Temari-Ethiopia
前往频道在 Telegram
A channel created for sharing 🔺study tips, 🔺short notes, 🔺tutorials, 🔺educational news, 🔺life tips and some motivational quotes ... Ads @TemariAdsBot
显示更多📈 Telegram 频道 Temari-Ethiopia 的分析概览
频道 Temari-Ethiopia (@temariethiopia) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 57 451 名订阅者,在 教育 类别中位列第 2 924,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 549 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 57 451 名订阅者。
根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 940,过去 24 小时变化为 -41,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 6.54%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.91% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 759 次浏览,首日通常累积 1 674 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“A channel created for sharing
🔺study tips,
🔺short notes,
🔺tutorials,
🔺educational news,
🔺life tips and some motivational quotes ...
Ads @TemariAdsBot”
凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
57 451
订阅者
-4124 小时
-3557 天
-1 94030 天
帖子存档
57 451
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥ ወቅት ፈተና ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ የሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል። - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም በበይነ መረብ እና በወረቀት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሒዷል።
የፈተናው አጠቃላይ ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀና ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተቀናጀ ሁኔታ መሰራት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል፡፡
ፈተናውን ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ የሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል።
ብሔራዊ ፈተናውን ለመስጠት በመሠረተ ልማት፣ ደህንነት እና ሌሎች መስኮች ተገቢው ዝግጅት መደረጉ ተመላክቷል።
ፈተናውን ለመውሰድ 563,501 ተፈታኞች (306,456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257,045 የማኅበራዊ ሳይንስ) ተፈታኞች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡ #MoE
@TwmariEthiopia
57 451
#MoH
በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለወስዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች የብቃት ምዘና ፈተና #በሐምሌ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ለመስጠት መታቀዱን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
ለዚህም በቅርብ ቀን ምዝገባ እንደሚጀመር ሚኒስቴሩ ገልጿል።
በመሆኑም በሰኔ ወር የመውጫ ፈተና የወሰዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች ለብቃት ምዘናው የሚያስፈልጉ የትምህርት ማስረጃዎችን እንድታሟሉ እና ለምዝገባው ዝግጁ እንድታደርጉ ተብሏል።
@TemariEthiopia
57 451
+1
ተማሪ ሩት አባተ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ Electrical Power and Control Engineering ትምህርት አጠቃላይ ውጤት 4.00 CGPA ውጤት በማምጣት ትምህርቷን አጠናቃለች።
በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ከወሰደቻቸው 60 ኮርሶች መካከል 47ቱን A+ እንዲሁም የቀሩትን 13 ኮርሶች A በማምጣት እጅግ የላቀ ውጤት አስመዝግባለች።የዋንጫ ተሸላሚም ሆናለች!
አጨብጭብ👏
@TemariEthiopis
57 451
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በኦንላይን የሚፈተኑ ተፈታኞች በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።
ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።ሙሉ የፈተናው ፕሮግራም ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።
@TemariEthiopia
57 451
ከ224 ሺህ በላይ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
ከ224 ሺህ በላይ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን እየወሰዱ መሆናቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡
ከነዚህ ተፈታኞች መካከል ግማሽ ያህሎቹ ፈተናውን በድጋሚ እየወሰዱ (Re-sitters) መሆናቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡
የመውጫ ፈተናው በ88 ማዕከላት እና በ287 የፈተና አይነቶች እየተሰጠ እንደሚገኝ ገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የግል እና የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች፣ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች እና የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች ፈተናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ዛሬ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡
@tikvahuniversity
57 451
#ቅሬታ #Pharmacy #Exit
ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡
"የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና አስቀድሞ ተሰርቋል" ያሉት ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል።
ለፈተናው ዝግጅት ሲያደርጉ ቢቆዩም፣ ኃላፊነት በማይሰማቸው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጨቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሷቸው ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ ገልፀዋል።
ይህ መሆኑም በከፍተኛ ጥረትና በራሳቸው ልፋት የተፈተኑ ተማሪዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ የጎዳና ፍትሃዊነትን የጎደለው ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል።
ጉዳዩ በትምህርት ሚኒስቴር፣ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማኅበር በኩል በአስቸኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደረግና ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው ተፈታኞቹ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከተፈታኝ ተማሪዎች የቀረበውን ይህንን ቅሬታ መነሻ በማድረግ፣ በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። ተጨማሪ ማብራሪያ እንዳገኘን የምናደርሳችሁ ይሆናል።
@TemariEthiopia
57 451
ነፃ የትምህርት ዕድሉ ሊያበቃ ነው!
የሞሮኮ መንግስት ለ50 ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል መስጠቱ ይታወቃል።በመሆኑም ማመልከቻው ዛሬ ሰኔ 8 ይዘጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ከመዘጋቱ በፊት ለማመልከት እዚህ ላይ ተመዝገቡ👇
http://www.marccalumni.ma
ለሁሉም ተማሪዎች አድርሷቸው! መልካም ዕድል ይሁንላችሁ!
@TemariEthiopia
57 451
#ጥቆማ
የሞሮኮ መንግሥት በ2026/27 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን ለሚያሟሉ 50 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል።
በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች ለዚሁ ዓላማ ተብሎ በተከፈተው ድረ-ገፅ www.marccalumni.ma በማመልከት የትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር በቀን 26/09/2018 ዓ.ም ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ገልጿል። ለሁሉም ተማሪዎች ላኩላቸው!
ለማመልከት 👇
www.marccalumni.ma
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኞ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
@TemariEthiopia
57 451
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን አሳውቋል፦
✅ 6ኛ ክፍል ፈተናው ከ ሰኔ 8 እስከ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም ባሉት ሶስት ቀናት ውስጥ የሚሰጥ ሲሆን፤ በአጠቃላይ 84,882 ተማሪዎች በ199 ጣቢያዎች ይፈተናሉ።
✅ 8ኛ ክፍል ፈተናው ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም (በሁለት ቀናት) የሚሰጥ ሲሆን፤ በአጠቃላይ 86,808 ተማሪዎች በ201 ጣቢያዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
ወላጆች ልጆቻችሁን ከወዲሁ እንድታዘጋጁ እናሳስባለን!
@TemariEthiopia
57 451
#Ads
ሰው መጋበዝ ሳይጠበቅባቹ ታስክ በመስራት እስከ 10$ ሰሩ🥰
Withdrew...... 3$ ጀምሮ ነው
https://timebucks.com/?refID=228182125
አሰራር.... @MoneyPremiumTG
57 451
የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጨምር) በኦንላይን እየተሰጠ ነው።
ፈተናውን እየወሰዱ ያሉት ለመጀመሪያ ጊዜ እና በድጋሜ የሚፈተኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግሥት እና የግል ተፈታኞች ናቸው።
ተፈታኞች ስለፈተናው አጠቃላይ ገለጻ ዛሬ ጠዋት የተሰጣቸው ሲሆን፤ በዛሬው የመጀመሪያ ቀን የፈተና ውሎ በጠዋት እና ከሰዓት መርሐግብር (ከ5፡00-7፡00 እና ከ8፡30-11፡00) የ62 ትምህርት አይነት ፈተናዎች እየተሰጡ ነው።
የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
@TemariEthiopia
57 451
#Ads
5$ ተቀበልኩ
❗️❗️❗️❗️❗️
🆕l በነፃ ነው ፍጠኑ
🎰🎲🌀🎉🎡🧩
📌 Join their official channel
to get additional lucky spin.
📇 Per Valid Invitation 1 Free Spin
💵 Minimum Withdrawal 1 USDT
Payment 😄 ✅
👇👇
https://t.me/earncraft_bot/app?startapp=NDcwNDM2NTkyXzE%3D
ደሞ Giveaway አዘጋጅተዋል
ቻናል. . .@MoneyPremiumTG ☑
57 451
በብልሃት አጥኑ፣ ውጤታችሁን አሳድጉ!
🧠📈
ጉልበት ሳይሆን ብልሃት ነው ውጤት የሚያመጣው። @kelem_academy_bot ብልሃተኛ ተማሪዎች
የሚጠቀሙበት ቦት ነው።
📘 ማጠቃለያዎች፦ ግልጽና ቀጥተኛ።
🎥 ቪዲዮዎች፦ ጊዜ የማይወስዱ።
✍ ልምምዶች፦ ጥንካሬን የሚጨምሩ።
🚨 ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያላችሁ፤ በተለይ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ9-12 ያለውን ትምህርት በአንድ ላይ
አዘጋጅተንላችኋል።
አሁኑኑ "Start" በሉና ተቀላቀሉ! 👉 @kelem_academy_bot
በ @kelem_academy የተዘጋጀ57 451
የመንግሥት እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና #በድጋሚ ተፈታኝ የሆናችሁ የፈተና መግቢያ ትኬታችሁን https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ በመግባት አውርዳችሁ ፕሪንት ማለት ይኖርባችኋል። ከላይ በምስል የተያያዘውን ቅደም ተከተል በመጠበቅ ማውረድ ትችላላችሁ።
@TemariEthiopia
57 451
ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርጉትን ጉዞ ዛሬ ይጀምሩ!
✈🎓
ህልማችሁን ለማሳካት የብሔራዊ ፈተና ውጤታችሁ ወሳኝ ነው። ለዚህ ደግሞ @kelem_academy_bot
አስተማማኝ ጓደኛችሁ ነው።
📘 የጥናት ማስታወሻዎች
🎥 የቪዲዮ ማብራሪያዎች
✍ የልምምድ ጥያቄዎች
‼️ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያላችሁ ተማሪዎች፤ ለብሔራዊ ፈተናው ከ9-12 ያለውን በአንድ ላይ ማግኘት ለምትፈልጉ 12ኛ
ክፍሎች።
አሁኑኑ "Start" በሉና ተቀላቀሉ! 👉 @kelem_academy_bot
በ @kelem_academy የተዘጋጀ57 451
Repost from N/a
🚀 SCHOLARSHIP NAVIGATOR 🗺 ✨
የስኮላርሺፕ መረጃዎችን ይፈልጋሉ? የውጭ ሀገር ነፃ የትምህርት ዕድል ማግኘት ይፈልጋሉ? ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ለመማር ለምታስቡ ተማሪዎች ሁሉ ሙሉ ወጪያቸው የተሸፈኑ (Fully Funded) ምርጥ ዕድሎችን ወደ እናንተ እናደርሳለን!
🌟 What We Provide:
✅ Verified Deadlines
✅ Step-by-Step Application Guides
✅ IELTS & SOP Tips
🔗 አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል የህልምዎን ትምህርት ይጀምሩ!
👉 t.me/ScholarshipNavigator
57 451
#ማሳሰቢያ
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች የትምህርት መረጃችሁን ከፋይዳ ጋር እንድታስተሳስሩ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል
🔸ለማስተሳሰር ወደ https://verify.ethernet.edu.et/ ድረ-ገጽ ግቡ!
🔸ከሚመጡት ምርጫዎች Exit Examination የሚለውን ምረጡ
🔸በመጨረሻም Start Verification የሚለውን በመጫን መረጃችሁን አስተካክሉ።
ማሳሰቢያ፡ ይህን ያላደረገ ተማሪ ፈተናውን ለመውሰድ ስለሚቸገር መረጃው ላልደረሳቸው ጓደኞቻችሁ በአስቸኳይ #Share በማድረግ አሳውቋቸው!
Join @TemariEthiopia
57 451
የ4 ዓመት ጉዞ... በአንድ ቦት!
⏳🎓
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሆይ፤ የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ማስታወሻዎቻችሁ የታሉ? የ11ኛ ክፍልስ? ብሔራዊ ፈተናው
ሁሉንም እንደሚያካትት ታውቃላችሁ። መጽሐፍ ፍለጋ አትባክኑ! በ @kelem_academy_bot
ከ9-12 ያለውን
ሁሉንም ትምህርት በአንድ ላይ አዘጋጅተንላችኋል።
📘 የ4 ዓመት ማጠቃለያ፦ ከ9-12 ያሉ ዋና ነጥቦች።
🎥 የቪዲዮ ማብራሪያዎች፦ የቆዩ ትምህርቶችን ለማስታወስ።
✍ የልምምድ ጥያቄዎች፦ ለብሔራዊ ፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ።
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተለየ ትኩረት፦ ሁሉንም በአንድ ላይ በማግኘት ጊዜያችሁን ቆጥቡ
አሁኑኑ "Start" በሉና ተቀላቀሉ! 👉 @kelem_academy_bot
በ @kelem_academy የተዘጋጀ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
