ch
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

前往频道在 Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

显示更多
2 278
订阅者
+324 小时
+137
+3830
帖子存档
4ቱ ታላላቅ ነገሮች ሁላችንም ማወቅ ያለብን!! ነጮችን አምላኪ ትውልድ ፈጥረናል!! እኛ ስብከት መስማት እንጂ መኖር አልቻልንም!! እሳት ላይ የወደቀ ትውልድ! https://youtu.be/vGpikBUHRLg

+++ በዚህ ድንቅ ዝማሬ እራሳችንን እያበረታን በምስጋና ሰዓቱንና ጊዜውን ማሳለፍና እግዚአብሔርን በሁሉ ነገር ማሳተፍ ሁለም ቢሆን ይኖርብናል ቤተሰቦቼ። ምስጋና ልቋረጥ የሚገባ ነገር መሆን የለበትም! እንበርታ፣ እንጠንክር። ባላችሁበት ሁሉ ማመስገንን እንለማመድ። ቅዱስ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይገባዋል። ለእናቱ ለቅድስት ድንግል ማሪያም ክብር ይገባታል። ረድኤት በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን።

+++ ሙሴ ከሲና ተራራ ወርዶ ከሕዝቡ ጋር ሲገናኝ የፊቱን ማንጸባረቅ አይተው "ተሸፈንልን" ያሉት ሕዝቡ ናቸው። እርሱ "ከእግዚአብሔር ጋር ስነጋገር ቆይቼ እኮ አሁን መውረዴ ነው? ምነው የፊቴ ብርሃ
+++ ሙሴ ከሲና ተራራ ወርዶ ከሕዝቡ ጋር ሲገናኝ የፊቱን ማንጸባረቅ አይተው "ተሸፈንልን" ያሉት ሕዝቡ ናቸው። እርሱ "ከእግዚአብሔር ጋር ስነጋገር ቆይቼ እኮ አሁን መውረዴ ነው? ምነው የፊቴ ብርሃን አስቸገራችሁ? ልሸፈንላችሁ እንዴ?" አላለም። እንዲያውም ቅዱስ መጽሐፍ "ሙሴም ከተራራው በወረደ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ተነጋገረ የፊቱ ቁርበት እንዳንጸባረቀ አላወቀም ነበር" ነው የሚለው።(ዘጸ 34፥29) ለቅዱሳን እግዚአብሔር በፊታቸው የሚሥለው የክብር ብርሃን እነርሱን ለሚመለከታቸው እንጂ ለራሳቸው አይታወቃቸውም። እውነተኞቹ ቅዱሳን "ተሸፈኑልን" የሚባሉ እንጂ "ልሸፈንላችሁ" የሚሉ አይደሉም። +++ ጥቂት በጎ ሥራ ሠርተህ ጻድቅነትህን በግድ ለማሳየት አትሞክር። ሌሎች ተሸፈንልን ይበሉህ እንጂ፣ አንተ ራስህ "ልሸፈንላችሁ" እያልህ የዋሐንን አታስጨንቅ። +++ በአገራችን የሚታወቅ ተረት አለ። አንድ ጊዜ ትንኝ በሬ ቀንድ ላይ ቆመችና "ከብጄህ እንደ ሆነ ንገረኝና ልነሣልህ" አለችው። በሬውም "እንኳን ልትከብጅኝ መኖርሽንም አላወቅሁም" አላት። "ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው" ሉቃስ 18፥9 🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ወዳጆቼ! መዝሙር ተጋበዙልኝ። እንዴት ናችሁ ሁሉ መልካም ነው። ጸሎት፣ ስግደት በአጠቃላይ የአምልኮት ሕይወት እንዴት ይዟችኋል? በርቱ፣ ጠንክሩ! እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።

" ✝️ ክርስቲያን ✝️ ማለት፦ *የክርስቶስን ፈለገ የሚከተል፣ *በኹለንተናው ክርስቶስን እና ቅዱሳንን ለመምሰል የሚጥር፣ *እንደተጻፈው በቃሉ የሚኖር፣ *'በክርስቶስ እኖራለኁ' የሚል፣ ... *ለሁሉ
" ✝️ ክርስቲያን ✝️ ማለት፦ *የክርስቶስን ፈለገ የሚከተል፣ *በኹለንተናው ክርስቶስን እና ቅዱሳንን ለመምሰል የሚጥር፣ *እንደተጻፈው በቃሉ የሚኖር፣ *'በክርስቶስ እኖራለኁ' የሚል፣ ... *ለሁሉም ምሕረት የሚያደርግ፣ *በምንም ዓይነት መከራ የማይሸበር፣ *ርሱ ባለበት ስፍራ ሁሉ፣ ድሆች ሲንገላቱ ማየትን የማይፈቅድ፣ *ርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ የሚረዳ፣ *ካዘኑት ጋር የሚያዝን፣ *የሌሎችን ኀዘን የራሱ አድርጎ የሚቆጥር፣ *በተገፉት ሰዎች ዕንባ፣ የሚያስለቅሰው፣ *ቤቱ ርዳታውን ለሚፈልጉ ሰዎች ሁሉ ቤት የሆነ፣ *በሩ በማንም ሰው ላይ ያልተዘጋ፣ *ከማዕዱ ሀብታሞችም ድሆች ተካፍለው የሚበሉ፣ *በቀን እና በሌሊት እግዚአብሔርን የሚያገልገል፣ *በዚህም ዓለም ራሱን በመንፈስ ድሃ በማድረጉ፣ በእግዚአብሔር እና በመላእክቱ ፊት ሞገስን ያገኘ፣ *ነቁጥ የሌለበትና የምትወደድ ነፍስ ያለችው፣ *አእምሮው በንጹሕ እምነትን የተሞላ፣ *በአጠቃላይ አሳቡን፣ እምነቱን እና ኑሮውን ወደ እግዚአብሔር እና ወደ መንግሥቱ ያደረገ፣ ሙሉ ተስፋው ክርስቶስ የሆነ፣ ሰማያዊ መዝገብን እንጂ ምድራዊ መዝገብን የማያከማች፣ "ክርስቲያን" ማለት ርሱ ነው' ቅዱስ አውግስጦስ (Hugh, Pope St. Augustine of Hippo [1961] USA) (ቅዱስ ፡ ጎርጎርዮስ ፡ ዘእንዚናዙ ፡ ሕይወቱ ፡ እና ፡ ትምህርቱ፤ ፡ በዲ.ን ፡ ታደለ ፡ ፈንታው፤ ፡ ገጽ ፡ ፲፱/19) #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ቀሲስ ሄኖክ አሁን ላየቪ ናቸው እባካችሁ ገባ ገባ በሉ ቤተሰቦቼ።

ይኼንን ብታዳምጡ ብዙ ታተርፋለችሁ!! በጋብቻ ሕይወት ውስጥ መረዳትና መገንዘብ ያለብን ነገር!! #ጋብቻ #ሰርግ #ethiopia #memhirgirma 😭💥🚩😱 https://youtu.be/w0BjrweD2XA

ንቁ!! እንደዚህ ያለ ዘመን የማይፈትነው ሰው የለም!! ሕይወትን የሚቀይሩ ድንቅ ምክሮች!! #አባ_ገብረኪዳን_ግርማ #abagebrekidan #ethiopia https://youtu.be/BitgiawaEM8

#መናፍስት_እንዲህ_ያደርጋሉና_እንንቃ_ወገን!! የመናፍስት ከባዱ ፈተና በቤተሰቦቻችን! Memehir Girma Wondimu Video 2025 #ethiopia https://youtu.be/F-9OVCW_Qdk

በመኪና አጋጭቼ ልገድለው ነበር አልተሳካልኝም!! ድብቁ የመናፍስቱ የጥቃት መንገድ ሲገለጥ!! #ethiopia #አባ_ገብረኪዳን_ግርማ #orthodox 😱😭💥🔥 https://youtu.be/qejzPO5OWRM

+++ #ቅድስት_አርሴማ +++ ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ እናቴ ክብርሽን አንግሼ ሆንኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ #እናቴ_ቅድስት_አርሴማ ዝናሽ ለዓለም ተሰማ #ስመጣ_ባልጋ_
+++ #ቅድስት_አርሴማ +++ ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ እናቴ ክብርሽን አንግሼ ሆንኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ #እናቴ_ቅድስት_አርሴማ ዝናሽ ለዓለም ተሰማ #ስመጣ_ባልጋ_ነበረ ተስፋዬም የተሰበረ በእምነትሽ በፀበልሽ ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ ልናገር ዝናሽን ላውራ ይደነቅ የአምላክሽ ሥራ #ተጋድሎሽ_የእምነትሽ_ፅናት #ሆኖኛል_የእምነቴ_መብራት #ደምግባት_ከንቱ_ብለሽ ለሰማይ ክብር ታጭተሽ የእምነቴ አሰረ ፍኖት በምልጃሽ አለሁ በህይወት የልቡን ለነገረሽ ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል እርዳታሽ የደረሰለት ያመጣል የልቡን ስለት ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው #ባንቺ_አፍሮ_የሄደው_ማነው የልቡን ለነገረሽ ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል #የጠራሽ_ማን_አፍሮ_ያውቃል /ዘመሪት ሲ/ር ሊዲያ ታደሰ/ ✨ የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን✨ ቃልኪዳኗ ሀገራችን ኢትዮጵያን ከክፉ ይሰውርልን 🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

++ ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እ
++ ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

+ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፤ + + የብርሃኑ ጸዳል እጅግ በሚያበራ ዓምደ ብርሃን ለተቀረፀ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። ክቡሩ አባት ሆይ፤ በኃጢያት ድጥ ላይ ለመውደቅ የሚፍገመግሙትን በኃይል ክንድ
+ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፤ + + የብርሃኑ ጸዳል እጅግ በሚያበራ ዓምደ ብርሃን ለተቀረፀ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። ክቡሩ አባት ሆይ፤ በኃጢያት ድጥ ላይ ለመውደቅ የሚፍገመግሙትን በኃይል ክንድህ ፈጥነህ የምትደግፍ ነህና በዓለም ላይ መልካም ዝናን ለአተረፈው ስም አጠራርህ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፤ ግብፅም ትዘምራለች። (መልክዐ ገብረመንፈስቅዱስ: ለዝክረ ስምከ) + ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሆይ ስምህን እየጠራን ዝክር ላደረግን፣ ፀበልህን ለጠጣን፣ እምነትህን ለተቀባን፣ በተቀደሰዉ የመታሰቢያህ ቅዱስ ቦታህ በመገኘት ለተማጸንህና ለጸለይን ሁሉ ፈዉስንና ምሕረትን ስጠን ፡፡ + ከሰለጠነብን ጽኑ የሥጋ ይሁን የነፍስ ደዌ እንድንድን፣ ስለኃጥያታችን ፀፀትና መመለስን፣ ስለ እዉነት በእውነት እንድንቆም ፤ + የእግዚአብሔርን ፍቅር አዉቀን ትእዛዛቱን የምንፈጽምበት ጽናት ብርታት እንድናገኝ ስምህን እየጠራን እንማጸንሃለን ታማልደን ዘንድ ቅዱስ ፈቃድህ ይሁንልን፡፡ 🙏 አሜን 🙏 #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@estifo2239

ይኼንን ሳታዳምጡ በጭራሽ እንዳትቆርቡ!!! ስንጠመቅ አባል ስንቆርብ ደግሞ አካል እንሆናለን!!! መብራትና የውሃ ቆጣሪ የሚዘጋው አጋንንት!!! #ethiopia https://youtu.be/QBzeVpYiTxQ

የጋብቻ ትምህርት እያላችሁ ስትጠይቁኝ ለነበራችሁ ቤተሰቦቼ ይኼው እንዳያመልጣችሁ!! አሁኑኑ በመመዝገብ መማር ይችላሉ!! #ሸር_ይደረግ!!
የጋብቻ ትምህርት እያላችሁ ስትጠይቁኝ ለነበራችሁ ቤተሰቦቼ ይኼው እንዳያመልጣችሁ!! አሁኑኑ በመመዝገብ መማር ይችላሉ!! #ሸር_ይደረግ!!

አባታችን ከዚህ በላይ የሚያገለግሉበትን ዕድሜ እግዚአብሔር ያድልዎት!! #_በአያት_ዮሐንስ_አገልግሎት_አቁምያለሁ! #_በቅርቡ_አገልግሎት_የምጀምርበትን_ደብር_አሳውቃቹሃለሁ! የወለላይቱ እመቤት ልጆች፣ አያት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ስሰጥ ነበር። ብዙዎቻችሁ እዛ መጥታችሁ በሥጋ ከክፉ መናፍስት ተላቃችሁ ተፈውሳቹሃል። ንስሐ ገብታችሁ ቄደር ተጠምቃችሁ በነፍሳችሁ ድናቹሃል። በዚህም አምላከ ቅዱስ ዮሐንስ ክብር ምስጋና ይድረሰው! በቅርቡ ለአገልግሎት ወደ ውጭ ሀገር እሄዳለሁ ከዛ ስመለስ የተለመደውን አገልግሎት በሰፊው ሰጣለሁ፤ የማገለግልበትንም ደብር አሳውቃቹሃለሁ። እስከዚያው በጸሎት በስግደት በአምልኮት ሕይወት እየበረታችሁ ትጉ! ኃያሉ መድኃኔ ዓለም በቸርነቱ፣ ወለላይቱ እመቤት በጸሎቷ ዳግም ለአገልግሎት ያገናኙን! "አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተ ኑር፣ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና" 2ኛ ጢሞ 3፥14 #_ቦታው_ላይ_የሠራናቸው_የበረከት_ሥራዎች! 1ኛ/ 560 ሺ ብር ትልቅ ጄኔሬተር ገዝተን አስገብተናል። 2ኛ/ ከ 200 ካሬ ሜትር በላይ ቦታ 1.5 ሚሊዮን ብር በመክፈል መሬት ገዝተን አስረክበናል። 3ኛ/ በመጀመሪያ ዙር 1.5 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት በማሽኖች ጊቢውን አስተካክለናል። 4ኛ/ በሁለተኛው ዙር አንድ ወዳጃችን ሙሉ ጊቢውን በግሬደር በመጥረግ፣ ሪዳሽ በመድፋት በሎደር በማስተካከል ወጪው 1.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ሥራ ሰርቶልናል። 5ኛ/ ለመጠመቂያ የሚሆን ትልቅ ዱንኳን 280 ሺ ብር ገዝተን ሰጥተናል። 6ኛ/ ሁለት ባለ 10 ሺ ሌትር የውኋ ሮቶ እያንዳንዳቸው 60 ሺ ብር እና ማጥመቂያ ፓንምፖች ገዝተን ሰጥተናል። 7ኛ/ ጸበል መጠመቂያ ቦታ በማሽኖች ሠርተናል። 8ኛ/ የቤተ ክርስቲያን መድረክ ሠርተናል። 9ኛ/ ለድልድይ የሚያስፈልጉ ብረቶችና ሲሚንና ሌሎች እነዚህንና ሌሎችንም የበረከት ሥራ በቦታው ሰርተናል። በአጠቃላይ 7 ሚሊዮን ብር የፈጀ የበረከት ሥራዎች ሠርተናል። ❤️ በዚህ የበረከት ሥራ ሁሌም ከጎኔ ያላችሁ፣ ይሄ ይደረግ ስላችሁ ፈጥናችሁ መልስ የምትሰጡኝና የምታግዙኝ "የወለላይቱ እመቤት" ማህበርተኞች እና አብራችሁን የምታገለግሉ ወጣቶች በሙሉ እጅጉን አመሰግናቹሃለሁ። እነዚህን የበረከት ሥራዎች በሌላ ደብርም አብረን እንደምንሠራ ተስፋ አለኝ። አክባሪያችሁ አገልጋያችሁ ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም! ጥር 28-6-17 ዓ.ም አዲስ አበባ

የሀገራችን ሰይጣኖች በተንኮል ልምድ አላቸው!! Memehir Girma Wondimu Video @estifo2239 #memhirgirma #ethiopia https://youtu.be/YaalxTnzHPI