ዉሉደ ብርሃን ሚዲያ
前往频道在 Telegram
ይህ የእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ፤ ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ገፅ ነው ። በዚህ ገፅ ፦ ● መንፈሳዊ ትምህርቶች ፣ መልዕክቶች ፣ ምክሮች ● መዝሙሮች ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ● ወቅታዊ የቤተክርስቲያን እና የሰ/ት/ቤት ጉዳዮች ● የሰ/ት/ቤት መልዕክቶች ፣ ማስታወቂያዎች ይቀርቡበታል። ኦዲዮቪዥዋል ክፍል ለመቀላቀል ➠ @Wuludebirhane7
显示更多1 199
订阅者
无数据24 小时
+27 天
+330 天
帖子存档
1 199
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ዉሉደ ብርሃን ዛሬ ያሳደግሽው
ዮሴፍ ልጅሽን አሁን እንዳጣሽው
ምን ተሰማሽ አገልጋይሽ ነበር
በትምህርት ክፍሉ ዘወትር የሚታትር
በሥርዓት ያሳደግሽው ከማዕከላዊ ጀምሮ
መቸም አይረሳም ሲሠራ ጠንክሮ
ወዮ! ... ልበል ዛሬ ዮሴፍ ወንድማችን
ላይመለስ ሄደ ጠፋ ከጎናችን
አይ' ሞት ... ክፉ ነው' ሞት አይመርጥም ሰው
ከአብራክሽ ሲወጣ የተሰማሽ ምንድነው?
የሒሳቡ ሊቅ በየክፍሉ ያደገው
ትምህርት በማስተማርና ሥርዓት ያሲያዘው
በጥበብ በሞገስ ነው እዚህ የደረሰው
ዉሉደ ብርሃን እናቴ ልጠይቅሽ ዛሬ
ልጅሽ ሲለይሽ ያፈራሽው ፍሬ
ይድናል ብለው እንዲያ ሲሯሯጡ
ሞትን ማስቆም አልተቻለም ሆነና ቁርጡ
ዮሴፍን አጣነው ከማኅበር የለም
ከመዝሙር አገልግሎት ከትምህርት ክፍልም
ከበሮ ሲመታ ወረቡን ሲወርብ
ቅዳሴ ላይ ሲያስተባብር በግብረገብ
ያሁሉ ትጋት በሰኔ ወር ጠፋ
በእለተ ቀዳሚትት በጣም አንቀላፋ
ስንጠብቀው ቀረ ዛሬ ተቀበረ
ሀዘናችን ልዩነው አንጀታችን አረረ
ቀድሞም ፈጣሪ አውቆበት ለእራሱ
አገልጋይ አድርጎት ለቤተ መቅደሱ
ከሥላሴ ወደ ሥላሴ መገስገስ
ሥልጣኑ ነውና የሥሉስ ቅዱስ
ውዱ ወንድማችን የውሉደ ብርሃን አለኝታ
ከህይወት በእረፍተ ሥጋ ብትረታ
አናለቅስም እኛ ትንሣኤ ስላለን
በዳግም ምጽአት እንገናኛለን
ቤተሰቦቹን መጽናናት ይስጥልን!
ውሉደ ብርሃን ፈጣሪ ያበርታን!
በል እንግዲህ ዮሲ ሞትን አንጠይቅም
ነፍስህን ይማረው መድኃኔዓለም
ዉሉደ ብርሃን አይዞሽ አታልቅሺ
ልጅሽ አልሞተም ነጭ ልብስ ልበሺ
ቤተሰቡም ተጽናኑ ሥላሴ ጠርተውት ነው
ዮሴፍ አልሞተም ከአብረሃም እቅፍ ነው
የአብርሃሙ ሥላሴ ብሎ እንደዘመረ
አለምን በመተው ከቅዱሳን ጋር አደረ
እንግዲህ ተጽናኑ እንጽናና አብረን
እኛ ወደ እርሱ ነን ይህን ቃል አስበን
መጽናናቱን ይስጣችሁ እዚህ የታደማችሁ
የሀዘን ዳርቻ ፈጣሪ ያድርግላችሁ
አሜን!
ከመ/ት ትዕግስት በወንድማችን ዮሴፍ እረፍት ሥርዓተ ቀብር በደብራችን አውደ ምህረት ያቀረበችው ግጥም ፦
እህታችን ትዕግስት፦ የህይወት ቃል ያሰማልን!
1 199
+1
#የሐዘን መግለጫ
"ያገለገለ ሰው ሲሞት ቸል አትበል።"
📖ሲራክ 38-16
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው ወንድማችን ዮሴፍ ያማ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሰኔ 13/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል።
በወንድማችን እረፍተ ስጋ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመግለጽ እንወዳለን ለቤተሰቦቹ መጽናናትን እንመኛለን!!!
"ትንሳኤና ህይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ህያዉ ይሆናል።"
ዮሐንስ ወንጌል 11÷25
ለቤተሰቦቿ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለውሉደ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት አባላት በሙሉ እግዚአብሔር አምላክ መፅናናትን ያድለን የወንድማችንን ነፍስ እግዚአብሔር አምላክ በአብርሃም በይስሃቅ በያዕቆብ እቅፍ ያቆይልን
ምን እንበል እርሱ የወደደውን ይወስዳል በቅንነት ያገለገለቻቸው ቅድስት ሥላሴ ነፍስህን ይቀበሏት ።
ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
1 199
+1
የሐዘን መግለጫ
🏥🏥🏥🏥🏥🏥
"ያገለገለ ሰው ሲምት ቸል አትበል።"
📖ሲራክ 38-16
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው ወንድማችን ዮሴፍ ያማ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሰኔ 13/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል።
💒💒💒💒💒💒💒💒
በወንድማችን እረፍተ ስጋ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመግለጽ እንወዳለን
ለቤተሰቦቹ መጽናናትን እንመኛለን!!!
ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
1 199
Repost from የእንጦጦ መ/ስ/ቅ/ሥላሴ ቤ/ክ. ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ
የሐዘን መግለጫ
🏥🏥🏥🏥🏥🏥
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው ወንድማችን
ዮሴፍ ያማ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሰኔ 13/2018ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል።
💒💒💒💒💒💒💒💒
በወንድማችን እረፍተ ስራ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመግለጽ እንወዳለን
ለቤተሰቦቹ መጽናናትን እንመኛለን!!!
ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
1 199
Repost from የእንጦጦ መ/ስ/ቅ/ሥላሴ ቤ/ክ. ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ
የሐዘን መግለጫ
🏥🏥🏥🏥🏥🏥
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው ወንድማችን
ዮሴፍ ያማ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሰኔ 13/2018ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል።
💒💒💒💒💒💒💒💒
በወንድማችን እረፍተ ስራ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመግለጽ እንወዳለን
ለቤተሰቦቹ መጽናናትን እንመኛለን!!!
1 199
+++ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል +++
ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት ሁሉ አለቃ ወይም "ሊቀ መላእክት" ተብሎ ይጠራል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዳንኤል መጽሐፍ፣ በይሁዳ መልእክትና በዮሐንስ ራእይ ላይ ስሙ ተጠቅሶ እናገኘዋለን። በተለይም በሰማይ ሰልፍ በሆነ ጊዜ ሳጥናኤልን ድል አድርጎ የጣለ የሰራዊት አለቃ እንደሆነ ይታወቃል።
አማላጅና ጠባቂ
ምእመናን ቅዱስ ሚካኤልን የሚወዱት በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፦
• ፈጣን ረዳትነት፦ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምህረትና ለበረከት የሚላክ፣ አማላጅ መልአክ እንደሆነ ይታመናል።
• ጠባቂ መላእክ፦ የእስራኤል ዘስጋ (የጥንቶቹ አይሁድ) እና የእስራኤል ዘነፍስ (ክርስቲያኖች) ጠባቂ ተደርጎ ይወሰዳል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ያለዉ ክብር
በኢትዮጵያ በየወሩ በ 12 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ይታሰባል። በተለይም በዓመት ሁለት ታላላቅ በዓላት አሉት፦
• ህዳር 12፦ ሳጥናኤል በትዕቢት በወደቀ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ የተሾመበትና "በሰማይ ሰልፍ የሆነበት" ቀን ተብሎ ይከበራል።
• ሰኔ 12፦ ቅዱስ ሚካኤል ባህራንን ከሞት ያዳነበትና ለሰው ልጆች ምህረትን የሚያሰጥበት ታላቅ በዓል ነው።
በስዕለ አድኖው ላይ የሚታዩ ምልክቶች
በአብዛኛው የቅዱስ ሚካኤል ስዕል ላይ የሚከተሉትን ምልክቶች እናያለን፦
• ሰይፍ፦ የድል አድራጊነቱና ክፉዎችን የመቅጣቱ ምልክት።
• ሚዛን፦ የሰዎችን ስራ የሚመዝን መልአክ መሆኑን ለማሳየት።
• ዲያብሎስ (ዘንዶ)፦ በእግሩ ስር ተረግጦ ይታያል፣ ይህም በክፋት ላይ ያለውን ድል ያሳያል።
የምሕረትና የድል መልአክ
ቅዱስ ሚካኤል "መጋቤ ሐዲስ" እና የሰው ልጆች ሁሉ ጠባቂ ተደርጎ ይታመናል። መጽሐፍ ቅዱስ "ከመላእክት አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ" (ዳን 10፡13) በማለት የእርሱን ረዳትነት ይመሰክራል።
በድርሳነ ሚካኤል የሚጠቀሱ ታዋቂ ተአምራት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን "ድርሳነ ሚካኤል" መጽሐፍ በየወሩ የሚነበቡ የቅዱስ ሚካኤልን ተአምራት ይዟል። ጥቂቶቹ እነሆ፦
• ባህራንና የታሸገው ደብዳቤ፦ አንድ ሀብታም ሰው ድሃውን ባህራንን እንዲገደል ደብዳቤ ጽፎ ቢልከውም፣ ቅዱስ ሚካኤል ግን ደብዳቤውን በመለወጥ ባህራን የሀብታሙን ልጅ እንዲያገባና የሀብቱ ወራሽ እንዲሆን አድርጎታል።
• አፎምያ፦ ሰይጣን በቅዱስ ሚካኤል አምሳል ተገልጦ አፎምያን ሊያስታት ሲሞክር፣ ቅዱስ ሚካኤል ደርሶ እንዳዳናትና ሰይጣንንም እንዳሳፈረው ይነገራል።
• ዱራታኦስና ቴዎብስታ፦ እነዚህ ደግ ሰዎች ለቅዱስ ሚካኤል ዝክር ሲሉ ያላቸውን ሁሉ ሰጥተው በነበረበት ወቅት፣ መልአኩ በሰው አምሳል መጥቶ ቤታቸውን በበረከት እንደሞላው ይተርካል።
ለምን በ12 ቁጥር ይከበራል?
በቤተክርስቲያን ትውፊት መሠረት ቅዱስ ሚካኤል በወደቀው በሳጥናኤል ምትክ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው በ12ኛው ሰዓት (በእለተ እሁድ) ስለሆነ፣ በየወሩ በ12ኛው ቀን ይታሰባል።
በምልጃው የሚታመኑ ነጥቦች
ምእመናን ወደ ቅዱስ ሚካኤል ሲጸልዩ የሚከተሉትን ተስፋዎች ያደርጋሉ፦
• ከክፉ መናፍስት ጥቃት እንዲጠብቃቸው።
• በሞት ጊዜ ነፍስን ተረክቦ ወደ ገነት እንዲያሳርግ።
• በምድር ላይ በረከትንና ረድኤትን እንዲያሰጥ።
ለማጠቃለል፦ ቅዱስ ሚካኤል ለሰው ልጆች የሚራራ፣ በፍርድ ቀን የሚቆም እና በእግዚአብሔር ፊት ስለ ሰው ልጆች ምሕረትን የሚለምን ታላቅ መልአክ ነው።
ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://t.me/weludebirhane
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
1 199
📖 ✨ መንፈሳዊ የክረምት ትምህርት ምዝገባ ✨ 📖
በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ
በውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ለወጣቶች እና ለሁሉም ምእመናን
መንፈሳዊ ዕውቀትን ለማጠናከር የተዘጋጀ
የክረምት ትምህርት መርሃ ግብር!
🕊 የሚሰጡ ትምህርቶች
• ትምህርተ ሃይማኖት
• የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
• የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
• ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር እና ሕይወት
• ልሳነ ግእዝ
📍 የምዝገባ ቦታ
• በትምህርት እና ሐዋርያዊ ተልእኮ አገልግሎት ክፍል
• በሰንበት ትምህርት ቤቱ ቤተ መጽሐፍት
⏰ የትምህርት ሰዓት
ዘውትር ከሰኞ እስከ አርብ
ከምሽቱ 11፡30 – 1፡30
በተጨማሪ ከ 4ኛ - 8 ኛ ክፍል ላሉ የዓለማዊ ትምህርት ተማሪዎች አማጠናከርያ ትምህርት እንሰጣለን
📞 ደውለው ይመዝገቡ
0923 108 992
0943 318 747
“ልጆቻችሁን በጌታ ትምህርትና ተግሣጽ አሳድጉአቸው”
(ኤፌሶን 6፥4)
https://t.me/weludebirhane
1 199
🔔🔔🔔የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ🔔🔔🔔
ለዉሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ
የሥራ አመራር ጉባኤ ፣ ለስራ አስፈጻሚ እጩ አባላት የሚሆኑ አስመራጭ ኮሚቴ ለመምረጥ እና የወደፊት የሰ/ት/ቤት ጉዞን ለመገምገም በ07 10 2018 ዓ.ም ከ8 ሰዓት ጀምሮ ልዩ ጉባኤ ተዘጋጅቷል በእለቱ ተገኝተው ግዴታዎን እንዲወጡ በአክብሮት ተጋብዘዋል ።
ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://t.me/weludebirhane
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
1 199
+3
የእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የ2018 ዓ.ም የ2ኛ ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ የናሙና ምዘና የ4ኛ፣8ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን በትላንትናው ዕለት ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም አስፈትኗል።
በማጠቃለያ ዋና ምዘና በሐምሌ ወር 2018 ዓ.ም እንደሚኖራቸው ይታወቃል ለዚህም አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ከወዲሁ እየተደረገ ይገኛል።
ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://t.me/weludebirhane
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
1 199
ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም)
❖ ይህ ጾም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ አጽዋማት ውስጥ አንዱ ሲሆን ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችንን ምሣሌ አድርገው የጾሙት ጾም ነው።
❖ የሰኔ ጾም ይህ ጾም የሐዋርያት ጾም በመባል ይታወቃል ስለ ምን የሐዋርያት ጾም ተባለ ቢሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት ጾም ስለሆነ ነው።
የሰኔ ጾም የሚጾምበት ጊዜያት
❖ የሰኔ ጾም ቢያንስ 15 ቢበዛ 45 ቀናት ያህል ይጾማል
❖ የሰኔ ጾምን እስከ 9 ሰአት እንድንጾም ቤተክርስቲያን አውጃለች ።
❖ ጾሙ የሚገባበት ቀን በየዓመቱ የተለያየ ቢሆንም የጾሙ ማብቂያ ዕለት ግን ሐምሌ 5 ድረስ ነው ።
❖ ቅዱሳን ሐዋርያት የአምላካቸውን የመምህራቸውን አርአያ ተከትለው እርሱ ወደ ማዳን ሥራው ማለትም ህሙማነ ሥጋን በተዓምራት ሕሙማነ ነፍስን
በትምህርት ከማዳን አስቀድሞ የስራውን መጀመሪያ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ 40 ቀን 40 ሌሊት እንደ ጾመና እንደጸለየ ሁሉ ቅዱሳን ሐዋርያትም አብነቱን ተከትለው ጾመዋል፡፡
❖ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ዓለምን ዕጣ ተጣጥለው (ተከፈፍለው) ዞረው ከማስተማራቸው አስቀድመው የሥራቸው መጀመሪያ ጾምን አድርገዋል፡፡
❖ ሐዋርያትም ይህንን ጾም እንደሚጾሙ ጌታችን አስቀድሞ የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው በጠየቁት ጊዜ ተናግሮ ነበር፡፡
‹‹ እኛና ፈሪሳውያን ብዙ ጊዜ የምንጦመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለምንድን ነው? አሉት
ኢየሱስም እንዲህ አላቸው
ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወስድበት ወራት ይመጣል በዚያን ጊዜም ይጦማሉ››
ማቴ 9፥15-16
❖ እኛም ይህን ጾም የምንጾመው የሐዋርያትን በረከት ለመላበስ፣ እነርሱ ድል ያደረጉትን ዓለም እንድናሸንፈው አምላካችንን ለመማጸን በመሆኑ ይህንን ‹‹መሣሪያ›› አንጣለው ጾሙም ለመላው ክርስቲያን የተሰጠ ነው፤ አንድ አንዶች እንደሚሉት የቀሳውስት ብቻ አይደለም ለቄስና ለምዕመናን ተብሎ በክህነት ደረጃ የተለየ ጾምም የለም፡፡
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን በሰላም ያስፈፅመን አሜን በእውነት
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያበመልጣል"
ምሳ 1፥33
1 199
+++ በዓለ ኀምሳ / ጰራቅሊጦስ /+++
በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።
በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር… ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ።
ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ፡- እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እኛም እያንዳንዳችን የተወለድንበትን የገዛ ቋንቋችንን እንዴት እንሰማለን? …የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን። ሁሉም ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው፡- እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ። ሌሎች ግን እያፌዙባቸው፡- ጉሽ የወይን ጠጅ ጠግበዋል አሉ።
ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው፡- አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ።ለእናንተ እንደ መሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም፥ ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና፤
ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው።
እግዚአብሔር ይላል፡- በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ።
…. የእስራኤል ሰዎች ሆይ… ስለዚህ በእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ ብሎና (ክርስቶስ) የመንፈስ ቅዱስን የተስፋ ቃል ከአብ ተቀብሎ ይህን እናንተ አሁን የምታዩትንና የምትሰሙትን አፈሰሰው።…እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን እግዚአብሔር ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ። ይህንም በሰሙ ጊዜ ልባቸው ተነካ፥ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት፡- ወንድሞች ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉአቸው።
ጴጥሮስም። ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።….ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ ( የሐዋ 2 ) ፡፡
+ ማብራሪያ
በዓለ ኀምሳ በብሉይ ኪዳን የመከር በዓል በመባል የሚከበር በዓል ነው ( ዘጸአት 23÷16፤34÷22 ) ፡፡ ኀምሳው ቀን የተቆጠረው ከፋሲካ ጀምሮ ነው፡፡
በአዲስ ኪዳን ቃል እንደ ተገባለቸው በሐዋርያት ላይ መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ቀን ነው፡፡ በዓለ ኀምሳ ከዘጠኙ ዐበይት የጌታ በዓላት አንዱ ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ ማለት አጽናኝ ማለት ነው፡፡ይህ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳለው፡- መንፈስ ቅዱስ ባይወርድላት ኑሮ የቤተ ክርስቲያን ሕልውና ኮስምኖ ቀጭጮ ይቀር ነበር፤ ስለዚህ በሚገባ አነጋገር ይህች ዕለት የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን ትባላለች ይላል፡፡ ብዙ ሊቃውንት ይህችን ዕለት የበዓላት ሁሉ እመቤት ይሏታል፡፡ ( የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ በአቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ 125 )
ጰንጠቆስጤ በግሪክ ቋንቋ ሃምሳኛ ማለት ነው ( መዝገበ ቃላት ገጽ 251 ) ፡፡
ኃይል እስክትለብሱ ከኢየሩሳሌም አትውጡ የተባሉት መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ ወረደላቸው፡፡ ሰው ያለ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ሥራ መሥራት አይችልም ፡፡ መጽናትም አይችልም፡፡ መንፈስ ቅዱስን ላክልኝ ለማለት መስፈርት አያስፈልግም፡፡ እኔ ኃጢአተኛው እንዴት መንፈስ ቅዱስን ላክልኝ? እላለሁ ማለት አይጠበቅብንም፡፡ እንዲያውም የሚባለው ቅዱስ መንፈስን ከኔ አታርቅ ነው፡፡ ሥጋችሁ… የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? (ቆሮ 6÷19፡20) ተብለናል፡፡ ለሚለምኑት አብዝቶ መንፈስ ቅዱስን እንደሚሰጣቸው ተነግሯል (ሉቃ 11፥13) ፡፡
እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ለኛም ቅዱስ መንፈሱን ይላክልን ፡፡
ለአብ፣ለወልድ፣ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን!
ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://t.me/weludebirhane
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
