ch
Feedback
ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

前往频道在 Telegram

🌷ይህ ቻናል የተከፈተው ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን ዋና አላማውም ምዕመናን በንስሐ ህይወት ተመላልሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት እንድወርሱ የሚያስችል ትምህርት መስጠት ነው፡፡ 🌷💚የቅዱሳን ገድላት 🌷💛ስንክሳር 🌷♥ ቅዱሳን ስዕላት መንፈሳዊ ትምህርቶችና ጽሑፎች 🎤 ስብከቶች ............ይቀርቡበታል፡፡🌎

显示更多
2 415
订阅者
-124 小时
+97
+3030

数据加载中...

吸引订阅者
八月 '26
八月 '26
+84
在0个频道中
七月 '26
+80
在1个频道中
Get PRO
六月 '26
+53
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+36
在1个频道中
Get PRO
四月 '26
+49
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+43
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+42
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+37
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+46
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+59
在1个频道中
Get PRO
十月 '25
+37
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+25
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+53
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+49
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+34
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+58
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+59
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+69
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+62
在1个频道中
Get PRO
一月 '25
+85
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+75
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+56
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+49
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+32
在1个频道中
Get PRO
八月 '24
+75
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+58
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+53
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+52
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+77
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+86
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+38
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+41
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+57
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+54
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+30
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+46
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+58
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+43
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+79
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+31
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+53
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+77
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+94
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+96
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+79
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+78
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+112
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+111
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+92
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+88
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+69
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+109
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+119
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+44
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+60
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+35
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+52
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+52
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+31
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+37
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+69
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+57
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+75
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+125
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+77
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+91
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+78
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+672
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
26 八月+1
25 八月+2
24 八月+6
23 八月+3
22 八月+3
21 八月+2
20 八月+2
19 八月+3
18 八月+2
17 八月+6
16 八月+3
15 八月+6
14 八月+3
13 八月+3
12 八月+4
11 八月+5
10 八月+6
09 八月+4
08 八月+5
07 八月+4
06 八月0
05 八月0
04 八月+1
03 八月+6
02 八月0
01 八月+4
频道帖子
"…በዚህ ዓለም 64 ዓመት ኑራ ጥር 21 ቀን ያረፈችው የእመቤታችን የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ… "…ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው። ቅዱስ ዮ
+2
"…በዚህ ዓለም 64 ዓመት ኑራ ጥር 21 ቀን ያረፈችው የእመቤታችን የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ… "…ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው። ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ 2ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል። በ3ኛ ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች። ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት። ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከኀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ። እመቤታችንም አይዞህ አትዘን እሊያ ትንሣኤዬን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ? አላቸው። አግኝተን ቀበርናት አሉት። ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተዉ ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። ቅዱስ ጴጥሮስም መልሶ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት። ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብየ እንጅ እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው። የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው። ለበረከትም ተካፍለውታል። "…በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን ዓይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ16ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች። ወስብሐት ለእግዚአብሔር @mahiberekidusan

2
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_ዘለዓለም_ሥላሴ_አሜን። #እንኳን_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_ጾመ_ፍልሰታ የፍቺ በዓል ና ለእመቤታችን የትንሳኤና የዕርገት በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ! በአጽናፈ  ዓለም የምትኖሩ/የምትገኙ ውድ  የክርስትና እምነት ተከታዮች የተዋህዶ ልጆች ክርስቲያናዊ ሰላምታችን በቅዱስ እግዚአብሔር ስም ይድረሳችሁ፡፡ #የእመቤታችን_ትንሣኤና_ዕርገት_ ነሐሴ 16 ቀን የእመቤታችን ድንግል ማርያም ሥጋዋ ያረገበት ዕለት ነው። #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሳ_አራት ዓመት ነው፡፡ እነዚህ ዓመታት ሲተነተኑ ሦስት ዓመት በወላጆቿ ሐናና ኢያቄም ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ፣ ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አሥራ አምስት ዓመት ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር ነው፡፡ እመቤታችን እመ አምላክ በስዕለት የተወለደች ፣ በጸጋ የተሞላች፣ ባለሟልነትን የተጎናጸፈች፣አምላክን በአጭር ቁመት ፣በጠባብ ደረት የወሰነች፣የመለኮቱ እሳትነት ስጋዋን ሳያቃጥላት አምላክ ፈጣሪዋን ጸንሳ የወለደች ፣ በግብፅ በርሃ በስደት የተንከራተተች፣ በእውነቱ የህይወትን ምግብ አዝላ ስለእኛ የተራበች ፣የተጠማች፣ ከመዓር ከስኳር የሚጥም ጡቶቿን ያጠባችው ልጇ በቀራኒዮ ኮረብታ ተሰቅሎ ሲሞት መሪር እንባን ያለቀሰች፣ ለቅዱሳን ስደትን ለመባረክ ምሳሌ በመሆን የተጓዘች የተንገላታች ... ድንቅ ዘለዓለማዊ እናት ነች። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በቅዳሜ አርጋኖን ሶስቱ ያልተከፈቱ ደጆች ይልና ። ያብራራል ። አንድም በድንግልና መጽነሷን፦ ድንግልናዋን ሳይለውጠው እግዚአብሔር ወልድ በግብረ መንፈስ ቅዱስ የመጸነሱ፤ በሁለተኛ ደረጃ ክርስቶስን በምትወልድበት ጊዜ የሴቶች ልማድ ሳያገኛት በጥበበ እግዚአብሔር መውለዷ፤ በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ ከወለደችው በኋላ ማህተመ ድንግልናዋ አልተፈታም። እመቤታችን ዘላለማዊ ድንግል ናት። የስጋ ብቻ ያይደለ የሀሳብም ድንግል ናት። አጠር ባለ አገላለጽ አምላክን ከመውለዷ በፊት፣ አምላክን በምትወልድበት ጊዜ እና አምላክን ከወለደች በኋላ ፍጹም ዘላለማዊ ድንግል መሆኗን ሊቁ ያስረዳል ።  እመቤታችን ጥር 21 ቀን በ50 ዓ.ም ከዚህ አለም ድካም አርፋ ወደ ልጇ ተጠርታ ሄዳለች። ወላድተ አምላክ ባረፈችበት ወቅት ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሔዱ አይሁድ "ቀድሞ ልጇ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ በአርባኛውም ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ተመልሶም ይህን ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ በማስተማር ሕዝባችንን ወስደውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷም እንደ ልጇ ተነሳች እያሉ በማስተማር ሊያውኩን አይደለምን? ኑ! ተሰብስበን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ክፉ ምክር ተማከሩ፡፡ አይሁድም ከተማከሩ በኋላ ከመካከላቸውም ብርቱ ጉልበተኛ ሰው የሆነው #ታውፋንያ የተባለ ቅድስት ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ለማስቀረት ክቡር ሥጋዋ ያለበትን የአልጋ ሸንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጣ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ከዚህ የጥፋቱ ሥራው ተምሮ እመቤታችንን በመለመኑ እመቤታችን የተቆረጠች እጁን መልሳለታለች፡፡ ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የተቀደሰ ሥጋዋን ጌታችን ይወደው የነበረ ተብሎ የተነገረለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሆነውን ሁሉ ለወንድሞቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነሱም የእመቤታችን ሥጋ በክብር ለማሳረፍ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ፡፡ ከሁለተኛ ሱባኤ ቆይታቸው በኋላ በአሥራ አራተኛ ቀናቸው ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ሰጣቸው፡፡ ሐዋርያትም በዝማሬና በታላቅ ምስጋና በጌቴ ሴማኔ ቀበሯት፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት› › ተብሎ ትንቢት የተናገረውን ሲተረጉሙት ‹‹ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታሳርፈው የመቅደስህ ታቦት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ›› ብለው ያመሰጥሩታል፡፡ /መዝ. 131፥8/፡፡ የእመቤታችንን ቅድስት ሥጋዋን ሐዋርያት ሲቀብሯት በሀገረ ስብከቱ ሕንድ የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመናሰረገላ ተጭኖ ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ አገኛት። ለማረጓ ምልክት ይሆን ዘንድ ለምልክት እንዲሆነው ሰበኗን (የመግነዟን ጨርቅ) ተቀብሏት ይለያያሉ፡፡ ለወንድሞቹ ለቅዱሳን ሐዋርያት ያየውን ምስጢር/የተመለከተውን ድንቅ ተዓምር/የወላድተ አምላክን ዕርገት ነገራቸው፡፡ እመቤታችን ለበረከት የሰጠችውንም ሰበን አሳያቸውና አካፈላቸው ፤ ሐዋርያት ‹ ‹ዕርገቷን እንዴት እሱ ብቻ ተመልክቶ ለምን እኛ ይቀርብናል› › ብለው በዓመቱ ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ፡፡ ነሐሴ 16 ቀን የልባቸው መሻት ተፈጸመላቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ፣ ቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና ዲያቆን) አድርጎ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡ በንጽህና፣ በፍጹም እምነት ፣በትኅትና የያዙት በተስፋ የጠበቁት በአንድነት ወደ እግዚአብሔር ያቀረቡት ሱባኤም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገቷን ለማየት አበቃቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን መሠረት አድርጋ ከነሐሴ 1-16 ጾመ ፍልሰታ በማለት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ አድርገን እንድንጠቀምበት ሥርዐት ሠራችልን፡፡ በቅዱሳን አበው በነቢያትና በሐዋርያት በቅዱሳን ሁሉ መሠረት ላይ የታነጽን ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች በየዓመቱ ይህን ጾም በሱባኤ በማሳለፍ ከእመቤታችን ጸጋና በረከት ተሳታፊዎች እንሆናለን፤ ሆነናልም፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት ትንሳኤዋን ፣ ዕርገቷን እንደገለጸችላቸው ለእኛም ምስጢርን ፣ እውቀትን ታድለን ። ትግለጽልን ። የአመት ሰው ይበለን። መልካም በዓል ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከወላድተ አምላክ በረከት፣ረድኤት ፍቅር፣ምልጃና ጸሎት ተካፋዮች ያድርገን፡፡                      አሜን! ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን🙏🙏🙏 #ለወዳጅዎ_ዘመድ_ ፣_ለተዋህዶ_ልጆች #ሼር_ያድርጉ! 💚 @mahiberekidusan 💚 💛 @mahiberekidusan 💛 ❤️ @mahiberekidusan ❤
364
3
የሐሙስ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan
250
4
#በስመ-አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን            መንፈሳዊ  ግጥም             #ደብረ_ታቦር ከደብሮች ሁሉ ልቀሽ   እውነት ብርሃንን አጥልቀሽ ተንቀሽ የነበርሽ ተራራ አንቺ የምሥጢር ሥፍራ የመለኮት ብርሃን በር የሥሉስ ቅዱስ ምሥጢር ልቆ የታየብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!! ከአድማሳት ከፍ ከፍ ብሎ የስምሽ ተረፈ ውሉ የተዘከረው በዓለሙ ምን ይሆን ወርቅ ሰሙ? ምን አገኘሽ ያኔ ታቦር እንዲያ ተከፍቶ የብርሃንሽ በር የክብሩ ግርማ የዋጠሽ እኮ ማን ነው የረገጠሽ? ጌታሽ ነው አሉ ስሰማ ከተራራሽ አናት ማማ የብርሃን ጉንጉን ሸማ ያጎናፀፈሽ በግርማ ግሩም እኮ ነው! ከተራሮች አንቺን መርጦ ከነአባቱ ተገልጦ ደጅሽን ሳይንቅ ማክበሩ እንዴት እንዴት ይሆን ምሥጢሩ?   ይህንንም ደግሞ ዳዊት ተናግሯል አሉ በትንቢት ታቦር ወአርሞንኤም በሚል ቅኔ በስሙ ተደሰቱ ያኔ እያለ ዘመረ በክብር የዚህችን ተራራ ምሥጢር ያ ልበ አምላክ ዳዊት የተናገረው ትንቢት ለካ ይህ ኖሯል ግቡ ደጅሽ በብርሃን ማበቡ ኧረግ! አንቺስ ታድለሻል የማይቻለውን ችለሻል እሳተ መለኮትን ይዘሻል ለመሆኑ እንዴት ቻልሽው ታቦር ያን እውነተኛ ፍቅር? ከመንበሩ የሳበው ንጉሥ በብርሃን ሠረገላው ሲፈስ መሠረትሽ ሳይናጋ ባለበት ቆሞ የረጋ ምን ይሆን ምሥጢሩ የፅናትሽ በፊቱ ቆመሽ መታየትሽ? ልብሱ ነጭ ሆኖ በረድ አብም ከሰማይ ሲወርድ ዙሪያው በክብር ደመና ተመልቶ በብርሃን ፋና ሙሴ ከመቃብሩ ተጠርቶ ኤልያስ ከብሄረ ሕያዋን መጥቶ     በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ሲወያዩ ላስተዋለው ምን ይመስል ይሆን ገጹ? የብርሃን መለኮት መገለጹ ደግሞ የሐዋርያቱ የእነዚያ የሦስቱ ሲጋልቡ ርደው እንደ ቄጤማ ወርደው ከሰሩ የተነጠፉቱ ምንድን ይሆን ምክንያቱ? ጴጥሮሰማ ተሽብሮ ናላው በድንጋጤ ዞሮ ለእያንዳንዳችሁ በጋራ ሦስት ዳሶችን እንስራ ብሎ በዚያች የብርሃን እልፍኝ የዘለዓለም ደስታን ሊያገኝ አስቦ በቅጽበት መመኘቱ ገርሞትም አይደል ክስተቱ የብርሃን ፀዳል ድምቀቱ? እኮ እንደምን አይገርመው ሙሴና ኤልያስ ቆመው ክብሩን ሲያውጁ እያዩ ማነው የሙሴን አምላክ ሙሴ ባዩ? ሲል ሙሴ ባሕር ከፋዩ የኤልያስንስ ክብር ጌታ አውርደውት ከሰው ተርታ ኤልያስ ባዮቹ እነማን ናቸው? ሲል ኤልያስ ገርሟቸው ይህን ሲሰሙ ሐዋርያቱ በድንጋጤ ሲመቱ ደግሞ ወርዶ አባቱ ልጄን ስሙት በማለቱ በፍርሃት ማዕበል ሲንገላቱ ይህ ሁሉ ምስጢር መታየቱ በአንቺም አይደል ታቦር መገለጹ የሦስትነት ምስጢር ጥንትስ ታሪክሽ ተዘክሮ መቼ ያልቅና ተነግሮ እንዲያው ድንቅ እንበል እንጂ ድንቅ ድንቅ! የብርሃንሽ ሰንደቅ ከአድማሳት ልቆ ሲደምቅ ክብር እንበልሽ ክብር!ክብር!   አንቺ እውነተኛ የምስጢር በር የሥሉስ ቅዱስ ነገር የተገለጸብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!! ያበራሽ ይብራ ስሙ ይግነን ዛሬም ለእኛ ብርሃን ይሁነን ገኖ ያግነን በፈቃዱ በራ ይሁንልን መንገዱ ክብሩም ከፍ ከፍ ወደ ላይ ከሰማየ ሰማያት በላይ እንዲሁም በምድር በቀላይ የአምላካችን አዶናይ ክብርሽ ዛሬም ነገ ይነገር መሆንሽ እውነተኛ የብርሃን በር የሥሉስ ቅዱስ ምስጢር የተገለጠብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!! ልዑል አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በብርሃነ መለኮቱ ዘመናችንን ፣ ህይወታችንን ያብራልን። መልካም በዓል 🙏🙏🙏 ወስበሐት ለእግዚአብሔር። @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan
415
5
የረቡዕ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekiduaan
222
6
✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን፡፡ #እንኳን_ለደብረ_ታቦር_በዓል_በሰላም_አደረሰን፡፡        ደብረ ታቦር/ቡሔ ነሐሴ 13 ቀን ጌታችን መድኃኒታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሀነ መለኮቱን የገለፀበት ዕለት ነው፡፡ በዚች ዕለት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሶስቱን ደቀ መዛሙርቱን ጴጥሮስን፣ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ተራራ ላይ ወጡ መልኩም በፊታቸው ተለወጠና ብርሃነ መለኮቱን ገለጸባቸው ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ ሉቃ 9፥28 ማቴ 17 ፥1 እነሆ ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ህያዋን ጠቅሶ አምጥቶ አሳያቸው፡፡ ጴጥሮስም ይህንን አይቶ ጌታችንን እንድህ አለው፡፡አቤቱ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር መልካም ነው ሶስት ሰቀላዎችንም እንስራ አንዱን ለአንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ አለው፡፡ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሰራ ማደሪያ የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልፅ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንድህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ     ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩት ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋግጦ ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱ ነቢያት እና ሐዋርያት ደስ አላቸው፡፡ በአጠቃላይ ይህ ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ሙሴና ኤልያስን ለሶስቱ ምስጢረ ሐዋርያት ያሳየበት እርሱም ሁለመናው ነጭ ልብስ መልኩ እንደመብረቅ ሆኖ የታየበት ዕለት ነው ፡፡ በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ይህ በዓል ከጌታችን አበይት በዓላት አንዱ እንደሆነ ታስተምራለች፡፡ ምዕመናንም በዓሉን በድምቀት ያከብሩታል፡፡ ዳቦ በመጋገር ምሳሌውም እረኞች በተራራው ላይ ብርሀኑን እያዩ በወጡበት አልተመለሱም ነበረና ቤተሰቦቻቸው ዳቦ ይዘው የመሄዳቸው ምሳሌ ነው ጅራፉ የነጎድጓድ ችቦ የሚበራው ወይም ደመራው የብርሃነ መለኮቱ ምሳሌ ነው፡፡ #እናት_ቤተ ክርስቲያን ሁሉንም በምሳሌ ሰንዳ አስቀምጣለች፡፡ ለአባቶቻችን ምስጢሩን የገለጸ ለእኛም ይግለጽል፡፡ ስለ ሁሉም ነገር የቸርነቱን ስራ ይስራልን፡፡ ከበዓሉ በረከት ከቅዱሳን ምልጃና ጸሎት ከመላዕክት ጠባቂነት ከቅድስት ድንግል ማርያም እናትነትና ምልጃ ይክፈለን፡፡ "አድህነኒ እግዚኦ እስመ ኃልቀ ኄር ወውህዴ ኃይማኖት እመእጓለ እመህያው" መዝ 11፥1 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላድቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፡፡ @mahiberekidusan
535
7
የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan
384
8
+1
የእሁድ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan
415
9
👉 የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም አንድምታ 🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን #ለወዳጅዎ-ለተዋህዶ ልጆች_ሼር ያድርጉ! 💚 @mahiberekidusan💚 💛 @mahiberekidusan💛 ❤️ @mahiberekidusan❤
635
10
@mahiberekidusan
617
11
+3
የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan
1
12
የሐሙስ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan
583
13
የረቡዕ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekiduaan
566
14
👉 ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በሁለተኛው ክፍል ለክርስቶስ ምሳሌ ሁኖ የቀረበውን ወፍ ታሪክ ላጋራችሁ ስለ ከራድዮን ወፍ ምን ያክል እናውቃለን "ከራድዮን ወፍ ምንድነው ከራድዮን ነጭ ወፍ ሲሆን በሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ነው። ጠቢባን በድካም ፈልገው አድነው ይይዙታል፣ የታመመ ሰው ቢኖር ያቀርቡታል ፤ እሱም በሽተኛውን ትኩር ብሎ ያየዋል የማይድን ለሞት የቀረበ ከሆነ ፊቱን ይመለሳል፣ የሚድን ከሆነ ግን አፉን ከፍቶ ከበሽተኛው አፍ አድርጎ እስትንፋሱን ይወስዳል፣ የሰውየው ደዌ ሙሉ ለሙሉ ወደ ወፉ በእስትንፋሱ ይተላለፋል። ሰውየው ይድናል ወፉ ይታመማል። 👉ነጭ የነበረው እንደ ክሰል ይጠቁራል፣ ህመም ሲሰማው ወደ አየር ይነጠቃል ሲብስበት ወደ ባሕር ራሱን ይወረውራል። በባሕር 3 መዓልት 3 ሌሊት ቆይቶ ጽጉሩን መልጦ አዲስ ጸጉር ተክቶ ፣ድኖ፣ታድሶ፣ኃያል ሆኖ ይወጣል። ይህን ወፍ ሊቃውንቱ የክርስቶስ ምሳሌ ወይም የምስጢረ ትንሣኤ ሙታን ምሳሌ አድርገውታል ከራድዮን ወፍ ---- የክርስቶስ ምሳሌ የታመመው ሰው --- የአዳም ዘር ምሳሌ ሲሆን ወፉ በዐይኑ መመልከቱ --- በክርስቶስ ላመነ ሁሉ ድኅነት ምህረት ማግኘቱ ምሳሌ ወፉ መታመሙ---- ክርስቶስ ስለ እኛ በደል መታመሙ ምሳሌ። መጥቆሩ ---- ስለእኛ ቤዛ ከኀጢአተኛ የመቆጠሩ ምሳሌ ወፉ ወደ ላይ መውጣቱ---- ክርስቶስ ከፍ ብሎ መሰቀሉ ምሳሌ ወፉ በባህር 3ቀን 3ሌሊት መኖሩ ----ክርስቶስ በከርሰ መቃብር 3ቀን 3 ሌሊት መቆየቱ ምሳሌ 👉ከራድዮን ወፍ ታድሶ ኃያል ሆኖ ከባህር መውጣቱ -ክርስቶስ በሲዖል የነበሩ ነፍሳትን አድሶ አንጽቶ ገነት አስገብቶ፤ እርሱም ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሣው በለበሰው ሥጋ ወደ ቀደሞ መለኮታዊ ሥልጣኑ ኃይሉ መቀመጡ ምሳሌ ነው። የታደለው ወፍ የክርስቶስ ምሳሌ ሲሆን ያልታደለው የሰው ልጅ የክርስቶስ ምሳሌ መሆን ሲገባው የዲያብሎስ ምሳሌ ሆነ 🤔🤔🤔 በኦሪቱ ፈርዖን እና ሠራዊቱ በዲያብሎስ በአጋንንት ተመስለዋል ግብጽ የገሃነም ወይም የሲዖል ምሳሌ ሁናለች። @mahibrrekidusan
789
15
የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan
497
16
+3
የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan
806
17
ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan): የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan 👉 የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም አንድምታ 🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን #ለወዳጅዎ-ለተዋህዶ ልጆች_ሼር ያድርጉ! 💚 @mahiberekidusan💚 💛 @mahiberekidusan💛 ❤️ @mahiberekidusan❤ የእሁድ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan
1
18
ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan): በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን። #ጾመ_ፍልሰታ ፍልሰታ የግእዝ ቃል ነው፤ #ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገን፤ ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን የምንጾመው ታላቅ ጾም ነው። እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለኾነ፤ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት፤ ዕዝራ በመሰንቆ፥ ዳዊት በበገና እያጫወቷት፤ በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን #በ48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች። ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት (ከየሀገረ ስብከታቸው) ወደ መኖሪያ ቤቷ (የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት) ተሰባስበው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች ሥጋዋን ገንዘውና ሸፍነው ወስደው ለመቅበር ወደ #ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤  ይህንንም ማድረግ የፈለጉበት ምክንያት፤ የሐዋርያት ትምህርት (የጌታችን ከሞት መነሳትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት)ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። ‹‹የፈሩት ይነግሣል፥ የጠሉት ይወርሳል›› እንዲሉ አበው፤ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት አይቀሬ ሁኗል። አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም #ታውፋኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ የእመቤታችንን ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር፤ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ (ቆርጦ) ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነት (የአምላክ እናት መሆኗ)ና ክብርን ለመመስከር በቅቷል። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ #በዕፀ ሕይወት ሥር መቀመጡ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ሐዋርያው ዮሐንስ ስለ እመቤታችን ሥጋ ነገራቸው። ቅዱሳን ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ለዮሐንስ ተገልጾ ለኛ ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለመኑ ከጥር 21 አንስተው ለስድስት ወራት ከዐሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህም በኋላ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ፥ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን አምጥቶ ስለሰጣቸው፤ ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች። ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ  እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ.፪፥፲/። እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ሐዋርያው #ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ  ከሀገረ ስብከቱ  (ሕንድ) ወደ   ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ ከደመናው ላይ ሊወድቅም ፈለገ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን/የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው።     ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት አስረዱት። እርሱ ግን ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር›› እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን ለማሳመንና ለማሳየት ወደ መቃብሯ ወሰዱት፤ ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት የነበረውን ጨርቅ/ አሳያቸው፤ የራሱን ድርሻም አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው፤ #ዛሬም_ካህናት ከእጅ መስቀላቸው ጋር የሚይዙት እራፊ ጨርቅ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው።        ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለ፪ኛ ጊዜ ሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል። በአጠቃላይ #የእመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት መታየት፣ የሥጋዋና የነፍሷ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፍልሰት ሲባል ከዚህ የተነሣ #የነሐሴ ጾም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት መሠረት ሐዋርያት ያገኙትን በረከት ለማግኘት ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን።  የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ጸሎት አይለየን :: ኦርቶዶክሳዊ ወንድሞች እና እህቶች ሆይ ለኦርቶዶክሳዊ ወንድምዎ እህትዎ ሼር በማድረግ የቤተክርስቲያናችንን ቀጥተኛ ትምህርት ያሳውቁ ይመስክሩ ። 👇👇👇👇👇👇👇👇 👇@mahiberekidusan 👇@mahiberekidusan      @mahiberekidusan 👆👆👆👆👆👆👆👆 የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan
886
19
​​#ቅዱስ_ገብርኤል እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!! በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡ በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡ ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡ መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡ መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡ በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡ እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡ ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡ አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።🙏🙏🙏Ⓜ #ይቀጥላል 💚 @mahiberekidusan 💚 💛 @mahiberekidusan 💛 ❤️ @mahiberekidusan ❤️
934
20
"እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ 'በእውነት እየባረክኹ እባርክኻለኹ:: እያበዛኹም አበዛኻለኹ' ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ:: እንዲኹም እርሱ ከታገሠ በኋላ
"እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ 'በእውነት እየባረክኹ እባርክኻለኹ:: እያበዛኹም አበዛኻለኹ' ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ:: እንዲኹም እርሱ ከታገሠ በኋላ ተስፋውን አገኘ::"                       ዕብ. ፮:፲፫ @mahiberekidusan
920