HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
前往频道在 Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
显示更多2 279
订阅者
无数据24 小时
+57 天
+3230 天
帖子存档
ሰው ካልተሰራ ሀገር አይሰራም! ሰው እየገደልን ሕንጻ እንገነባለን || የአባታችን ድንቅ ንግግር || ሰው መሆን ይሻለናል! #ethiopia #orthodox 😭😰 https://youtu.be/56VZJlcOMWE
ይገርማል! ወደ ጅብነት የምቀየሩ ቤተሰቦች 7 አመት ከቆረበች በኋላ ነው መንፈሱ የተለያት የዘመናችን ትልቁ በሽታ ዘረኝነት #በማለዳ_ንቁ_2024 😰😭
https://youtu.be/DRiiIp0tdxA
በእውነት ያሳፍራል፣ ያሳዝናልም 😰😰
---------
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።
ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል።
ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው እንደሚገኙ ታውቋል።
@EOTCMK
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
“ጸሎትና ጾም በሌለበት ሰው ውስጥ ሰይጣን አለ ብለን ማሰብ እንችላለንን? ብሎ ይጠይቅና ሲመልስ “አዎ፣ አጋንንት ወደ ሰው ውስጥ ሲገቡ መግባታቸውን በገሀድ አያሳውቁም፣ መግባታቸው እንዳይታወቅባቸው ለማድረግ ሲሉ ራሳቸውን ይደብቃሉ እንጂ፤ ሆኖም የገቡበትን ያን ሰው ክፉውን ነገር ሁሉ በስውር ከውስጥ ያስተምሩታል፣ መልካም የሆነውን ነገርደ ግሞ ያስጠሉታል፡፡ ያ ሰው የሚፈጽመው የጠላትን ፈቃድ ሆኖ ሳለ እርሱ ግን እርሱ ራሱ እያደረገው እንደሆነ ያስባል፡፡ ጠላት ትቶህ የሚወጣውና ሌላ መመለሻ አጋጣሚ እሰኪያገኝ ድረስ ከአንተ ርቆ የሚጠባበቀው ጸሎትና ጾምን ስትታጠቅ ብቻ ነው፡፡ ጸሎትና ጾም ከተተው ግን እንደገና ተመል ሶይመጣል፡፡” (Theophan the Recluse, Thoughts for Each Day of the Year, pp. 245-246)
ስለሆነም ጾምና ጸሎት በተተውበትና በሌሉበት ሕይወት ዘንድ ኦርቶዶክሳዊነት ሽታውም አለ ማለት አይቻልም፤ የአጋንንት መሥሪያ ቤት እንጂ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ አይኖርም፡፡ “ዘመነኛ” ወይም “ሊበራል” በሚል ሽፋን ሰይጣን የሚሰብከውን “ጾም የለሽ” ክርስትና ወይም እምነት ልብ እንበል፣ እንወቅበት! ኦርቶዶክሳዊነት በባሕርዩ ትህርምታዊ ነው፡፡ “ሕዝቡንም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ።” (ማር.8፡3468)
“የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ። በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።” (ገላ.5፡24-25) ጊዜውንና ሕይወቱን በተድላና በደስታ ለማሳለፍ የሚፈልግና ራስን ስለ መካድና ራስን ስለ መግዛት የማያስብ ሰው፣ ሥጋዊ ደስታንና ምኞትን ብቻ የሚከተል ሰው ኢኦርቶዶክሳዊ ነው፣ ኢክርስቲያናዊነው፡፡ “የእግዚአብሔር መንገድ በየዕለቱ የሚሆን መስቀል ነው፡፡ ያለ ውጣ ውረድና ተጋድሎ፣ እንዲሁ ተዘልሎ የሚኖር ማንም ሰው ወደ መንግሥተ ሰማያት ሊወጣ አይችልም፡፡ እንዲህ ያለው ተዘልሎ የመቀመጥ ሕይወት መንገድም የት እንደሚያደርስ እናውቃለን፡፡ ይህም ራሱ ጌታችን ፍጻሜው ጥፋት ነው ብሎናልና፡፡”
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
«መተት ለምን እኛ ላይ ይሠራል?»
ቤተሰቦቼ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹በያዕቆብ ላይ አስማት የለም›› ይላል፡፡ ይህ አባባል በእግዚአብሔር ሰው በቅዱስ ያዕቆብ ሕይወት ውስጥ አጋንንት በአስማት፣ በመተት፣ በድግምት ጣልቃ ገብነት ፈጥሮ ውድ ሕይወቱን የማበላሸት ኃይል የለውም ለማለት ነው፡፡ /ዘኅ 23÷23/ የበለዓም አስማት በያዕቆብ ላይ ያልሠራው ያዕቆብ በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠ የተስፋ ዘር ነበር፡፡ እንዲሁም እምነቱ በፈጣሪው ላይ የጸና ነበር፡፡ የያዕቆብን መመረጥ እና እምነት ቅዱስ ጳውሎስ በሁለቱ መልእክቶቹ ላይ በሰፊው ገልጾታል፡፡ /ሮሜ 9÷10-16‚ ዕብ 11÷9-21/
ወዳጆቼ በሕይወታችን ለእግዚአብሔር የማንገዛ፣ ትእዛዙን የማንጠብቅና የማናከብር፣ ሰማያዊ አምልኮታችንን በዚህ በምድር በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት የማንገልጽ ከሆነ የአጋንንትን የበላይነት፣ የሰዎችን ክፋት ተግባረ ሕይወት ማስተናገዳችን አይቀርም፡፡ ምክንያቱም መለኮታዊ ዋስትናና ጥበቃ ከእኛ ስለሚርቅ ነው፡፡ የማናመልከውን፣ የማናከብረውን ሕጉን የማንጠብቀውን እግዚአብሔርን ከአጋንንት ውጊያ፣ ከክፉ ሰዎች እጅ በባዶ አድነኝ ማለት ሞኝነት ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ያልተንበረከከ ጉልበታችን አጋንንት ቢያስረው፣ እግዚአብሔርን የማያስብ አእምሮአችን በሰዎች መተት ቢሰለብ፣ መልካም እድላችን የሌላ ሰው ቀለብ ቢሆን ሊገርመን አይገባም፡፡ አንዳንዴ መተትን ወደ እኛ የሚያመጣው የራሳችንም መንፈሳዊ ስንፍናም ጭምር ነው፡፡ ሕይወታችን በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት የታጠረ ካልሆነ ሥጋዊ እድላችንን ብቻ ሳይሆን ሰማያዊ ተስፋችንንም ልናጣ እንችላለን፡፡
በዚህ በተቃራኒ ደግሞ እግዚአብሔርን እያመለኩ፣ ለእርሱም እየተንበረከኩ፣ በመንፈሳዊ ሕይወታውም ጠንካራ ሆነው መተት በሕይወታቸው ጣልቃ በመግባት ብዙ ነገራቸውን የሚያሳጣቸው ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን ‹‹እንዲህ ሲያስደርጉኝ፣ ይህን ሲያሳጡኝ፣ ይህን ነገሬን ሲያበላሹብኝ ለምን ዝም አልከኝ፣ ለምን አሳልፈህ ሰጠኸኝ›› በማለት ሊማረሩ እና እምነታቸውን ሊሸረሽሩ ይችላሉ፡፡ ያላወቁትም በመተት በየ ገዳሙና በየጸበሉ በመንከራተት ሲኖሩ ሲያዩ ምንም ጽድቅ እንደሌላቸውና ከኃጢአተኞች ጎራም ሊፈርጇቸው ይችላሉ፡፡ ግን እግዚአብሔር የሚጠላውን ሳይሆን የሚወደውን እንደ ወርቅ እሳት በሆነ ፈተና ይፈትናል ይቀጣል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገስጻቸዋለሁ እቀጣቸውማለሁ›› ያለን፡፡ /ራዕ 3÷19/ ሌላው እግዚአብሔር በመከራችን ሊባርከን፣ የእሱ መሆናችንን ሊፈትነን ለፈተና አሳልፎ ይሰጠናል፡፡ ያዕቆብ በመልእክቱ ‹‹በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው›› ብሎናል፡፡ /ያዕ 1÷12/
ቤተሰቦቼ ሰው በአጋንንት ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ሰው ትልቅ የሕይወት መከራ ሊቀበል ይችላል፡፡ መከራ ለመቀበል የግድ ኃጢአተኛ መሆን አይጠበቅብንም በጽድቃችን መከራን ልንቀበል እንችላለን፡፡ ጻደቁ አቡነ ተክለ ሐዋርያት ያንን ሁሉ መከራ የተቀበሉት በአፄ ዘርዓያዕብ ነው፡፡ አፄ አርዓ ያዕቆብ ለአቡነ ተክለ ሐዋርያት መፈተኛ እና ጸጋ ማግኛ ነበሩ፡፡ ንጉሥ ሱስንዮስ ለአቡነ አምደ ሥላሌ፣ ለአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ፣ ለቅድስት ወለተ ጴጥሮስ፣ ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ወዘተ መፈተኛቸው ነበረ፡፡ ስለዚህ አጋንንት ብቻ ሳይሆን ሰው ለሰው መፈተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ወደ እኛ የሚመጣውን ፈተና ለጸጋ አድርግልኝ ማለት ብዙ ሽልማት አለው።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
«የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል። እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች። ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች። ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥ ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።» (ያዕ.5:15-20)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
«መተት እኛ ላይ በሁለት መልኩ ሊሠራ ይችላል»
1ኛ በአጋንንት ክፋት፦ አጋንንቱ የእኛን መልካም ነገር ለሰዎች አግንኖ በማሳየት የእኛ የሆነውን ነገር መቀማት እንደሚቻል በማሳሰብ ሰዎችን በተለይም የእኛ የምንላቸውን ሰዎች በቅናት በማስነሳት ሰውዬውን አጋንንታዊ መሣሪያ አድርጎ በመጠቀም ይሠራብናል፡፡
2ኛ በሰዎች ቅናት፦ ከላይ እንዳልኩት ድሮ በሰው የሚቀናው በውበታቸው፣ በቁመናቸው ወዘተ ነው፡፡ አሁን ይህ ቀርቷል፡፡ ሰው በሰው የሚቀናው በዕድሉ ነው፡፡ እድል ደግሞ የፈጣሪ ስጦታ ነችና በዚህ በመቅናት ሊያስመትቱ፣ የእኛን እድል በአጋንንት ጥበብ ወደ ራሳቸው ሊጎትቱ ሊያስጉትቱ ይችላሉ፡፡ ይሄን ሲናገር ብዙ ሰዎች እንዴት ልሉ ይችላሉ፤ ነገር ግን ዛሬ ብዙ ሰዎች በዚህ የመተት አሰራር ዕድላቸው፣ ሰላማቸው፣ በረከታቸው፣ ሥጦታቸው ተወስዶባቸው ይቸገራሉ እና ልንጠነቀቅ ይገባል።
‹‹ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቶአል›› ት.ሆሴ 4÷6
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"ኸረ አላውቀውም"
ይሄን አስተውሉ! ሐዋሪያቱን ከክርስቶስ ለመለየት ዲያቢሎስ የተጠቀመው ዘዴ ይሄ ነው፡፡ ከውጪ ሰይፍና ገመድ የያዘ ባለ ብዘ ጭፍራዎችን ይዞባቸው መጣ፡፡ አጠገባቸው ያለው ኃያል አምላክ መሆኑን ፍጹም ረስተው ተረበሹ፡፡ እንደውምማ ስምዖን የተባለ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ፥ ካንተ ጋር ሞትንም ለመቀበል ዜግጁ ነኝ" ያለበትን አንደበት ለወጠና "ኸረ አላውቀውም" እስኪል ድረስ ከውጪ በሚያየው ክስተት ተሸነፈ፡፡ ልብ እንበል! ዲያቢሎስ የውጪ ክስተትን ካመጣ በኋላ፤ ከውስጥ ደግሞ የአዘሪት ሹክሹክታውን በዚ ክስተት መሠረት ያስከትላል፡፡ ጴጥሮስ ከላይ በዓይኑ በሚያየው የግርፋትና የእንግልት ጊዜ እንዲደነግጥ ካደረገው በኋላ፤ ከውስጡ ቀድሞ የነበረው ዓይነጥላ
"አላውቀውም አላውቀውም" እያለ ሲያሾከሹክበት፤ ወደ ውጪም ይህንን ድምፅ አወጣና ሦስት ጊዛ "አላውቀውም" ሲል ካደ፡፡ ነገር ግን ዶሮ በጮኸ ጊዜ ወደ ጌታ ዓይኖች በቀጥታ ቢመለከት፤ ከቁጣ ይልቅ ፍቅር፣ ከንዴት ይልቅ ይቅርታ፣ ከበቀል ይልቅ ምሕረትን ሲያነብበት፤ ነፍሱ በዚህች ቅጽበት ጉልበት አገኘችና ከውስጥ ያለውን ጥፋት በንስሐ አጠበው፡፡ ከዚ በኋላ አይደለም ከውጪ ባለ ክስተት ሊደናገጥ፤ እጅግ የከፉ መከራዎችን እየታገለ፣ ብዘ እንግልቶችን እየተዋጋ፣ በአንድ ስብከት ሺዎችን ወደ ጌታው በረት እየመለሰ፣ ርዕሰ-ሐዋሪያት ሆኖ የተሰጠውን ሰማያዊ ክህነት በምድር ላይ ገልጦ በትክክልም የቤተክርስቲያን ዓለት መሆኑን አሳይቶ ዲያቢሎስን ሙሉ በሙሉ በማሸነፍ ለክርስቲያኖች አርአያ ሆኖናል፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስ በረከት ይደርብን። ዛሬም ብዙዎቻችን ባላወቅነው መንገድ በዲያብሎስ እንፈተናለን ቢሆንም እንደ ጴጥሮስ ልንነቃ እና ልናሸንፈው ይገባል።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🌹 እንሆ፥ ልጆች፡ የእግዚአብሔር፡ስጦታ፡ ናቸው፥ የሆድም፡ ፍሬ፡ የርሱ፡ ዋጋ፡ ነው። (መዝ.127፡3-4)
🌹 በእግዚአብሔር ቸርነት በቅድስት ድንግል ማሪያም አማላጅነት፣ በቅዱስ ሚካኤል ረዳትነት እና ጥበቃ፣ በሁሉም ቅዱሳን ምልጃና ልመና እግዚአብሔር የተባረከ ልጅን ስጥቶኛልና እግዚአብሔርን አመስግኑ በእውነት። በጣም ደስ ብሎኛል ቤተሰቦቼ።
🌹 ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንን ሁሌም እናሸንፋለን። በፈተና ውስጥም ቢሆን ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንን አንወድቅም። ቤተሰቦቼ እንበርታ፣ እንጠንክር። እግዚአብሔር እኔንና ቤተሰበን እንደረዳ ሁላችሁንም ይርዳችሁ። እግዚአብሔር ስሙ በፍጥረት አንደበት የተመሰገነ ይሁን።
"ሃሌ ሉያ፦ ምስጋና ለጌታ ለአምላካችን ይሁን" 🙏🙏🙏
🙏 ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ሳክራሚንቶ በደብረሰላም ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን የካቲት 15/16/17 አይቀርም። February 23/24/ 25 የወንጌል ትምህርትና የፀበል አገልግሎት ይከናወናል! ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። በዚህ አከባቢ ያሉ ቤተሰቦች እንድሳተፉ መረጃውን ሸር እናድርግ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"ክፉ ሀሳብ እያሰቃያችሁ ነውን?"
◈ ክፉ ሀሳብ ሳትፈልጉት መጥቶ አዕምሯችሁ ውስጥ ይታሻል? በጣም የሚዘገንን ክፋት በአዕምሯችሁ ውስጥ ይርመሰመሳል! እኔኮ ይሄን ላስበው በፍፁም አልችልም አዕምሮዬ የሌላ ሰው እየመሰለኝ ነው ትላላችሁ? ኸረ ይሄ ክፉ ሀሳብ ውስጤ ከረመብኝ በምን ላስወግደው ብላችሁ ተጨንቃችኋል?
◈ አዕምሮ ሀሳብን እንዳይገባ የሚከለክል አጥር የለውም። አጥር የሌለው ቤት ሁሉ ነገር ዘው እንደሚልበት አዕምሮ ውስጥም ብዙ ዓይነት ሃሳብ ዘው ብሎ ይገባል። አዕምሯችን የተጠረገ አስፓልት ነው ሃሳቦች እንዳሻቸው እየነጠሩ ይጓዛሉ። የእግዚአብሔር ሀሳብ ያልፍበታል፤ የሰይጣን ሀሳብ ያልፍበታል፤ የስጋና የደም የምኞት ሃሳብ ያልፍበታል። እነዚህ ሁሉ ሃሳቦች የኛ አይደሉም።
◈ በመንገድ የሚያልፈው ሰው ሁሉ የምናውቀው የኛ ሰው አይደለም። የምናውቀውን ብቻ አቁመን ሰላምታ እንሰጠዋለን። ሃሳብም በአዕምሯችን ሽው ብሎ ሲያልፍ ለሁሉም ሀሳብ እጅ አንነሳም፤ የእግዚአብሔር ሃሳብ የሆነውን ቅልብ አድርገን እንይዘዋለን አላሳልፍም ብለን የራሳችን እናደርገዋለን።
◈ የተበላሸ ነገር ወደ ሆዳችን ስናስገባ በፍጥነት በሽታው ይጀምረናል ወደ አዕምሮም መጥፎ ሀሳብ ሲገባም አጣዳፊ የአዕምሮ ሁከት ይጀምረናል ከዛ በአዕምሮህ ወደላይ ወደታች ያሯሩጥሀል። ስለዚህ ምን እንደምትሰሙ፣ ምን እንደምታዩ ተጠንቀቁ ይላል ቃሉ። ይሁዳም የሆነው እንደዚሁ ነው። ሰይጣን በይሁዳ አዕምሮ ውስጥ ሀሳብ አገባበት እርሱም ሃሳቡን ንብረቱ አድርጎ ተቀበለው። ወዲያው አዕምሮው ተቃወሰ።
◈ ሃሳብ ወደ አዕምሯችን እንዳይገባ መከላከል አንችልም። ይህ ከኛ አቅም በላይ ነው። ነገር ግን አንድ ነገር ማድረግ ትችላለህ እርሱም የገባውን ክፉ ሃሳብ በተሻለ ሃሳብ ማሸነፍ ትችላለህ። ሰይጣን ጠላት ነው፡፡ አእምሮ ደግሞ ቤት ነው፡፡ ሰይጣን መቼም የማይታረቅህ የዘላለም ጠላትህ ነው።
◈ ሰይጣን ቤትህን የቆሻሻ ዓለም እስኪያስመሰለው ድረስ ክፉ ሃሳብን ከመጣል አያንቀላፋም፡፡ ጠላት የጣለውን ከቤትህ ማስወጣት ያንተ ትጋት ነው፡፡ ችላ ካልከው ግን አንተ ራስህ ለመግባት እስክትቸገር ድረስ ቤትህ ቆሻሻ በቆሻሻ ይሆናል፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ሳይበዛ የጣለውን ጥቂት በጥቂት አስወጣው፡፡ በዚያም ቤትህ በእግዚአብሔር ጸጋ ንጹህ ይሆናል።
◈ ስለዚህ ለምን ክፉ ሀሳብ ውስጤ ገባ ብለህ አትብሰልሰል። ይሁዳ ከነጴጥሮስና ዮሀንስ የተለየ ፍጥረት ስለነበር አይደለም ሰይጣን የተጠቀመበት ይሁዳ ውስጥ የገባው ክፉ ሀሳብ እነጴጥሮስ ውስጥም ገብቶ ድል ነስተውት ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ሃሳቡ እንዳይገባ ማድረግ አትችልም እንዲወጣ ግን ማድረግ ትችላለህ።
◈ ክፉ ሀሳብ ውስጥህ ሲመጣብህ መልካም በሆነው ድል በሚነሳው በወንጌል ቃል አክሽፈው። አቤቱ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ ውስጤ ሰርጎ የገባውን ክፉ ሀሳብ በስምህ ጠርገህ አስወግድልኝ፤ ከነዚህ ክፉ ሃሳቦች መዳን ወዳለሁና አቤቱ ከስራቸው ነቅለህ ጣላቸው ብለህ ፀልይ። እግዚአብሔር ይንቀልላችሁ!!
◈ "ወፍ ከራስሕ በላይ እንዳትበር ማድረግ አትችልም ይሁን እንጅ በአናትህ ላይ መጥታ ጎጆ እንዳትሠራ ማድረግ ትችላለህ፡፡ ልክ እንደዝሁ መጥፎ ሐሳብ ወደ አዕምሮህ እንዳይገባ ማድረግ አትችልም ነገር ግን የገባውን #አለማስተናገድ ትችላለህ"
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
የምስጢር መተት የሚደገመው የእኔ በምትሉት በቅርብ ሰው ነው ዲያብሎስ ተለይተን እንዳንወጣ ይታገላል የቅዱስ ሩፋኤል ድንቅ ተዓምር #ethiopia 😰😭
https://youtu.be/uk7SZerHzQ0
ሰግደን የሚሰግድ ትውልድ እንድናፈራ ነው ክርስትናችን የፓስተር ሶፎንያስ አሳዛኝ ንግግር የይቅርታ ልብ ይኑረን #ethiopia #orthodox 😭🙄😰
https://youtu.be/boqTR-uT7zM
3ቱ የኃጢአት አፈጻጸም መንገዶች እና መፍትሔዎቹ የኀልዮ ኃጢአትን ለማራቅ መፍትሔዎቹ በማሰብ የሚፈጸሙ ኃጢአቶች #ethiopia #orthodox 😭
https://youtu.be/TC94KCiYKwg
ሰይጣን አራት ምርጫዎች ያቀርብልሃል ጠንቋይ ሆነው ዝክር የሚዘክሩ የጥሎሽ አመጣጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ #ethiopia #orthodox #sibket 😰😭🙄🙏
https://youtu.be/F_7ng7IDLUk
ሰይጣን አራት ምርጫዎች ያቀርብልሃል ጠንቋይ ሆነው ዝክር የሚዘክሩ የጥሎሽ አመጣጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ #ethiopia #orthodox #sibket 😰😭🙄🙏
https://youtu.be/F_7ng7IDLUk
