ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
前往频道在 Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
显示更多637
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1130 天
帖子存档
በእያንዳንዱ ገዳም ሃምሳ ሃምሳ ዓመት በጸሎት ኖረው በአጠቃላይ በ500 ዓመታቸው ነው ያረፉት፡፡ ዐፅማቸው መንዝ ከአርባ ሐራ መድኃኔዓለም አጠገብ ፍርኩታ ኪዳነ ምሕረት ገዳም ውስጥ ይገኛል፡፡
ከአባታች ከእጨጌ አቡነ ዮሐንስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፲፰ (18) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት በፀሐይ ላይ 50 ዓመት፣ በጨረቃ ላይ 50 ዓመት፣ በደመና ላይ 50 እንዲሁም ዓለምን በክንፋቸው በመዞር በደመና ላይ 50 ለኖሩ ከሰው ተወልደው ከመላእክት ለተደመሩ ጻድቅ #ለእጨጌ_እጨ_አቡነ_ዮሐንስ_ዘጠገሮ_ለፍልሰተ አጽማቸው በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #እጨጌ_እጨ_አቡነ_ዮሐንስ_ዘጠገሮ፦ ጻድቁ አባታችን የተወለዱት በኢየሩሳሌም አውራጃ ልዩ ስሙ ሳሬራ በሚባል ቦታ ነው፡፡ የካቲት 28 ቀን ተፀንሰው ህዳር 29 ተወለዱ፡፡ አባታቸው ድላሶር እናታቸው እምነ ጽዮን ይባላሉ፡፡ ሲወለዱ በወላጆቻቸው ቤት ውስጥ ብርሃን ወርዷል፡፡ ወላጆቻቸውም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ አባታችን ገና በተወለዱ በ5 ዓመታቸው ወላጆቻቸው ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዘዋቸው የእመቤታችንን ሥዕል ተመልክተው በደስታ ተመልተው ሳቁ፡፡ አምላክን የወለደች የብርሃን እናቱ እመቤታችንም ከምሥሉ ወጥታ "በምን አውቀኸኝ ነው?" ብላ አቅፋ ሳመችውና "ከእንግዲ ወዲህ የልጄ አገልጋይ ትሆናለህ ኑሮህም እንደ መላእክት ይሆናል በአንተ ምክንያት ብዙ ሰዎች ይድናሉ በምድር ላይም 500 ዓመት ትኖራለህ…" ብላ ባርካው ተሰወረች፡፡
❤ ከዚያችም ቀን ጀምሮ አባ ዩሐንስ ለክርስቶስ ተላልፎ ተሰጠ፡፡ 50 ዓመትም በበረሃ ሲጋደል ኖሮ ከ50 ዓመት በኋላ በደመና ተጭኖ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል መሪነት ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ጻድቁ አባታችን በአቡነ ተክለሃይማኖት ዘመን መጨረሻ የመጡ ሲሆን ምንኵስና ከደብረ ሊባኖስ ገዳም ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተቀብለው በዚያው በድብረ ሊባኖስ ገዳም ለ50 ዓመት በጾምና በጸሎት በተጋድሎ ኖዋል፡፡ ከዚኽም በኋላ አባ ዮሐንስ ወደ ተዘጋጀላቸው ምድር በቅዱስ ገብርኤል አሳሳቢነት ወደ ጠገሮ መጡ፡፡ ይኽም ጠገሮ ያለው ገዳማቸው በሰሜን ሸዋ በመንዝና ይፋት ክልል መዘዞ በሚባል ቦታ ሲደርሱ በእግር አንድ ሰዓት ከተጓዙ በኃላ ይገኛል፡፡
❤ ሕዝቡ በተለምዶ እጨ ዮሐንስ እያለ ይጠራቸዋል እንጂ ስማቸው እጨጌ ዮሐንስ ነው፡፡ አቡነ እጨጌ ዮሐንስ መስቀል ከሰማይ የወረደላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መስቀሉም ሁልጊዜ ተአምር ይሠራል፡፡ በልደታቸው ቀን ኅዳር 29 ቀን መስቀሉ ከመቅደሱ ወጥቶ በካህናቱ ታጅቦ ወደ ጸበሉ ሲወርድ ከየት እንደመጣ ሳይታሰብ ደመና መጥቶ ከመስቀሉ ላይ ብቻ እረቦና እንደ ጃንጥላ ተዘርግቶ አብሮ ወደ ጸበሉ ይወርዳል፡፡ እዛው ቆይቶ መስቀሉ ሲመለስም አብሮ አጅቦ ይመለስና መስቀሉ ቤተ መቅደስ ውስጥ ሲገባ ደመናው ወዴት እንደተበተነ ሳይታወቅ ይጠፋል፡፡ ይህ በዘመናችንም ጭምር እየታየ ያለ ታላቅ ተአምር ነው፡፡
❤ አባታችን በታላቀ ተጋድሎ ሣሉ ሰይጣን የሀገሩን ሰዎች በጠላትነት እንዲነሡባቸው አደረገ፡፡ ሰዎቹም አባታችንን እንዴት እንደሚያጠፏቸው ይማከሩ ጀመር፡፡ ሊገድሏቸው ፈልገው ቅድስናቸው በሁሉ ዘንድ የታወቀ ነውና ፈሩ፡፡ ከዚህም በኋላ "ለምን ከመንደራችን ከወንድ ያረገዘች ሴት ፈልገን እሳቸው አስረገዟት ብለን በሐሰት እንከሳቸው?" ብለው ተማከሩ፡፡ ብዙ ወርቅና ብርም ለአንዲት ሴት ሰጥተው በሐሰት ከእርሱ አርግዣለሁ ብላ እንድትመሰክር አደረጓት፡፡ አባታችንም በሕዝብ ፊት በሐሰት ተከሰሱ፡፡ ጻድቁም "አንቺ ሴት ከእኔ ነው ያረገሽው?" አሏት እርሷም "አዎ ከአንተ ነው ልትክድ ነው እንዴ?" አለቻቸው፡፡ አባታችንም በዚህ አዝነው "በአንቺና በእኔ መካከል እግዚአብሔር ይፍረድ" ሲሉ ያች ሴት ወዲያው ለሁለት ተሰንጥቃ ሞተች፡፡ የአገሩ ሰዎችም እጅግ ፈሩ፡፡ አባታችንም ምድሪቱን እረገሟት፡፡ "የተዘራው ዘር አይብቀልብሽ፣ የተተከለው አይፅደቅ፣ ብርድና ውርጭ ይፈራረቅብሽ" ብለው እረግመዋት በደመና ተጭነው ወደ ሰሜን ጎንደር እስቴ ጉንደ ተክለተሃማኖት ሔዱ፡፡
❤ አቡነ ዮሐንስ በመላው ኢትዮጵያ ወንጌልን እየተዘዋወሩ ያስተማሩ ሲሆን ከቅድስናቸው የተነሣ በፀሐይ ላይ 50 ዓመት፣ በጨረቃ ላይ 50 ዓመት፣ በደመና ላይ 50 እንዲሁም ዓለምን በክንፋቸው በመዞር በደመና ላይ 50 የኖሩ ከሰው ተወልደው ከመላእክት የተደመሩ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በይፋት ጠግሮ በዓለወልድ፣ በአፋር አዘሎ፣ በመንዝ ፍርኩታ ኪዳነምሕረት፣ በደብረ ሊባኖስ፣ በጎንድ ተክለ ሃይማኖት በሌሎችም ቦታዎች በመዘዋወር በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡
❤ አባታችን ከሰማይ መስቀል የወረደላቸው ሲሆን ዛሬም በገዳማቸው የሔደ ሰው በወረደው በእጃቸው መስቀል እየተዳበሰ ቆመው በጸለዩበት ባሕር በጠበላቸው ይጠመቃል፡፡ በተጨማሪም ይይዙት በነበረውም መቋሚያቸው በመዳበስ በረከትን ማግኘት ይቻላል፡፡ ቆመው ከጸለዩበት ባሕር ውስጥ ደረቅ አሸዋ ይወጣል፡፡ አባ ዮሐንስ 500 ዓመት ከኖሩ በኋላ ዕረፍተ ዘመናቸው ሲደርስ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከ15 ነቢያት፣ ከ12 ሐዋርያት፣ ሄሮድስ ያስፈጃቸው ከመቶ አርባ አራት ሺ ሕፃናት፣ ከአብርሃም ከይስሐቅ፣ ከዕቆብ ጋር ሁሉንም ነገደ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ መጥቶ ታላቅ ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ "ስምህን የጠራ ገዳምህን የረገጠ፣ መባ የሰጠ፣ ቤተ ክርስትያንህን የሠራ ያሠራ የረዳ፣ ገድልህን የሰማ ያሰማ ያስተረጎመ፣ መታሰቢያን ያደረገ እስከ 10 ትውልድ እምርልሀለው፤ ንስሀ ሳይገባ አይሞትም፣ ልጅ መውለድ ባይችል እኔ ልጅ እሰጠዋለሁ፤ ገድልህን በቤትህ ያስቀመጠ እርኩስ መንፈስ፣ ክፉ አጋንንት ቸነፈር ወባ መልአከ ጽልመት አይነካውም፡፡ በገዳምህ መነኵሴ ቢቀበር በሰማይ ክንፍ አበቅልለታለሁ፤ አይሁድም አረማዊም ያላመነ ያልተጠመቀ በገዳምህ መጥቶ ቢያርፍ ይቅር እልልሃለሁ፣ እንደ መቃብሬ ጉልጎታ እንደተቀበረ አድርጌ እቆጥርልሃለሁ…" የሚል ቃል ኪዳን ከሰጣቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡
❤ ቅዱስ አባታችንም በ 500 ዓመታቸው ሐምሌ 29 ቀን ዐርፈው በጎንድ ተክለ ሃይማኖት ተቀብረዋል፡፡ በሰሜን ጎንደር የሚገኘውን ይህንን ገዳም ጻድቁ ራሳቸው ናቸው የመሠረቱት፡፡ ነገር ግን የገዳሙን ስያሜ በአባታቸው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ስም አድርገውታል፡፡ አቡነ ዮሐንስ ካረፉ በኋላ በእርግማናቸው መሠረት በመንዝና በይፋት ብርዱ ድርቁ ስለበዛባቸው አንድ ብቁ ባሕታዊ ከበዓታቸው ወጥተው "በሐሜታችሁ ምክንያት እጨ ዮሐንስ ስለረገማችሁ ነው የእርሱን ዐፅም ካላመጣችሁ ብርዱ ውርጩ ድርቁም አይጠፋላችሁም" አሏቸው፡፡ ሕዝቡም አባታችን በጉንድ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከተቀበሩ ከ 134 ዓመት በኋላ በቅዱሳን እየተመሩ ሄደው በሌሊት ግማሽ ዐፅማቸውን አምጥተው በሀገራቸው አምጥተው ስላስቀመጡ ብርዱና ውርጩ በመንዝ እየቀነሰላቸው መጥቷል፡፡
❤ ዛሬም በሀገሩ ብርዱና ውርጭ ሲበዛ የጻድቁን ታቦት ሲያወጡ ውርጩ ይጠፋል፡፡ ጠገሮ በሚባለው ገዳማቸው ውስጥ የሚገኘው ጠበላቸው እጅግ አስደናቂ ነው፡፡ ግማሽ ዐፅማቸውን ከጉንደ ተክለሃይማኖት አምጥተው አርባ ሐራ መድኃኔዓለም አጠገብ በላይ በፍሩክታ ኪዳነምሕረት መጋቢት 18 ፍልሰተ ዐፅማቸው ተከናወነ፡፡ ምድሪቷም ተባረከች፣ የዘሩትንም አበቀለች፣ ውርጩም ብርዱም ቀነሰ፣ ዝናብ አልዘንብ ሲል ወይም ሰብል የሚጨርስ አንበጣ ሲመጣ ታቦታቸው ወጥቶ ምህላ ይያዛል ወድያውም መቅሰፍት ይርቃል፣ ዝናብም ይዘንባል፡፡ ጻድቁ ደመናን፣ ጨረቃንና ፀሐይን በእጃቸው እየያዙ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጠገሮ፣ በአዘሎ፣ በፍርኩታና በሌሎቹም ታላላቅ ቦታቦዎች ላይ
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን #ጌታችን_አምላካችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ይወደው ለነበረው #ለቅዱስ_አልዓዛር ጌታችን ከሞት ከማስነሳቱ በፊት መጀመርያ ለዐረፈበት መታሰቢያ ቀንና #ለአጒንስጢስ_ለቅዱስ_ቴዎቅሪጦስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከታጋዩ #ከቅዱስ_ጊዮርጊስና ከሰማዕቱ #ከቅዱስ_ተላስስ፣ #ከኤጲስቆጶስ_ዮሴፍ ከመታሰቢያቸውና #ከሊቀ_ካህናት_ኒቆር ከሥጋው ፍልሰት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ጌታችን_ቅዱስ_አልዓዛር_ከሙት_እንዳስነሳው፦ ይህም ጻድቅ ሰው ከእስራኤል ልጆች ውስጥ ነው። ማርያምና የተባሉ ሁለት እኅቶች አሉት። ማርያም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሽቱ የቀባችው ናት። እርሱም በጌታ ደቀመዛሙርቶቹ ናቸው ስለ ምግባራቸውም ጌታችን ይወዳቸዋል ሁሉም ያላገቡ ደናግል ናቸው።
❤ ለሰው ወገን ሁሉ ላይ የተቆረጠውና የተወሰነው ሰዎችም ሊጠጡት ያላቸው የሞት ጽዋን እጁን ለሞት የሚሰጥበት ለዚህ ጻድቅ ጊዜው ሲደርስ እርሱም እጁን በመስጠት ዐረፈ።
❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ግን የሚሠራውን ያውቃልና መጀመሪያ ከሞት አላዳነውም ጠርቶ እስከሚያስነሳው ድረስ ሙቶ በመቃብር አራት ቀን እንዲኖር በዚህ በአራት ቀንም የጻድቃንን ማደሪያዎችንና የኃጥአንን የሥቃይ ቦታዎች እንዲያይ ተወው እንጂ አላዳነው ያን ጊዜም ታላቅ ምልክት ትሆናለች።
❤ ከአራት ቀኖችም በኋላ የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ "አልዓዛር አልዓዛር ና ውጣ" ብሎ ከመቃብር ውስጥ ጠራው ያን ጊዜ እጆቹና እግሮቹ እንደታሠሩ ሙታኖችንም እንደሚጠቀልሏቸው በሰብን ፊቱ ተጠቅልሎ ወጣ። እጆቹና እግሮቹ እንደ ተጠቀለሉና እንደ ታሠሩ ከመቃብር የመውጣቱ ምክንያት ሰዎች ሁሉ መሞቱን እንዲረዱ ሌሎችም ይህ በመካከላቸው በስምምነት የሆነ ነው ብለው እንዳያስቡ። ስለዚህም እንደ ገነዙት ሁኖ እንዲወጣ ጌታችን አዘዘው ይችም ምልክት እንድትሆን። ከሀዲዎችም በመቃብር ውስጥ ሕያው እንደነበር ቢያስቡም እጆቹና እግሮቹ ፊቱም እንደ ተጠቀለሉ እንዴት ይወጣ ነበር እኛ የክርስቲያን ወገኖች ግን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ከአራት ቀኖች በኋላ አልዓዛርን ያስነሳው እርሱ እንደሆነ እናምናለን እንታመናለንም እርሱ በሥራው ሁሉ ላይ ችሎታ አለውና።
❤ ለጌታችንና ለፈጣሪያችን ለመድኃኒታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ ከቸር አባቱና ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ክብር ስግደት ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አናጒንስጢስ_ቅዱስ_ቴዎቅሪጦስ፦ ይህም ቅዱስ የሮሜ አገር ሰው ነው። ዐላውያንም ለጣዖት እንዲሠዉ ክርስቲያኖችን ይዘው በአስገደዷቸው ጊዜ ከእርሱ ጋር ያዙት ወደ ንጉሥም አቀረቡት ያንጊዜ የዐሥራ አምስት ዓመት ልጅ ነበር።
❤ ንጉሥም "በማመጣብህ ሥቃይ ትፈተናለህን ወይስ ለአማልክት ትሠዋለህ" አለው። ቅዱስ ቴዎቅሪጦስም እኔስ ለክብር ባለቤት ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እሠዋለሁ" አለው። ንጉሡም "ቴዎቅሪጦስ ሆይ በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአማልክት መሥዋዕት አቅርብ" አለው። እርሱም "ንጉሥ ሆይ መሥዋዕቴን እንድታይ ና" አለው ንጉሡም ወደ ጣዖቱ ቤት እንዲወስዱትና በዚያ እንዲሠዋ አዘዘና እርሱም በበር ቆመ። ቅዱሱም በጸለየ ጊዜ ንውጽውታ ሁኖ አጽቀላጽዮስ የሚሉት አምላካቸው ተሰበረ። ንጉሡም እንደ ዘበተበት አይቶ አፍንጫውን ቆርጠው አሥረው በወህኒ ቤት እንዲያስገቡት አዘዘ። በማግሥቱም አውጥተው በብረት ምጣዶች ውስጥ ጨመሩት ደግመው ጥልቅ ጉድጓድ ቆፈሩ በውስጡም እንጨት ረብርበው ሥጋው ከመለያያው እስቲቦጫጨቅና ቅልጥሙም ከአጥንቶቹ እስቲፈስ ድረስ ወረወሩት። በዚህም ሊያጠቁት አልቻሉም የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከእርሱ ጋር አለና።
❤ ከዚህ በኋላም አማልክቶቻቸው የሚበቀሉት መስሏቸው ከአማልክቶቻቸው ቤት አስገብተው በዚያ ዘጉበት ቅዱስ ቴዎቅሪጦስ ግን ከጣዖታቱ ላይ ያለውን ወርቅ ቀጥቅጦ በሥውር ይዞ እየወጣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች መጸወተው። ተመልሶ ሲገባም በደጃፉ እንደ ቀድሞው ራሱ ይዘጋል።
❤ በስምንተኛውም ቀን ንጉሥ መጣ ከደጃፍም ሁኖ አየ አማልክቶቹም ተጥለው ተሰባብረው የከበረ ቅዱስ ቴዎቅሪጦስ ሲዘብትባቸው አገኛቸው። እውነተኛ ቅዱስ ቴዎቅሪጦስንም የሆድ ዕቃው እስኪታይ እንዲሰነጣጥቁት አዘዘ። ደግመው ወደ ጨዋታ ቦታ እንዲያስገቡትና በላዩ አንበሶችን እንዲያስገቧቸው አዘዘ። አንበሶችም ቁስሎቹን ላሱለት። ዳግመኛም ሕዋሳቱ ከሚያጣብቅ ቦታ እንዲያስገቡት መላ አካላቱም ታጥፎ እስቲቆለመም እንዲያሠቃዩት አዘዘ። በዚህም ተሽብሮ አላሸነፉትም ንጉሡም ብርታቱን አይቶ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዘዘ።
❤ የከበረ ኤጲስቆጶስ ኤሞሬዎስና ሕዝቡ ሁሉ በጸሎት እየተራዱት ቅዱስ ቴዎቅሪጦስን ተከተሉት በቅዱሳን ሰላምታ ተሳልመውት ተሰናበቱት ባለወግ ወታደርም ሰይፉን አንሥቶ መጋቢት17 አንገቱን ቆረጠው ምስክርነቱንም ፈጸመ። የአናጒንስጢስ ቅዱስ ቴዎቅሪጦስ አማላጅነቱ በረከቱም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት17 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለጊዮርጊስ_ወተላስስ_ዳግማዊ። ወኤጲስቆጶስ ዮሴፍ ዘመርዔተ ክርስቶስ ኖላዊ። ጸዋዕኩክሙ ትርድኡኒ እምሥገርተ አርዌ ነዓዊ። ወትፈውሱኒ በጸሎትክሙ ማሕየዊ። እስመ ቀሳውስተ ይጼውዕ ዘይደዊ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_17።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወሰምዐኒ እምደብረ መቅደሱ። አንሰ ሰከብኩ ወኖምኩ። ወተንሣእኩ እስመ እግዚአብሔር አንሥአኒ"። መዝ 3፥4-5። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 15፥14-ፍ.ም፣ ያዕ 5፥14-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 2፥22-25። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 11፥1-17። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የጾም ወራትና በዓል። በሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፲፯ (17)።
❤ እንኳን ከዘጠኙ_ቅዱሳን_አንዱ_ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ይስሐቅ በሚያደርጉት ተአምር ስማቸው ተለውጦ #አባ_ገሪማ ለተባሉት #በመልአኩ_ቅዱስ_ገብኤል_ተራዳኢነት ሥንዴና ወይንን በአንድ ቀን ዘርተው ለሠርክ መሥዋዕት ላደረሱበት ለተአምራታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የአባታችን_አቡነ_ገሪማ_ያደረጉት_ድንቅ ተአምር፦ ...ያንጊዜም ቅዱስ አቡነ ገሪማ "ልጄ አባ ጴጥሮስ ሆይ እናርስ ዘንድ ስንዴንም እንዘራ ዘንድ በምሥራቅ በኩል በፊታችን ባለችው እርሻም ወይንን እንተክል ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን እናቅብ ዘንድ ማረሻ አዘጋጅ" አለው። "ተአምርን የምትሠራ ብፁዕ አባቴ ገሪማ ሆይ በሬዎችን የምንዘራው የስንዴን ዘርና የምንተክለውን የወይን ፍሬን ከየት አመጣለሁ? " አለው።
❤ ያንጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ከቅዱስ አቡነ ገሪማ ፊት ደርሶ ቆመ። "የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን" አለው። "ዘር ይሆንህ ዘንድ በላይዳን መስፈርያ ሦስት መስፈሪያ የስንዴ እህል ውሰድ፤ በነግህ ጊዜም ዝራው በቅሎም በስድስት ሰዓት ይፈራል፤ በሰባት ሰዓትም እንጨደው፤ በስምንት ሰዓትም ሥንዴውን በግራር ዛፍ ላይ አበራየው፤ በአቁ ማዳህም ክተት፤ መሥዋትም ሠርተህ በሠርክ ጊዜ አሳርግ። የወይን ፍሬንም የሰማይና የምድር ጌታ ለክቶ በሰጠህ (በወሰልህ) በቤተ ክርስቲያን በስተምሥራቅ ትከል። በዚያች ዕለት ሠርክ ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን ታሳርግበት ዘንድ እንካ ተቀበል፤ እንደ አባትህ አዳም ዝራ ትከል"። ይህንም ከሰጠው በኋላ መልአኩ ከእርሱ ተሰወረ።
❤ ከተቀበለም በኋላ ልጆቹ አባቶች መነኰሳት ጥንድ በሬዎችን አመጡ። በሬዎቹንም ተአምርንና ድንቅ ሥራን ወደሚሠራ ቅዱስ አቡነ ገሪማ አቀረቧቸው። ጻድቁ አቡነ ገሪማም እሊህን በሬዎች አይቶ ታላቅ ደስታን ተደሰተ። ልብሱን ለብሶ መታጠቂያን ይዞ ወገቡን ታጠቀ።
❤ ቅዱስ አቡነ ገሪማም ደቀ መዛሙርቱ አባ ሳሙኤል፣ አባ ጴጥሮስ፣ አባ ፊቅጦር፣ እየተከተሉት ተነሥቶ ወደዚያች እርሻ ሄደ። በብፁዕ አቡነ ገሪማ ነጋሢ ፊትም አውሬን የገደለ አባ ጳውሎስ በሬዎችን እየነዳ በአህያም የስንዴ ዘር ጭነው ያንጊዜ ወደዚያች እርሻ ደረሱ።
❤ ጥንድ በሬዎችንም ጠምዶ ተልሞ ያርስ ጀመረ፤ አርባ አራት ትልሞችን ተለመ። ያንም የስንዴ ዘር በዚያ እርሻ ላይ ዘራው። ያንጊዜ በነግህ (በጠዋት) ፈጥኖ በቀለ፤ ሐሙስን ቀን በስድስት ሰዓትም እሸትን ሆነ፤ ሐሙስ በሰባት ሰዓትም ጐምር ሁኖ ለመታጨድ ደረሰ። በስምንት ሰዓትም አጨዱት። ከግራር ዛፍ ላይም አወጡት። ቅዱስ አባታችን ገሪማም የግራሩን ዛፍ እንደ እህል አውድማ አደረገው። ሦስት በሬዎችን በግራር ላይ አውጥቶ ሥንዴውን በላዩ አበራየ (ወቃ) የሥንዴውን ምርት ወደ አቁማዳው ጨመረ።
❤ ጻድቁ ብፁዕ አቡነ ገሪማ ያን ሥንዴ ወስዶ ለቤተ ክርስቲያኑ አገልጋይ ሰጠው፤ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓትም ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን አቀረበ። የሥንዴውም ምርት በእንቅብ መስፈሪያ ሰባ ሰባት መስፈሪያ ሆነ። ለመንፈስ ልጆቹ አበው መነኰሳትና ለድሆች ሰጠ። ያስቀረውም አልነበረም። የእግዚአብሔር ፍቅር ገንዘብ አደረገ።
❤ ይኸውም ተአምር የተደረገው በመጋቢት ሃያ ቀን አምላክን በወለደች በእመቤታችን ማርያም የበዓል ዋዜማ የአኵስም ንጉሥ አፄ ገብረ መስቀል በነገሠ በሦስተኛው ዓመት ሐሙስ ቀን ነው። በዚያ ዘመን ዓመተ ምሕረቱ አምስት መቶ ሠላሳ ስድስት ዓመተ ምሕረት ነበር። የከበረች በረከቱ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋር ትኑር፤ ለዘለዓለሙ አሜን። ከአቡነ ገሪማ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ገሪማ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊ_ጻድቅ ከመቃብራቸው እስከ አሁን ድረስ ለበሽተኞች የሚሆን #ፈዋሽ_ቅባ_ቅዱስ_ለሚያፈልቁት ኤርትራ አገር የሚገኙ አምስት ታላላቅ ገዳማትን ለመሰረቱ #ለታላቁ_አባት_ለአቡነ_ዮናስ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ ቀን እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ዮናስ፦ ከአባታቸው ንዋየ እግዚእ ከእናቻው ሂሩተ ማርያም ሕዳር 17 በ1357ዓ.ም በጉናጉና ቤተ መስቀል ተወለዱ ስመ ክርስትናቸው ሀብተ እግዚእ ተባሉ። ሀብተ እግዚእ ገና ልጅ እያሉ የበጎች እረኛ ሆነው እየጠበቁ ሳለ መንፈስ ቅዱስ መልአኩን ልኮ 70 መዝሙረ ዳዊት አስተማራቸው ፍላጎታቸውም ወደ መንፈሳዊ ትምህርት እና ምናኔ ነበር። ከዛም ከተወለዱበት ቦታ ተነስተው ወደ ደብረ ሲና የምትባል ገዳም ሄዱ ከዛ የእናታቸው የሥጋ ወንድም አጎታቸውን አገኙ። አቡነ ዲያምኖስ የሚባሉ በጣም ትልቅ ባለጸጋ አባት አገኙ ከዛም በኋላ የመጡበትን ምንክንያት ለምናኔ መሆኑን ካወቁ በኋላ ሐዲስ ኪዳን እና ብሉይ ኪዳን እና ስርዓተ ምንኩስናን ከተማሩዋቸው በኋላ በ14 ዓመታቸው በ371ዓ.ም ስርዓተ ምንኲስናን ተቀበሉ የምንኲስናቸውም ስም አቡነ ዮናስ ተባሉ። ዮናስ ማለት የዋህ ልክ እንደ ርግብ ማለት ነው። ባሕር ውስጥ ገብተው እየጸለዩ በቀን 5 የዛፍ ፍሬ ዋርካ ወይም 5 ፍሬ እየተመገቡ በከባድ ጾምና በጸሎት በመንፈስዊ ተጋድሎ ይኖሩ ነበር።
❤ አቡነ ዮናስ ያደረጉት ተአምር።
1. ሶስት ሙታን አስነስትዋል።
2. ከኤርትራ በደመና ተጭነው ወደ ኢሩሳሌም ሄደው ቀድሰው ወደ ደብረ ጽጌ ገዳም ተመልሰው መክፈልት ይቀምሱ ነበር።
3. ዕረፍታቸው ቀን ሲደርስ በ5ቱ ገዳም የሚገኙ ልጆቻቸው ሰብስበው እኔ የዕረፍቴ ቀን እየደረሰ ነው ከእኔ በኋላ ልክ እንደእኔ አባት የሚኖናችሁ አባ ጳውሎስ ናቸው። እና ለእርሳቸው ልክ እንደ እኔ ታዘዙ አሏቸው። ልጆቻቸውም ይህን ሲሰሙ በጣም አዘኑ መጋቢት 17 ቀን 1452 በ92 ዓመታቸው በዐቢይ ጾም ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የዕረፍት በዓላቸው የሚከበረው ግን ጥር21 ቀን ነው። ልጆቻቸውም ከሀዘን ብዛት የተነሳ በትንሣኤ ቀን ምንም ሳያደርጉ ዝም አሉ። ከዚያም አቡነ ዮናስ ተገልጸው "ልጆቼ ከእኔ ሀዘን የጌታዬ ትንሣኤ ይበልጣል። እና አሁን ትንሣኤውን አድርጉ" አሏቸው ልጆቻቸውም ደግሞ "እኛ ምንም ነገር የለንም እና እንዴት እናደርግ" አሉ ጻድቁ አቡነ ዮናስ "ሦስት አጋዘኖች ወደ እናንተ ይመጣሉ እና እነርሱን አርዳችሁ በዓሉን አሳልፉ እንቢ ቢሏችሁ እንኳን በአቡነ ዮናስ ስም ገዝቷቸው" አሉ። ከዛ ጻድቂ እንዳሉ ሦስት አጋዘኖች መጡ ሁለቱ ታረዱ አንዱ ደግሞ ሊሮጥ ብሎ "በጻድቁ አቡነ ዮናስ ስም ቁም" ብለው ሲገስጹት ቆመ።
4 ጻድቁ አቡነ ዮናስ ካረፉ በኋላ በአምስቱም ገዳማት ዘይት ፈልቋል። በአሁን ጊዜ ግን በመቃብራቸው ብቻ ነው የሚገኘው።
5 ጻድቁ አቡነ ዮናስ የአምስቱ ገዳማት አባት ናቸው። 1.ደብረ ጽጌ 2.ደብረ ድሁሃን 3.ደብረ ሳህል 4.ደብረ ጽዮን 5.ደብረ ጸሪቅ በኢትዮጵያና በኤርትራ አገር ውስጥ ይገኛል።
6. ጻድቁ ባህር ውስጥ ገብተው ሲጸልይ እጃቸውም ልክ እንደ ጸሐይ ያበራ ነበር።
❤ #ቃል_ኪዳናቸው፦ በዚህ ከባድ መንፈሳዊ ተጋድሎአቸው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሳን መላእክት ጋር ወርደው ለአባታችን አቡነ ዮናስ እንደዚህ የሚል ትልቅ ቃልኪዳን ገባላቸው "ወዳጄ ዮናስ ሆይ ጾምህንና ጸሎትህን ተቀብዬልሀለው ከአሁን በኋላ ገድልህን የሰማ፣ ያሰማ፣ ያነበበ አስኬማህንና ቆብህን በስምህ የተቀበለ የ135 ሺ ከእናንተ ጋር የሚነግሱ ዓስራት አድርጌ ሰጥቼሀለው፤ በስምህ እና በጸሎትህ የተማጸነ ያለ ቁጥር እንደ ክረምት ዝናብ ምሬልሀለሁ ዝክርህን የዘከረ መጽሐፍ ገድልህን የጻፈ ያጻፈ፣ ለገዳሙ ዘቢብ፣ ዕጣን ፣ ስንዴ፣ ጧፍ፣ ሻማ፣ ንዋየ ቅድሳት የሰጠ፣ ገዳሙን ያነፀ፣ በስምህ የተማጸነ፣ ገዳምህን የረገጠ፣ እንደነጭ ሀር አነጻዋለሁ። ኃጢያቱ ልክ እንደ ቁራ ቢጠቁርም እንደነጭ በረዶ አነጸዋለሁ ብሎ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው። ከአባታች አቡነ ዮናስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን። ምንጭ፦ ገዳሙ ካሳተመው ከአቡነ ዮናስ ስዕል ጀርባ የተወሰደ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት፲፮ (16) ቀን።
❤ እንኳን #ለእስክንድርያ_አርባ_ሰባተኛ ሊቀ ጳጳሳት በተሾሙ ጊዜ ለሦስት ቀናት ስለ ቅድስናቸው እግዚአብሔር ዝናብን ላዘነበላቸው፤ በግብፅ አገር አሕዛብ በእሥራትና በስደት ብዙ ላሠቃዩአቸውና #የኢትዮጵያው_ንጉሥ_ሦስት_መቶ_ሺህ_ሠራዊት አዝምቶ ከዚህ ሥቃያቸው ታድጎ ነፃ ላወጣቸው ለከበሩ አባት #ለአባ_ሚካኤል ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሚካኤል፦ ይህም አባት በእስክንድርያ ከተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሰባተኛ ነው፡፡ በአስቄጥስ በአባ መቃርስ ገዳም መንኰሶ ኖረ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎድሮስ በዐረፈ ጊዜ በላዩ የትንቢት መንፈስ ያደረበት አንድ ጻድቅ ሰው እስከ ሚያስረዳቸው ድረስ ለዚች ሹመት ስለሚሻል ሲመክሩና ሲመረምሩ ብዙ ቀኖች ኖሩ።
❤ ከዚህም በኋላ ያ ሰው እኔ በአባ መቃርስ ገዳም በነበርኩ ጊዜ ስጸልይ "የሊቀ ጵጵስና ሹመት ለሚካኤል ይገባዋል ለዚች ሹመት የሚሻል እሱ ነውና የሚል ቃልን ከሰማይ ሰማሁ" አላቸው። ሁሉም ስለ ትሩፋቱ ተናገሩ ስለ እርሱም ተስማምተው ከገዳሙ ወደ እስክንድርያ ሊያመጡት ከምስር ገዥ ዘንድ ደብዳቤ አጽፈው ያዙ። ሊያመጡትም ሲሔዱ ስለ ገዳሙ አገልግሎት ከሽማግሌዎች መነኰሳት ጋራ ወደ ጋዛ ከተማ ሲመጣ በመንገድ አገኙት ይዘውም አሠሩት። ወስደውም በመስከረም17 ሊቀ ጵጵስና ሾሙት ያቺም ዕለት በጌታ ደም የከበረ መስቀል በዓሉ የሚከበርባት ናት።
❤ ይህም የሆነው ከዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በኋላ የሐሚድ ልጅ እልሲድ በሚገዛበት ዘመን ነው። በሹመቱ ወራትም መርዋን አልጋዲን ነገሠ። የእስክንድርያም አገር ሰዎች ከጥቂት ካፊያ በቀር ብዙ ዝናብ ሳይዘንብላቸው ብዙ ዓመታት ኖሩ። በዚች እርሱ በተሾመባት ቀን በሁለተኛውም በሦስተኛውም ብዙ ዝናብ ዘንቦላቸው እጅግ ደስ አላቸው።
❤ በዚህም አባት ዘመን በክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራ ደረሰ ከምዕመናንም ብዙዎች ሸሹ የክብር ባለቤት ክርስቶስም የካዱት ሰዎች ቁጥራቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነ። ለዚህለመለካውያን ነገር ምክንያት የሆነውን ከእርሱ እግዚአብሔር እስከአጠፋው ድረስ ይህ አባት ስለዚህ በታላቅ ኀዘን ውስጥ ነበር።
❤ ዳግመኛም በዚህ አባት ዘመን ቆዝሞስ ሊቀ ጵጵስና ተሹሞ ሳለ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ክርስቶስ ተዋሕዶ ከዚህ አባት ከአባ ሚካኤል ጋራ ተከራክሮ ይህ አባት አባ ሚካኤል እንዳስረዳው አመነ። እንዲህም ብሎ በእጁ ጻፈ "የክብር ባለቤት ክርሰቶስ በተዋሕዶ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስ እንደተናገረ የመለኮቱና የትስብእቱ አንድ ባሕርይ በመሆን ጸንቶ ይኖራል ሲል ኤጲስቆጶሳቱም እንዲሁ ከተዋሕዶ በኋላ ክርስቶስ የተለያዩ ሁለት ባሕርያት ሁለት ገጻት አሉት ይሉ ዘንድ የሚገባ አይደለም" ሲሉ ጻፈ። ሐዋርያትም በሰበሰቧት በከበረች በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአንድነት ጸንተው ሊኖሩ ተስማሙ።
❤ ከዚህም በኋላ ከእስክንድርያ ሰዎች መለካዊ የሆነ ስሙ አንስጣስዮስ የሚባል ሰው በላያቸው ጥፋትን አመጣ እርሱ ኤጲስቆጶስነት እንዲሾሙት ሽቶ አልሾሙትምና። ስለዚህ ወደ እስላሞች ንጉሥ ሒዶ በአባ ሚካኤል ነገር ሠራበት ከዐመፀኞች የነገሥታትም ብዙ መከራ ደረሰበት ጽኑዕ የሆነ ሥቃይም አሠቃዩት ብዙ ግርፈትም ገርፈው ለረጂም ጊዜ በእግር ብረት አሠሩት። አንገቱንም በሰይፍ ሊቆርጡ ወደ መኰንኑ አቅርበውት ነበር ስለ መንጋዎቹም ጥበቃ እግዚአብሔር አዳነው።
❤ ዳግመኛም በመዋርዋን አልጋዲ ዘመነ መንግሥት የሙሴ ልጅ በሆነ በንጉሥ አገልጋይ አደባባይ ታላቅ ሥቃይ አሠቃዩት፡፡መኰንኑም ገንዘብ እንዲሰጠው ሽቶ ሊቀ ጳጳሳቱን አባ ሚካኤል አሠረው ሰዎች መጥተው ዋስ ሁነው አወጡት። ምጽዋትም ጠይቆ ለመኰንኑ ብዙ ገንዘብ አምጥቶ እንዲሰጠው ወደ ላይኛው ግብጽ ወሰዱት። ይህ አባትም ወደ ላይኛው ግብጽ በሔደ ጊዜ በዚያ ብዙ ተአምራትን አድርጎ የክብር ባለቤት ክርስቶስ የካዱትን ምዕመናን ብዙዎቹን ወደቀናች ሃይማኖት መልሶ አስገባቸው።
❤ የኢትዮጵያ ንጉሥም ይህን አባት የእስላሞች መኳንንት እንዳሠቃዩት በሰማ ጊዜ ፍጹም ኀዘንንም አዘነ። መንፈሳዊ ቅናትንም ቀንቶ ወደ ግብጽ አገር ዘምቶ ከላይኛው ግብጽ ደረሰ። ከርሱ ጋርም መቶ ሺህ ፈረሰኞች አርበኞች፣ መቶ ሺህ በበቅሎ የተቀመጡ አሁንም በግመል የተቀመጡ መቶ ሺህ አርበኞች ነበሩ ብዙ አገሮችንም አጠፋ ብዙዎችንም ማረካቸው።
❤ የግብፁ ንጉሥም ይህ ሁሉ የሆነው ስለ ሊቀ ጳጳሳቱ ስለ አባ ሚካኤል እንደሆነ ዐውቆ ከእስራቱ ፈታው፡፡ ታላቅ ክብርንም አከበረው፡፡ የክርስቲያንን ወገኖች ሁሉ እጅግ አከባረቸው። ከዚህም በኋላ ለኢትዮጵያ ንጉሥ ደብዳቤ ጽፎ ይልክ ዘንድ ወደ አገሩም እንዲመለስ ያዝዘው ዘንድ የግብጽ ንጉሥ ይህን አባት አባ ሚካኤል ለመነው።
❤ ይህም አባት ወደ ኢትዮጵያ ንጉሥ እርሱንና መኳንንቱን መሳፍንቱንና ሠራዊቱን እየባረከና እየመረቀ ደብዳቤ ጽፎ ላከ። እንዲህም አለው "እንሆ በአንተ ምክንያት ከአሥራትና ከሥቃይ ሁሉ እግዚአብሔር አድኖናልና አሁን ወደ አገርህ በሰላም በፍቅር ተመለስ ስለ እኔና ስለ ክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ስለ ደከምክ መልካም ዋጋ እግዚአብሔር በመንግሥተ ሰማያት ይስጥህ"። የኢትዮጵያ ንጉሥም የዚህን አባት የሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤልን ደብዳቤ በአነበበ ጊዜ ፈጥኖ ተነሥቶ ወደ አገሩ በሰላም በፍቅር አንድነት ተመለሰ።
❤ አባ ቆዝሞስና ወገኖቹም ከሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋር በተስማሙ ጊዜ አባ ቆዝሞስ በውዴታው ለምስር ኤጲስቆጶስ ሁኖ ተሹሞ ከዚህ አባት ከአባ ሚካኤል ሥልጣን በታች ሆነ።
❤ ይህም አባት መልካም ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር መጋቢት16 ሔደ። የአባ ሚካኤል አማልጅነቱ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይሁን አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት16 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ዝርዎሙ ለአሕዛብ እለ ይፈቅዱ ቀተለ። ይምጽኡ ተናብልት እምግብፅ። ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር"። መዝ 67፥30-31። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 4፥1-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 1፥12-19 እና የሐዋ ሥራ 11፥23-27። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 14፥28-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ወራትና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፲፭ (15) ቀን።
❤ እንኳን #ለከበረች_ተጋዳይ_ለመነኰሳዪት ሰይጣንን በትሕትና ድል ላደረገች #ለቅድስት_ሣራ ዘላዕላይ ግብጽ ለዕረፍት በዓልና #ለቅድስት_አስጠራጦኒቃ እጮኛዋ ለሆነ #ለቅዱስ_ሰለፍኮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ናህስ ከሚባል አገር ከሆኑ ከሰማዕቱ ከከበረ #ከአባ_ሕልያስ_ከሰፍንዮስና_ከሐዲስ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_ሣራ፦ ይቺም ቅድስት ከላይኛው ግብጽ ናት ወላጆቿም የክብር ባለቤት ክርስቶስን የሚያመልኩ ክርስቲያን ናቸው። እጅግም ባለጸጎች ነበሩ። ነገር ግን ከእርስዋ በቀር ልጆች የሏቸውም በመልካም አስተዳደግም አሳደጓት ለክርስቲያን የሚገባ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩዋት ደግሞም ጽሕፈትን አስተማራት ሁሉጊዜም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ታነባለች ይልቁንም የመነኰሳትን ዜና ታነብ ነበር። መጻሕፍትንም አዘወትራ ስለምታነብ የምንኵስና ልብስ ለመልበስ ፈለገች በላይኛው ግብጽ ከሚገኙ ገዳማትም ወደ አንዱ ገዳም ሒዳ ገባች ብዙ ዘመናትም ደናግልን እያገለገለች ኖረች።
❤ ከዚህም በኋላ የምንኵስና ልብስን ለበሰች ሰይጣንን ድል እስከ አደረገችው ድረስ። ሰይጣን የሚያመጣውን ሥጋዊ ፍትወት እየታገለች ዐሥራ ሦስት ዓመት ኖረች። ንጽሕናን ከመውደዷ ጽናት በተሸነፈ ጊዜ በትዕቢት ሊጥላት ወዶ በቤት መዛነቢያ ልትጸልይ ቁማ ሳለች ተገልጦ "ሣራ ሆይ ሰይጣንን ድል አደረግሽዋልና ደስ ይበልሽ" አላት እርሷም መልሳ "እኔ ደካማ ሴት ነኝ ከክብር ባለቤት ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ድል አድርጌ ላበረው አልችልም" አለችው።
❤ ይህችም ቅድስት አብረዋት ላሉ ደናግል ጥቅም ያላቸውን ብዙ ትምህርቶችን ታስተምራቸው ነበር። እንዲህም ትላቸዋለች "ከቀን ብዛት ጠላት እንዳያስተኝ እኔ እንደምሞት አስቀድሜ ሳላስብ እግሬን ከአንዱ መወጣጫ ደረጃ ወደ ሁለተኛዋ አውጥቼ አላኖራትም"። ዳግመኛም "ለሰው ርኅራኄ ማድረግ በተሻለው ነበር ይህንንም በሚያደርግ ጊዜ የኋላ ኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ይኖራል" በዜና አረጋውያን መነኰሳት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፉ ሌሎች ብዙ ቃሎችንም ተናግራለች።
❤ ታላቅ ተጋድሎም እየተጋደለች በዓቷም በባሕር ዳርቻ ሁኖ ሰባት ዓመት ኖረች አንዲት ቀን እንኳን ከሰው አንዱም አላያትም እርሷ ግን ሁሉን ታይ ነበር። ሸምግላ እስከ ሰማንያ ዓመት በደረሰች ጊዜ ከዚህ ዓለም የሕይወት ማሠሪያ ተፈትታ የዘላለም ተድላ ደስታ ወደሚገኝበት መጋቢት15 ቀን ሔደች። የቅድስት ሣራ ጸሎቷ በረከቷ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሰለፍኮስ፦ የዚህን ቅዱስ ዜና ክርስቲያን እንደሆነ ከሃዲ ንጉሥ በሰማ ጊዜ ያመጡት ዘንድ አዘዘ ወደርሱም ሲቀርብ "የአስጠራጦኒቃ እጮኛዋ ሰለፍኮስ የተባልክ አንተ ነህን" አለው "አዎን ነኝ" አለ። ዳግመኛም "ማንን ታመልካለህ" አለው እርሱም እኔ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አመልከዋለሁ" ብሎ መለሰ። ንጉሡም መርዝ ያላቸው እባቦች ወዳሉበት እንዲጨምሩት አዘዘ እግዚአብሔርም አዳነው።
❤ ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዝዞ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊል ተቀበለ። የቅዱስ ሰለፍኮስ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት15 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለሕልያስ_ሰማዕት_ሐዲስ። ዘአገረ ናህስ። ብቊዓኒ ሊተ በእንተ ክርስቶስ። ከመ ተሀበኒ መድኃኒት ሥጋ ወነፍስ። እምነ ብዕልከ እስእል ጽኑስ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_15።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ጻድቃንሰ ይወርስዋ ለምድር። ወይነብሩ ውስቴታ ለዓለመ ዓለም። አፉሁ ለጻድቅ ይትሜሐር ጥበበ"። መዝ 36፥29-30። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 5፥21-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 5፥14-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 26፥1-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥19-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም ወራት ጊዜና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ቄርሎስ፦ ይህም አባት የእስክንድርያ ሰባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳሳት ነው። እርሱም በምግባሩ ፍጹም ዐዋቂ ሆነ በአገሩ ፍዩም ይባላል በእርሷም ቅስና ተሹሞባት ነበር። ከዚያም ለቆ ወደ አባ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ እርሱም ከምስር ከተማ ውጭ የኢትዮጵያውያን ዐዘቅት የዐባይ ግድብ በአለበት ነው። በዚም ታላቅ ገድልን እየተጋደለ ብዙ ዘመናትን ኖረ። ብዙ መጻሕፍትንም ተምሮ ትርጓሜያቸውንና ምሥጢራቸውን ጠንቅቆ ዐወቀ። አሸናፊ ወደሚባለውም ንጉሥ አደባባይ ቀርቦ የእስላሞች ታላላቅ ሊቃውንቶቻቸውና ከምሁራኖቻቸው ውስጥ መምህሮታቸውን ተከራከሩት። ጠቃሚ የሆነ ዕውቀት የተመላበትን መልስ አገኙ የሚጠይቁትንም ሁሉ በመልካም አመላለስ ነገራቸው ከዚህ በኋላ የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ፈቃዱ ይዘው በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም ጠበቀ በጸሎትና በቅዳሴ ያገለግሉ ዘንድ ለካህናት ሥርዓትንና መመሪያን ሠራ።
❤ ይህም አባት በሊቀ ጵጵስናው ሰባት ዓመታት ከዘጠኝ ወር ከዐሥር ቀኖች ኖረ። ከቀኑም በሦስት ሰዓት መጋቢት14 ቀን ዐረፈ። በምስክርነት አደባባይም ተቀበረ። ከአባ ቄርሎስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ የከበሩ #ቅዱሳን_አጋንዮስ_አውንድርያኖስና_ብንድዮስ፦ እሊህም ቅዱሳን ከአባቶቻቸው ጀምሮ ክርስቲያኖች ናቸው። አምላካዊ ትምህርትንም ሁሉ የተማሩ ናቸው።
❤ በእግዚአብሔርም ሕግ ጸንተው ሲኖሩ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አርሞስ መርጦ ኤጲስቆጶሳት አድርጎ ሾማቸው ግን በታወቁ ቦታዎች ላይ አይደለም በብዙዎች አገሮች ውስጥ እንዲሰብኩ ላካቸው እንጂ። በአገሮችም ያሉ ከሀድያን ያዟቸው ያለርህራሄም አብዝተው ገረፏቸው በደንጊያም ወገራቸው መጋቢት 14 ቀን ነፍሳቸውንም በጌታች እጅ ሰጡ። የከበሩ ቅዱሳን አጋንዮስ፣ አውንድርያኖስና ብንድዮስ በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት14 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለቶማስ_እንዘ_ይገብር_መድምመ። እምነ ብእሲት አግኂሦ ትድምርተ ጋኔን ኅሡመ። መንጽሔ ኃጢአት መጠዋ ሥጋ ወደመ። በጊዜ ትቤሎ ሀበኒ ማሕተመ። ከመ ላዕሌየ ኢይግባእ ዳግመ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢ_14።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 7፥9-ፍ.ም፣ ያዕ 4፥6-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 6፥1-8። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 7፥1-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፲፬ (14) ቀን።
❤ እንኳን #ለሐዋያው_ለቅዱስ_ቶማስ ሰባት ዓመት ያህል የጋኔን ግንኑኙነት በአስቸገራት በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን ላደረገበት በዓል፣ ለአረጋውያን ፍጹማን መነኰስ አመንዝራ ሴቶች ብር እየሰጠ በጥበብ ለትዳርና ምንኵስና ላበቃ #ለአባ_ባጥል ለዕረፍት በዓል፣ ለቅዱስ አባት #ለአባ_ሲኖዳ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍት በዓል፣ ለእስክድርያ ሰባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ቆርሎስ ለዕረፍት በዓል፣ ለከበሩ #ቅዱሳን_አጋንዮስ_ለአውንድርያኖስና_ለብንድዮስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ቶማስ ሰባት ዓመት ያህል የጋኔን ግንኑኙነት በአስቸገራት በአንዲት ሴት ላይ ያደረው ተአምራትን ይህ ነው፦ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስንም በአየችው ጊዜ "የክርስቶስ ሐዋርያው ሆይ እጅግ ከሚያሠቃየኝ ጠላት አድነኝ" ብላ ወደርሱ ጮኸች። እርሱም "በምን ምክንያት አገኘሽ" አላት። እርሷም "ከመታጠቢያ ከውሽባ ቤት ስወጣ እንደ ሰው ድው ድው እያደረገ በመታወክ መጣ ድምጡም ሰላላና ቀጭን ነው በሴትና በወንድ ሥራ ሁሉ ነይ እርስበርሳችን አንድ እንሁን አለኝ በተኛሁም ጊዜ በሌሊት መጥቶ ከእኔ ጋር አንድ ሆነ ብሸሽም አይተወኝም መጥቶ ያሠቃየኛል እንጂ እኔም ከጸሎትህ የተነሣ አጋንንት እንደሚንቀጠቀጡ አውቃለሁና ጸልይልኝ አድነኝም" አለችው።
❤ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስም ሰምቶ ጸለየ ጋኔኑንም ከእርሷ እንዲወጣ አዘዘው ያንጊዜም በእሳትና በጢስ አምሳል ከሴቲቱ ላይ ወጥቶ ተበተነ ከዚህ በኋላ በክርስቶስ መስቀል በላይዋ አማተበ ሥጋውንና ደሙንም አቀበላት ወደ ዘመዶቿም አሰናበታት። የሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ልዩ የሆነች በረከቱም በሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ላይ ትደር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ባጥል፦ ይህም ቅዱስ ሰው ከአባ ዮሐኒ የተባለ አበ ምኔት በመነኰሳት ላይ ነገረ ሠሪን እንደሚቀበል በሰማ ጊዜ በዓቱን ትቶ ወደ እስክንድርያ መጥቶ የሴት አዳሪዎችንና የአመንዝራዎችን ሁሉ ስማቸውን ጻፈ። ከኪራይ ሠራተኞችም ጋራ ሲሠራ ይውላል። ደመወዙን በተቀበለ ጊዜ የሽንብራ ቂጣ ገዝቶ ይበላል የቀረውንም ገንዘብ ይዞ ወደ አንዲቱ ሒዶ ይሰጣታል "በዚች ቀን ከአንቺ ጋራ አድራለሁና ራስሽን ለእኔ አዘጋጂ" ይላታል። ከኀጢአትም ሊጠብቃት ከእርስዋ ዘንድ ያድራል ሌሊቱን ሁሉ ተነሥቶ ሲጸልይና ሲሰግድ እግዚአብሔር ሲለምን ያድራል ሲነጋም ሥራውን ለማንም እንዳትገልጥ አምሏት ወደ ተግባሩ ይሔዳል።
❤ በየዕለቱም ወደ የአመንዝራዎቹ እየሔደ እንዲህ ያደርግ ነበር አንዲቱም ሴት ምሥጢሩን ገለጠች ጋኔንም ይዞ አሳበዳት። ሰዎችም ስለዚህ ክፉ ሽማግሌ ክፉ ሥራ የለበትም ብላ ወሽታለችና እግዚአብሔር መልካም አደረገባት ተባባሉ። እርሷም "እንዳናመነዝር ገንዘብ በመስጠት ከኃጢአት ይጠብቀናል እንጂማ ነውር የለበትም" ብላ ነበርና። የቀሩት አመንዝራዎች በእርሷ ላይ የሆነውን በአዩ ጊዜ ደነገጡ እንደርሷም እንዳያብዱ እውነቷን ነው ማለትን ፈሩ። እርሱም "ይችስ በእገሌ ዕለት ትጠብቀኛለች" ይል ጀመረ ሰዎችም ሁሉ ያሙት ጀመር እርሱም "እንደ ሰው ሁሉ ሥጋ የለኝምን ወይስ እግዚአብሔር መነኰሳትን ተቆጥቶ በፍትወት ተቃጥለው እንዲሞቱ ትቷቸዋልን" አላቸው። እነርሱም "ልብስህን ለውጠህ ሚስት አግባ ይህ ይሻልሃልና" አሉት። እርሱም "አዎን ብወድ በሚስቴ እጠነቀቃለሁ በዚህም በክፉ አኗኗር እኖራለሁ እናንተ ግን ከእኔ ዘንድ ሒዱ ምን ትሻላችሁ በእኔ ላይ እግዚአብሔር ፈራጆች አድርጓችኋልን ይልቁንስ እናንተ እንዳይፈረድባችሁ ለራሳችሁ አስቡ ፈራጅ አንድ ነውና ዕለቲቱም አንዲት ናትና" አላቸው።
❤ ይህም ቅዱስ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አገኘ በሰው ዘንድ ግን የተናቀ ሁኖ ኖረ። ከእርሱ ጥቅም የአገኙ አመንዝራዎችም ዝሙታቸውን ተዉ። ከእርሳቸውም ሕጋዊ ጋብቻ ተጋብቶ የኖረ አሉ ወደ ገዳምም ገብቶ መንኵሶ በጾም በጸሎት ተወስኖ የኖሩ አሉ።
❤ በአንዲት ዕለትም ከአንዲት አመንዝራ ቤት ሲወጣ ያቺን ሴት አስቀድሞ የለመዳት አንድ ሰው አገኘውና "ይህ ሽማግሌ እስከ መቼ ድረስ በዚህ በክፉ ሥራ ይኖራል" ብሎ ፊቱን በጥፊ መታው።
❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን በበዓቱ ውስጥ ሰግዶ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ሰጥቶ በቤቱም መድረክ "የዚች አገር ሰዎች ጊዜው ሳይደርስ በማንም ላይ አትፍረዱ እንዳይፈረድባችሁ" የሚልም ጽሑፍ ተጽፎ ተገኘ። ከአባ ባጥል በጸሎቱ የሚገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሲኖዳ፦ እርሱም በግብጽ አገር ከብሕንሳ ነው። ወደ መክስምያኖስም ክርስቲያናዊ ሲኖዳ "አማልክትን የሚያመልክ ነው" ብለው ነገር ሠሩበት። እርሱም አስቀርቦ ስለ ሃይማኖቱ ጠየቀው በንጉሡም ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ እርሱም ዕውነተኛ አምላክ እንደ ሆነም መሰከረ።
❤ መክስምያኖስም ይህን የከበረ አባ ሲኖዳን በምድር ላይ ዘርግተው በበትሮች እንዲደበድብት አዘዘ። ዐጥንቶቹ እስቲሠነጠቁ ደሙም በምድር ላይ እንደ ውኃ እስቲፈስ እንዲሁ አደረጉበት። ከዚህም በኋላ እግሩን ይዘው ጐትተው ወስደው ሽታው በሚከረፋ በጨለማ ወህኒ ቤት ጣሉት የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለት። ቊስሎቹንም አድኖ ጤነኛ አደረገው አበረታውም "በርታ አትፍራ ስለ መከራህም የክብር አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና ደግሞም በጽኑዕ ሥቃይ ትሠቃይ ዘንድ አለህ እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ እኔም ከአንተ ጋራ እኖራለሁ" አለው። ከዚያም ከእርሱ ተሠወረ።
❤ በነጋ ጊዜም "የነገሥታትን ትዕዛዝ የሚተላለፍ ያንን ዓመፀኛ ሒዳችሁ እዩት ሙቶም ከሆነ ለውሾች ጣሉት" ብሎ መክስምያኖስ ወታደሮቹን አዘዘ። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ቁሞ ሲጸልይ አግኝተውት "ያለምንም ጥፋት ጤነኛ እንደሆነና በሥጋውም ውስጥ የሕማም ምልክት እንደሌለ እርሱም ከቶ ምንም ሥቃይ እንዳላገኘው ጤነኛና ደስ እንዳለው ሰው ተግቶ እንደሚጸልይ" ስለርሱ ለንጉሡ ነገሩት። ንጉሡም ወደርሱ አስመጣው ከሕይወቱም የተነሣ አደነቀ ልብሶቹንም አስወልቆ ያለጉዳት ጤነኛ እንደሆነ ሥጋውን አየ ደግጦም "ይህ ያየሁት ሥራይ ታላቅ ነው" አለ። ከዚያም ዘቅዝቀው ሰቅለው ከታቹ እሳትን እንዲያነዱ አዘዘ። ይህንንም አደረጉበት ደግሞ በመንኰራኵር አሠቃዩት በአለንጋዎችም አብዝተው ገረፉት ደበደቡትም።
❤ ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ቆርጠው ለውሾች እንዲጥሉት አዘዘ ውሾች ግን ፈጽሞ አልቀረቡትም ሌሊትም ሲሆን ምዕመናን መጥተው ሥጋውን ወሰዱ በአዳዲሶች ልብሶችና በጣፋጭ ሽቶዎች ገነዙት በሣጥንም አድርገው ቀበሩት። ከሥጋው ብዙዎች አስደናቂዎች ተአምራቶች ተደረጉ። የአባ ሲኖዳ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለዐቢይ_ጾም_ስድስተኛ_ሳምንት_ለገብር_ኄር እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የገብር_ኄር_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምዕመን ዘይረክቦ እግዚኡ በምግባረ ሠናይ ወይሠይሞ ዲበ ኵሉ ንዋዩ ካዕበ ይቤሎ እግዚአብሔር ገብር ኄር ወምዕመን ዘበውኁድ ምዕመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሠይመከ ባዕ ውስተ ፍሥሓሁ ለእግዚእከ"። ትርጉም፦ በመልካም ሥራ ጌታው ያገኘው በጎ ታማኝ አገልጋይ ማነው? በንብረቱ ላይ ሁሉ የሚሾመው ታማኝ በጎ አገልጋይ ማነው? ዳግመኛም እግዚአብሔር አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ።
✝ ✝ ✝
❤ #ገብር_ኄር፦ ማለት ቸር አገልጋይ ማለት ነው።
"መንግሥተ ሰማያት ነጋዴ ናት "
❤ መንግሥት ሰማያት ነጋዴ ናት ትርፍን ትፈልጋለች ስለዚህ በመጽሐፍ መንግሥት ሰማያት ብላቴኖቹን ጠርቶ ወጥተው ወርደው ያተርፉበት ዘገድ ገንዘቡን የሰጣቸውን ነጋዴ ትመስላለችና ይላል። ማቴ ፳፭፥፲፭
❤ ሹመትም ውርደቱም ፣ መጽደቅ መኰነንም በዋጋ (በጸጋ) ሳይሆን በትርፍ ነው። 5 እና 2 መክሊት የተሰጣቸው አገልጋዮች የተሾሙት በትርፋቸው እንጂ ቀድሞ የተሰጣቸውን መክሊት በማቆየታቸው አይደለም፤ 1 መክሊት የተሰጠውም ባሪያ የተኮ
ኰነነው የተሰጠውን መክሊት በማጥፋቱ አይደለም ባለማትረፉ እንጂ መክሊቱንስ አስቀምጦ ጌታው በመጣ ጊዜ መልሶለት ነበር በተሰጠው ባለማትረፉ ግን ቀድሞ የተሰጠውን መክሊት ሳያጠፋ ጠብቆ በመገኘቱ ብቻ ከመኰነን አላዳነውም። ስለዚህ ጽድቅና ኵነኔ በትርፍ መሆኑን ተረዳን።
❤ በማቴ 25 ላይም በምሳሌው የተገለጸው ይህንን የሚያስረዳ ነው፦ ባዕል ነጋዴ ብሎ ጌታን (መንግሥተ ሰማያት) ፣ አግብርት ብሎ መምሕራንን ካህናትን ማምጣት ነው።
❤ ባለ ፭፣ ፪ትም የተባሉት ፍጹም ትምህርት ተምረው መክረው አስተምረው ራሳቸውን አስመስለው ያወጡ መምህራን ናቸው። ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን፣ ጳውሎስ ጢሞቴዎስን እንዳወጡ። እነዚህ መምህራን በትምህት የሚወልዱ በመሆናቸው ብዙ ተባዙ ያለውን ቃል የፈጸሙ ናቸው።
❤ ባለ ፩ የተባለ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ ነው:: ዐላውያን እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ፣ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ ቢያሳጡኝ ብሎ፤ ሃይማኖቱን በልቡ የያዘ ነው። ይህን ባሪያ የመሰሉ በትምህርት የማይወልዱ የጋን መብራቶች ሜልኮላውን ናቸው። ይህም በአባ መልክአ ክርስቶስ ታውቋል። ፍጹም ትምርት ተምረው ሳለ ሳያስተምሩ ቀርተዋል በተባሕትዎ መላ ዘመናቸውን ፈጽመውታል። በሚሞቱበት ጊዜ መልአክ ገሠጻቸው። ቀለሙ አካል እየገዛ ሲወጣ ታይቷል።
❤ ጸጋ ስጦታ ነው መመስገኛም መወቀሻም የሚሆነው ግን በተሰጠ ጸጋ በሚሠሩት ሥራ እና ባለ መሥራት ነው። የነጋዴ ጥቅሙ በትርፍ እንደሆነ ሰው መሾም መሻሩ፤ መጽደቅ መኰነኑ በተሰጠው ጸጋ ሌላው ምዕመናን ትርፉ በማድረጉ ነው።
❤ በምሳሌውም "ላለው ይጨመርለታል" ያለው ጸጋ ላለው ጸጋ ይጨመርለታል ማለቱ ሳይሆን በተሰጠው ጸጋ ትርፍ ያለው ሰው ሌላ ያተርፍ ዘንድ ጸጋ ይጨመርለታል ማለት ነው። "ለሌለው ግን ያለውን ይወሰድባታል" ማለቱም ትርፍ ለሌለው ግን እንኳንስ ሌላ ጸጋ ሊሰጠው ቀርቶ ቀድሞ የተሰጠው ጸጋ ይወስድበታል ማለቱ ነው።
❤ ስለዚህ መንግሥተ ሰማያት ነጋዴ ናት ያተረፉ የሚገቡበት የትሩፋን ሀገር ናት። ገብር ኄር ተብሎ በወንጌል የሚነገረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ሲያስተምር ካስተማረቸው ትምህርት አንዱ ነው። እንዲህ ሲል ይጀምራል፦ ወደ ሌላ ሀገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናል። ምንጭ፦ አምኃ ሥላሴ (መኩሪያ ተስፋዬ) ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ። ወሕግከኒ በማእከለ ከርሥየ። ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበረ ዓቢይ"። መዝ 39፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 2፥1-16፣ 1ኛ ጴጥ 5፥1-12 እና የሐዋ ሥራ 1፥6-9። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 25፥14-31። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓል፣ ዕለተ ሰንበት (ገብረ ኄር)ና የወራት ጊዜና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
የዐብይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡
ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ስለ ታማኝ አገልጋይ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ስንኖር ለፈጣሪያችን ያለንን ታማኝነትና የምናገኘውን ዋጋ በመዋዕለ ሥጋዌው አስተምሯል፡፡
••
ቅዱስ ያሬድ ለዜማ መክፈያነት የዐብይ ጾምን ሳምንታትን ሲከፍል ገብርኄርን ተጠቅሟልና እኛም ስለ ገብር ሄር ጥቂት እንበል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በነቢዩ አንደበት አድሮ ፤ “ እከሥት በምሳሌ አፉየ ፤ ወእነግር አምሳለ ዘእምትካት ፤ አንደበቴን / ነገሬን / በምሳሌ እገልጣለሁ ፤ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ ታሪክና ምሳሌ እናገራለሁ ” አለ፡፡
••
ይህም ማለት ወንጌልን በምሳሌ አስተምራለሁ ፤ በመልከ ጼዴቅ ዘመን አስቀድማ የተሠራችና ታይታ የጠፋችውን ወንጌልን እናገራለሁ፡፡ ይህን ታላቅ ምሥጢር ሐዋርያው ሲያብራራ “ ከመ በአሚን ያጸድቆሙ እግዚአብሔር ለአሕዛብ አቅደመ አሰፍዎቶ ለአብርሃም ከመ ቦቱ ይትባረኩ ኲሎሙ አሕዛብ ፤ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ ” ብሏል፡፡ /ገላ. ፫፥፰፣ መዝ. ፸፯፥፪
••
በዚሁ መሠረት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ ከላይ በተገለጠው ኃይለ ቃል መነሻነት ሁለት ምሳሌያትና አንድ ቃለ ትንቢት ቀርበዋል፡፡ ከምሳሌያቱ የመጀመሪያው በዐሥሩ ደናግል አንጻር የቀረበው ምሥጢር ሲሆን ፤ ሌላኛው ደግሞ ወጥተው ወርደው ነግደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን ስለሰጠ አንድ ነጋዴ የሚናገረው ነው፡፡
••
የትንቢቱ ምሥጢራዊ ይዘት የሚያስረዳውም ስለ ኅልቀተ ዓለም አይቀሬነት ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕትማችን ወጥተው ወርደው ነግደው እንዲያተርፉበት ከጌታቸው የተሰጣቸውን መክሊት ስለተቀበሉት አገልጋዮች ሕይወት እንመለከታለን፡፡ ፈጣሪያችን አእምሮውን ለብዎውን /ማስተዋሉን / ያድለን፡፡
••
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው ምሳሌያዊ ትምህርቶች በቅዱስ መጽሐፋችን በሰፊው ተጽፈው እናገኛለን፡፡ የእነዚህ ትምህርታዊ ምሳሌዎች መሠረታዊ ሀሳብና ዓላማም የእግዚአብሔርን መንግሥት የምናገኝበትን የታማኝነትን ሥራ እንዴት መሥራት እንደሚገባንና መሥራትም እንደምንችል ማስተማር ነው፡፡
••
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች መካከልም እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ስለተመሰገኑት መልካም አገልጋዮች ፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰነፍ ሰው ታሪክ ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል የተጻፈው ትምህርት ነው።
••
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ምሳሌ የተናገረው / ያስተማረው / በሚከተለው መልኩ ነበር ፤ ‹‹ ወደ ሌላ ሀገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ ሀገር ወዲያውኑ ሔደ፡፡
••
አምስት መክሊትም የተቀበለው ሔዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ ፣ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ ፣ አንድ የተቀበለው ግን ሔዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡
••
👉🏻 ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡
•
💰
አምስት መክሊት -
የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፡- ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር ፤ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡
📌
ጌታውም -
መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡
••
💰
ሁለት መክሊት
የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡፡ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡
📌
ጌታውም -
መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
••
💰
አንድ መክሊትም -
የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ ፤ ፈራሁም ሔጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት ፤ እነሆ መክሊትህ አለልህ አለው፡፡
📌
ጌታውም -
አንተ ክፉና ሐሰተኛ ባሪያ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር።
••
እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት። ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል። ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡ የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት ፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል የሚል ነው፡፡
••
መክሊት ጥንት የክብደት መለኪያ ነበር:: አንድ መክሊት 30 ኪሎ ግራም ያህል ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ ላይ እንደተገለጸውም መክሊት የሚለው ቃል ገንዘብን ያመለክታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ እርሱን የምናገለግል ሁላችን እንደየዓቅማችን ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ የአገልግሎት ሥራንና በአገልግሎታችን ውጤታማ በመሆናችንም ከእርሱ የምናገኘውን ዘለዓለማዊ ክብርና ዋጋን እንዲሁም መሥራት የሚገባንን ባለማድረጋችንም ምክንያት የሚገጥመንን መለኮታዊ ቅጣትን አመልክቶናል፡፡
••
በዚህ ምሳሌ ውስጥ ባለ አምስት የተባለው በቂና ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ የተካ ያወጣ ነው፡፡
••
በተመሳሳይም ባለ ሁለት የተባለው እንደ መጀመሪያው ሁሉ ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ሲሆን ባለ አንድ የተባለው ደግሞ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ በስንፍና በቸልተኝነት በማን አለብኝነት ሕይወት ተገድቦ የቀረ ሰው ነው፡፡
••
እንደ ስራ ሊከፍለን ወልደ እግዚአብሔር በመጨረሻው ዘመን ሲመጣ አትርፈን እንጂ ያለንን ጥለንና የተሰጠንን ቀብረን የምንጠብቅ መሆን የለብንም።