ch
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

前往频道在 Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

显示更多
638
订阅者
-224 小时
-57
-1130
帖子存档
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፲፮ (16) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ዐሥራ ሁለት ክንፈ ጸጋ ለተሰጣቸው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሐዋርያ_ክርስቶስ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወሩበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ሐዋርያ_ክርስቶስ፦ እኒህ ታላቅ ጻድቅ በኢትዮጵያ ሸዋ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ መርሐ ቤቴ በሚባል አካባቢ በሕግ ተወስነው ከሚኖሩ ደግነታቸው ከሚታወቁ የእመቤታችን ፍቅር ከበዛላቸው ዝክሯን ከሚዘክሩላት ቅዱሳን ቤተሰብ ከአባታቸው ከንዋየ ጽዮንና ከእናታቸው ፍቅርተ ኪሮስ ከተባሉ ደጋግ ክርስቲያኖች የተገኙ ናቸው። ❤ ቅዱስ ንዋየ ጽዮን እና ቅድስት ፍቅርተ ኪሮስ በደግነት ተግባራቸው ጸንተው በመገኘታቸው ከዕለታት አንድ ቀን የእመቤታችንን ዝክር ዘክረው እንግዶችን በሚያስተናግዱበት ወቅት ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስት ቅዱሳን እመቤታችን ድንግል ማርያም በቤታቸው በእንግድነት ተገኘች። እነርሱም በኢትዮጵያዊ የእንግዳ አቀባበል ሥርዓት በቤታቸው አስገብተው ምንጣፍ አንጥፈው፣ እግሯን አጥበው፣ በክብር አስተናግደው ሲሸኟት የጻድቁን የልደት ብሥራት ከእመቤታችን አንደበት ተነገራቸው። ❤ በዚህ ሁኔታ በዓመቱ ሐምሌ ፲፮ (16) ጻድቁ ተወልደው ዕድሜያቸው ፲፰ (18) ዓመት እስኪሞላ ድረስ ቤተሰባቸውን ሲረዱ ትምህርት ሲማሩ ቆይተው የምናኔን ሕይወት ጀመሩ። ❤ በአየለነ (በተለምዶ እየላ) ቅዱስ ሚካኤልና በሰሜን ደብረ በንኰል የምናኔ ሕይወታቸውን እያካሄዱ ሳለ ምንኲስናቸውም በደብረ በንኰል ተፈጸሞ በፈቃደ እግዚአብሔር በእመቤታችን አመልካችነትና በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ወደ ታላቁ የገድልና የትሩፋት ቦታቸው ተከዜ መጡ። በገዳሙም በታላቅ ተጋድሎ ገዳማዊ የምናኔ ኑሮአቸውን አጠናክረው በመቀበል በርካታ መናንያን መነኰሳትን ሲያስተዳድሩ ቆይተው ከፈጣሪ ጋር በግልጽ እስመነጋገር ድረስ ለከዊነ እሳት ደረጃ የደረሱ አባት ናቸው። ❤ ጻድቁ ጌታችን ስለ ሰው ልጆቾ ድኅነት የተቀበላቸውን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ከእሾህ እየወደቁ ደማቸውን እያፈሰሱ፣ በብዙ እያነቡ በቀራንዮ የተከፈለውን ውለታ እያዘከሩ በገድል በትሩፋት ሲኖሩ የዓለም መድኃኒት መድኃኔዓለም ተገልጦላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል። "እንዘ ለጸልዮ ትተግህ ለኑኃ ሌሊት ኲላ፤ ወእንዘ ትሰግድ በአሜከላ፤ ለምድረ ተከዜ እማዕከላ መሠጠከ አምላከ ቡላ" እንዲል። (መልክዐ አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ) ተከዜን ገዳማቸውንም አስባርከው፤ "ገዳምከ ትኩን ምዕራፈ ቅዱሳን አምሳሊሃ ለብሔረ ብፁዓን፤ ስሟም ምዕራፈ ቅዱሳን ትባልልህ የብሔረ ብጹዓን አምሳል ናት"፤ "ኢይትቀበር ውስቴታ ዓለማዊ ዘእንበለ ብእሲ ገዳማዊ፤ በውስጧም ገዳማዊ ውጪ አይቀበርባትም" በማለት ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። ❤ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም እጅ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን የተቀበሉ ሲሆን ግንቦት ፲፮ (16) ከልዑል እግዚአብሔር ዐሥራ ሁለት ክንፈ ጸጋ ተሰጥተዋቸው እንደነ ቅዱስ ነአኲቶ ለአብ፣ ቅዱስ ያሬድ ዐይነ ሞትን ሳያዩ ተሠውረዋል። መባርቅትን የሚያዙ፣ አጋንንትን የሚያሳድዱ ታላቁ ጻድቅ አባት ዛሬም ከገዳሙ አርድእት ጋር ከሚወጣው ጋር እየወጡ ከሚወርደውም ጋር እየወረዱ የሚረዱ በቅርብም በሩቅም ሆነው በቃል ኪዳናቸው ለተማጸናቸው በአማላጅነታቸው ለታመነባቸው የሚረዱ ናቸው። ከአቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ተከዜ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ አንድነት ገዳማ ከታተመው መጽሔት ላይ የተወሰደ።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለትንሣኤ_ሰባተኛ_ሳምንት #የክብር_ባለቤት_የጌታችን_የአምላክችን_የመድኃኒታች_የኢየሱስ_ክርስቶስ_የዕርገቱ_በዓል ለሚነገርበት ሰንበት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና እግዚአብሔር አምላክ አደረሰን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ #ሃሌ_ሉያ በ፫ "#በሰንበት_ዐርገ_ሐመረ ገሠፀ ባሕረ ወገሠፆሙ ለነፍሳት ወይቤሎሙ ኢትናፍቁ ወኢይምጻእ ኑፋቄ ውስተ ልብክሙ በከመ ፈነወኒ አቡየ አነኒ እፌንወክሙ #ውስተ_ቤተ_አቡየ ብዙኅ ማኅደር ቦቱ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ ከመ ተሀልዉ ምስሌየ #በመንግሥተ_አቡነ_ዘበሰማያት"። ትርጉም፦ #በሰንበት_ወደ_መርከብ_ወጣ፤ ባሕርን ገሠፀ፤ ነፋሳትንም ገሠፃቸው፤ አትጠራጠሩ፤ ጥርጥርም ወደ ልባችሁ አይምጣ አላቸው፤ #አባቴ_እንደላከኝ_እኔም_እልካችኋለሁ፤ በአባቴ ቤት ብዙ መኖርያ ማደሪያ አለ፤ ዳግመኛም ወደ እናንተ እመጣለሁ በሰማያት ባለው #በአባቴ_መንግሥት ከእኔ ጋር ትኖሩ ዘንድ እወስዳችኋለሁ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ በድጓው ላይ።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ። ወእግዚእነ በቃለ ቀርን። ዘምሩ ለአምላክ ዘምሩ"። መዝ 46፥5-6። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 10፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 1፥1-12። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 24፥45-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ዕርገቱ በዓል ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን።   

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ግንቦት ፲፭ (15) ቀን። ❤ እንኳን #ለሐዋርያው_ስምዖን ለተባለው #ለቅዱስ_ናትናኤል ለዕረፍት በዓል፣ በላይኛው ግብጽ ውስጥ በደንደራ ከተማ በሰማዕትነት ለዐረፉ #ለአራት_መቶ_ሰዎች ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከባሕታዊ_ሚናስ፣ #ከዲያቆንና_ከአባ_ሐርበጥላክያ ሰማዕታት ከሆኑ #ከኤስድሮስም_ማኅበር ከሆኑ #ቀርጢኖስና_ሚስቱ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያው_ስምዖን_የተባለው_ቅዱስ_ናትናኤል፦ እርሱም ናትናኤል ተብሎ ይጠራል በገሊላ አውራጃ የቃና ሰው ነው የኦሪትና የነቢያትንም መጻሕፍት ተምሮ ያወቀ ነው። መንፈሳዊ ቅንዓትም በውስጡ አለበት ስለዚህም ቀናዒ ተባለ እርሱም ንጹሕ ፊት አይቶ የማያደላ በሃይማኖቱ ዕውነተኛ ነው። ስለዚህ ፊልጶስ "ስለርሱ ሙሴ የጻፈለትን የዮሴፍ ልጅ የሚሉት የናዝሬቱን ኢየሱስ ክርስቶስን አገኘነው" ባለው ጊዜ "ከናዝሬት ደግ ሰው ሊወጣ ይችላልን?" አለው እንጂ አላደላለትም ፊልጶስም "ታይ ዘንድ ና" አለው። በመጣም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን "ይህ በልቡ ሽንገላ የሌለበት እውነተኛ እስራኤላዊ ነው" አለው። አሁንም ምስጋና ወደመቀበል አልተመለሰም "በየት ታውቀኛለህ" አለው እንጂ ልብንና ኵላሊትን የሚመረምር ጌታችንም "ፊልጶስ ሳይጠራህ በፊት በበለስ ዕንጨት ሥር አየሁህ" አለው። ያን ጊዜም የተሠወረውን የሚያውቅ አምላክ መሆኑን ተረድቶ "ጌታዬና ፈጣሪዬ በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ" አለው እንደ አይሁድ መምህራንም አልተቃወመም እርነሱ ከዚህ የሚበልጥ ድንቅ ተአምራትንና ኃይሎችን አይተው በእውነት አልተገዙምና። ❤ ስርሱ እንዲህ ተብሏል ጐልማሳ ሁኖ ሳለ ከአሕዛብ ወገን ከሆነ ጐልማሳ ጋራ ተጣልቶ አንዲት አመታትን መትቶ ገደለው በቤቱ ዐፀድም በአለ ዕፅ በለስ በሥሩ ቀበረው ይህንንም ማንም አላወቀበትም። ሁለተኛም በሕፃናት ዕልቂት ጊዜ እናቱ በአገልግል ውስጥ አድርጋ በበለስ ዕንጨት ላይ ሰቅላ ትሸሽገው እንደ ነበር በጭልታም አውርዳ አጥብታ መልሳ ትሰቅለዋለች የመከራውም ጊዜ ጸጥ እስከ አለ ድረስ እንዲህ ታደርግ ነበር። መድኃኒታችንም በምልክት ከእርሱ የሆነውን በገለጠለት ጊዜ የተሠወረውን የሚያውቅ ሁሉንም የሚመረምር በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተረዳ። ያንጊዜም ራሱን ዝቅ አድርጎ ለመድኃኒታችን ተገዛለት። ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ ተከተለው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያትም ጋራ ተቈጠረ። ❤ አጽናኝ የሆነ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በተቀበለ ጊዜ የአገሩ ሁሉ ቋንቋ ተገለጠለት መለኮታዊ ምሥጢርንም አወቀ ወደ ኵርጅ አገርና ወደ እልብጅህ ከተማ በሀድያን በድንቁርና ወደሚኖሩበት ሁሉ ገብቶ የሃይማኖትን ብርሃን አበራላቸው። ከተራቃቂዎችና ከሰነፎችም ብዙዎችን መልሶ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ሃይማኖት ልባቸውን አበራላቸው። የክርስትና ጥምቀትንም አጥምቆ ነጣቂዎች ተኵላ የነበሩትን የዋሃን በጎች አደረጋቸው። ❤ ሁለተኛም ወደሌሎች የከሀድያን አገሮች ወደ በራንጥያ ደሴትም ሒዶ በውስጣቸው ሰበከ። ይዘውም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት እርሱ ግን ኃይልና ብርታትን ተጨመረ በእግዚአብሔርም ኃይል ሙታንን አስነሣ እንዲአጠምቃቸውም ለመኑት የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ብዙ ዘመንም ኖረ። ከዚያም በኋላ ከሀድያን ይዘው በዕንጨት ላይ ሰቀሉት በዚህም ምስክርነቱን ፈጽሞ ከወንድሞቹ ሐዋርያት ጋራ የማይጠፋ መንግሥት ወረሰ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ናትናኤል ጸሎት ይማረን ለሁላችን የክርስቲያን ወገኖችም በረከቱ ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አራት_መቶ_ሰማዕታት፦ ብዙ ሥቃንም ሲያሠቃዩአቸው ከኖሩ በኋላ የምስክርነታቸው ፍጻሜ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት መጨረሻ ራስን በመቆረጥ ሆነ። በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 15 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ዕብል_ብእሴ_ምሁር። ዘመጽሐፈ ኦሪት ሕገ ወዘነቢያት መዝሙረ። አመ ውእቱ ወሬዛ ታሕተ ዕፀ በለስ ዘገብረ። #ወልደ_ማርያም_አምላክ ሶበ ኅቡአቶ አእመረ። ለትእዛዘ #ጽድቁ_ናትናኤል_ገረረ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_15።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ብፁዕ ብእሲ ዘኢኈለቈ ሎቱ እግዚአብሔር ኃጢአቶ። ወዘአልቦ ጽልሑት ውስተ ልቡ። እስመ አርመምኩ በልያ አዕፅምትየ"። መዝ 31፥2-3። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥44-ፍ.ም።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 8፥24-35፣ ይሁ 1፥17-23 የሐዋ ሥራ 1፥12-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥1-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ነው። መልካም የሐዋርያው ስምዖን የተባለው የቅዱስ ናትናኤል የዕረፍት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ በዚያም ዐሥራ አምስት ዓመት ከኖረ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአንድ ቄስ ተገለጸችለት ቦታውንም አመልክታ እንዲህ አለችው። "የእግዚአብሔር ሰው ገብረ ክርስቶስን ይዘህ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስገባው ከውጭ አትተወው" ቄሱም እመቤታችን እዳዘዘችው አደረገ። ❤ ከዚህም በኋላ የተመሰገነ ገብረ ክርስቶስ በሌሊት ተነሣ ከእመቤታችንም ሥዕል ፊት ቁም ጸለየ እንዲህም አላት "እመቤቴ ሆይ የተሠወረ ሥራዬን አንቺ ለምን ገለጥሽ አሁንም ወደሚሻለኝ ምሪኝ" ይህንንም ብሎ የእመቤታችንን ሥዕሏን ተሳልሞ በሌሊት ወጥቶ ወደ ባሕሩ ወደብ ደረሰ ወደሌላ ሀገርም ሊሔድ ወዶ በመርከብ ተሳፈረ። ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ከአባቱ አገር ደረሰ የአባቱና የእናቱም ባሮች እየናቁትና እየሰደቡት በአባቱ ደጅ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። ሲገቡና ሲወጡም ሽታው እንዳያስጨንቀን "ይህን ምስኪን አስወግዱልን" ይላሉ ወጭትና ድስትም አጥበው በላዩ ይደፉበታል ውሾችም እንዲናከሱበትና እንዲበሉት የሥጋ ትርፍራፊ ይጥሉበታል ውሾች ግን ቁስሉን ይልሱለት ነበር እንደዚህም አብዝተው አሠቃዪት ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ለመነ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአባቴና ለእናቴ ባሮች በደል እንዳይሆንባቸው ወዳንተ ውሰደኝ"። በዚያንም ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው። ከዚህም በኋላ ገድሉን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ጻፈ በእጁም ጨብጧት ጥቅምት 14 ቀን ዐረፈ። ❤ በእሑድ ቀንም ሕዝቡ ሁሉና ካህናቱ ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር በቅዳሴ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሳሉ "የእግዚአብሔርን ሰው በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ቤት ፈልጉት" የሚል ቃል ከሰማይ ሰሙ በዚያን ጊዜ ሔደው በአረፈበት ቦታ አገኙት። በእጁም ውስጥ የተጨበጠ ክርታስን አዩ ሊወስዷትም ሽተው መውሰድ ተሳናቸው ። ❤ በአንድነትም በጸለዩ ጊዜ እጁ ተፈትታ ወስደው አነበቧት አባትና እናቱም ልጃቸው እንደሆነ አወቁ ታላቅ ጩኸትም ሆነ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ አክብረውም ቀበሩት መቃብሩም በሽተኞችን ሁሉ በመፈወስ ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራትን የሚያደርግ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 14 ስንክሳር።

❤ አቡነ ያሳይ በ13ኛው መ.ክ.ዘመን በአባታቸው የዘመነ ንግሥና መጨረሻ ወደ አርባ ምንጭ ሄደው ከዚያው ሱባኤ ገብተው ፈጣሪያቸውንነ ቢማጸኑ እግዚአብሔርም ከዚያው አካባቢ የሚኖር አንድ ባሕታዊን የመድኃነዓለምን ጽላት እንዲወጣላቸው አዘዘላቸው፡፡ እርሳቸውም ጽላቱን ተቀብለው በጎጃም በኩል አድርገው ወደ ጣና ተመልሰው በዘጌ አከባቢ ሲደረሱ ከጣና ባሕር ዳር ቆመው በየብስ ያለውን ርቀትና በባሕሩ ያለውን ቅርበት አይተው አሁንም ወደ ፈጣሪያቸው በጸሎት ተማጸኑ፡፡ በዚህም ጊዜ ጌታችን ተገልጦላቸው "ወዳጄ ያሳይ ሆይ አትጨነቅ እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፣ ከጎንህ ያለውን ድንጋይ በባሕሩ ላይ ጫነው፤ ድንጋዩም ለልጅ ልጅ እኔ ዓለምን ለማሳለፍ እስከምመጣበት ሰዓት ድረስ መታሰቢያ ትሁንህ" አላቸውና ተሰወረ፡፡ አቡነ ያሳይም የመድኃኔዓለምን ጽላት ይዘው በድንጋዩ ላይ እንደተቀመጡ ድንጋዩ እንደታንኳ በባሕሩ ላይ ተንሳፈፈ፡፡ ባሕሩም ከማዕበሉ ብዛት የተነሣ ይታወክ ነበር፡፡ አባታችንም ያለ ምንም ቀዘፋ ልብሳቸውም ውኃ ሳይነካው ቁጭ እንዳሉ ማን እንደአባ ወደ ተባለው ቦታቸው ደረሱ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አቡነ ያሳይ ገዳማቸውን ገድመው ወንድሞቻቸውን ሰብስበው በተጋድሎ በመኖር ብዙ ቅዱሳንን አፍርተዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የጌታችንን እግር ያጠቡት አቡነ አብሳዲ፣ እንደ ነቢዩ ኤልያስ ዝናብንና ነፋስን የከለከሉት አቡነ ያዕቆብ፣ እሬትን እንደ ማር ያጣፈጡት አቡነ ገብረ ኢየሱስ፣ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተሞሉት አቡነ ዳንኤል፣ እንደ ንጉሥ ሰሎሞን ጥበብን የተሞሉት አቡነ ፊቅጦርና ሌሎችም ብዙዎች ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱም ብዙ የበቁ ቅዱሳን በአካባቢው ነበሩ፡፡ በአጽፋቸውና በእግራቸው በባሕሩ ላይ የሚሄዱ ነበሩ፣ በጸጋ ክንፍ ተሰጥቷቸውም የሚበሩ ነበሩ፡፡ የአቡነ ያሳይ ተአምራቶቻቸው ተነግረው አያልቁም፡፡ በወቅቱ የነበሩት ቅዱሳን ልጆቻቸው "ከቅዱሳን ማን እንደ አባ ያሳይ በከባድ ድንጋይ ላይ ተጭኖ በባሕር ላይ የተጓዘ አለና.." ብለው ይገረሙባቸው ነበር፡፡ ቦታቸውም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ "ማን እንደ አባ" ተባለ፡፡ ይህም የአቡነ ያሳይ ገዳም በሰሜን ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት በደንቢያ ወረዳ በጎርጎራ ጣና ሐይቅ አካባቢ ይገኛል፡፡ ❤ በጣና ደሴት ላይ ከሚገኙት ታሪካዊ ቦታዎች ውስጥ አንዱ "አትማረኝ ዋሻ" ነው፡፡ ይህም ዋሻ ታሪኩ ከአቡነ ያሳይ ጋር የተገናኘ ነው፡፡ ታሪኩም እንዲህ ነው፦ አትማረኝ ዋሻ በጣና ሐይቅ ደሴቶች መካከል ከሚገኙ ገዳማት መካከል ከማን እንደ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም በስተ ምዕራብ አቅጣጫ የጣና ሐይቅን ጉዞ ከገታው አንድ ተራራ ሥር የሚገኝ ዋሻ ነው፡፡ ይህ ዋሻ ለብዙ ዘመናት አንድ ታላቅ አባት የጸሎት በዓት አድርገውት "አትማረኝ" እያሉ የጸለዩበት ቦታ ነው፡፡ አቡነ ያሳይ ወደ ጣና ደሴት ከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እና አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ጋር በመሆን በጸሎት ይተጉ እንደነበር ገድላቸው ይናገራል፡፡ ከእግዚአብሔር በተሰጣቸውም ጸጋ በጣና ሐይቅ ላይ እንደ ጀልባ የሚጓዙበት አንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ በጣና ደሴት ላይ ለአገልግሎት በመፋጠን ላይ እያሉ ዛሬ አትማረኝ ዋሻ ተብሎ ወደሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ አንድ አባት ዋሻው ውስጥ "አትማረኝ፣ አትማረኝ፣ አትማረኝ" እያሉ ሲጸልዩ ያገኟቸዋል፡፡ አቡነ ያሳይም በሰውዬው ጸሎት በመገረም ቀርበዋቸው "አባቴ ምን ዓይነት ጸሎት ነው የሚጸልዩት?" አሏቸው፡፡ ያም አባት "አባቴ እንደ እርስዎ ያሉ አባት መጥተው "አትማረኝ" እያልክ ጸልይ ብሎኝ ነው" በማለት መለሱላቸው፡፡ አቡነ ያሳይም "እንዲህ ዓይነት ምክር የሚመክር ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡ ከዛሬ ጀምረው "ማረኝ" እያሉ ይጸልዩ በማለት አቡነ ዘበሰማያትን አሰተምረዋቸው ይሄዳሉ፡፡ "አትማረኝ" እያሉ ይጸልዩ የነበሩት አባትም "ማረኝ" እያሉ መጸለያቸውን ቢቀጥሉም ብዙ መግፋት ሳይችሉ ቀሩና ጸሎቱ ይጠፋባቸዋል፡፡ ወደ ሐይቁ ሲመለከቱም አቡነ ያሳይ ድንጋዩን እንደጀልባ ተጠቅመው እየሄዱ ነው፡፡ ጸሎቱን ያስጠኗቸው አቡነ ያሳይ ርቀው ሳይሄዱባቸው ያ አባት በውኃ ላይ በእግራቸው እየተራመዱ በመከተል ይደርሱባቸዋል፡፡ ከኋላቸውም ሆነው "አባታችን ያስጠኑኝ ጸሎት ጠፋብኝ፤ እባክዎን እንደገና ያስተምሩኝ" አሏቸው፡፡ አቡነ ያሳይም ሐይቁን በእግራቸው እረግጠው እስኪሄዱ ድረስ ጽድቃቸው የተገለጠውን የእኚህን አባት መብቃት ተመልከተው "አባቴ እግዚአብሔር የልብ ነውና የሚመለከተው እንዳስለመዱት ይጸልዩ የእርስዎ ይበልጣል" ብለዋቸው ሔዱ፡፡ በዚህም ምክንያት ቦታው "አትማረኝ ዋሻ" ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ከአባታችን ከአቡነ ያሳይ ዘመዳባ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የቊስጥንጥንያ_ንጉሥ_የቴዎዶስዮስ ልጅ መሽራው #ቅዱስ_ገብረ_ክርስቶስ፦ ይህም ቴዎዶስዮስ እግዚአብሔርን የሚፈራ ነው ሚስቱም በጎ የምትሠራ እግዚአብሔርንም የምትፈራ ናት ስሟም መርኬዛ ነው። እነርሱም ልጅ ስለሌላቸው ያዝኑ ነበር ወደ ኢየሩሳሌምም ሒደው ስእለትን ተሳሉ ቸር መሐሪ ወደሆነ እግዚአብሔርም ለመኑ እርሱም ልመናቸውን ተቀበሎ ይህን ያማረ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም "አብደልመሲህ" ብለው ሰየሙት ትርጓሜውም "ገብረ ክርስቶስ" ማለት ነው ። የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ የሥጋዊንም ትምህርት አስተማሩት ። ❤ አድጎ በጕለመሰም ጊዜ የሮሜውን ንጉሥ ልጅ አጭተው እንደ ሥርዓቱ አጋቡት ከሌሊቱ እኩሌታም በሆነ ጊዜ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ተነሥቶ ወደሙሽራዪቱ ገባ እጅዋንም ይዞ ከእርስዋ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ። ከዚያም የሃይማኖት ጸሎት በአንድ አምላክ እናምናለን የሚለውን እስከ መጨረሻ ጸለየ የተሞሸረበትንም ልብስ ከላዩ አውልቆ የግምጃ ልብስን ለበሰ ወደ ሙሽሪቷም ሒዶ ራስዋን ሳማት እንዲህም እያለ ተሰናበታት "እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይኑር ከሰይጣን ሥራ ሁሉ ያድንሽ"። እርሷም አልቅሳ "ጌታዬ ወዴት ትሔዳለህ ለማንስ ትተወኛለህ" አለችው እርሱም "በእግዚአብሔር ዘንድ እተውሻለሁ እኔም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን ልከተለው እሔዳለሁ የአባቴ መንግሥት አላፊ ነውና አንቺም መሐላሽን አስቢ" አላት ያን ጊዜ መሐላዋን አስባ ዝም አለች። ❤ ለሠርጉም የታደሙት ሁሉ እንደተኙ በሌሊት ወጥቶ ሔደ ወደ ባሕርም ዳርቻ ደርሶ በመርከብ የሚጓዙ መንገደኞችን አገኘ የዓመት መንገድ ወደሚሆን አርማንያም እስከሚደርስ ከእነርሱ ጋር ተጓዘ። ነግቶ ወደ ሠርጉ አዳራሽ አባትና እናቱ በገቡ ጊዜ ሙሽራውን ልጃቸውን አላገኙትም ሙሽሪትንም "ልጃችን ወዴት አለ?" ብለው ጠየቋት እርሷም እንዲህ አለቻቸው። "በሌሊት ወደ እኔ ገባ መሐላን አማለኝ ከእኔ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ ራሴንም ስሞኝ ከእኔ ዘንድ ወጣ እኔም እያለቀስኩ ብቻዬን አደርኩ" ነገርዋንም ሰምተው ወድቀው በመጮህ ታላቅ ልቅሶን አለቀሱ ። ❤ በዚያችም ጊዜ በሀገሮች ውስጥ ሁሉ ልጁን ገብረ ክርስቶስን ይፈልጉት ዘንድ ንጉሡ አምስት መቶ አገልጋዮቹን ላከ ለድኆችና ለምስኪኖችም ምጽዋት አድርገው የሚሰጥዋቸውን ብዙ ገንዘብን ሰጣቸው። ገብረ ክርስቶስ ግን በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በአርማንም አገር በተሠራች በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ደጅ የሚኖር ሆነ። አባቱ የላካቸውም ሁለቱ አገልጋዮች ከዚያ ደርሰው ስለርሱ መረመሩ ግን ወሬውን ማግኘት ተሳናቸው ለድኆችም ምጽዋትን ሰጡ እርሱም ከድኆችም ጋር ምጽዋትን ተቀበለ።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት ፲፬ (14) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_ከሰባቱ_ከዋክብት ለአንዱ ድንጋዩን እንደ ጀልባ ተጠቅመው የጣናን ሐይቅ ለተሻገሩት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ያሳይ_ዘማንዳባ ለዕረፍት በዓልና ለጻድቁ ቅዱስ #ገብረ_ክርስቶስ ከሙሽራ (ከጫጉላ) ቤት ለመነነበት ቀን ዓመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ያሳይ_ዘማንዳባ፡- አቡነ ያሳይ "ሰባቱ ከዋክብት" ከሚባሉት የሀገራችን ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ እነዚህም "ሰባቱ ከዋክብት" የተባሉት አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ ያሳይ ዘማንዳባ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየፃ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣ፣ አቡነ ታዴዎስ ዘባልታርዋ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤ እና አቡነ ዮሐንስ ዘጉራንቄ ናቸው፡፡ እነዚህን የመላእክትን ሕይወት በምድር የኖሩ ታላላቅ የሀገራችንን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ አስተምረውና አመንኲሰው ለጽድቅ ያበቋቸው አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን" የተባሉት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ የኢትዮጵያ ብርሃኗ በሆኑት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ ከመነኰሱ በኋላ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በተራቸው ያስተማሯቸውና ያመነኰሷቸው መነኰሳት ቁጥራቸው በውል አይታወቅም፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለአቡነ መድኃኒነ እግዚእ "ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከዋክብት ቅዱሳንን" በመንፈስ ቅዱስ እንደሚወልዱ ትንቢት ተናግረውላቸው ነበር፡፡ የተንቤኑን አቡነ ዐቢየ እግዚእን፣ የዞዝ አምባውን አቡነ አብሳዲን ጨምሮ አባታችን መድኃኒነ እግዚእ ብርሃን ሆነው በጣም ብዙ ቅዱሳንን ያመነኰሱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ነው "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን" የተባሉት፡፡ ❤ አቡነ መድኃኒነ እነዚህንም ሰባቱን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ ሲያመነኲሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድ ላይ የመነኰሱት እነዚህ ሰባቱ ቅዱሳን "ሰባቱ ከዋክብት" እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ እነዚህም ሰባቱ ከዋክብት የጣናን ባሕር በእግራቸው ጠቅጥቀው ተሻግረው ብዙዎቹን ደሴቱ ላይ ያሉ አስደናቂ የጣና ገዳማትን የመሠረቱት ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ባሕሩን በእግራቸውም እየረገጡ ጠቅጥቀው የተሻገሩ አሉ፤ በሌላም ቦታ በየብስ የተሰማሩትም ቢሆኑ መጻሕፍቶቻቸውን በአንበሳ ጭነው የተጓዙ አሉ፤ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይን እንደጀልባ ተጠቅመው በእርሱ ላይ ሆነው ወደ ደሴት የገቡ አሉ፡፡ አንዱ ዛሬ በዓላታቸውን የምናከብራለቸው አቡነ ያሳይ ናቸው፡፡ ቅዱስ ዳዊት "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው" መዝ 67፥35 ብሎ እንደተናገረ ጻድቁ አቡነ ያሳይ ከእግዚአብሔር በተሰጣቸውም ጸጋ ጣና ሐይቅን የሚያቋርጡት በአንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ድንጋዩን እንደ ጀልባ ተጠቅመው ነበር፡፡ ያ ድንጋይ ዛሬም ድረስ በገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ጻድቁ ከአቡነ ሳሙኤል ጋር አብረው ወደዚህ ቦታ መጡ፡፡ ከዚያም የቦታው አቀማመጥ የብስ መሬትና ደሴት መሆኑን አይተው "እግዚአብሔር ፈቅዶ ይችን ደሴት የጸሎት ቦታችን አድርጎ ቢሰጠን በጸሎት እንጠይቀው" ተባብለው ሁሉቱም ቅዱሳን ሱባኤ ገቡ፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንም ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ በገሃድ ተልጦላቸው "ወዳጄ ሳሙኤል ሆይ ይህ ቦታ የአንተ አይደለም የወንድምህ የያሳይ ቦታ ነው፡፡ እኔ ወዳዘጋጀሁልህ ቦታ ወደ ዋሊ ሂድ" ብሎ የዋልድባን ምድር አሳያቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤልም የጌታችንን ትእዛዝ ተቀብለው ወንድማቸውን አቡነ ያሳይን ተሰናብተው ወደ ዋልድባ ሄደው ገዳማቸውን አቅንተው ተጋድሎቸአውን በዚያ ፈጸሙ፡፡ ❤ ጌታችን ዳግመኛም ለአቡነ ያሳይ ተገለጠላቸውና "ወዳጄ ያሳይ ሆይ የአባትህን መንግሥትና የዓለሙን ክብር ከምኞቱ ጋር ለእኔ ብለህ ስለተውክ ይህንኑ ቦታ በዚህ ዓለም ሳለህ ለአንተ፣ ወደ ዘላለማዊ መንግሥቴ ከወሰድኩህ በኋላም ለልጆችህ ምንዳህ አድርጌ ሰጥቼሃለሁ፤ ምሕረቴንም በቦታህ አዘንባለሁ ቸርነቴም አይለያትም፣ ብዙ የመንፈስ ልጆችንም ታፈራለህ፤ ቦታህም እኔ ለፍርድ እስክመጣ ድረስ ትኖራለች" በማለት ቃልኪዳኑን አቆመላቸውና ተሰወራቸው፡፡ "ምንዳህ" ማለት ደመወዝ ማለት ነውና በዚህም "ማንዳባ" ማለት "የአቡነ ያሳይ ምንዳ-ደመወዝ" ማለት ነው ሲሉ አባቶች ገዳሙን "ማንዳባ-ምን እንደ አባ" ብለው ሰየሙት፡፡ ❤ አቡነ ያሳይ፦ የትውልድ ሀገራቸው ሸዋ ተጉለት ነው፡፡ አባታቸው ንጉሡ ዓምደ ጽዮን ቀዳማዊ ነው፡፡ ይኸውም ከ1296-1326 ዓ.ም የነበረው ነው፡፡ አቡነ ያሳይ በልጅነታቸው በንጉሡ አባታቸው ቤት ሲኖሩ የገዳማ መነኮሳት ለመንፈሳዊ ሥራ ወደ ንጉሡ ዘንድ እየመጡ ደጅ ሲጠኑ ያዩአቸዋል፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችን ገና በልጅነታቸው የመነኰሳቱን እግር ያጥቡ ስለነበር በዚሁ አጋጣሚ መነኰሳቱን ስለምንኲስና ሕይወት ይጠይቋቸው ነበር፡፡ መነኰሳቱም ሕይወታቸውን ያስረዷቸዋል፡፡ አቡነ ያሳይም ብሉያትንና ሐዲሳትን ከልጅነታቸው ጀምሮ የተማሩ ስለነበር የአባቶችን ትምህርትና የወንጌልን ቃል በማገናዘብ የፈጣሪያቸው ፍቅር በልቡናቸው እንደ እሳት ነደደ፡፡ ይልቁንም "ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል" የሚለውን የጌታችንን ቃል አሰቡ፡፡ ማቴ 16፥26፡፡ ከዚህም በኋላ የንጉሡ አባታቸውን የአልጋ ወራሽነት ማለትም የንጉሥነትን ክብር ፈጽመው በመናቅ "እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር እራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ" ማቴ 16፥27 ያለውን የጌታችንን ቃል አስበው ንጉሣውያን ቤተሰቦቻቸውን ጥለው ለምነና ወጡ፡፡ ❤ ለምነና እንደወጡም ከሸዋ ተነሥተው ወደ ትግራይ ክፍለ ሀገር በአክሱም አቅራቢያ ከሚገኘው ገዳም ደብረ በንኰል ከሚባለው ከአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ደረሱ፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም አቡነ ያሳይ የእግዚአብሔር ጸጋ ያደረባቸው ሰው መሆናቸውንና ወደ እርሳቸውም እየመጡ መሆኑን በመንፈስ ዐውቀውት ስለነበር በደስታ ተቀበሏቸውና በረድእነት ከወንድሞቻቸው ጋር ጨመሯቸው፡፡ አቡነ ያሳይም የገዳም መነኰሳትን በማገልገል በመንፈሳዊ ተጋድሎ ብዙ ደከሙ፡፡ በደብረ በንኰል ገዳምም ብዙ አስገራሚ ተአምራትን አደረጉ፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ ወደ መካነ ገድላቸው በጣና አካባቢ እንደሆነ ነገራቸው፡፡ "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን" የተባሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም ቀደም ብለን የጠራናቸውን "ሰባቱን ከዋክብት" ምግባር ሃይማኖታቸውን፣ ተጋድሎ ትሩፋታቸውንና ገቢረ ተአምራታቸውን አይተው ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቀው በአንድ ቢያመነኲሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ ከዚህም በኋላ ከሰባቱ ቅዱሳን ውስጥ ሦስቱ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ ያሳይ እና አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ሆነው ከደብረ በንኰል ገዳም አባታቸውን አቡነ መድኃኒነ እግዚእን ተሰናብተው ወደ ጣና ደሴት መጥተዋል፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ግንቦት ፲፬ (14) ቀን። ❤ እንኳን #ከመንፈሳውያን_ሐዋርያት ጋር አንድነት ላላቸው ለከበሩ አባት የገዳማውያን የአንድነት ማኅበር ለመሰረቱ #ለአባ_ጳኵሚስ ለዕረፍት በዓልና በምስር ገዢ በሆነ በቡላሚስ ዘመን ከአገረ ፈርማ ሰማዕት ከሆነ #ለአባ_ሲማኮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ ከሚታሰቡ፦ #ከአባ_ሲማኮስ ጋራ ሰማዕትነት ከተቀበሉ #ከአንድ_ሺህ_ሰባት_መቶ_ሃምሳ ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ጳኵሚስ፦ ይህም ቅዱስ ከአባ ጰላሞን ዘንድ መንኵሶ ሲያገለግለው የምንኵስናንም በጎ ሥራ እየሠራ ብዙ ዘመናት ኖረ። ከዚያም በኋላ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገልጾለት እንደ አባቶቻችን ሐዋርያት የአንድነትን ማኅበር ለመሥራት መነኰሳትን እንዲሰበስብ አዘዘው። ከዚህም በኋላ ብዙዎችን ሰዎችን ሰብስቦ በየቦታው ብዙ ገዳማትን ሠራላቸው። ለሁሉም በእጃቸው ሠርተው የሚአገኙትና በምግባቸው አንድነት እንዲሆኑ በጸሎት ጊዜ በመብልም የሚሠሩትን ሥርዓት ሠራላቸው እርሱ ከሁሉም በላይ አበ ምኔት ሁኖ ከበታቹ በገዳማት ለየአንዳንዱ አበ ምኔት ሾመላቸው። በአገረ እስዋን ወሰን ከአትፉ ከአክሚም ከተናዱስ እስከ ላዕላይ ግብጽ መጨረሻ ከደቡብም ከባሕራውያን የተመሳቀለ መንገድ ድረስ ሁሉንም ገዳማት በመዞር ይጐበኛቸዋል። ❤ ይህም አባት ስለዚህ ዓለም ከንቱ ውዳሴና በመካከላቸውም ጥል እንዳይኖር ከልጆቹ ክህነትን እንዲሾሙ አያሰናብትም ግን ለየአንዳንዱ ገዳም የሚቀድሱላቸውን ቀሳውስት ከዓለም አደረገ። ሊቀ ጳጳሳት ሐዋርያዊ አትናቴዎስ ወደ ላዕላይ ግብጽ በመጣ ጊዜ ይህን አባት ጳኵሚስን ቅስና ሊሾመው ወደደ። ከእርሱም ሸሸ። የከበረ አትናቴዎስም ልጆቹን "የማይናወጽ ቤትን የሠራህ ሆይ ከከንቱ ውዳሴ የራቅህ አንተ ብፁዕ ነህ ልጆችህም ብፁዓን ናቸው ብሎሃል በሉት አባታችሁን" አላቸው። ❤ አንድ ጊዜም ሲዖልን ያይ ዘንድ ወደደ እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ አውጥቶ በገነት የጻድቃንን ማደሪያ እንዲሁም በሲዖል የሥቃይን ቦታ አሳየው። ይህም አባት በአንድ ማኅበር ላይ እያጽናናቸውና ሥርዓትንም እየሠራላቸው አበ ምኔት ሁኖ አርባ ዓመት ኖረ። ከዚያም በኋላ በእርሱ ፈንታ ደመ መዝሙሩን ቴዎድሮስን ሹሙላቸው ግንቦት 14 ቀን በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጳኵሚስ በአማላጅነቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።                           ✝️ ✝️ ✝️              ❤ #አባ_ሲማኮስ፦ ይህ ቅዱስ ቀጭን ልብሶችንና የከበሩ የሐር ልብሶችን የሚሠራ ነው። ወላጆችም አሉት እነርሱም ቴዎድሮስና ሲሲኮስ ናቸው። ቡላሚስ የሚባለው ከሃዲ መኰንን ክርስቲያኖችን ሊያሠቃይና ሊገድል እንደመጣ በሰማ ጊዜ አባ ሲማኮስ ሰማዕት ይሆን ዘንድ ወደደና ቤተሰቦቹን ተሰናብቶ ወደ ሰማዕትነት አደባባይ ወጣ፡፡ ወደ ሀገረ ድሜራ ቅርብ ወደሆነ ወደ ሀገረ በክሩዝ ሄዶ ከሃዲውን መኰንን አገኘው፡፡ እርሱም አንዲቷን ሰማዕት ይዞ ሲያሠቃያትና ወደ እሳቱ ምድጃ ሲጨምራት እሳቱም በተአምራት ሲቀዘቅስ ተመለከተ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ሲማኮስ በፊቱ ቆሞ የጌታችንን ክብር መሰከረ፡፡ ❤ መኰንኑም አባ ሲማኮስን ይዞ ብዙ አሠቃየው፡፡ በዚህ ጊዜም አባ ሲማኮስ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነበር፡፡ በመጀመሪያ ሰቀሉት፤ ቀጥለውም ከመንኰራኩር ውስጥ ጨምረው አበራዩት፡፡ ከእርሱም ብዙ ደም ፈሰሰ፡፡ አንዲትም ዐይኗ ሥውር የነበረች ሴት ደሙ ፈሶ ዐይኗን በነካት ጊዜ ዐይኗ ዳነ፡፡ ❤ ከዚኽም በኋላ ደግመው በእንጨት ላይ ሰቅለው አሠቃየው፡፡ በሥቃይም ላይ ሆኖ ወደ ጌታችን በለመነ ጊዜ አዳነው፡፡ መኰንኑም የአባ ሲማኮስን ራስ በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ፡፡ ሰያፊውም ይቆርጠው ዘንድ ሰይፉን መዘዘ ነገር ግን ኃይል ተነሥቶት ማነቀሳቀስ አቃተው፡፡ እንዲሁም ሁለተኛው፣ ሦስተኛው … እስከ ዐሥራ አራት ሰይፈኞች ኃይላቸው ደከመ፡፡ እነርሱም በምድር ላይ ወደቁ፡፡ ከዚህም በኋላ በአንገቱ ገመድ አስገብተው እስከ ረጅም ተራራ አናት ድረስ ጎተቱት፡፡ ነፍሱንም በክብር ባለቤት በጌታችን እጅ አሳልፎ ሰጥቶ የምስክርነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ከወታደሮቹም ውስጥ ዲዳና ደንቆሮ የነበረ የቅዱሱን ሥጋ ባየጊዜ ጆሮዎቹ ሰሙ፣ አንደበቱም መናገር ጀመረ፡፡ ከሥጋውም ብዙ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ብዙ አረማውያንም የቅዱስ አባ ሲማኮስን ተአምራት አይተው በጌታችን አምነው ተጠመቁ፡፡ የጌታችንንም ክብር መስከረው በሰማዕት ዐረፉ፡፡ ቁጥራቸውም አንድ ሺህ ሰባት መቶ ኃምሳ ሆነ ወንዶችና ሴቶች ወጣቶችም፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሲማኮስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘዘላሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 14 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝   ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር። እግዚኦ አነ ገብርከ።  ገብርከ ወልደ አመትከ"። መዝ115፥15-16። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 6፥11-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-17 እና የሐዋ 4፥31-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥6-6። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ ጳኲሚስ የዕረፍት በዐልና የብርሃነ ዕርገቱ በዓለ ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ግንቦት ፲፫ (13) ቀን። ❤ እንኳን #ለከበረ_አባት_በገድል_ተጠምዶ_ለኖረ ለብልህ ከልቅሶ ብዛትም የተነሣ የቅንድቡ ጠጉር ለተነቀለ #ለአባ_አርሳንዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_አርሳንዮስ፦ ይህም ቅዱስ ከሮሜ አገር ሰዎች ከባለጸጎችና ከታላላቆቿ ነው። የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማረው ዲቁናን አሾሙት። ከዚህም በኋላ አቴና ወደሚባል አገር ሒዶ ፍልስፍናን የፀሐይንና የጨረቃን የከዋክብትም አካሔዳቸውን የዘመናትንም መለኪያና መቊጠሪያ ተምሮ በመልካም አጠና። ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ። በመንፈሳዊ ትምህርቱም ፍጹም ሁኖ አምላካዊ ትሩፍትን የሚሠራ ሆነ። ❤ በሮሜ አገርም ታላቁ ቴዎዶስዮስ በነገሠ ጊዜ ልጆቹን አኖሬዎስንና አርቃዴዎስን የሚያስተምርለት ጥበበኛ ደግ ሰው ፈለገ። ይህንንም ቅዱስ ወደ ንጉሥ ወሰዱት። ንጉሡም ልጆቹን አኖሬዎስንና አርቃዴዎስን እንዲያስተምርለት አዘዘው እርሱም ታዝዞ የንጉሡን ልጆች እንሚገባ ሊያስተምር ጀመረ። በብዙ ትግልና ድካም ስለሚአስተምራቸው ያለርኅራኄ ብዙ ድብደባን ይደበድባቸው ነበር። ❤ ንጉሥ ቴዎዶስዮስም በዐረፈ ጊዜ ልጆቹ አኖሬዎስ በሮሜ አገር አርቃዴዎስም በቊስጥንጥንያ ነገሡ። እግዚአብሔር በአርሳንኖስ ልብ ፍርሀትን አሳደረ በታናሽነታቸው ጊዜ ሲአስተምራቸው የሚመታቸው ስለሆነ በዚህ ምክንያት ከዓለም ይወጣ ዘንድ የነፍሳቸውንም ድኅነት ለሚሹ የሚበራ መብራት ሁኖ ሌሎች ይበሩበት ዘንድ አነሣሣው። ምን እንደሚአደርግ በልቡ እያሰበ ሳለ እንሆ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንዲህ የሚል ቃል መጣ "አርሳኒ አርሳኒ ከዚህ ዓለም ውጣ አንተም ትድናለህ"። ይህንንም ቃል በሰማ ጊዜ ፈጥኖ ተነሣ እንጂ አልዘገየም ወዲያውኑ ልብሱን ለውጦ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ። ከዚያም የከበረ የአባ መቃርስ ገዳም ወደ አለበት ወደ አስቄጥስ በረሀ ደርሶ በጾም በጸሎት በመስገድ በመትጋት በአርምሞና በትሩፋት ሁሉ ፍጹም ተጋድሎን ተጋደለ። ❤ ስለ ዝምታውም በጠየቁት ጊዜ "እኔ ስለ ራሴ ብዙ አዝናለሁ" አላቸው እርሱ ግን በውስጥና በአፍአ ትሑትና ቅን የዋህ ነው የእግዚአብሔርንም ሥራ ይሠራል ሁል ጊዜም እጀ ሥራውን አያቋርጥም ከዕለት ምግቡ የሚተርፈውንም ይመጸውታል። የነፍሳቸውንም ድኅነት ለሚሹ ጥቅም ያላቸውን ብዙ ድርሰቶችንና ተግሣጾችን ደረሰ። ❤ ወደ ቤተ ክርስቲያንም በሚገባ ጊዜ ሰው እንዳያየው ምሰሶ ኋላ ይሠወራል። ይህም አባት ድንቆች ተአምራትን ያደርጋል የብዙዎች ሰዎችን ገድል እግዚአብሔር ገልጦለታልና። ❤ መልኩም ያማረ ሕዋሳቱም የጸኑ ፊቱም ብሩህና እጅግ ደስ የሚል ጽሕሙም ከወገቡ መታጠቂያ የሚደርስ ረጅም ነው። ከልቅሶ ብዛትም የተነሣ የቅንድቡ ጠጉር ተነቀለ ቁመቱም ረጅም ነው ግን ያጐነብሳል ወደ መልካም ሽምግልናም ደረሰ ዕድሜውም ሁሉ መቶ ዓመት ሆነ። በሮሜም አርባ ዓመት ኖረ። በአስቄጥስ ገዳም ሠላሳ አምስት ዓመት በምስር ገዳም ሃያ ዓመት በእስክንድርያ ሦስት ዓመት ከዚህም በኋላ ወደ ምስር ገዳም ተመልሶ በዚያ ሁለት ዓመት ተቀምጦ ግንቦት13 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአርሳንዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት13 ስንክሳር።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤ ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለብርሃነ_ዕርገቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                                       ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የጌታችን_የአምላካችን_የመድኃኒታችን_የኢየሱስ+ክርስቶስ_ዕርገት፦ እርሱም በረቀቀ ጥበቡ በመከራው በሞቱና በመነሣቱ ሥራውን ከፈጸመ በኋላ አርባው ቀን ሲፈጸም በነፋሳት ክንፍ ላይ ሁኖ ዐረገ። ያን ጊዜ በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ ወጣ በነፋሳትም ክንፎች ላይ ሁኖ ወጣ ያለው የዳዊት ትንቢት ተፈጸመ። ❤ በዚህም ዕርገቱ የሚያምኑበት በልዕልና ወደሚኖሩበት የሚዐርጉ መሆናቸው ተረዳ ተረጋገጠ ራስ በአለበት ሕዋሳት ሊኖሩ ይገባልና። አዳም አስቀድሞ በምድራዊ ርስቶች በሲኦልም እንደኖረ መኖርንም እንደቀደመ እንዲሁ ዳግማዊ አዳም ጌታ በመንግሥተ ሰማያት ርስት መኖርን ቀደመ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዕርገቱን ከትንሣኤው አከታትሎ ወዲያውኑ አላደረገም መናፍቃን ዕርገቱ ምትሐት ናት ብለው እንዳያስቡ። ጌታችንም በረቀቀ ጥበቡ የደቀ መዛሙርቱን ተሽብሮ የነበረ ልቡናቸውን እያጽናና መነሣቱንም እያስረዳቸው ከትንሣኤው በኋላ አርባ ቀን ኖረ። ❤ በጌታችንም ዕርገት የቅዱስ ዳንኤል ትንቢት ተፈጸመ እንዲህ የሚል "ሌሊት በራእይ አየሁ እንሆ ታላቅ እንደ ሰው ልጅ የሆነ መጣ ዘመናትን ወደሚያስረጃቸው ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት። የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት፣ የዘላለም ሥልጣን ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የሚያልፍ የማይጠፋ ነዋሪ ነው"። ለእርሱም ምስጋና ይሁን ከቸር አባቱ ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት8 ስንክሳር።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘዐርገ ውስተ ሰማይ። ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ። ናሁ ይሁብ ቃሎ ቃለ ኃይል"። መዝ 67፥32-33። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 24፥45-ፍ.ም።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ። ወእግዚእነ በቃለ ቀርን። ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ"። መዝ 46፥5-6። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 1፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥18-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 1፥1-12። የሚነበበው ወንጌል ማር 16፥14-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ነው። መልካም የብርሃነ ዕርገቱ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ስለርሱም እንዲህ ተባለ በአንዲት ዕለትም ከንጉሥ አርቃዴዎስ ጋር ተቀምጦ ሳለ ንጉሡ እንዲህ አለው "አባቴ ሆይ ስለ አንድ ቃል እንድታስረዳኝ እለምንሃለሁ። ይህም ቃል ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በልቤ ውስጥ ይመላለሳል ወንጌላዊ ቅዱስ ማቴዎስ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምን የበኵር ልጅዋን እስከወለደች ድረስ ዮሴፍ አላወቃትም ስለምን አለ? ወንዶች ሴቶችን እንደሚአውቋቸው ዮሴፍ አወቃትን?" አለው። የከበረ ዮሐንስም "ንጉሥ ሆይ እንዲህ አትበል እንዲህ አንተ እንደምትለው አይደለም የከበረች ድንግል እመቤታችንስ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሆድዋ ውስጥ በነበረ ጊዜ የእርሱ ኅብረ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋራ መልኳ ይለዋወጥ ነበር። በንጹሕ ብርሌ ውስጥ ውኃ በጨመሩ ጊዜ ውኃ መስሎ እንደሚታይ ወይን ጠጅም ቢጨምሩ ያንኑ መስሎ እንደሚታይ ወይም ከውስጡ በተጨመረው ቀይም ቢሆን ቀልቶ እንደሚታይ ቅጠልያም ቢገባበት ቅጠልያ መስሎ እንደሚታይ። ድንግልም በሆድዋ ውስጥ የልጅዋ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋራ መልኳ ይለዋወጥ ነበር። እንደ ሮማን አበባ የምትቀላበት ጊዜ አለ እንደናርዶስም የምታብለጨልጭበት ጊዜ አለ የለመለመ ቅጠል የምትመስልበትም ጊዜ አለ ከወለደች በኋላ ግን አልተለወጠችምና ዮሴፍ በአንድ በቀድሞው ኅብረ መልኳ ተወስናለት መልኳን ተረዳ ማለት ነው" አለው። በዚያን ጊዜ በንጉሥ አዳራሽ ውስጥ ከወርቅ የተሠራች የድንግል ማርያም ሥዕል ነበረችና "አፈ ወርቅ ዮሐንስ፣ ልሳነ ወርቅ ዮሐንስ፣ አፈ በረከት ዮሐንስ መልካም ተናገርክ" የሚል ቃል ከእርሷ ወጣ። ❤ ንጉሡና ከእርሱ ጋራ ያሉት በሰሙ ጊዜ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት በዚያን ጊዜ ንጉሥ አዝዞ ወርቅ ልሳን አሠርቶ ለሚያየው ሁሉ መታሰቢያ ምልክት ሊሆን አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ሥዕል ዘንድ ሰቀለው። ቅዱስ ዮሐንስም ከዚያች ቀን ወዲህ ልሳነ ወርቅ ብሎ ጠራው አፈ ወርቅም ተብሎ እስከዛሬ ተጠራ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ጸሎት ይማረን በረከትም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የመላልዔል_ልጅ_ቅዱስ_ያሬድ፦ ያሬድም መቶ ስልሳ ሁለት ዓመት ኑሮ ኄኖክን ወለደው ኄኖክንም ከወለደው በኋላ ስምንት መቶ ዓመት ኖረ ወንዶችንና ሴቶች ልጆችን ወለደ። መላው ዘመኑም ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሁለት ዓመት ሆነው በዕለተ ዓርብም በሦስት ሰዓት ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቀደሙ አባቶቻችንም በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን #በኢየሩሳሌም_አገር_በጎልጎታ ላይ ፀሓይ በልጦ በሚበራ ብርሃን የከበረ መስቀል መገለጥ ሆነ። ይኸውም ለኢየሩሳሌም አባ ቄርሎስ ኤጲስቆጶስ ሆኖ በተሾመበት በታላቁ ቈስጠንጢኖስ ልጅ በሚያንሰው ቈስጠንጢኖስም ዘመነ መንግሥት ነው። መገለጡም የሆነው ከቀኑ ከስድስት ሰዓት ነው። የመስቀሉም ብርሃን የፀሐዩን ብርሃን ሸፍኖ በግልጥ እየታየ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ቆየ ሰዎችም ሁሉ ያዩት ዘንድ ከቦታው ሁሉ ይወጡ ነበር። ❤ አባ ቄርሎስም እንዲህ የሚል መልክትን ወደ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሲልክ "ንጉሥ ሆይ ዕወቅ አስተውል በከበረ አባትህ በጻድቁ ቈስጠንጢኖስ ዘመን እንደ ከዋክብት መስቀል በሰማይ ታየ። ሁለተኛም በዘመንህ በቀራንዮ ላይ የብርሃን መስቀል የፀሐይንም ብርሃኑ ሸፈነው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብርና እስከ ደብረ ዘይት ተዘረጋ" አለው። ሁለተኛም በዚች ደብዳቤ እንዲህ አለው "ንጉሥ ሆይ ከከፋችና ከረከሰች ከአርዮስ ሃይማኖት ተጠበቅ የሚያምኑባትንም አትቀበላቸው በምንም በምን አትሳተፋቸው" አለው። ❤ ከዚህም በኋላም አባ ቄርሎስ ይህ የከበረ መስቀል በተገለጸበት ቀን በዓልን አደረገ እርሱ በሥውርና በግልጥ ለሚመጣብን ጠላት ተዋግተን የምድንበት የጦር መሣሪያችን ነውና በጸና እምነት በምንማፀንበት ጊዜ። እግዚአብሔርም በመስቀሉ ላዳነን በከበረ ደሙም ፈሳሽነት ለአነጸን ምስጋና ይሁን ዛሬም ከሚጣላን ሁሉ ይጠብቀን ይቅርም ይበለን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የንግንቦት12 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዮሐንስ_እንተ_አብደረ_ስደተ። እምይሳተፍ በግፍዕ መፍቀሪተ ንዋይ ንግሥተ። እምነ አፉሁ ዘይወጽአ ሰሚዖ ግዘተ። እንበለ ይዕርግ ላዕለ ወንእንበለ ይረድ ታሕተ። መልአከ ሰማይ ቆመ ፲ተ ዓመተ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_12።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ማቴ5፥1-17።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "በዓመፃ ሰደዱኒ ርድአኒ። ሕቀ ክመ ዘእምደምሰሱኒ ውስተ ምድር ወአንሰ ኢኀደጉ ትእዛዘከ"። መዝ 118፥86-87። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 6፥1-9፣ ዕብ 13፥13-22 እና የሐዋ ሥራ 13፥16-20። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ10፥29-38 ። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ፣ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዐል፣ የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የዕረፍት በዐልና የበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ግንቦት ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን #የዓለም_ሁሉ_መምህር ለሆነ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ ለዕረፍቱ በዓልና #ለመላልዔል_ልጅ_ለቅዱስ_ያሬድ ለዕረፍት በዓልበሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ ከሊቀ መላእክት ከቅዱስ ሚካኤል ወደ ነቢዩ ዕንባቆም ከተላከበት፣ ከኢትዮጵያዊው ንጉሥ ከእስክድር ዕረፍት፣ በኢየሩሳሌም አገር በጎልጎታ ላይ ከፀሐይ በልጦ በሚበራ ብርሃን ከከበረ መስቀል መገለጥ ከሆነው፣ ሰማዕታት ከሆኑ ከዲያቆን ሚናስና ከእስጢፋኖስ ከመታሰቢያቸው፣ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #የዓለሙ_ሁሉ_መምህር_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ፦ ይህም አባት ከእስክድርያ አገር ሰዎች ወገን ነው የተወለደውም በ349 ዓ.ም ነው። የአባቱም ስም አስፋኒዶስ የእናቱም ስም አትናስያ ነው። እሊህም እጅግ ባለጸጎች ነበሩ ይህንንም ልጃቸውን በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት ትምህርትንና ጥበብንም ሁሉ አስተማሩት እርሱ ወደ አቴና ሒዶ በመምህራን ቤት ትምህርትን ሁሉ ተምሮ በዕውቀቱ ከብዙዎች በላይ ከፍ ከፍ ብሏልና። ❤ ከዚህም በኋላ ገና በታናሽነቱ መነኰሰ የዚህንም የኃላፊውን ዓለም ጣዕም ንቆ ተወ ከእርሱም ቀድሞ በዚሁ ገዳም ቅዱስ ባስልዮስ መንኵሶ ነበር በአንድነትም ተስማምተው ብዙ ትሩፋትን ሠሩ ወላጆቹም በሞቱ ጊዜ ከተዉለት ገንዘብ ምንም ምን አልወሰደም ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጠ እንጂ ከዚያም በምንኵስና ሥራ በመጠመድ ፍጹም ገድልን እየተጋደለ ኖረ። ❤ በዚህም ገዳም ሶርያዊ ጻድቅ ሰው ስሙ ሲሲኮስ የሚባል መነኰስ ነበረ እርሱም ወደፊት የሚሆነውን በመንፈስ ቅዱስ ያይ ነበር በአንዲት ሌሊትም ለጸሎት እየተጋ ሳለ ሐዋርያትን ቅዱስ ጴጥሮስንና ቅዱስ ዮሐንስን አያቸው ቅዱስ ጴጥሮስ መክፈቻ ሰጠው ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስም ወንጌልን ሰጠው እንዲህም አሉት "በምድር ያሠርከው በሰማይ የታሠረ ይሆናል በምድርም የፈታኸው ደግሞ በሰማያት የተፈታ ይሆናልና በውስጥህ መንፈስ ቅዱስ ያደረብህ አዲስ ዳንኤል ሆይ የክብር ባለቤት ከሆነ ከታላቅ መምህር ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወደአንተ ተልከናልና ዕወቅ "እኔም የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ የተሰጠኝ ጴጥሮስ ነኝ"። ሁለተኛም እኔም "በመጀመሪያው ስብከቴ በከበረ ወንጌል ቃል አስቀድሞ ነበረ ያልኩ ይህም ቃል በጠላት ላይ የእሳት ሰይፍ የሆነ ዮሐንስ ነኝ"። ለአንተም ከክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወገኖችህ ምእመናንን በቀናች ሃይማኖት ታሳድጋቸው ዘንድ ዕውነተኛ አእምሮ ደግሞ ተሰጥቶሃል"። ጻድቅ ሲስኮስም ይህን ራእይ በአየ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ቸር ታማኝ እረኛ ሁኖ እንዲሾም ዐወቀ። ❤ ከዚህ በኋላ በቅዱስ ዮሐንስ ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በላዩ ወርዶ አደረበትና ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ ዲያቆን ሁኖ ሳለም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ብሉያትንና ሐዲሳትን ተረጐመ። በአንዲት ሌሊትም ቅዱስ ዮሐንስ ሲጸልይ እግዚአብሔር መልአክ በድንገት እንደ በረድ ነጭ በሆነ ልብስ ተገለጠለት ቅዱስ ዮሐንስም ሲያየው ደንግጦ በምድር ላይ ወደቀ መልአኩም አርአያውን ለውጦ እንደ ሰው ሁኖ ታየው "ወዳጄ አዲስ ዳንኤል ሆይ አትፍራ ተነሣ " አለው የእግዚአብሔር መልአክም "ትሠራው ዘንድ የሚገባህን ልነግርህ ወዳንተ የተላክሁ ነኝ። አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ያዘዘህን ለመሥራት ልብህን አበርታ ቃልህ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በአራቱ ማእዘን ይደርሳልና እልፍ አእላፋትም ትምህርትህን ተቀብለው ትእዛዝህን ሰምተው ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ተመልሰው ይድናሉና በእግዚአብሔር መንግሥትም ውስጥ የጸና የብርሃን ዐምድ ትሆናለህና። እነሆ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንተ ይመጣል ከእርሱም ጋራ ሁሉም ካህናትና ዲያቆናት በማዕረጋቸው የሚያዝህም አድርግ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነውና ልትተላለፍ አይገባህም" አለው። ❤ ከዚህ በኋላ ያ መልአክ ለአባ ፊላትያኖስ ተገልጦ ቅዱስ ዮሐንስን ቅስና እንዲሾመው አዘዘ በመግሥቱም ሊቀ ጳጳሳቱ መጣ ከርሱ ጋራም ካህናት አሉ ይህን ቅዱስ ዮሐንስንም ይዞ ቅስና ሾመው። የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳትም በዐረፈ ጊዜ ንጉሥ አርቃድዮስ ልኮ አስመጥቶ ቅዱስ ዮሐንስን በቊስጥንጥንያ ላይ ሊቀ ጵጵስና በ397 ዓ.ም ሾመው አባቶቻችን ሐዋርያት እንደሚአደርጉት በሊቀ ጵጵስናው ሥራ ላይ ጸና ሕይወትነት በአላቸው ትምህርቶችና ተግሣጾች ሕዝቡን ሁልጊዜ የሚአስተምር ሆነ። ከኢጲስቆሳትም ሆነ ከመንግሥት ወገን ሕግን የሚተላለፋትን ሁሉ ይገሥጻቸዋል ማንንም አይፈራም ፊት አይቶም አያደላም። ❤ ንጉሥ አርቃድዮስ ሚስቱ አውዶክስያንም ገንዘብ ወዳጅ ስለሆነች የአንዲት ድኃ መበለት ቦታዋን በግፍ ወሰደች ያቺ መበለትም ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መጥታ ንግሥት አውዶክስያ ቦታዋን እንደነጠቀቻት ነገረችው እርሱም የድኃዋን ቦታዋን መልሺላት ብሎ ከብዙ ምክር ጋር እንድትመልስላት ንግሥት አውዶክስያን ለመናት እርሷ ግን እምቢ በማለት አልታዘዘችለትም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውን ደሙን እንዳትቀበል አውግዞ ለያት። ቊጣንና ብስጭትንም ተመልታ ስለ ክፉ ሥራቸው ከሹመታቸው እርሱ የሻራቸውን ኤጲስቆጶሳት ሰበሰበች እነርሱም ንግሥቲቱን ስለ ተቃወመ ስደት እንዲገባው በእርሱ ላይ ተስማምተው ጻፋ እርሷም አጥራክያ ወደ ሚባል ደሴት ሰደደችው። ከዚያም በደረሰ ጊዜ የዚያች ደሴት ሰዎች በክፉ ሥራ ጸንተው የሚኖሩ ከሀድያን ሁነው አገኛቸው ቅዱስ ዮሐንስም አሰተማራቸው ገሠጻቸውም በፊታቸው ስለ አደረጋቸው ድንቆች ተአምራት ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው። ❤ የሮሜ ንጉሥ አኖሬዎስ ሊቀ ጳጳሳቱ ዮናክኒዶስ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ስደት በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ በንጉሥ አርቃድዮስ ላይም በመቆጣት እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፈው ላኩ "ከዚህ ከክፉ ሥራ ተጠበቅ ትእዛዛችንንም ተቀብለህ የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ ከአልመለስከው በአንተና በእኛ መካከል ሰላም አይኖርም"። መልእክታቸውንም በአነበበው ጊዜ እጅግ አዘነ ሚስቱንም አግዶ ልኮ ቅዱስ ዮሐንስን ከስደቱ መለሰው በተመለሰ ጊዜም የቊስጥንጥንያ ሰዎች በመመለሱ ታላቅ ደስታ አደረጉ። ❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላም ንግሥቲቱ ወደ ክፋቷ ተመልሳ ሁለተኛ ወደ አጥራክያ ደሴት ሰደደችውና በዚያው በ407 ዓ.ም ግንቦት12 ቀን ዐረፈ። ንጉሥ አኖሬዎስ ሊቀ ጳጳሳት ዮናክኒዶስም በሰሙ ጊዜ መልክትን ላኩ ሊቀ ጳጳሳቱም የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ እስከምትመልሰው ድረስ ሥጋውንና ደሙን እንዳትቀበል አውዶክስያን አወገዛት። ❤ ከዚህም በኋላ የከበረ ዮሐንስን ይመልሱት ዘንድ ንጉሥ ላከ ግን ሙቶ አገኙት ሥጋውንም ተሸክመው ወደ ከቊስጥንጥንያ ከተማ አደረሱት። የከበረ ዮሐንስም በተሰደደበት አገር እንደዐረፈና ሥጋውንም ወደ ከቊስጥንጥንያ ከተማ እንደአመጣጡ ወደ አባ ዮናክኒዶስ መልእክት ጽፈው አስረዱት። ❤ ሁለተኛም የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውንና ደሙን እንዳትቀበል ልኮ አውዶክስያን አወገዛት እየለመነችውም ስምንት ወር ያህል ኖረች በብዙ ልመናም ፈታት። ነገር ግን ጭንቅ በሆነ ደዌ እግዚአብሔር አሠቃያት ያድኗት ዘንድ ገንዘቧን ለባለ መድኃኒቶች ጥበበኞች እስከ ሰጠች ድረስ ግን አልዳነችም። ወደ ቅዱስ ዮሐንስም መቃብርም ሔዳ በእርሱ ላይ ያደረገችውን በደል ይቅር ይላት ዘንድ እየሰገደችና እያለቀሰች ለመነችው እርሱም ይቅር አላት ከደዌዋም ፈወሳት። ጌታችንም ከሥጋው ታላላቅ ድንቆች ታምራትን ገለጠ።

ለኔ ቢሆን እወዳለሁ" አለችው። "እንግዲያስ ላንቺ የተዘጋጁ ናቸው" አላት። "በምን ሥራዬ ለኔ ተሰጡኝ" አለችው። "ዐሠርቱ ቃላት ኦሪትን ስድስቱን ቃላተ ወንጌል ጠብቀሽ ቤትሽን ጥለሽ ይህን ዓለም ንቀሽ አጥቅተሽ የክርስቶስን ቀምበር ተሸክመሽ ፈጣሪሽን ስለተከተልሽው ነው" አላት። ይህንንም በአላት ጊዜ እጅግ አድርጋ ተደሰተች ሁሉን ማድረግ የሚችል እግዚአብሔርንም ፈጽማ አመሰገነች። ምንጭ፦ ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ።                                                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የመነኰሳት_ሁሉ_አለቃ_ሐዋርያ_ሰማዕት_የታላቁ_መምህር_የክቡር_አባታችን_የአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት የሥጋው ፍልሰት፦ የፍልሰቱም ምክንያት በሃምሳ ስድስት(57) ዓመት ከዋሻ (ደብረ አስቦ) ውስጥ ወደ አነፁልህ መቃብር ያፈልሱታል ብሎ እግዚአብሔር የነገው ዘመን በደረሰ ጊዜ ያንጊዜም ተአምር ተደርጎ ዕውራን አዩ አንካሶች ተስተካከሉ። ❤ ይህም በወራሴ መንበሩ በአባ ሕዝቅያስ ዘመን ሆነ ዕለቱም ግንቦት ዐሥራ ሁለት ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም ተጋዳይ በሆነ ሰው በጻድቁ አባታችን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጌታን ደስ በአሰኙት በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 12 ስንክሳር።

ያች የተከተለቻት አገልጋይ ግን ከእመቤቷ እግር እየተቆረጠ የሚወድቀውን የአካል ቊራጭ እያነሳች በልብሷ ትቋጥረው ነበር። በዚህ ዓይነት ችግርና ፀሐይ ሐሩር የብዙ ጐዳና ጉዞ ተጉዛ ከአሰበችበት አገር ደረሰች። በደብረ ሊባኖስ አቅራቢያ ወይም አካባቢ ስትደርስ የራስ ፀጒራን ይዛው በነበረ ምላጭ ላጨች ልብሷንም አውልቃ ለነዳያን አከፋፈለች የያዘችውንም ገንዘብ በመንገድ ላይ ላገኘችው ሁሉ መፅውታ ጨረሰች። ከዚያም አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብስ ምንኵስና ማለት ቀሚስዋን አጥልቃ አጽፋን ተጐናጽፋ ቆቧን ደፍታ ደብረ ሊባኖስ ከሴቶች ገዳም ደረሰች። የገዳሙ መነኰሳትም በታላቅ ክብር ተቀብለው ወደበዓታቸው አስገቧት ... ❤ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ለሳጥናኤል ምሕረት እንደለመነች፦ ከዕለታት በአንድኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ጓንጉት በምትባል ደሴት ውስጥ ዓርብ ዕለት ከቀኑ በስድስት ሰዓት ላይ ስለሰው ልጆች ስትጸልይ ሣለ። ዓለሙ ሁሉ ከንቱ እንደሆነና የሰውም ልጅ ሕይወት እንደጥላ ኃላፊ ጠፊ መሆኑን ፈጽማ ተመለከተች። ነቢዩ ዳዊት "ሰው ከንቱ ነገርን ይመስላል ዘመኑ ወይም ሕይወቱ እንደጥላ ያልፋል" ሲል ተናግሯልና። ዳግመኛም "ሰው ክብር እንኳ ቢሆን ሊኖር አይችልም እንደሚጠፋ ወይም ማስተዋል እንደሌለው እንስሶች መሰለ... አለ ክቡር ዳዊት። ስለዚህም ሁሉ ነገር አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው መፃተኛዋ ባሪያህንም ኃጢአቷን አታስብባት እያለች ወደፈጣሪዋ መሪር ዕንባን አለቀሰች። ያን ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በታላቅ ግርማ ወደስዋ መጣ። በታላቅ ግርማ ሆኖ ባየችውም ጊዜ ደነገፀች ከእግሩ ሥርም ወደቀች። ከዚህ በኋላ ነውር በሌለባቸው ንዑዳት ክቡራንና ንጹሐን በሆነ እጆቹ አነሣት። ቀጥሎም "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ አትደንግጭ ነገር ግን የልብሽን ሃሳብ ንገሪኝ" አላት። እስዋም "አቤቱ ባሪያህንስ በባለሟልነት ካሠለጠንካት አባታችን አዳምን በአርአያህና በአምሣልህ ስለምን ፈጠርከርው። በእንጨት መስቀልስ ላይ ለምን ተሰቀልክ ስለአዳምና ስለልጆቹ አይደለምን?" አለችው። "አዋን ስለነሱ ስል ተሰቅያለሁ" አላት። "እግዲያውስ መሰቀልህ ወይም የተሰቀልከው ስለነሱ ከሆነ ከአቤል ጀምሮ እስከ ዛሬ የሞቱን ከዛሬም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሞቱትን አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው" አለችው። "አንተ ቸር ይቅር ባይ መዓትህ የራቀ ምሕረትህ የበዛ ነህና ከአንተ ሌላ አምላክ የሌለ እውነተኛ አምላክ ነህ ሁሉ ይቻልሃልና የሚሣንህ ነገር ከቶ የለምና ዓለም በጠቅላላዋ በእፍኝህ አትሞላም" በማለት እያለቀሰች ለመነችው። በዚያ ጊዜ ጌታ መልሶ "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ እስኪ አንቺ ራስሽ ፍረጅ አዳም ከነልጆቹ ከሠራው ኃጢአት እና እኔ በጰንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን በቀያፋና በሐና አደባባይ በዕለተ ዓርብ ከተቀበልኩት ሕማማተ መስቀል ቢመዘን የትኛው ይመዝን ይመስልሻል?" አላት። ይህንም ባላት ጊዜ ደነገጠችና ከመሬት ላይ ወደቀች። በዚህ ጊዜ ቅዱሳት በሆኑ እጆቹ ከወደቀችበት አነሣትና "እንግዲህ ይህን ሁሉ መከራ የተቀበልኩ ለማን ወይም በማን ምክንያት ይመስልሻል" አላት።... ❤ ጌታም "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ እስኪ የልብሽን ሃሳብ ወይም ፍላጐትሽን ንገሪኝ" አላት። በዚህን ጊዜ "አቤቱ ፈጣሪየ ፈቃድህስ ቢሆን የአዳም ልጆች ከሥቃይ ከኵነኔ ይድኑ ዘንድ ዲያብሎስን ይቅር ትለው ወይም ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ። የኃጥእን መመለሱን እንጂ ጥፋቱን አትወድምና" አለችው። "የምለምንህ ወይም ማረው የምልህ ዲያብሎስን ወድጄው አይደለም ነገር ግን እርሱ ከተማረ በአዳም ልጆች ላይ ሥቃይና ኵነኔ ሊኖር አይችልም ብየ በመገመት እንጂ። የነሱ ሥጋ ሥጋየ እንደሆመኑ መጠን የኔም ሥጋ ሥጋህ ነውና" አለችው። ይህንም ባለችው ጊዜ ጌታ ፍግግ ብሎ "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ ሌሎች ካንቺ በፊት የነበሩ ካንቺም በኋላ የሚነሱ የማያስቡትን እጅግ የሚያስደንቅ ልመና አቀረብሽ" አላት። ይህንም ካለ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ጠርቶ "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ዲያብሎስን ማርልኝ ስትል ልመና አቅርባለችና እሺ ካላት ታወጣው በንድ ወደሲዖል ይዘሃት ሂድ" ብሎ አዘዘው። በዚህ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እሺ ብሎ ሰግዶ እጅ ነሥቶ ወደሲዖል ይዞአት ሄደ። አብረው በሚጓዙበትም ጊዜ "እንግዲህ ዲያብሎስ ከታረቀ ወይም ከተማረ የሰው ልጆች ሁሉ ያርፋሉ" እያለች ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ታሳስበው ነበር። ይህን አምላክነትን ሲሻ ከክብሩ የተዋረደ ዲያብሎስ ምሕረት ለማግኘት ይሻ መስሏት ነበርና። ❤ ከሲዖል አፋፍ በደረሱም ጊዜ የተመለከተችው ሥቃይ ተነግሮ የማያልቅ ነው ሰዎች ከሰዎች ጋር እንደውሻ ይናከሱ ነበር። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል "ምሕረት የሚፈልግ ከሆነ እስኪ በይ ዲያብሎስ ብለሽ ጥሪው" አላት። በዚህ ጊዜ በመላእክት ቋንቋ ሦስት ጊዜ "ሣጥናኤል ሣጥናኤል ሣጥናኤል" በማለት ጠራችው። ዲያብሎስም "ከዚህ በብዙ ሠራዊት ላይ ነግሼ ከምኖርበት አገር ማን ነው እሱ የሚጠራኝ" እያለ በታላቅ ቃል አሰምቶ ተናገረ። ከዚህም በኋላ "ለብዙ ዘመን ስፈልግሽ ወይም ሳድንሽ ቆይቼ ነበር ዛሬ ግን ከምኖርበት ቤቴ ድረስ መጣሽን" አላት። እርሷም "ጌታ ይቅርታ አድርጓልሃልና ከዚህ ከሥቃይና ከመከራ ቦታ ከወገኖችህ ጋራ ና ፈጥነህ ውጣ" አለችው። ይህንም በለችው ጊዜ ልቡ እንደ እሳት ነደደ አፈፍ ብሎ ተረማምዶ በግራ እጁዋን ይዞ ከሲዖል ረግረግ ውስጥ ወረወራት። በዚያን ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የእሳት ሰይፍ ይዞ ከኋላ ከኋላዋ ይከተላት ነበርና ይህን ምሕረት የሌለው ዕቡይ ዲያብሎስ በያዘው ሰይፍ ቢቀጣው የሲዖል ደጃፍ ተከፈተች። በዚህ ሰዓት ታላቅ ጨኸትና ውካታ ወይም መደበላለቅ ሆነ በሲዖል ያሉ የሰዎች ነፍሳት እንደንብ ከበቧት ወይም ሠፈሩባት። በዚያን ጊዜ በቅዱስ ሚካኤል ክንፍና በስዋም በተሰጣት ክንፈ ረድኤት ከሲዖል የወጡት ነፍሳት ቁጥር ዓሥር ሺህ ያህል ነበር። እነዚህ ከመከራ ያመለጡ ከሥቃይ የወጡ ነፍሳትን ባየች ጊዜ እጅግ አድርጋ ተደሰተች ከደስታዋም ብዛት የተነሣ የእናቱን ጡት እየጠባ እንደሚዘል እምቦሳ ጥጃ በመካከላቸው ትዘል ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ፈጣሪዋ ሄዳ "አቤቱ ፍርድህ ከቶ እንደዚህ ነውን?" እያለች አደነቀች። ጌታም "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ ዲያብሎስን ድል አድርገሽ ጥቂት ምርኮን አገኘሽን" አላት። እስዋም "አዋ ጌታዬ በኃይልህና በቸርነትህ አገኘሁ" አለችው። ከዚህ በኋላ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሚካኤል ጠርቶ "እሊህን ነፍሳት ዓለም ሳይፈጠር ወደ አዘጋጀሁላት ወደ ክርስቶስ ሠምራ መኖሪያ ቦታ ውሰዳቸው" አለው። በዚህ ጊዜ "አቤቱ ፈጣሪየ የእኔ መኖሪያየ ወዴት ነው?" አለችው። ጌታም "መኖሪያሽ ከእናቴ ከድንግል ማርያም ጋራ ነው እነሆ በትረ ማርያም ብየ ሰየምኩሽ መቀመጫሽን ወይም ደረጃሽን ከእርስዋ ቀጥሎ ሁለተኛ አደረግሁልሽ የባለሟልነት ግርማ አጐናጸፍኩሽ አንቺን የሚወዱ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው" አላት። ይህንም ባላት ጊዜ ፈጽማ ደስ ተሰኘች ወደ ኋላዋም መለስ ብላ ብትመለከት ለዓይን የሚያንፀባርቁ ዓሥር አክሊላት አየች። በየአንዳንዳቸው አክሉል ላይ ዐራት ከዋክብት አሉ ባቸው የእሊህ ከዋክብት ቊጥራቸው ሲደመር አርባ ይሆናል። በዚህ ጊዜ ከስዋ ጋራ የነበረውን መልአክ "እሊህ በላያቸው ብርሃናውያን ከዋክብት ያሉባቸው አክሊላት ለማን የተዘጋጁ ናቸው ሰውነቴ እጅግ አድርጋ ወዳቸዋለችና" አለችው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም "ላንቺ ቢሆን ደስ አይልሽምን?" አላት። እርስዋም "አዎን ጌታየ