለ ነፍስ ሒዶ በጦር ወጋውና በክፉ አሟሟት ሙቶ ወደ ዘላለም ሥቃይ ሔደ። እሊህ ቅዱሳት ደናግል ግን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ገቡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ደናግላንና በእናታቸው በቅድስት ሶፍያ ጸሎት ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑ ለዘላለሙ አሜን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ዕለት #በእስክንድርያ_አገር_ሊቀ_ጳጳሳት #በአባ_ድሜጥሮስ_ዘመን_ስለ_ጾም_ሥርዓት ቅዱሳን ሊቃነ ጳጳሳትና የኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ ተደረገ። በዚህም የአንድነት ጉባኤ የመሰብሰባቸው ምክንያት እንዲህ ነው የክርስቲያን ወገኖች በጥር ዐሥራ አንድ ቀን በከበረች በጥምቀት በዓል ተጠምቀው በማግሥቱ የከበረች የአርባ ቀንን ጾም መጾም ይጀምራሉ እስከ የካቲት ሃያ ሁለት ቀንም ጾመው ጾምን ይፈታሉ። ❤ ከዚህም በኋላ በመጋቢት በሃያ ሦስት የሕማማትን ሰሞን መጾም ይጀምራሉ በዚህም ወር በሀያ ሰባት የስቅለቱን በዓል ያከብራሉ በሃያ ዘጠኝም ክብር ይግባውና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤውን በዓል ያክብሩ ነበር። ❤ ይህ ድሜጥሮስም በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ሁኖ በተሾመ ጊዜ በእርሻ የሚተዳደር መጻሕፍትን የማያውቅ ጨዋ ሰው ሲሆን እግዚአብሔር በመለኮታዊ ስጦታው ልቡን ብሩህ አድርጎለት የብሉይንና የሐዲስ መጻሕፍትን የቤተ ክርስቲያንንም ሕግ አወቀ ከእርሳቸውም ብዙዎችን ተረጎመ። ❤ ከዚህም በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት ባሕረ ሐሳብ የተባለ የዘመን ቁጥርን ጻፈ ይህም ክብር ይግባውና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አጽዋማትና በዓላቶቹ የሚታወቁበት እሊህም የከበረች የአርባ ቀን ጾም የሆሣዕና ዑደት ስቅለቱ ትንሣኤው በአርባ ቀን ዕርገቱ ከትንሣኤውም በኋላ በኀምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ናቸው። ይህንንም ጽፎ ወደ ሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊቅጦር ላከ ሁለተኛም ወደ አንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ መክሲሞስ ላከ ዳግመኛም ወደ ኢየሩሳሌም አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ አጋብዮስ ላከ እነርሱም በአነበቧት ጊዜ እጅግ ደስ ተሰኙባት። ❤ የሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊቅጦርም በሮሜ አገሮች ሁሉ ያሉትን ኤጲስቆጶሳቶቹን አዋቂዎችን ብዙዎች ሊቃውንትንም ሰበሰባቸው ይህንንም የዘመን ቁጥር አስነበበላቸው እጅግ በጣም ጥሩ ሁኖ አግኝተውት ደስ ተሸኙበት በደስታም ተቀበሉት አባዝተውም በመጻፍ ለሁሉ አገሮች ላኩት እስከዚች ዕለትም ጸንቶ ተሠርቶ ኖረ። ከዚህም በኋላ ልዩ ሦስት የሆነ አንድ እግዚአብሔርን ፈጽሞ እያመሰገኑት ወደየሀገራቸው ገቡ።  ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ሥርዓትን በሰሩልን አባቶች ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 10 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለደናግል_እምተደልዎ_ወእምተሐውዞ። ለወልደ ማርያም ድንግል እንዘ ይተልዋ ግዕዞ። ሶበ ዑልያኖስ ቀተሎን ለእሎን በተጋዕዞ። እግዚአብሔር መስተበቅል #ለመርቆሬዎስ_አዘዞ። በቀለ ደሞን በኲናት ይርግዞ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር_10።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ። ወኮነኒ ጽዕለተ። ለበስኩ ሠቀ ወኮንክዎሙ ነገረ"። መዝ 68፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 2፥1-12 ወይም ቲቶ 2፥1-9፣ 1ኛ ጴጥ 3፥1-7 እና የሐዋ ሥራ 17፥34-30። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 25፥1-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም የሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።        

❤ በዚያም ወራት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ ጸሐፊ የሚሆነውና የሚረዳው ብልህ ሰው ፈለገ ስለ አባ ይስሐቅም ነገሩት እርሱም መልክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ይጽፍለትም ዘንድ ደብዳቤ ሰጠው እርሱ ግን አባ ይስሐቅ እያወቀ ጽሕፈቱን አበላሸ ሊቀ ጳጳሳቱ እንዲተወውና ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመለስ ነበር የዚህን ዓለም ክብር ይጠላልና። ሊቀ ጳጳሳቱም እንዲተወውና እንዲአሰናብተው አውቆ ማበላሸቱን በአወቀ ጊዜ "በጥሩ ጽፈሃል ከዚህም እንድትሔድ እኔ አልተውህም" አለው አባ ይስሐቅም እንደማይለቀው አውቆ የሚያውቀውን ሁሉ ጥበቡን ያማረ ጽሕፈቱንም ገለጠለት ሊቀ ጳጳሳቱም በእርሱ እጅግ ደስ አለው። ❤ ከጥቂት ወራትም በኋላ አባ ይስሐቅ ወደ አስቄጥስ ገዳም ተመለሰ አባ ዮሐንስም የሚያርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ ስለርሱ ሊቀ ጵጵስና የሚሾም ማን እንደሆነ ያስረዳው ዘንድ ክብር ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመነው ጌታም በራይ "ከአንተ በኋላ ለዚች ሹመት የሚጠቅም ረዳትህ ይስሐቅ ነው" አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ሕዝቡን ጠራቸውና ከእርሱ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት ሁኖ የሚሾም ረዳቱ ይስሐቅ እንደሆነ አስረዳቸው ከዚህም በኋላ አባ ዮሐንስ በዐረፈ ጊዜ ይህን ቅዱስ አባ ይስሐቅን ይዘው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት በዘመኑም ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆነች ብዙዎች አብያተ ክርስቲያንንም አደሳቸው ይልቁንም የወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስን ቤተ ክርስቲያን አሳምሮ አደሳት የሊቀ ጵጵስናውንም ቤት አደሰ። ❤ ይህንም አባት ብዙ ችግርና መከራ ደርሶበታል በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ መንበርም ሰባት ዓመት ተኩል ኑሮ ኅዳር 9 ቀን በሰላም ዐረፈ። በዚህም ቅዱስ አባት በመጽሐፈ ገድሉ ከእሑድ ቀን በቀር ሊቀ ጳጳሳት እንዳይሾም የሚያዝ ጽሑፍ አለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሊቀ ጳጳሳት በአባ ይስሐቅ ጸሎት ይመረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 9 ስንክሳር።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ንጉሥሰ ይትፌሣሕ በእግዚአብሔር። ወይከብር ኲሉ ዘይምሕል ኪያሁ። እስመ ይትፈጸም አፍ ዘይነብብ ዐመፃ"። መዝ62፥11። የሚበበው ወንጌል ማቴ 18፥12-23።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወነበቡ ዓመፃ ውስተ ዓርያም።  ወአንበሩ ውስተ አፉሆሙ። ወአንሶሰወ ውስተ ምድር ልሳኖሙ"። መዝ 72፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ቈላ 2፥5-13፣ 2ኛ ዮሐ 1፥6-12፣ የሐዋ ሥራ 15፥22-30። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ10፥25-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የሠለስቱ ምዕት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።         

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ኅዳር ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን #ሃይማኖት_ላቀኑ_ለአባቶቻችን_ለሦስት_መቶ_ዐሥራ-ስምንቱ (ሠለስቱ ምዕት) ኤጲስቆጶሳት ከሃዲ መናፍቅ የሆነውን አርዮስን #በ325_ዓ.ም #በኒቅያ_ጉባኤ #በጻድቁ_ንጉሥ_በቈስጠንጢኖስ ዘመን አውግዘው ለለዩበት ቀን ለበዓላቸው መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከእስክድርያ አርባ አንደኛ ሊቀ ጳጳስ #ከቅዱስ_አባት_አባ_ይስሐቅ እግዚአብሔር አምላክ ዕረፍት ረድኤት በረከትን ያሳትፈን።                                                            ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ቀን ዳግመኛ #የሦስት_መቶ_ዐሥራ_ስምንት_የኤጲስቆጶሳት_ስብሰባ_በኒቅያ_ከተማ_በጻድቅ_ንጉሥ_በቈስጠንጢኖስ ዘመን ሆነ። ከእርሳቸውም ጋራ አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት አሉ እሊህም አባ እለእስክንድሮስ የእስክንድርያ፣ አባ ዮናክንዲኖስ ከሮሜ አገር፣ አባ ሶል ጴጥሮስ የቊስጥንጥንያና የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ኤዎስጣቴዎስ ናቸው። ስብሰባቸውም የሆነበት ምክንያት በእስክንድርያ አገር ቄስ ሁኖ ስለ ነበረው ስለ አርዮስ ነው። እርሱ ስቶ የክብር ባለቤት ወልድን በመለኮቱ ፍጡር ነው በማለቱ ነው። ❤ ከእሊህሜ ቅዱሳን ተጋዳዮች አባቶች ከውስጣቸው እንደ ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ በሽተኞችን የሚፈውሱ ድንቆች ተአምራትን የሚያደርጉ አሉ ብዙ ዘመናትም ስለ ቀናች ሃይማኖት የተሠቃዩ አሉ። ከእርሳቸውም የእጃቸውንና የእግራቸውን ጥፍሮች ያወለቋቸው አሉ ዳግመኛም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን የቆረጧቸው አሉ። ጥርሶቻቸውን የሰበሩአቸውና ጎናቸውን የሠነጠቋቸውም አሉ። ❤ ከውስጣቸውም ስሙ ቶማስ የሚባል የአገረ መርዓስ ኤጲስቆጶስ አለ ከሀድያንም ሃያ ሁለት ዓመት አሥረው ርኅራኄ የለውን ሥቃይ አሠቃዩት በየዓመቱም ወደርሱ በመግባት ከሕዋሳቱ አንዱን ይቆርጣሉ እንዲህም በማድረግ እጆቹን፣ እግሮቹን፣ ከንፈሮቹን፣ አፍንጫውንና ጆሮዎቹንም ቆርጠው ጨረሱ። ጥርሶቹንም ሰበሩ በእሳትም ተለብልቦ እንደ ጠቆረ ግንድ አደረጉት የርሱ ወገኖችም እንደሞተ አስበው እንደ ሌሎች ሰማዕታት በየዓመቱ መታሰቢያውን አደረጉ። ❤ እሊህ አባቶችም ወደ ኒቅያ ከተማ በደረሱ ጊዜ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ታላቅና ሰፊ የሆነ መሰብሰቢያ አዳራሽ አዘጋጁላቸው በውስጡም ለየአንዳንዳቸው ወንበርን አኖረ የእርሱንም ወንበር ከእርነርሱ ወንበሮች ዝቅተኛ አደረገ መሳለምን በመርዓስ ኤጲስቆጶስ በቅዱስ ቶማስ ጀመረ ሰገደለት ሕዋሳቶቹ ከተቆረጡበት ላይ ተሳልመው። እንዲሁም አባቶችን ሁሉንም ተሳለማቸው። ከዚህም በኋላ በትረ መንግሥቱን ሰይፋን ቀለበቱን ሰጣቸውና እንዲህ አላቸው "እነሆ አሁን በካህናት ሁሉና በመንግሥት ላይ ሃይማኖቱ እንደናንተ የቀና ከሆነ ታኖሩት ዘንድ ሃይማኖቱ የቀና ካልሆነ ግን ከምእመናን ለይታችሁ ታሳድዱት ዘንድ ሥልጣንን ሰጠኋችሁ"። ❤ እነርሱም ሕግንና ሥርዓትን ሠሩ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመካከላቸው ይቀመጥ ነበር ልቡናቸው በመንፈስ ቅዱስ የበራላቸው ሰዎች አይተውታልና በሚቆጥሩአቸው ጊዜ ግን ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ቊጥር ሁነው ያገኙአቸዋል። ❤ ከዚህም በኋላ ለካህናትና ለሕዝባውያን ለነገሥታት ለመሳፍንት ለሚገዙና ለሚሽጡ ነጋዴዎች፣ ለድኆችም፣ ለሽማግሎችና ለጎልማሶች፣ ለሙት ልጆችም ለወንድና ለሴት ሥርዓትን ሠሩ። ❤ ከዚህም በኋላ ወልድ በመለኮቱ ከአብ ጋር ትክክል እንደሆነ እያስረዱ የቀናች ሃይማኖትን አስተማሩ የተረገመ አርዮስንና በረከሰች ትምህርቱ የሚያምነውን አውግዘው ለዩ። ❤ የሠሩዋት ያስተማሩዋትም የሃይማኖት ትምህርት ይቺ ናት እንዲህ ብለው "ሁሉን በያዘ ሰማይና ምድርን የሚታይና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን። ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ የተፈጠረ ያይደለ የተወለደ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል። ሁሉ በርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምንም ምን የሆነ የሌለ በሰማይም ያለ በምድርም ያለ። ስለእኛ ስለ ሰው ስለ መዳናችን ከሰማ ወረደ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ፈጽሞ ሰው ሆነ። ሰው ሁኖ በጰንጤናዊ ጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ ታመመ ሞተ ተቀበረም በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ። በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም ሕያዋንንና ሙታንን ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም"። ❤ ከዚህም በኋላ የመንፈስ ቅዱስ ጠላት ስለሚሆን ስለመቅዶንዮስ በቊስጥንጥንያ ከተማ መቶ ሃምሳው የኤጲስቆጶሳት በተሰበሰቡ ጊዜ ከዚህ የቀረውን ሠሩ። እንዲህ አሉ "ጌታ ማሕያዊ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋር በነቢያት የተናገረ። ከሁሉ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰብዋት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተሥረይ በአንዲት ጥምቀትም እናምናለን። የሙታንንም መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን"። ❤ እሊህም አባቶቻችን ይችን ሃይማኖት ትምህርት ምዕመናን ሁሉ በቀንም በሌሊትም በጸሎታቸው ጊዜ እንዲአነቡዋት በቅዳሴም ጊዜ እንዲጸልዩባት አዘዙ ወንዶችና ሴቶች፣ ሽማግሎችና ልጆች፣ አገልጋዮችም ሁሉ እንዲማሩዋት አዘዙ። ሠርተው ወስነው ለቤተ ክርስቲያን የሃይማኖትን ፋና ከአስቆሙላት በኋላ ወደ አገራቸው በፍቅር አንድነት ተመለሱ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሠለስቱ ምዕት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ይስሐቅ፦ ይህም አባት በእስክንድርያ አገር ከተሾሙ መካከል ለአባቶች ሊቀ ጳጳሳት አርባ ዘጠነኛው ነው። ይህም ቅዱስ ቡርልስ ከሚባል አገር ነው ወላጆቹም እግዚአብሔርን የሚፈሩ እጅግም ባለጸጎች ናቸው ከረጅም ዘመንም በኋላ  ይህን ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በታላቅ ደስታ ደስ ተሰኙበት። ❤ ከዚህም በኋላ ያጠምቀው ዘንድ ወደ ኤጲስቆጶሱም በአቀረቡት ጊዜ ኤጲስቆጶሱም ሲያጠምቀው በሕፃኑ ራስ ላይ የብርሃን መስቀልን አየ በዚያንም ጊዜ የሕፃኑን እጅ ይዞ በራሱ ላይ አኖረ። እንዲህም ብሎ ትንቢት ተናገረት "ይህ ሕፃን በእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾማል" አባቱንም እንዲህ አለው "ይህን ልጅ ጠብቀው እርሱ ለእግዚአብሔር የተመረጠ መሣሪያ ይሆናል"። ❤ ጥቂትም በአደገ ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ጽሕፈትን አስተማሩት የቅዱሳንንም ዜና የሚያነብ ሆነ ወላጆቹንም ትቶ ወደ አስቆጥስ ገዳም ሔደ በአበ ምኔቱ በአባ ዘካርያስም ዘንድ መነኲሶ በገድል ተጠመደ። በአንዲትም ዕለት አንድ ጻድቅ ሰው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አየው በእርሱም ላይ "ይስሐቅ በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾም ዘንድ አለው" ብሎ ትንቢት ተናገረ።

                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦"ተፅዕነ ላዕለ ኪሩቤል ወሠረረ። ወሠረረ በክነፈ ነፋስ። ወረሰየ ጽልመተ ምሥዋሮ"። መዝ 17፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥21-ፍ.ም ወይም 1ኛ ቆሮ 15፥24-37፣ 1ኛ ጴጥ 3፥18-ፍ.ም ወይም ራዕ.ዮሐ 4፥6-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥29-ፍ.ም።  የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥10-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ወይም የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የአርባዕቱ እንስሳና የመላእክት አለቃ የቅዱስ አፋኒን በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta) Saints Of The Orthodox Tewahedo Church.: ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤       ❤ #ኅዳር ፰ (8) ቀን። ❤ እንኳን #የቅድስት_ሥላሴ_መንበር_ለሚሸከሙ ሥጋ ለሌላቸው #ለአርባዕቱ_እንስሳ_ለኪሩቤል ለመታሰቢያ ዓመታዊ በዓላቸው፣ ለመላእክት አለቃ #ለቅዱስ_አፍኒን_ለተሸመበት_በዓል፣ #ለአቡነ_አምደ_ሚካኤል ዘወሎ ለልደታቸው በዓል፣ #ለታላቁ_አባት_ለአቡነ ኪሮስ ለቅዳሴ ቤታቸው  መታሰቢያና ለበዓላቸው ለአረማዊ መኰንን ልጅ ለነበረ #ለአባ_ቅፍሮንያ_ለዕረፍትበዓል በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሊቀ ጳጳሳት #ከአባ_ዮሐንስ ከመታሰቢያው፣ #ከንጉሥ_ቈስጠንጢኖስ መስቀል ከተገለጠለትና ከሰማዕት #ከቅዱስ-ኤስድሮስ ማኅበር ከሆኑ #ከመቶ_ሰማንያ ሁለት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ #በዚች_ቀን_ሥጋ_የሌላቸው_የአርባዕቱ_እንስሳ በዓላቸው ሆነ። እሊህም መንበሩን የሚሸከሙ የእግዚአብሔር ሠረገላዎቹ ናቸው ስለ እርሳቸውም ወንጌልን የጻፈ ዮሐንስ እንዲህ ሲል እንደመሰከረ "በዚያ ዙፋን ፊት በረድ የሚመስል ባሕር አለ በዙፋኑም ዙሪያ አራት እንስሶች አሉ በፊትም በኋላም ዐይንን የተመሉ ናቸው። የፊተኛው አንበሳ ይመስላል ሁለተኛውም ላም ይመስላል ሦስተኛውም የሰው መልክ ይመስላል አራተኛውም የሚበር አሞራ ይመስላል። የእሊህም የአራቱ እንስሶች እያንዳንዱ ክንፋቸው ስድስት ስድስት ነው ሁለንተናቸውም ዐይኖችን የተመሉ ናቸው የነበረ የሚኖር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ጽዑዕ ክቡር ልዩ ነው እያሉ በመዓልትና በሌሊት ዕረፍት የላቸውም። ❤ ሁለተኛውም ስለእርሳቸው ኢሳይያስ እንዲህ አለ "ከዚህም በኋላ ንጉሡ ኦዝያን በሞተ ጊዜ አሸናፊ እግዚአብሔርን ሰፊ በሆነና ከፍ ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ ብርሃኑም ቤቱን መልቶ ሱራፌልም በዙሪያው ቁመው አየሁት። የአንዱም የአንዱም ክንፋቸው ስድስት ነው በሁለቱ ክንፋቸው ፊታቸወን በሁለቱ ክንፋቸው እግሮቻቸውን ይሸፍናሉ በሁለቱ ክንፎቻቸው ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ይበራሉ። አንዱም አንዱም ከአንዱ ጋር ፍጹም አሸናፊ የሆንክ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብለህ የምትመሰገነው ምስጋናህ በምድርና በሰማይ የመላ ነው እያሉ ያመሰግናሉ"። ❤ ነቢዩ ዳዊትም "በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ" አለ ሁለተኛም "በኪሩቤል ላይ የተቀመጠ እርሱ ምድርን አናወጻት" አለ። ❤ ሕዝቅኤልም እንዲህ አለ "ከወደ ሰሜን እነሆ ጥቅል ነፋስ ሲመጣ አየሁ ታላቅ ደመና አለ በዙሪያውም ብርሃን አለ ከእርሱም እሳት ቦግ ብሎ ይወጣል። በደመናውም መካከል ባለ በእሳቱ ውስጥ እንደ አራት ራስ አሞራ መልክ የሚመስል አለ በመካከሉም እንደ አራቱ ኪሩቤል መልክ ያለ አለ። መልካቸውም እንዲህ ነው በውስጣቸው የሰው መልክ አላቸው የአንዱም የአንዱ ፊት አራት ነው ክንፉም አራት ነው። እግራቸውም የቀና ነው ከእግራቸውም ክንፍ አላቸው ሰኰናቸው ግን እንደ ላም ሰኰና ነው ከሱም እሳት ቦግ ይላል እንደጋለ ብረት ፍንጣሪም ይበራል"። ❤ ወንጌላዊ ዮሐንስም ዳግመኛ እንዲህ አለ "በዚያው ዙፋን ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ የእንስሶቹንም የእነዚያ አለቆችንም ቃል ሰማሁ ቊጥራቸውም እልፍ አለቆች ያሉአቸው ብዙ የብዙ ብዙ ነው። ለዚያ ለተገደለው በግ ኃይልን ባለጸግነትን ጥበብን ጽናትን መንግሥትን ክብርን ጌትነትን ምስጋናን ገንዘብ ሊያደርግ ይገባል ብለው በታላቅ ቃል ተናገሩ። በሰማይና በምድር ከምድር በታች በባሕር ውስጥ በእነዚያም ውስጥ የተፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ጌትነት ክብር ኃይል በረከት በዙፋኑ ለተቀመጠው ለሱ ለበጉም ለዘላለሙ ይገባል" አሉ "በእውነት ይገባል"። እሊህም አራቱ እንስሶች "አሜን" ይላሉ። እሊያም አለቆች ይሰግዳሉ"። ❤ ስለ ልዕናቸውና ስለ ክብራቸው ለእሊህ አርባዕቱ እንስሳ ከብሉይና ከሐዲስ ብዙ መጻሕፍት መስክረዋል መሐሪና ይቅር ባይ እግዚአብሔርም ስለ ሁሉ የሰው ፍጥረት ይለምኑት ዘንድ ቀራቢዎቹ አደረጋቸው። ዳግመኛም እንዲህ ተባለ "ገጸ ሰብእ ስለሰው ፍጥረት ይለምናል ገጸ አንበሳ ስለ አራዊት ይለምናል ገጸ ላሕም ስለ እንስሳ ይለምናል ገጸ ንስርም ስለ አዕዋፍ ይለምናል" ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ እነርሱ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት እጅግ የቀረቡ ናቸውና። ❤ ስለዚህም በዓለሙ ሁሉ በስማቸው አብያተ ክርስቲያን እንዲታነፁ በዚችም ቀን መታሰቢያቸው እንዲደረግ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ እነርሱ  ስለ ሰው ወገን በእግዚአብሔር ዘንድ ይማልዳሉና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ኪሩቤል አማላጅነት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_አፍኒን፦ ይህም ከሱራፌልና ከኪሩቤል ጋር የልዑልን የጌቱነቱን ዙፋን የሚጠብቅ ነው ስለርሱ ሄኖክ እንዲህ አለ "ያንን ቤት ሱራፌልና አፍኒን ዙሪያውን እየዞሩ ይጠብቁታል" እነርሱም የልዑልን የጌትነቱን ዙፋን ሲጠብቁ የማያንቀላፉ ናቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ ቅዱስ አፍኒን አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ቅፍሮንያ፦ ይህ አባት የአረማዊ መኰንን ልጅ ነው። ከዕታትም በአንዲቱ ስሙ መርቆሬዎስ የሚባል መነኰስ ከአባ ጳኲሚስ ገዳም ወደ አገሩ መጣ እርሱ ክርስቲያን እንደሚሆን በእርሱ ላይ ትንቢት ተናገረ። ከጥቂት ወራትም በኋላ ገዳማትን ሊአጠፋ ምርኮንም ሊማርክ ሠራዊቱን ሰብስቦ ወደ ግብጽ አገር ዘመተ ወደ አባ ጳኲሚስም ገዳም በደረሰ ጊዜ አበ ምኔቱ ወደርሱ ወጥቶ "እኔ ነኝ" አለው ቅፍሮንያም ሰምቶ አበ ምኔቱን ለብቻው አግልሎ እንዲአጠምቀውና የምንኲስናንም ልብስ እንዲአለብሰው ለመነው አበ ምኔቱም "እሺ በጎ" አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ሠራዊቱ ወደ አገራቸው በተመለሱ ጊዜ ብቻቸውን ቀረ በዚያንም ጊዜ ተጋድሎውንም በመጾምና በመጸለይ ጀመረ። ሰይጣንም በእርሱ ላይ ቀንቶ ነገረ ሠሪ አስነሣበት በመኳንንቱም ዘንድ ወነጀለው እነርሱም "አገራችንን ያጠፋ የመኰንን ልጅ ከዚህ አለ" ብለው ገዳሙን ከበቡ እግዚአብሔር ሠወረው በአጡትም ጊዜ ነገረ ሠሪውን ገደሉት። ❤ ይህም ቅዱስ በገድል ተጠምዶ ኖረ በየሰባት ቀንም ይጾማል ያለ መራራ አደንጓሬ አይመገብም። በዚያም ወራት የምድር አውሬ እንስሶቻቸውን እየገደለ በገዳሙ ላይ ጥፋትን አደረሰ አባ ቅፍሮንያም ወደርሱ መጥቶ እንደ በግ ይዞ አሠረው ዐሥር ዓመትም ቆይቶ ሞተ። ❤ ቅድስ ቅፍሮንያም የእግዚአብሔር መልአክ እየመራው ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ በአንዲትም ቀን ደረሰ በዚያም ታላቅ ምሥጢርን አየ ከከበሩ ቦታዎችም ተባርኮ ወደ መኖሪያው ተመልሶ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 8 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ነግሠ ደንገፁ አሕዛብ። ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል አድለቅለቃ ለምድር። እግዚአብሔር ዐቢይ በጽዮን"።  መዝ98፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ማር16፥14-ፍ.ም                

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለዘመነ_አስተምህ(ሕ)ሮ_የመጀመርያ_ሳምንት ለዕለተ እሑድ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፰ " #ኢትዘኪሮ_አበሳነ ዚአነ ፍጹመ ኢኀደገነ ፍጹመ ንማስን #ኄር_እግዚአብሔር_አዘዞሙ_ሙሴ ለሕዝብ ያክብሩ ሰንበተ ጽድቅ"። ትርጉም፦ #ቸር_እግዚአብሔር በደላችንን ሳያስብ ፈጽሞ እንጠፋ ዘንድ አልተወንም፤ በእውነት ሕዝብህ #ሰንበትን_ያክብሩ_ብሎ_ሙሴን አዘዘው። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                             ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ዘመነ_አስተምሕሮ፦ ይህ ዘመን አስተምሕሮ ከኅዳር ፮ (6) እስከ ታኅሣሥ 7 (13) ፯ (፲፫) ያለው ወቅት ሲሆን አስተምሕሮ ማለት ኹለት ትርጉም አለው፤ ይኸውም በመሐሩ "ሐ" (አስተምሕሮ) በሚለው ከተጻፈ ምሕላ፣ ምልጃና፣ ልመና፣ ይቅርታ ማለት ነው። ይህም "መሐሪ" ይቅር አለ በደልን ተወ፤ ወይም አስተምሕሮ ስለ እግዚአብሔር ቸርነትና ርኅራኄ የምንመሰክርበት እርሱ በደላችንን ሁሉ ይቅር ብሎ ሊታረቀን በሰማይ መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን የምናዘክርበት እንዲሁም እርሱ ይቅር እንዳለን ተገንዝበን እኛም እርስ በእርሳችን ይቅር መባባል እንደሚገባን ትምህርት የሚሰጥበት ወቅት ነው። በተለይ ይህ ዘመነ አስተምሕሮ ቤተ ክርስቲያን ስለ ልጆቿ ምልጃ የምታቀርብበት ምዕመናንንም ስለ በደላቸው ይቅርታ የሚጠይቁበት ዘመን ነው። ❤ በሃሌታው "ሀ" (አስተምህሮ) በሚለው ከተጻፈ ትምህርት ሥርዓት ማለት ነው፤ አስተምህሮ የሚለው ቃል "መሀረ" አስተማረ፣ መከረ፣ ዘከረ ከሚለው ሥርወ ግሥ የተገኘ ነው ይኸውም የእግዚአብሔር ቸርነት፣ ርኅራኄ፣ ትዕግሥትና የማዳን ሥራው በቤተ ክርስቲያን በስፋት የሚሰበክበት ጊዜ ስለኾነ ወቅቱ ዘመነ አስተምህሮ ተብሏል የሥርዓትና የትምህርት ወቅት ማለት ነው። "ፊደል አይቀነስም" ብለው ሊቃውንቱ የሚሟገቱት ከዚህ የተነሣ ነው፤ እነዚህ ተመሳሳይ ድምጽ ያላቸው ፊደላት በአገባባቸው ሰፊ የትርጉም ለውጥ ሊያመጡ ይችላሉና። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ዘመነ አከፋፈል መሠረት ከኅዳር ፮ (6) እስከ ታኅሣሥ 7 (13) ፯ (፲፫) ቀን ድረስ ያለው ወቅት ዘመነ አስተምሕሮ ተብሎ ይጠራል። ❤ በዘመነ አስተምሕሮ የእግዚአብሔርን ቸርነት፣ ታጋሽነት፣ ይቅር ባይነት በየጊዜው የሰዎችን በደል ሳይመለከት የቸርነቱን ሥራ መሥራቱን፣ ለሰዎች የዕረፍት ቀን እንዲሆን ሰንበትን መቀደሱ ይታሰባል። በተለይ ደግሞ ቅዱሳን ነቢያት ስለ ክርስቶስ መምጣት የቆጠሩት ሱባኤ፣ የመሰሉት ምሳሌ፣ የተናገሩት ትንቢት፣ የጸለዩት ጸሎት የጾሙት ጾም የሚዘከርበት ሰሞን ነው። ምንጭ፦ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቁጥር 1 መጽሐፍ በሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ የተዘጋጀ መጽሐፍ የተወሰደ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_የዕለቱ_ምስባክ፦ "ኢትዝክር ለነ አበሳነ ዘካትካት። ፍጡነ ይርከበነ ሣህልከ እግዚኦ። እስመ ተመንደብነ ፈድፋደ"። መዝ 78፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 5፥10-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 2፥1-18 እና የሐዋ ሥራ 1፥22-1-12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥5-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ወይም የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የሠለስቱ ምዕት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።             

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ኅዳር ፯ (7) ቀን። ❤ እንኳን #ከዘጠኙ_ቅዱሳን_አንዱ_ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ይስሐቅ ባደረጉት ተአምር ስማቸው #አባ_ገሪማ_ለተባሉት ለልደታቸው ዓመታዊ መታሰቢያ በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ ይስሐቅ (ገሪማ)፦ ሕፃን ይስሐቅ ከተፀነሰ በኋላ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በሆነው ጊዜ ብፅዕት ከምትሆን ከእናቱ ስፍንግያ ማሕፀን ኅዳር 7 (ሰባት) ቀን ተወለደ። የሮም የንጉሥ የመስፍያኖስ ልጅ በተወለደ ጊዜ በንጉሥ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ። በንጉሥ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ። ሁንተናው ፈጽሞ ያማረ እንደ ጽጌ ረዳ ቀይ፣ ዓይኖቹም እንደ ንጋት ኮከብ የደመቁ፣ እንደ ፀሐይ ብርሃንም የሚያበሩ የአፉ አገላለጥ ያማረ፣ ከንፈሮቹም እንደ ፍሕሶ ቀይ ናቸው። ❤ አቡነ ገሪማ የሚባል ይህ ይስሐቅ የንጉሥ መስፍያኖስ ስሙ ቴዎዶስዮስ የሚባል የቊስጥንጥንያ ንጉሥ ልጅ የንግሥት ስፍንግያ ልጅ አርባ ቀን በሆነው ጊዜ ወደ ታላላቆች ሐዋርያት ቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት። የጳጳሳቱ አለቃ አባ ቴዎፍሎስም ከጳጳሳት ከኤጲስ ቆጶሳት፣ ከቀሳውስት፣ ከዲያቆናት፣ ከአናጒስጢስና፣ መዘምራን ከሕዝቡም ሁሉ ጋር ከደጋጎችን ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ሳለ፤ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወደ ሕጻናት መጠመቅያ ገቡ። በዚያ በተቀደሰው ቦታም የእግዚአብሔር መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል በመንፈስ ቅዱስ የተሠራ ጥሩ የሆነ የወርቅ ልብስ ይዞ ታኅሣሥ 17 ቀን ወረደ። ይህም ለሰማዕቱ ፊቅጦር ጥሩ የወርቅ ልብስ እንደ ወረደለት ነው። ያንም ልብስ ለጳጳሳቱ አለቃ ለአባ ቴዎፍሎስ ሰጠው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልም ለሊቀ ጳጳሳቱ ለአባ ቴዎፍሎስ ጥሩ የሆነ የወርቅ ልብስ በመስጠቱ ንጉሡንና ንግሥቲቱን ደስ አሰኛቸው። የጳጳሳቱ አለቃ አባ ቴዎፍሎስም ያን ልብስ ተቀብለው ከቅባ ሜሮን ጋር አስቀመጠው። የጳጳሳቱ አለቃ አባ ቴዎፍሎስም ለክርስትና ጥምቀት ሥርዓት የሚያስፈልገውን ሁሉን አቅርቦ የክርስትና ጸሎት ሥርዓትን ጀመረ ያን ጊዜ በቅብጽ ቀንድ ያለው ሜሮንና ቅብዕ ቅዱስ ውኃውም ፈላ። ❤ ከዚህ በኋላ አጠመቀው ቅብዕ ቅዱስና ቅብዐ ሜሮንን ቀባው መንፈስ ቅዱስም በነጭ ርግብ አምሳል ወረደለት። የክርስትና ጥምቀትን ከጠመቀው በኋላ አባ ገሪማ የሚባለው ሕጻን ቅዱስ ይስሐቅም ብርሃንን ለበሰ። እንደ መላእክትም ንጹሕ ሆነ። ያን ጊዜም የጳጳሳቱ አለቃ አባ ቴፍሎስም በታቦቱ ፊት አቀረበው። "የእንበረም ልጅ የእግዚአብሔር አገልጋይ ቅዱስ ሙሴን የባረከ የቅዱሳን አብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ ይባርክህ እያለ ባረከው። ንጽሕናሕንም እንደ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ያድርገው በዚህ ዓለም እርኩሰት እንደሌለባቸው መላእክትም ንጹሕ ሁን። ዳግመኛም ፊቱ ከሚከፍ መልአከ ሞት አይን ፊት ተሰውረህ ጌታችን በጌትነቱ እስሚመጣና እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሕያው ሁነህ ኑር" አለው። ይህንን ብሎ የጳጳሳቱ አለቃ ትንቢትን ተናገለት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ከተቀበለ በኋላ አባ ቴዎፍሎስ ሆይ የምሥራች መልክተኛ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ጽኑዕ በሚሆን በዚህ ማኅተም ይስሐቅን ታትሙት ዘንድ ይህን የፀጋ ማኅተም ተቀበሉ በሚል ቃል ወጣ። መልአከ ሞትና ክፉ የሚሆኑ አጋንንት እንዳያስደነግጡት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልና አባ ቴዎፍሎስ ይህን ሰምተው ጌታችን በጌትነቱ እኪመጣ ድረስ መልአከ ሞት እንዳይቀርበው አጋንንትን የሚያስደነግጥ በእግዚአብሔር ስም ማኅተምነት ሕጻን ይስሐቅን አተሙት። ❤ ዳግመኛም የጳጳሳቱ አለቃ አባ ቴዎፍሎስ "የሕይወትን ዘመን የእስራኤል አምላከ እግዚአብሔር የክብር ባለቤት የእግዚአብሔር ነቢያት እንደ ሆኑ እንደ ቅዱስ ዕዝራ፣ ቅዱስ ሄኖክና ቅዱስ አልያስ ሕይወት ያድርግ" ብሎ ባረከው። ያንጊዜም ያዩ ሕዝብ ፈጽመው አደነቁ። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዳሴ ቊርባን አዘጋጀ ቀድሶም በታወቀችውና በተረዳችው ታኅሣሥ 17 ቀን በኢትዮጵያ አገር የመደራ ሰው አባ ገሪማ የሚባል ንጉሥ ልጅ ሕጻን ቅዱስ ይስሐቅን አቈረበው። ቅድስት የምትሆን የሕጻን ቅዱስ ይስሐቅ በረከቱ ከአገራችን ኢትዮጵያና ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋር ትኑር ለዘለዓለም። በጸሎቱ ይማረን!አሜን። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ገሪማ።             

ብንያም፣ ዮሴፍ ነው። ❤ አባታችንም በሞት እንደሚያርፍና ቃልኪዳን እንደተሰጠው ነገራቸው። እነርሱም ስለ አባታችን ዕረፍት አዘኑ እርሱ ርእሰ ባሕታውያን ነውና። በቀዳሚት ሰንበትም እያላበው በድካም እንደልማዱ ለፍጥረቱ ሁሉ ወደ አምላኩ መማለድን ሳያቋርጥ ዋለ። በመሸም ጊዜ ሰውነቱ ሁሉ ደከመ፤ መናገርም ተሳነው፤ እነዚያ ቅዱሳን ግን ዕረፍቱን አይቶ ምስክር ይሆን ዘንድ ገብረ እንድርያስን ሊጠሩት ሔዱ፤ ቅዱሳኑም ወደ እርሱ ደርሰው የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ዕረፍት ነገሩት። እርሱም በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ፤ መራራ ለቅሶንም አለቀሰ፤ ተነሥቶም ከእነርሱ ጋር ሔዶ ብፁዓዊ አባታችን ወዳለበት ደረሰ። ያንጊዜም ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ ነበረ"። ❤ የአቡነ ገብረ እንድርያስ በዓለ ዕረፍታቸውም ኅዳር 7 ቀን በገዳማቸው በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ከአቡነ ገብረ እንድርያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከአቡነ ገብረ እንድርያስ ገድል መግቢያ ላይ የተወሰደ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_ወለተ_ክርስቶስ፦ ትውልዷ ሰሜን ጎንደር ሲሆን ከወለተ ጴጥሮስ ጋር አብራ በመሆን ካቶሊኮችን የተቃወመች ታላቅ እናት ናት። ካቶሊኮች በእጅጉ አሠቃይተዋቸዋል። ከእናታችን ቅድስት ወለተ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷም ይማረን!።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_እኅተ_ክርስቶስ፦ ትውልድ አገሯ ሸዋ ቡልጋ ጽላልሽ ነው። ታላቅ ሰማዕት ናት። ከወለተ ጴጥሮስ ጋር በሰማዕትነት ብዙ ከተሠቃየች በኋላ ካቶሊኮች አንገቷን በሰይፍ ቆርጠውታል። ከእናታችን ቅድስት እኅተ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷም ይማረን። ምንጭ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።               

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ኅዳር ፯ (7) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ደቡብ ወሎ ከወግዲ ከተማ በስተ ምዕራብ አቅጣጫ ከባሕር ጠለል 6652 ጫማ ከፍታ ላይ የሚገኘውን #ታላቁ_ገዳም_ደብረ ቆዘት_ለመሰረቱትና ያፈለቁት፤ #ጠበል_መቊጠሪያ_ለሚሰራው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ገብረ_እንድርያስ፣ #ለቅድስት_ወለተ_ክርስቶስና_ለቅድስት_እኅተ_ክርስቶስ ለበዓላቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የአቡነ_ገብረ_እንድርያስ_ደብረ ቆዘት፦ የሚባለው ገዳማቸው ደቡብ ወሎ ከወግዲ ከተማ በስተ ምዕራብ አቅጣጫ ከባሕር ጠለል 6652 ጫማ ከፍታ ላይ ይገኛል። ገዳሙ በአባይ ተፋሰስ ዙሪያ ከጣቀት ወንዝ በስተሰሜን፣ ከደብረ ዘመዶ ማርያም (ዘሞድ) መንደር በስተደቡብ ምሥራቅ እና ከደብረ ሰኮሩ ሥላሴ በስተምዕራብ አቅጣጫ ላይ ይገኛል። ❤ ደብረ ቆዘት አቡነ ገብረ እንድርያስ ገዳም የተመሠረተው በ995 ዓ.ም 10ኛው መ/ክ/ዘ ላይ ነው። የገዳሙም መሥራች አባ ገብረ ክርስቶስ የተባሉ ታላቅ ጻድቅ መሆናቸውን የአቡነ ገብረ እንድርያስ ገድል ይናገራል። ❤ ገዳሙ ያለበት አካባቢ አቡን ውኃ ተብሎ ይጠራል። ከገዳሙ ፊት ለፊት ከጣቀት ወንዝ ማዶ ደግሞ ዳቆን ውኃ (ደቆኑ) የሚባል አካባቢ ይገኛል። እነዚኽ አካባቢዎች ይኽንን መጠሪያ ያገኙት ቀድሞ በዚኽ አካባቢ በርካታ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት የነበሩበት እንደሆነና የቦታዎች መጠሪያም በቦታው ካሉ ምእመናን መኖሪያ ጋር የተያያዘ መሆኑን አባቶች ይናገራሉ። አቡን ውኃ በሚባለው አካባቢ አባ ኤልሳዕ፤ አባ ጎርጎርዮስ፣ አባ ገብረ ክርስቶስ፣ አባ ቅዱስ፣ አባ መስቀል፣ አባ ጉባ… የተባሉ ሰባት ቅዱሳን አባቶች በቦታው ይኖሩ እንደነበርና ከዚኽ ብዙ ሳይርቅ የዲያቆኖች መኖሪያ ሰፈር ስለነበር ቦታው "ደቆኑ" የሚለውን ስያሜ እንደተሰጠው አባቶች ሲናገሩ አካባቢው ዛሬም ድረስ ይኽንን መጠሪያ እንደያዘ ነው። አቡን በቀድሞው ዘመን ለጳጳስ ብቻ ሳይሆን ሥልጣነ ክህነት ላላቸው ቀሳውስትና መነኰሳት መጠሪያነት ያገለግል እንደነበር ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ባሕረ ሀሳብ በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ገልጠዋል።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የአቡነ_ገብረ_እንድርያስ፦ አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ እናታቸው አርሴማ ይባላሉ። ሁለቱም ደጋግ ቅዱሳን ናቸው። ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለመምህር ሰጧቸው። መምህሩም ጸጋ እግዚአብሔር እንዳደረባቸው ዐውቀው "ብዙዎችን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ" ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል። የመጻሕፍትንም ትርጓሜ በሚገባ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሌም ይባል አቡነ ገብረ እንድርያስ የነበረውን ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው። ጻድቁ በአቡነ ዮሐንስ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል። አባታችን ሙታንን በማስነሣትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። የትዉልድ ሀገራቸው በቤተ አምሃራ ክፍል ሀገረ ወለቃ ከገዳማቸው ቅርብ ርቀት ላይ "ደብረ ደብቄ ማርያም" እንደሆነና የአቡነ ገብረ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንደነበሩ እንዲሁም የመጀመሪያ ስማቸው ንፌታሌም ይባል እንደነበር፣ ካህንና የአምስት ልጆች አባትም እንደሆኑ በገድላቸው ላይ ተጽፎ ይገኛል። ❤ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ጽኑ የሆነውን ተጋድሏቸውንና መልካም አገልግሎታቸውን ፈጽመው በሞት ከማረፋቸው በፊት የገዳሙ አበምኔት ሆነው እንዲያገለግሉ ንፌታሌምን (አቡነ ገብረ እንድርያስን) መርጠው እንደሾሟቸው በመጽሐፈ ገድላቸው ላይ ተጽፏል። አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት ከሀገረ ወለቃ እስከ ጎጃም ድረስ ስብከተ ወንጌል እንዳስፋፉ የቤተ ክርስቲያን መዝገበ ቃላት በሚለው መጽሐፍ ላይ ተጽፎ ይገኛል። ❤ አቡነ ገብረ እንድርያስ በደብረ ርስኩር (በአሁኑ ደብረ ብርሃን ሰኮሩ ሥላሴ) ቤተ ክርስቲያን በሱባኤ ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በወርቅ ጽዋ ሰማያዊ ወይንና ሰማያዊ ኅብስት መግቧቸዋል። እንዲሁም አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ጽዋ ማየ ሕይወት ካጠጣቻቸው በኋላ ሕሙማንን እንደፈወሱ፣ ዕዉራንን እንዳበሩ፣ ሙት እንዳስነሡ በገድላቸው ላይ ተጽፏል። ❤ የአቡነ ገብረ እንድርያስ አባት የሆኑት የአቡነ ገብረ ክርስቶስ ጥንታዊ ውቅር ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ ጠፍ ሆኖ ስለቀረ ከዚሁ ገዳም አቅራቢያ የልጃቸው የአቡነ ገብረ እንድርያስ ገዳም ተመሥርቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አዲሱ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመርያ ጊዜ የተሠራው በዐፄ ድል ነአድ ዘመነ መንግሥት ሲሆን ከዚያም በኋላ በተደጋጋሚ እድሳት ተደርጎለታል። ❤ የአቡነ ገብረ እንድርያስ ገዳም ውጫዊ ገጽታ ጻድቁ አቡነ ገብረ እንድርያስ እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ጣቀት ወንዝ ከተባለው ቦታ ላይ በአንገታቸው ላይ ትልቅ ድንጋይ እየተሸከሙ ይጸልዩ እንደነበርና ይጸልዩበት ከነበረው ወንዝ ውስጥ በተኣምራት መቊጠሪያ የሚሠራ ጠበል እንደፈለቀላቸው በገድላቸው ላይ ተጽፏል። ❤ ከገዳሙ በስተደቡብ አቅጣጫ እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ጣቀት ወንዝ ከተባለው ቦታ ላይ በአንገታቸው ድንጋይ አሥረው ይጸልዩበት ከነበረው ጣቀት ወንዝ ላይ በተኣምራት መቊጠሪያ የሚሠራው ወንበረ ሥላሴ ጠበል እና ሌሎችም በርካታ ጠበሎች ይገኛሉ። እነዚኽም ጠበሎች ሕሙማን ከተለያዩ በሽታዎች ለመፈወስ ከማገልገላቸውም በላይ መነኰሳት ለጸሎት የሚገለገሉበትን መቊጠሪያ በተኣምራት ይሰጣሉ። አዘገጃጀቱም እንዲህ ነው፡- በመጀመርያ በጠበሉ ላይ ገመድ፣ ሣር ወይም ቀጭን ዕንጨት በመንከር ከቆይታ በኋላ በተነከረው ገመድ፣ ሣር ወይም ዕንጨት ላይ ጠንካራ ዓለት ይሠራል፤ ጠበሉ ውስጥ በተነከረው ገመድ ወይም ክር ላይ ውኃው በተኣምራት ወደ ጠንካራ ዓለትነት ይቀየራል። ከዚያም ገመዱን ወይም ክሩን ወይም ዕንጨቱን አሾልኮ በማውጣት ውስጡ ክፍት ስለሚሆን ያንን አስተካከለው እየከረከሙ መቊጠሪያ መሥራት ይቻላል። ❤ አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘወትር ዐርብ ዐርብ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደው የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን መካነ መቃብር ተሳልመው ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለው ለመምጣት ይመላለሱ የነበረው በአንድ ትልቅ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ነው።  ድንጋዩንም እንደ ደመና ይጠቀሙበት ነበር። ❤ ከዚኽም ሌላ ጻድቁን የዛፍ ዋርካ እንደ ጥላ ሆኖ ያገለግላቸው ነበር። እርሳቸውም ድንጋዩን እንደ አቡነ ገብረ እንድርያስ ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱበት ሠረገላ፣ ዋርካውን እንደ የነበረው ታላቅ ድንጋይ ጥላ እየተጠቀሙባቸው ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ እንደነበር በገድላቸው ላይ ተጽፏል። ያ እንደ ደመና ሠረገላ ሆኖ ለመጓጓዣነት ያገለግላቸው የነበረው ትልቅ ድንጋይ ዛሬም ድረስ በገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል። ❤ አቡነ ገብረ እንድርያስ ታላቁን ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ያሟሟቱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፤ ይኽም ማለት አቡዬ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል በሚገኘው ገዳማቸው በምድረ ከብድ ባረፉ ጊዜ አቡነ ገብረ እንድርያስ ከደቡብ ወሎ ወለቃ በእግዚአብሔር መንፈስ ተመርተው በቅዱሳንም ጥሪ ተደርጎላቸው ወደ ምድረ ከብድ መጥተዋል። ይኽም በአቡዬ ገድል ገጽ 83 ላይ እንዲህ ተብሎ በግልጽ ተጽፏል፡- "የአባታችን የገብረ መንፈስ ቅዱስ ዕለተ ዕረፍቱ በደረሰ ጊዜ ብዙ ኅቡዓን ቅዱሳን ወደእርሱ መጡ፣ ስማቸውም ፍሬ ቅዱስ፣ ዘርዐ ቡሩክ፣ ያዕቆብ፣