ch
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

前往频道在 Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

显示更多
2 277
订阅者
-124 小时
+107
+3530
帖子存档
«መዳን በሌላ በማንም የለም» ◈ "መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ ከሰማይ በታች እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰው የተሰጠ ሌላ ስም ከቶ የለምና።" በሚለው ንባብ ውስጥ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ መድኃኒት መኾኑ ተገልጿል። "ሌላ ስም የለም" ሲል የአብንና የመንፈስ ቅዱስን ስም አያድንም ለማለት አይደለም፤ ነገር ግን አብ ወልድን የላከው በእርሱ ስም በኩል ለዓለም ድኅነት እንዲኾን ነው። የወልድን ስም መጥራት ከእርሱ የማይለዩትን አብንም መንፈስ ቅዱስንም መጥራት ነውና። ሦስቱ የማይለያይ አንድነት ሥራ አላቸውና። (Tadros, Yacob Malaty, Commentary on Act, p 214)። ◈ ስለዚህ የዚህ ጥቅስ ጭብጥ የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ መድኃኒት መኾኑን መግለጥ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም አምኖ የሚጠራ ይድናል የሚል ኹሉ አለ። ይህም የስሙን ታላቅነት መግለጥ ላይ መሠረት ያደረገ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሐሳብ ነው። ለምሳሌ ቅዱስ ጳውሎስ "የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል" ይላል። ሮሜ 10፥13። ይህንኑ ሐሳብ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ጽፎታል። ሐዋ 2፥21። እነዚህ የሐዲስ ኪዳን ጥቅሶች የሚያስረዱት የክርስቶስን እግዚአብሔርነት እንደ ኾነ ለማስረዳት ነቢዩ ኢዩኤል አስቀድሞ "የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል " ብሏል። ኢዩ 2፥32። እንግዲህ ይህ በግልጽ የኢየሱስ ክርስቶስን የስሙን መድኃኒትነትና ኀይል የሚገልጥ ነው። ◈ ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ የክርስቶስን ስም ባልተገባ ምግባር ውስጥ ኾነው ቢጠሩት መዳን የማይቻል መኾኑን የሚያስረዳ ንባብ አለ። "ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚወርስ አይደለም" እንዲል። ማቴ 7፥21። ይህ ማለት እምነት ኖሮን በፍጹም ምግባር ጉድለት ውስጥ ኾነን፡ በተግባራዊ ሕይወት የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ሳናከብር ብንጠራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አንችልም ማለት ነው። ከላይ "የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል" የሚለውን ይተረጉመዋል ማለት ነው። ዝም ብሎ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚል በሕይወቱ የጌታን ትእዛዛት የማይጠብቅ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባ ዘንድ እንዴት ይኾናል? ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዲህ ይላል "ከመንግሥተ ሰማያት ውጭ የሚኾነው እምነት እያለው ምግባር ግን የሌለው ሰው ብቻ አይደለም። እምነት ከመያዙም ባሻገር ብዙ ገቢረ ተአምራትን መፈጸም ስንኳ ቢችል፥ መልካም ምግባር ግን ከሌለው ይህ ሰው ሳይቀር ከዚያ ከተቀደሰው ደጅ ውጹእ ይኾናል።" (ገብረ እግዚአብሔር ኪደ (ተርጓሚ)፣ የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንደ ተረጎመው ድርሳን 1-24፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 470)። ◈ ከላይ ከያዝነው ሐሳብ ጋር ተመሳሳይ በኾነ ኹኔታ ኢየሱስ ክርስቶስን በአግባቡ ለመጥራት የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መኾንን ይጠይቃል። ሰውነታችን በኃጢአት ምክንያት የርኩስ መንፈስ ማደሪያ ከኾነብን እንግዲያውስ እንዴት በአግባቡ ኢየሱስን የባሕርይ አምላክነቱን በሚገልጥ ኹኔታ ልንጠራው እንችላለን? ቅዱስ ጳውሎስ "ስለዚህም ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ ሲናገር "ኢየሱስ ውጉዝ ነው" የሚል እንደ ሌለ፥ በመንፈስ ቅዱስም ካልኾነ በቀር "ኢየሱስ ጌታ ነው" ሊል አንድስ እንኳን እንዳይችል አስታውቃችኋለሁ።" ይላል። 1ቆሮ 12፥3። ትርጓሜያችን ይህን ሐሳብ "በብዔል ዜቡል ከሚል ከአይሁዳዊ በቀር አንድም ብዔል ዜቡል አድሮበት ፍጡር ከሚል ሰው በቀር፤ በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ኢየሱስ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ልዩ ነው የሚል እንደሌለ አስተምራችኋለሁ። አንድም ብዔል ዜቡል አድሮበት በኅድረት ነው ከሚል በቀር በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት መለኮት ከትስብእቱ ፡ ትስብእቱ ከመለኮቱ ልዩ ነው የሚል እንደሌለ እነግራችኋለሁ። ◈ "ወአልቦ ዘይክል ብሂለ እግዚእ ኢየሱስ ዘእንበለ ዘመንፈስ ቅዱስ ላዕሌሁ።" ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ካደረበት ሰው በቀር ኢየሱስ የባሕርይ አምላክ ነው ብሎ ማመን የሚቻለው እንደሌለ እነግራችኋለሁ። " ይላል። (ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሐፍ ንባቡ ከነትርጓሜው፣ 2007 ዓ.ም፣ ገጽ 257)። እንግዲህ ይህም የሚገልጠው በእውነተኛ እምነት ውስጥ በመልካም ምግባር መኖር የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሚያደርግ መኾኑንና በሚያድርብንም መንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ኢየሱስ ክርስቶስን በአግባቡ የምንጠራ መኾናችንን ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ አምነው ሲጠሩት ያድናል ማለት ነው። ◈ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ "ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው" በማለት ኢየሱስን ጌታ ነው ብሎ በአግባቡ ለመጥራት መንፈሳዊ ልደትን ገንዘብ ማድረግ የሚገባ መኾኑን ይጠቅሳል። (St Gregory, Bishops of Nyssa, On the Faith)። ስለዚህ በአንዲት ጥምቀት በኩል መንፈሳዊ ልጅነትን ገንዘብ ያላደረገ ኢየሱስ ክርስቶስን ጌታ ነው ብሎ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ጋር ያለውን ዕሪና መናገር አይችልም። እንግዲህ የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ለእኛ የተሰጠን አምነንበትና ተረድተን በመድኃኒትነቱ እንድንጠቀም ነው። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

◈ በዚህ ዓለም ሳለን የእኛ ማዕረግ የሚወሰነው እንደ እድሜያችን እንደ ተሰጥአችን ወይም እንደ ችሎታችን ነው። በዘላለማዊው ሕይወት ግን ማዕረጋችን የሚወሰነው እግዚአብሔርን የበለጠ በምታውቅ ልብ ነው
◈ በዚህ ዓለም ሳለን የእኛ ማዕረግ የሚወሰነው እንደ እድሜያችን እንደ ተሰጥአችን ወይም እንደ ችሎታችን ነው። በዘላለማዊው ሕይወት ግን ማዕረጋችን የሚወሰነው እግዚአብሔርን የበለጠ በምታውቅ ልብ ነው፤ ምናልባት ብዙዎች የተናቁ የተጠሉና ችላ የተባሉት እነዚያ ተሰጥኦ ወይም ሥልጣን ያላቸውን ሊበልጧቸው ይችላሉ፤ ስለዚህ ታናናሽ የተባሉትን በሙሉ እንዳትንቁ ይሁን። ◈ እግዚአብሔር ኢያሪኮን ለማዳን በወደደ ጊዜ የመረጠው ጋለሞታዋን ረዓብን ነበር፤ ከዚህ የተነሳ ረዓብ በጌታ የዘር ሐረግ ውስጥ ከተጠቀሱት የእግዚአብሔር ሰዎች መካከል አንዷ ሆና እንድትቆጠር ሆኗል። ያለፈው ሕይወቷ ስለ ተረሳና ቅድስት ስለ ሆነች ለሚያስታውሳት ሁሉ ሕያው ምሳሌ ወይም አርአያ ሆናለች፤ እግዚአብሔር ጋለሞታዋንና አጋንንት የነበሩባትን ሴት ምን ያህል እንደተከባከባት ስትመለከት ልትደነቅ ትችላለህ፤ እርሱ እንዲህ ያለውን እንክብካቤ ለተናቁት ለተጠሉትና ምንም ዓይነት ነገር አይገባቸውም ለተባሉት ሁሉ ያደርጋልና። "ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤ እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ።" (1ኛ ቆሮ 1፥27-28) ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ዓይነጥላና ዛር ያለ ጊዜ ያወፍራል፣ ያስረጃል፣ ያገረጅፋል || የትዳር ዕድልን መልክና ቁመናን ያበላሻል | የብዙ እህት ወንድሞች እና የባለትዳሮች ፈተና 🙄😭😰 https://youtu.be/mBynAHrzd9M

እንኳን አደረሳችሁ 🙏🙏 ደብረ ዘይት የዓብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት 🙏 እግዚአብሔር አምላካችን ጾሙን፣ ጸሎቱን የበረከት ያድርግልን። 🙏
እንኳን አደረሳችሁ 🙏🙏 ደብረ ዘይት የዓብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት 🙏 እግዚአብሔር አምላካችን ጾሙን፣ ጸሎቱን የበረከት ያድርግልን። 🙏

ጠቋር ያመነኩሳል አባቶችን ይፈትናል | በሽታ መሆን የምችሉ ርኩሳን መናፍስቶች | የጴንጤዎች ክህደት | ለምን ማሸነፍ አቃተን? #ethiopia #eotc 😭🙄😰 https://youtu.be/BgjdASIUP0w

በቆረበች ቀን ግደላት ተብሎ የተላከ መተት | ሸረሪት ዘራችን ነው ይላሉ! | ሰው ሆነው ወደ ጅብነት የምቀየሩ | በጋሻው ይቅርታ ጠየቀ! #ethiopia 🙏😭🙄 https://youtu.be/1DDihMkC_ac

ከልክ በላይ የመዋብ ልክፍት! | የዕድል መተትና ጣጣው | የስልብና መንፈሶች | አገልግሎታችን ስሜት ብቻ ሆኗል | ያልተናቀ ነገር ምን አለ? #ethiopia https://youtu.be/3kcfsJd0ipM

"በበጎነት መጽናት" ◈ ማር ወግሪስ እንዲህ ይላል፦ "ዳግመኛም ስማኝ ልንገርህ! ለዘለዓለም ላንተ ይብስብሃልና ባደርክበት ኹሉ ቃልህን አትለውጥ። በሰዎች መካከል ጥልን አትዝራ፤ አነዋወርህ ኹሉ በሰላም ይኹን፤ ወደ ልቡናህም ቍጣን አታስገባ፤ ወንድምህ የበደለህን ከቶ አታስብ። የቍጡ ሰው ድካሙ ኹሉ በዐይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ ፈጥኖ ያልፋልና። ቂምን በልቡናው የሚያኖር ሰው የሰይጣን ደቀ መዝሙሩ ነው፤ የዘለዓለም ሕይወትንም አያያትም። ማንንም ማንን አትማ፤ ከማንም ጋር አትከራከር፤ የባልጀራህን ንብረት አትመኝ የሌላውንም አትቀማ። ◈ ሐሜተኛ ሰው የእግዚአብሔር ጠላቱ ነው። በጠላትህ ውድቀትና ሞት ደስ አይበልህ፤ ባዘኑት ላይ አትሣለቅ፤ ለዕውሩ መሰናክል አታኑርበት። ስትጸልይ ለመቀመጥ አትቸኩል፤ ለጸሎት ጽሙድ ኾነህ በቆምክበት ቦታ ኹሉ አትነቃነቅ፤ በመካነ ጸሎትህ ላይ አዘውትረህ ቆመህ ተገኝ። ለለመነህ ኹሉ ስጥ፤ ከሌለህ ደግሞ እግዚአብሔር ይስጥህ ካለው ያድርስህ ብለህ በለዘበ ቃል ተናገር። የምትሠራውን ሥራ ኹሉ ፊት አይተህ አድልተህ አትሥራ። የደረሰብህን ኹሉ እግዚአብሔርን አመስግነህ ተቀበል። ይህንን ያደረግህ እንደ ኾነ በእግዚአብሔር ትእዛዛትና ሕግጋት አንተ በእውነት ፍጹም ነህ። እኔስ በእውነት የእግዚአብሔርን ጥበብ አደንቃለሁ።" እንዲል። (ገብረ ኪዳን ግርማ (አባ፣ የአራቱ ጉባኤያት የምስክር መምህር)፣ መጽሐፈ ወግሪስ፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 51)። ◈ የሕይወት መርሐችን ከላይ በተገለጸው መሠረት ቢኾን በበጎ መጽናት እንችላለን። ክፉ ነገር በሕሊናች ውስጥ በመጣ ጊዜ ወዲያው አስወግደን ብናስወጣው እና ሕሊናችን ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ኹል ጊዜ ብናስቀምጥ፥ በዚያም ቃል ብንመሰጥበት ሕይወታችን የተስተካከለ ይኾናል። ድንገት ስሜታዊ ኾነን ወደ ክፉ ልንሳብ ስንል ራሳችንን የምንቆጣጠርበት የእግዚአብሔር ቃል ውስጣችን ሊኖር ይገባል። በእርግጥም የሕይወት መርሐችንን በቃለ እግዚአብሔር እያደረግን ስንሄድ ስሜታችን በራሱ በቃለ እግዚአብሔር እየተገራ ይሄዳል። ውስጣችንም በቃለ እግዚአብሔር መመራትን እንደ ግዴታ መቀበል ይጀምራል። እንዲህ ሲኾን ብንጣላ ወዲያው ይቅር እንባባላለን፥ ቢበድሉን እንታገሳለን፥ ቢሰድቡን ስድብ የሚገባን ኃጥእ እንደ ኾን አድርገን እንቀበላለን፣ ቢንቁንም የክፉ ሥራችን ውጤት መኾኑን አምነን ያለተቃውሞ እንቀበላለን። እንዲህ በበጎ እየጸናን ስንሄድ የሚረብሸን ነገር በእኛ ላይ ኃይሉን እያጣ ይሄዳል፤ ሕይወታችንም በፍጹም ሰላምና ዕረፍት ይመላል። ◈ እንግዲህ ምክንያታዊ ነኝ ብለን ከምናስበው አጸፋዊ መልስ ኹሉ እየራቅን እንሄዳለን። እንዲህ ያደረግኹት እንዲህ ስላደረገችኝ/ገኝ ነው እያሉ ከመናገር ኹሉ ነጻ እንወጣለን። በሕይወታችን የሚገጥሙንን ችግር የምንላቸውን ነገሮች ኹሉ የመጋፈጥና የማሸነፍ ብርታታችን ታላቅ ይኾናል። የብዙ ዓመታት ሕማም ቢኾን፣ ወይም የገንዘብ እጦት ችግር ቢኾን፣ ወይም ከሰዎች ዘንድ ፍቅር አጣኹኝ ብሎ የማሰብ ፈተናም ቢኾን እንሻገረዋለን። መጀመሪያ መስተካከል ያለበት አስተሳሰብ እና ነገሮችን የምንረዳበት መንገድ ነው። ሲቀጥልም የመኖር ትርጒሙና ዓላማው ግልጽ ኾኖ ሊገባን ያስፈልጋል። ◈ ይህ በትክክል ሲገባን ያን መፈጸም ዋና ዓላማችን እየኾነ ይመጣል። ስለዚህ ሰይጣን ሊጥለንና ጥቅም አልባ ሊያደርገን የሚፈጽምብን ጥቃት ኹሉ ይከሽፋል። በበጎነት ጽናታችንም ድል ይነሣል። ስለዚህ ስንኖር ለምንድን ነው የምኖረው? እንዴትስ እንድኖር ነው ፈጣሪ የሚፈልገው? ፈጣሪስ እንደሚፈልገው መኖር ያልቻልኩት ለምንድን ነው? ለመኾኑ በበጎነት ጸንቼ እንዳልኖር የሚከለክለኝ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ለራሴ እየጠየኩ ሕይወቴን እያስተካከልኹኝ ልኖር ይገባኛል። በምን መመሪያ እንዳንል ከላይ ማር ወግሪስ ያስቀመጠልን ድንቅ የሕይወት መመሪያ አለልን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

የምስጥር መተትና መፍትሔዎቹ | በጋሻው ምን ነካው? መጨረሻችን ምን ይሆን? በመጠመቃችን ብቻ መንፈስ የለብኝም ማለት ትልቅ ስህተት ነው! #ethiopia 😭🙄 https://youtu.be/OldC_ii3CnM

ውዶች መዝሙር ተጋበዙልኝ! ሰላም ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ። ሁሉ መልካም ነው። እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ሰላም ነኝ። በርቱ፣ እንበርታ፥ እንጠንክር፥ እንንቃ! ሰላም ዋሉ! 🙏🙏🙏

«ነገ ለአንተ የተሻለ ነው!» ◈ ያለህበት ዛሬ ለአንተ እጅግ አሰልቺ ከሆነ ለነገህ ኑር፤ በዚህ ነገህ ዉስጥ አንተን ለማረጋጋት የእግዚአብሔር እጅ ወደ አንተ መዘርጋቱን ተመልከት፤ ይህንን ካደረግህ
«ነገ ለአንተ የተሻለ ነው!» ◈ ያለህበት ዛሬ ለአንተ እጅግ አሰልቺ ከሆነ ለነገህ ኑር፤ በዚህ ነገህ ዉስጥ አንተን ለማረጋጋት የእግዚአብሔር እጅ ወደ አንተ መዘርጋቱን ተመልከት፤ ይህንን ካደረግህ በዚህ ነገህ ዉስጥ ለችግሮችህ ብዙ መፍትሔዎችን መመልከት ትችላለህ፤ የአንተ ዛሬ ጨለማ ከሆነ ነገህ በፊትህ የብርሃን መስኮቶችን ይከፈትልሀል፡፡ ◈ ነገ ለሚያገኙት የዘለዓለም ህይወት ስለ ኖሩ ተስፋቸዉን ሁሉ በዚህ ነገ ላይ ጥለዉት ነበር። ሳዖል ባሳደደዉ ጊዜ ነብዩ ዳዊት የኖረዉ ለነገዉ ነዉ፤ ነብዩ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ዉስጥ ሳለ የኖረዉም ለነገዉ ነዉ፤ ቅዱስ ዮሴፍ በወኅኒ ሳለ አባቱ ቅዱስ ያዕቆብ ደግሞ በወንድሙ በዔሳዉ በተሳደደ ጊዜ የኖሩት ለነጋቸዉ ነበር፤ ያዕቆብም ከመሰደድ ዮሴፍም ከግዞት ህይወት እንደሚወጡ በእግዚአብሔር ታምነዋልና። ◈ ነገሮች ለአንተ አስቸጋሪ ከሆኑ ለራስህ ነገ መፍትሔ ይገኝላቸዋል ብለህ ንገረዉ፤ ከዚህም በኋላ ለዚህ ነገህ በፈገግታና በደስታ ኑር። (ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«የምትወድቁ አትደነቁ!» ◈ ዮሐንስ ዘሰዋስው "አንተ በየዕለቱ የምትወድቅ አትደነቅ፤ በቦታህ ላይ በርትተህ ቁም እንጂ አታቋርጥ። በርግጥም የሚጠብቅህ መልአክ ትዕግሥትህን (ጽናትህን) ያከብረዋል። ቍስል ገና ትኩስና አዲስ ኾኖ ሳለ ለማዳን ቀላል ነው፤ የቆየ፣ የተተወ፣ የሚመግልም እንደ ኾነ ግን ለማዳን የሚያስቸግር፣ ብዙ ክብካቤ፣ መቍረጥ፣ ማሸግ፣ መብጣትም የሚፈልግ ነው። ብዙዎች ከረዥም ቸልታ የተነሣ መዳን የማይችሉ ወደ መኾን መጥተዋል። ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ኹሉ ይቻላል። (ማቴ 19፡26) አስተውሉ! ከመውደቃችን በፊት አጋንንት እግዚአብሔር ሰውን ወዳጅ ነው ይሉናል፣ ከወደቅን በኋላ ግን ጨካኝ ነው ይሉናል። ... ◈ ሕሊናችን ከንጽሕና በመነጨ ሳይኾን በክፉ ከመስጠሙ (ከመዘፈቁ) የተነሣ እኛን መውቀስ አቍሞ እንደ ኾነ በጥንቃቄ ማጤን ይገባናል። ከውድቀት የመዳናችን ምልክቱ ያለማቋረጥ ራሳችንን እንደ ባለ ዕዳ አድርገን ማሰባችን ነው። የእግዚአብሔርን ምሕረቶች የሚተካከል ወይም የሚበልጥ ምንም ነገር የለም። በመኾኑም ተስፋ የሚቆርጥ ሰው ራሱን መግደል እየፈጸመ ነው።" ይላል። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ146-147)። ◈ ከመውደቅ በላይ ትልቁ ችግር ያለው ለመነሣት አለመጣር ላይ ነው። መውደቅ አዳማዊ ነው፤ ወድቆ መቅረት ግን ሰይጣናዊ ነው። ወንድሜ ሆይ አንድ ቀን ብቻ አይደለም! ብዙ ዕለታትን በተደጋጋሚ ልትወድቅ ትችላለህ ወይም አኹንም በተደጋጋሚ እየወደቅህ ይኾናል። ነገር ግን መነሣት እንዳለብህ እወቅ! ለመነሣት ከልብ በመነጨ ፍላጎት ስትፍጨረጨር እግዚአብሔር ኃይል ይኾንሃል ትነሣማለህ። ክርስትና የመነሣት ሕይወት መኾኑን ኹል ጊዜ በሕሊናህ ውስጥ አስቀምጠህ ያለ መሰልቸት ትጋ። የሰይጣን ትልቁ ትግልና ውጊና ያለው መነሣት አትችልም የሚለውን ሐሳብ በማሳሰብ ማደካከም ላይ መኾኑን ልብ ብለህ እንደ ብልህ ወታደር በጥንቃቄ ተዋጋ። ◈ በልብህም ውስጥ ወደ ቀቢጸ ተስፋ የሚወስዱ ምክንያትችን አታስቀምጥ፤ ይልቅስ የእግዚአብሔርን ምሕረት እያሰብክ ሳታቆርጥ ተጋደል። በክፉ ሕይወት ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜ እየገባው እንዴት እግዚአብሔር ፊት ቆሜ ይቅር በለኝ እለዋለሁኝ አትበል። እግዚአብሔር ካንተ የሚፈልገው የእውነት መጸጸትህን እና በእርሱ ይቅር ባይነት ማመንህ ነው። ይህንም እኮ አላደረኩም፤ ሌላው ቢቀር ንስሐም እኮ አልገባኹም ለመግባትም እፈራለሁኝ እያልክ ራስህን በሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትክተት። አእምሮ እንዳለው ሰው አስበህ ኹል ጊዜም የእግዚአብሔርን ምሕረት ፈልግ። እስካኹን የንስሐ ሕይወት ባይኖርህም ከእንግዲህ እንዲኖርህ ማድረግ የምትችል መኾንህ አውቀህ ሳትሳነፍ ወደ እግዚአብሔር ቅረብ። እግዚአብሔር የኹላችንንም ዐይነ ልቡና ያብራልን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ሀገርን በደም ለሚሰሩ ወዮላቸው! | መስገድና መጸለይ ሁለቱ የተለያዩ ናቸው | በቁም ላለመቀበር መንቂያው ጊዜው አሁን ነው | እጮኛሞች ይሄን ተጠንቀቁ! 😭🙄🙏 https://youtu.be/KimdBHU9WSc

ለአመቺሳ የተሰጡ ሰዎች ችግራቸውና መከራቸው | ቁርባን የራስ ምታት ማስታገሻ አይደለም | የመናፍስት መናበብ | ቤተመቅደስ ፋርማሲ አይደለችም https://youtu.be/iHvB6G6DX28

◈ እውነተኛ ወዳጅ፥ ወዳጅ መኾኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፤ ኹላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሠራለን፤ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ኾነን ለማለፍ እንጥራለን፤ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን ወይም ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን፤ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፤ እስኪ ራስህን መርምር ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ጓደኛህ ኃጢአት ሠርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ያደረገው ይቅርታ ትክክለኛ እንዳልኾነ እንዲያውቅ ታደርጓለህን? እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ምናልባት ጓደኛህ አለአግባብ ሊቆጣህ ይችላል፤ ታዲያ ሲቆጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትኾነው? ◈ ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊኾን የሚገባውን መኾን አለበት፤ ስንቆጣው እንኳን ቁጣችንን ታግሶ ስናጠፋ የሚያርመን ሊኾን ይገባል፤ እንደዚህ ካልኾነ ጓደኝነት ጥልቀት አይኖረውምና፤ ጓደኞች ነን መባባላችን ጥቅም የለውምና ልናውቀው የሚገባን ነገር ግን አለ፤ ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው አይገባንም፤ ተግሣጻችን ኹልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መኾን የለበትም፤ ጥፋቱን ስንነግረው ኹልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ እንዲኾን ማድረግ አለብን፤ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሣ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልኾነ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፤ እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነውና፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

" . . . ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ . . . ” #መጻጉዕ
" . . . ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ . . . ” #መጻጉዕ

የመተት ዕድሳትን ለማስቆም | ስንት ዘመን ታግሶን ይሆን | የጸሎት ቤት አስፈላጊነት | ኩል የምትኳሉ ሴቶች ተጠንቀቁ | የቅዱስ ቁርባን መሠረታዊ ጥቅሞች 😭🙄 https://youtu.be/3w3trGMmrS4

ጸበል እንጠመቃለን፣ እንጸልያለን፣ እንጾማለን ስለዚህ ዓይነጥላ የለብኝም ማለት እንችላለን? ለምን ፈተና በዛብን፣ ለምን ነገሮች ተዘጋጉብን? #ethiopia 🙏 https://youtu.be/c66WBluUR9I

«የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ» ◈ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፤ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና (ዲያብሎስ)፤ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡ አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፤ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ/ሰይጣን ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፤ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፤ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ አስተውሉ! ◈ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፤ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፤ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፤ ስለዚህ በርታ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና በርታ፡፡ (ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«ወደ ቤተክርስቲያን መጥተህ ታከም»   ❖ በክርስትና ጸንተህ መኖር አለመኖርህን ለማረጋገጥ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራስህን ጠይቅ ፩. ጠዋትና ማታ በቋሚነት ትጸልያለህ? ፪. ሳታቋርጥ በቤተክርስቲያን የጋራ ጸሎት ትሳተፋለህ? ፫. በመምህረ ንስሐ በመመራት በቅዱስ ቍርባንና በሌሎች የቤተክርስቲያን ምሥጢራት ትሳተፋለህ? ፬. በቤተክርስቲያን ግጻዌ መሠረት ትጾማለህ? በተሠራው ቀኖና መሠረት በዓላትን ታከብራለህ? በአጥቢያ አገልግሎት ትታዘዛለህ? ፭. ኃጢአተኛነትህን አምነህ ራስህን በመርመር ለጸሎት በቆምክበትም ሆነ በሁሉ ቦታ የአምላክን ምሕረት ትጠይቃለህ? በሌሎች ከመፍረድ ራስህን ታቅባለህ? ፮. ዘመኑ ካመጣው ወከባ፣ አልጠግብ ባይነት፣ ያጡትን እያሰቡ ባገኙት አለመደሰት ከኢአማንያን የሚለይህ የተረጋጋ ሕይወት አለህ? ፯. በእጅህ ላይ ባለውና እግዚአበሔርን በሚያስደስተው ሥራ ታተኩራለህ ወይንስ በማይጨበጠውና ምኞታዊ በሆነ አሳብ ትዳክራለህ? ፰. በቃለ እግዚአብሔር በመመራት በቅዱሳን ምሳሌነት ራስን መግራትና መግዛት ላይ ታተኩራለህ ወይስ ፍተወታትን እያዳመጥህ ራስህን በማርካት ትጠመዳለህ? ፱. ሌሎችን በመርዳት ትደሰታለህ ወይስ በራስ ወዳድነት ሮጠህ አሸናፊ ለመሆን ትፈልጋለህ? ፲. ከሌሎች በመማር እምነትህን ታጸናለህ፣ የግብረ ሠናይና መልካም ሥነ ምግባር አርአያ ትሆናለህ? ሌሎችን ለመርዳት ትሳተፋለህ ወይስ ከዓለማውያን ጋር ጊዜህን በጭፈራና በዋዛ ፈዛዛ ታሳልፋለህ? ፲፩. መጽሐፍ ቅዱስን፣ ስንክሳርና ገድላትን ለማንበብ ቋሚ ጊዜ አለህ ወይስ በማይጠቅም መረጃ ብቻ ትጠመዳለህ? ፲፪. ከዘረኝነት ደዌ አምልጠህ የሰው ልጅን ሁሉ እኩል የምትወድበት ልብ አለህ ወይንስ ከአራዊት በከፋ ጭካኔ በጎራ ተሰልፈው ከሚናከሱት ጋር ሆነህ ራስህን ትወጋለህ? ፲፫. የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ሰውንና እግዚአብሔርን መውደድ መሆኑን ተረድተሃል? ወይስ ለአንተ የሚስማማህን የግል እምነት ፈጥረህ ከአንዲት ቤተክርስቲያን ተለይተሃል? ፲፬. ፍቅርን፣ ተስፋን፣ እምነትን መያዝ አለመያዝህን ራስህን ትጠይቃለህ? ተስፋ ቢስነት፣ ኑፋቄና ክህደት ወርሶህ በቍሳዊ ሀብት የምትተማመን ከሆንህ ፈጥነህ ወደ ቤተክርስቲያን ተመልሰህ ታከም:: #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube