2 948
订阅者
无数据24 小时
-27 天
+430 天
数据加载中...
吸引订阅者
一月 '25
一月 '250
在0个频道中
十二月 '24
+41
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+120
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+136
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+13
在0个频道中
Get PRO
八月 '240
在0个频道中
Get PRO
七月 '240
在0个频道中
Get PRO
六月 '240
在0个频道中
Get PRO
五月 '240
在0个频道中
Get PRO
四月 '240
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+3
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+22
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+8
在0个频道中
Get PRO
十二月 '230
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+64
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+31
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+97
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+32
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+25
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+24
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+11
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+32
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+31
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+28
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+37
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+176
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+82
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+37
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+33
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+31
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+15
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+21
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+22
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+53
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+60
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+199
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+228
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+156
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+170
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+124
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+106
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+304
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+455
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+726
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+926
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 01 一月 | 0 |
频道帖子
| 2 | ኢንስቲትዩቱ የቅበላ አድማሱን በማስፋት ከዚህ ቀደም ሠልጣኝ ከሚቀበልባቸው አማራጮች በተጨማሪ በሬሚዲያል 12 ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን እንደሚቀበል ተገለጸ።
መስከረም 21/2017
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሴኔት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በመጀመሪያ
በ2017 ዓመት የሠልጣኞችን አቀባበል በተመለከተ ውይይት የተደረገ ሲሆን ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ አማራጮችን ተጠቅሞ ሠልጣኞችን በስፋት ለመቀበል እንዲሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል። በዚህም መሠረት ከዚህ ቀደም ከሚቀበልባቸው አማራጮች በተጨማሪ በሬሚዲያል 12 ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን እንደሚቀበል ተገልጿል። የሠልጣኞችን አቀባበል በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው መመሪያ መሠረት እንደሚተገበር ተገልጿል።
በመቀጠል ሴኔቱ የ2017 የሥልጠና ዓመት ካሌንደር (Academic Calender) ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።
በመጨረሻም የ2016 ዓመት ተመራቂ የነበሩ እና በተለያየ ምክንያት ሳይመረቁ የቀሩ ተመራቂዎችን ጉዳይ በተመለከተ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከሪጅስትራር እና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት የቀረበለትን ውጤት መርምሮ አጽድቋል።
ዌብሳይት http://www.ftveti.edu.et/
ፌስቡክ https://www.facebook.com/TVTI.EDU.ET
ቴሌግራም https://t.me/fdretvti | 1 965 |
| 3 | ማስታወቂያ ለተመራቂ ተማሪዎች
በመደበኛው እና በተከታታይ ስልጠና ፕሮግራም በ2014 ዓ.ም ና በ2015 ዓ.ም ከኢንስቲትዩቱ በመጀመሪያ ድግሪና በሁለተኛ ድግሪ የሚትመረቁ ተማሪዎች የምረቃ ስነስርዓቱ የሚካሄደው ነሐሴ 20/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ከዕለቱ አስቀድማቸሁ የመመረቂያ ጋወን ከየትምህርት ክፍላችሁ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
To all graduating class trainers:
All graduating trainers in regular or extension programs of academic year 2014 E.C/2022 and 2015 E.C/2023, both undergraduate and postgraduate, has to report and collect graduation gown before the graduation date on 26 August 2023 from respective departments. | 2 002 |
| 4 | የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አዲስ አርማ (logo)
FDRE Technical and Vocational Training Institute new Logo
ኢንስቲትዩታችን የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ዘርፈ-ብዙ የለውጥ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ይህንን የጀመረውን የለውጥ ምዕራፍ የሚገልጽ አዲስ የአርማ (Logo) በማዘጋጀት የቀድሞውን አርማ ቀይሯል። | 1 570 |
| 5 | 没有文字... | 1 080 |
| 6 | ጭስ አልባ ከሰልን እውን ያደረገው የፈጠራ ሥራ
ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በኢትዮጵያ በዓመት 0.21 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ የከሰል ምርት በባህላዊ መንገድ ይመረታል፡፡ የምርቱ 70 በመቶ የሚሆነን ደግሞ የሚቀርበው ለከተማ ገበያ ነው፡፡ ይህም ለደን መራቆት እና ለአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡
ጉዳቱን የተገነዘበው አቶ ከድር ጀማል መፍተሄ ያለውን ደን ሳይጨፈጨፍ ተፈጥሮ ሳይራቆት ከሰል ማምረት የሚያስችል ፈጠራ ይዞ ከወደ አዳማ ብቅ ብሏል፡፡
ከድር ከብዙ ልፋት በኋላ ወደ ውጤት የቀየረውን የፈጠራ ሥራ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባዘጋጀው 3ኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ላይ ቀርቦ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
ከድር እንደሚናገረው ወደዚህ የፈጠራ ሥራ እንዲገባ ምክንያት የሆነው በየአካባቢው የሚመለከተው የደን ጭፍጨፋ መሆኑን ነው፡፡ ‘ክረምት በመጣ ቁጥር ዛፍ ለመትከል ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ አያለሁ ነገር ግን በዘላቂነት ጭፍጨፋውን የሚያስቆም ርምጃ ሲወሰድ አልመለከትም፡፡ በመሆኑም ይህንን ሊገታ/ሊቀንስ የሚችል ሥራ መሥራት እንዳለብኝ ወሰንኩ “ ይላል፡፡
ፈጠራው ለየት የሚያደርገው የከሰል ምርቱ ከወዳደቀ የሻንኮራ አገዳ፣ ከቦቆሎ አገዳ፣ ከተሰባበረ ሸክላ እና ከማንኛውም ተረፈ ምርት መዘጋጀት የሚችል መሆኑ ነው፡፡
የሚያመርተው ጭስ አልባ የከሰል ምርትም በሰው ላይ ምንም ጉዳት እንዳያደርስ ጭስ ያለው ቁሳቁስ እንኳን ቢሆን በፈጠራ ሥራው የማስወገድ ሥራ ይሰራል፡፡ ሙሉ ለሙሉ ጭሱ ከተወገደ በኋላ ወደ ከሰልነት መቀየር የሚስችል ፈጠራ ነው ይላል የፈጠራው ባለቤት፡፡ በተጨማሪም በዚህ ሂደት የሚመረተው ከሰል በባህላዊ መንገድ ከሚመረተው ጥራቱ በእጅጉ የበለጠ በመሆኑ በጥቂት የከሰል መጠን ብዙ ነገር መሥራት የሚያስችል መሆኑን አስረግጦ ይናገራል፡፡
ከዚህ የፈጠራ ሥራ ባሻገር ሌሎችም ከአምስት ያላነሱ የፈጠራ ስራዎች መሥራቱን የሚናገረው ጀማል ሁሉንም ፈጠራ ሥራዎቹ ታዲያ ብክነት የሚያስወግዱ እና መልሶ መጠቀም ላይ ያተኮሩ መሆናቸውንም ይገልጻል፡፡
በእስካሁን ሂደት በአነስተኛ ማሽን አነስተኛ መጠን ያለው ምርት እያመረተ እንደነበርም ያስረዳል፡፡ አሁን ግን ይላል ጀማል ምስጋና ለአዳማ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ይግባና የፈጠራ ሥራዬን ተሳቢ ያደረገ ትልቅ ማሽን ሰርተውልኛል፡፡ በዚህ ማሽን በመታገዝ ከእንግዲህ እስከ 60 ቀረጢት ድረስ መጠን ያለው ጭስ አልባ ከሰል በቀን ማምረት እንደሚያስችለው ያብራራል፡፡
እስካሁን በመንግስት የተደረገለትን ድጋፍ አመሰግኖ በቀጣይ በተለይ የቦታ ድጋፍ ቢደረግለት በሥራው ይበልጥ ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ይገልጻል፡፡ ጀማል ከራሱ አልፎ ረዥም አስቦ ለሀገር የሚጠቅም ፈጠራ ይዞ መጥቷል፡፡ | 856 |
| 7 | የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የ2015 ክህሎት ውድድር አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።
ክህሎት ለተወዳዳሪነት በሚል መሪ ሀሳብ ከግንቦት 14/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው የ2015 ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ፍፃሜውን አግኝቷል።
ውድድሩ ፍፃሜውን ሲያገኝ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ በመውጣት ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች ከአንድ መቶ ሺህ እስከ 80 ሺህ ብር ድረስ የማበረታቻ ሽልማት፣ ዋንጫ፣ ሜዳሊያ እና የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስራ ሁለት ወርቅ፣ አራት ብር እና ሦስት ነሀስ በማግኘት በአጠቃላይ ውጤት አንደኛ በማግኘት የ2015 ክህሎት ውድድር አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዘጠኝ ወርቅ፣ ስአስር ብር እና ሰባት ነሀስ በማግኘት በአጠቃላይ ውጤት ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፤ አዲስ አበባ ከተማ ደግሞ ሰባት ወርቅ፣ ስምንት ብር እና ሦስት ነሀስ በማግኘት ሦስተኛ ደረጃን በማግኘት ውድድሩን አጠናቋል። | 1 029 |
| 8 | አካል ጉዳተኝነቱ ውጤታማ ከመሆን ያላገደው የፈጠራ ባለቤት
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0SM8AV2SdfjVHrcUSHWGWk9XdtH6qp7TSPvvzieEyBfaJcQPUHVKGQApSVGeCC5nDl&id=100069116383994&mibextid=Nif5oz | 1 174 |
| 9 | #Happeningnow
#አሁን
ክህሎት ለተወዳዳሪነት በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ የሚገኘው ሦስትኛው ሀገር አቀፍ
የክህሎት ውድድር በተለያዩ ሙያዎች እንደቀጠለ ነው፡፡
ክህሎት ለተወዳዳሪነት!
ግንቦት 15/2015 ዓ.ም፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር | 1 139 |
| 10 | እጃቸውን፣ ልባቸውን እና አዕምሯቸውን አስተሳስረው የሚሰሩ ሰዎች ያስፈልጉናል፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ሦስተኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተከፍቷል፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ ፈጠራ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ የእጅ ጥበብ ያላቸው፤ እጃቸውን፣ ልባቸውን፣ አዕምሯቸውን አስተሳስረው የሚሰሩ ሰዎች ያስፈልጉናል፡፡
ግብርናችን፣ ኢንዱስትሪያችንም ሆነ ኮንስትራክሽን ዘርፉ አልዘመነም፡፡ ብዙ ሴክተር በመፍጠር ሥራን ማቅለል የሚያስችል ሁኔታን መፍጠር የሚያስችል ሀገር ነው ያለን፡፡
ይህ ለማድረግ ግን ማንኛቸውን በአካባቢያችን ያሉ ፈተናዎች፣ ተግዳሮቶች እንዳያቆሙን በተባበረ፣ በተደመረና በተሳሰረ መልኩ ችግርን ብቻ በሚያወራ ሳይሆን መፍትሄ በሚያመጣ እሳቤ በመፍጠር ኢንዱስትሪያችንን እንድናዘምን አደራ ልላችሁ እፈልጋለሁ ብለዋል፡፡
እንበርታ፣ እንፍጠር፣ ፈተናንና ችግርን ለማለፍ መፍትሄ ላይ የምናተኩር እንሁን ያሉት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በዚህ መንገድ የበለፀገች ሀገር ለመፍጠር ሁላችንም በየሙያችን የምንረባረብ እንሁን ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ግንቦት 14/2015 ዓ.ም፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር | 847 |
| 11 | ፈጠራ ወደ ከፍታ በሚያስፈነጥሩ ብዙ ችግሮች የተከበበ ነው ፤ መፍትሔ ተኮር ከሆንን ወደ መልካም አጋጣሚ ልንለውጠው እንችላለን።
ክቡር ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
3ተኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር፣ “ክህሎት ለተወዳዳሪነት” በሚል መሪ ሀሳብ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አቢይ አህመድ(ዶ/ር)፣ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተከፍቷል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ሀገራችን ብዙ ችግሮች እንዳሉበባቸውና አንዱ ዘርፍ የሌላው ግብዓት ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ የተሳሰሩ ባለመሆናቸውና በሚፈለገው ጥራት ስለማይመረቱ ከውጭ እንደሚገቡ በማስታወስ የክህሎት ውድድሩ ይህንን ለማስቀረት እና ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለማግኘት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
ፈጠራ ወደ ከፍታ በሚያስፈነጥሩ ብዙ ችግሮች የተከበበ ነው ፤ መፍትሔ ተኮር ከሆንን ወደ መልካም አጋጣሚ ልንለውጠው እንችላለን።
የፋይናንስ፣ የቢሮክራሲ እና የመስሪያ ቦታ ችግርን የፈጠራ ሰዎች ከሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። ሆኖም መፍትሔ ተኮር መሆንን ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።
ውጤት ላይ ማትኮር ማለት በቀለለ ነገር አስቸጋሪ ነገርን ማለፍ መቻል ነው፤ ለዚህም የፈጠራን አስቸጋሪነት በመረዳት ፈተናዎች እንዳያቆሙን በተባበረ እና በተደመረ አቅም ኢንዱስትሪያችንን እናልማ ያሉት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ፈተና እና ችግርን ለማለፍ እንበርታ፣ እንፍጠር ፣ እንጠንክር ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተቋቋመ አንድ ዓመት ተኩል ቢሆነውም ተስፋ ሰጪ ሥራዎች ማሳየቱን እና በውድድሩ መክፈቻ ሥነ ስርዓት የፈጠራ ሥራቸውን ይዘው የቀረቡት የፈጠራ ባለሙያዎች ለችግር ያስቀመጡትን መፍትሔ በውድድር መማማሪያ እና ያለንን ብቃት ማሳያ ነው ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው
ባስተላለፉት መልዕክት የክህሎት ልማት ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ተወዳዳሪነት የሚረጋገጥበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
በክህሎት የበቁ፣ ምርትና ምርታማነትን በማረጋገጥ የአገራችን ብልፅግና ዕውን እንዲሆን የራሳቸውን አስተዋፅኦ የሚበረክቱ፣ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናዎችን በመጠቀም ለማፍራት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ ነው ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ‹‹ከሥልጠና በላይ›› በሚል መርህ የክህሎት ልማት ልህቀትን ለማረጋገጥ በሚተገብራቸው የሪፎርም ሥራዎች መካከል ገበያ መርና የመልማት ፀጋን በመጠቀም የስልጠና ማዕከላትን በዞን ማደራጀት አንዱ ስትራቴጂ መሆኑን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትሯ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን የማምረቻ ማዕከላት በማድረግ ተግባራዊ ውጤትን የሚያረጋግጡበት ሥርዓት በመዘርጋት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
የክህሎት ልማት የዕድገት ምንጭ መሆኑን በማስገንዘብ ለዘርፉ በቂ ትኩረት እንዲሰጠው ለማስቻል ብዙ ርቀትን መጓዝ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን መስራት ይጠይቃል ያሉት ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት በአገር ዓቀፍ ደረጃ የሚካሄዱ መሰል ውድድሮች የዘርፉን ገፅታ በመገንባትና ወጣቶች ዘርፉን ምርጫቸው እንዲያደርጉ በማነሳሳት ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወትም አመልክተዋል፡፡
ከኮሌጆች ጀምሮ በተካሄዱ ውድድሮች ሦስት ምዕራፎችን አልፈው በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር የበቁ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ተወዳዳሪዎችን ያካተተው 3ኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የቴክኖሎጂ ሽግግርን ዕውን ለማድረግ ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ነው ብለዋል፡፡
በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በየሁለት ዓመቱ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር ላይ ለመሳተፍና የዓለም ዓቀፉ የክህሎት ማህበረሰብ (skill society) አባል ለመሆን ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርባና ተገቢውን መስፈርት አሟልታ ምላሽ እየተጠባበቀች እንደምትገኝም ተናግረዋል፡፡
የክህሎት ልማት ዘርፍ ተጠናክሮ እንዲወጣ አደረጃጀቱን በመከለስና የነበረውን የፖሊሲ ማነቆ በመፍታት ረገድ የኢፌድሪ መንግስት ላሳየው ቁርጠኝነትም ክብርት ሚኒስትሯ ምስጋናቸውን ገልፀዋል፡፡
ግንቦት 14/2015 ዓ.ም፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፡ | 838 |
| 12 | 没有文字... | 857 |
| 13 | 没有文字... | 1 395 |
| 14 | በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2015 የትምህርት ዘመን በተቋሙ ዋና ግቢ ለመማር ያመለከታችሁና የመግቢያ ፈተና ያለፋችሁ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ጥር 23 እና 24/2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
በቅጣት ለመመዝገብ ጥር 25/2015 ዓ.ም። (ሙሉ መረጃው ከላይ ተያይዟል።) | 1 770 |
| 15 | የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ችግር የሚፈቱ፣ ህይወትን የሚቀይሩና ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ የፈጠራ ሀሳቦችን ለማበረታታት በትኩረት እንደሚሰራ ተገለፀ
ለክልል የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት ብሩህ የፈጠራ ሀሳብ ውድድርን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማስፋት የሚስችል ግንዛቤ ለማስጨበጥ የተዘጋጀውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ብሔራዊ ብሩህ የፈጠራ ሀሳብ ውድድር አዳዲስ ሀሳብ ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር የማበረታታት ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲካሄዱ የቆዩ ውድድሮችን ተሞክሮ በመቀመር ሀገር ዓቀፍ ይዘት ያለው ሰፊ ውድድር ለማዘጋጀት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
በያዝነው ዓመት ከእያንዳንዱ ወረዳና ቀበሌ የሚመረጡ እስከ 3ሺ የሚደርሱ የፈጠራ ሀሳቦችን ለማወዳደር መታቀዱን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመው በዚህ ሂደት ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በንቃት ተሳታፊ እንደሚሆኑ አመልክተዋል፡፡
የሀሳብ ፈጠራ ውድድሩ በዓለም አቀፍ አጋር ተቋማት ፋይናንስ ሲደረግ መቆየቱን የገለፁት ዶ/ር ተሻለ በቀጣይ ከሀገራችን ባንኮች ጋር በጋራ ለመስራትና ባንኮቹ ሀሳብን ፋይናንስ ማድረግ የሚያስችል ሥርዓትን እንዲዘረጉ ከመግባባት ላይ እየተደረሰ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም መሰረት ከልማት ባንክ ጋር የጋራ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ሥራ መገባቱንም ጠቁመዋል፡፡
ብሩህ የፈጠራ ሀሳብ ውድድር ዓላማው አዳዲስ ሀሳቦችን የሚያነሳሳና የሚደግፍ ሥርዓትን መዘርጋት ነው ያሉት የሥራ ዕድል ፈጠራ ሀሳቦች ማበልፀጊያ ዴስክ ሀላፊ ወ/ሮ አለምፀሀይ ደርሶልኝ ባለፉት ዓመታት ከተካሄዱት ውድድሮች የተገኙ ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ በመላ ሀገሪቱ ውድድሩን ለማስፋት የክልል የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት ድርሻ ወሳኝ በመሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን ማዘጋጀቱን አብራርተዋል፡፡ | 1 027 |
| 16 | በቴክኒክና ሙያ የሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች ጥራትን ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት የሚካሄደዉን የክህሎት ዉድድር አስመልክቶ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ክቡር ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በውይይቱ ላይ እንደገለፁት፤ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ ስልጠናዎች እና የሚደረጉ የጤክኖሎጂ ሽግግርች በአህጉር አቀፍ ደረጃ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ጥራትን ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በርከታ ቴክኖሎጂዎች እየተሰሩ ቢሆንም በህብረተሰቡ ዘንድ በበቂ መልኩ ከማስተዋወቅ አኳያ ውስንነት በመኖሩን ጠንካራ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎች በዋናነት የጥራት ችግር እና የሀብት ብክነት ስለሚስተዋልባቸዉ ይህንን በሚቀርፍ መልኩ ማከናወን ቅድሚያ ሊሰጠዉ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
በቀጣይ የሚደረገዉ የቴክኖሎጂ ዉድድር በዋናነት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚታዩ ችግሮችን ከመፍታት አንስቶ እስከ ማህበረሰብ ድረስ ያሉ ችግሮችን የሚቀርፉ መሆናቸዉን ባረጋገጠ መልኩ ይካሄዳል ብለዋል፡፡
ይህ መድረክም ዘንድሮ የሚደረገዉ የክህሎት ዉድድር አንድ ደረጃ ከፍ ባለ መልኩ ለማድረግ ተጨማሪ ሀሳቦች ለማሰባሰብ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ | 690 |
| 17 | ከግብርና ኮሌጆች አኳያ የምንሰራቸው ሥራዎች ከማሰልጠን ባለፈ ሀገራዊ የልማት ውጥኖችን የሚያሳኩ ሊሆን ይገባል፡፡
ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ባለሙያዎችን ማፍራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ የሚመክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡
ከክህሎት ልማት ሥራው አንፃር ለሥራ ገበያው ፍላጎት ምልሽ የሚሰጡ ተግባራት እየተከናወኑ ያሉ ሲሆን ከግብርና ኮሌጆች አኳያ የምንሰራቸው ሥራዎች ከማሰልጠን ባለፈ ሀገራዊ የልማት ውጥኖችን የሚያሳኩ ሊሆን ይገባል፡፡
በዚህም እንደ ሀገር ከታወጀው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አኳያ የግብርና ኮሌጆቻችን የወተት፣ የስጋና እንቁላል፣ የዓሣ እና የማር አቅርቦትን ከማሻሻል ጀምሮ የሀብት ልማቱን ከማዘመን አንፃር አርአያ የሚሆኑ ተግባራትን ማከናወን ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
የግብርናው ዘርፍን ማዘመንና በቴክኖሎጂ መደገፍ ከተቻለ ለሥራ ዕድል ፈጠራው ከፍተኛ ሚና እንዳለው የጠቆሙት ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ተቋሞቻችን በሂደት በበጀት ራሳቸውን የሚችሉበት ሥርዓት ለመዘርጋት ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የግብርና ቴክኒክና ሙያ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌታቸው ደምሴ በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ ከኮሌጆ፣ ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመቀራረብ ውጤታማ ሥራ ለመስራት ሰፊ ጥረት እየተደረገ ነው።
በተለይ ተቋማትን እንደየልማት ፀጋቸው በመክፈል ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃር ትርጉም ያለው ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በሚኒስቴሩ የግብርና ሙያ ደረጃ ምደባና ብቃት ምዘና ዴስክ ሃላፊ ዶ/ር ፍቃዱ አለማየሁ በዘርፊ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች ላይ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለፁት፤ በመንግስት የልማት የትኩረት አቅጣጫ በተለዩ መስኮችና የሥራ ገበያውን ፍላጎት በሚመልስ አግባብ ብቁና ተወዳዳሪ የግብርና ባለሙያዎችን ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።
በሂደቱም ለሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። | 698 |
| 18 | 没有文字... | 717 |
| 19 | በኢኖቬሽን የሚመራ ኢንተርፕረነርሺፕ ለማዳበር ምህዳሩን ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ማርሽ ቀያሪ የሆኑ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች እንዲሰባሰቡ፣ ተሠብስበውም እንዲበዙ ማድረግ የሚችሉ አዳዲስ ኢንተርፕረነሮችን የማበረታታት ስራ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በቅርቡም የተለያዩ የለውጥ ሐሳቦችን የሚያቀጣጥሉ አዳዲስ አሰራሮች ሊሠሩ ታቆዷል ብለዋል።
ሚኒስትሩ በንግግራቸው 17ኛውን ዓለማቀፍ የኢንተርኔት ጉባኤን አገራችን በተሳካ ሁኔታ አካሒዳ በስኬት ማጠናቀቋ ትልቅ ውጤት መሆኑን አስታውሰዋል።
በማጠቃለያ ሥነ-ሥርአቱ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሠውሐብት ልማት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የተለያዩ ሚኒስቴሮች ሚንስትሮችና ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተለያዩ ተቋማት የስራ ሐላፊዎች ተገኝተዋል። | 1 271 |
| 20 | #ዘጠነኛው_ዓለም_አቀፍ_የኢንተርፕረነርሺፕ_ሳምንት_በኢትዮጵያ ማጠቃለያ እና #ከህዳር_እስከ_ህዳር ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር ተካሔደ።
*****ህዳር 25/2015******
ለአንድ ሳምንት በተለያዩ ሥነ-ሥርአቶች ሲካሔድ የሰነበተው #ዘጠነኛው_ዓለም_አቀፍ_የኢንተርፕረነርሺፕ_ሳምንት_በኢትዮጵያ በዛሬው እለት የሚጠቃለያ ፕሮግራም እና #ከህዳር_እስከ_ህዳር ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሐግብር እየተካሔደ ይገኛል።
በሳምንቱ የተለያየ የፈጠራ ሐሳብ ባላቸው እና ከተለያዪ የህብረተሰብ ክፍል በተገኙ ስራ ፈጣሪዎች፣ በተለያዩ ቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች መካከል ውድድሮች ተካሒደል፤ ስራ ፈጣሪዎች ልምዶቻቸውን ለብዙሐኑ አካፍለዋል፤ ቴክኖሎጂዎች ቀርበው ተጎብኝተዋል፤ ስራ ፈጠራ እንደ አገር ባህል እንዲሆን ምን መሠራት እንዳለበት የሚጠቁሙ የተለያዩ ፓናሎች ሲካሔዱ ሰንብተዋል።
ክቡር አቶ #ንጉሱ_ጥላሁን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በሳምንቱ በተከናወኑ የተለያዩ ሁነቶች ኢትዮጵያ በአለም የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት አከባበር አንድ ተዋናይ መሆን ችላለች ብለዋል።
በፈጠራ ሀሳቦች፣ በቴክኖሎጂዎች የተወዳደሩ የእውቅና ሽልማት እንደሚሰጥም ተናግረዋል። ከሁሉም በላይ ስራ ፈጠራ እንደ አገር ባህል እንዲሆን እየተሠሩ ያሉ ስራዎች ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት ሳምንት እንደሆነ አንስተዋል።
ክቡር ዶ/ር #በለጠ_ሞላ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር በመክፈቻ ንግግራቸው የሚመሩት ሚኒስቴር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየተሠሩ ያሉ ስራዎችን አንስተዋል።
ሁለቱ መ/ቤቶች መግባቢያ ሰነድ ከመፈራረም አልፈው ወደ ተጨባጭ ተግባራዊ ስራ ገብተዋል ብለዋል።
#አንተርፕረነርሺፕ_የአሰራሮችንና_የትግበራ_ማነቆዎችን_አልፎ_የሚቆናጠጡት_መልህቅ_ነው ብለዋል ሚኒስትሩ። | 1 063 |
