HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
前往频道在 Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
显示更多2 273
订阅者
+224 小时
+177 天
+2930 天
帖子存档
ስንታረድ ስንገደል እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?? ገዳማት በማዞር ዕድሜያችንን የሚጨርሱ ክፉ መናፍስትና ሴራቸው! በድመት ሥጋ የተደገመ መተት ያስከተለውጣጣ! https://youtu.be/Cr1fsh1E8Nw
ኅዳር ፱ /9/
በዚች ዕለት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ አንደኛ የእስክንድርያ አገር ሊቃ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ይስሐቅ አረፈ።
ወላጆቹ ይህን ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በታላቅ ደስታ ደስ ተሰኙበት። ያጠምቀው ዘንድ ወደ ኤጲስቆጶስ በአቀረቡት ጊዜ ሲያጠምቀው በሕፃኑ ራስ ላይ የብርሃን መስቀልን አየ። እንዲህም ብሎ ትንቢት ተናገረለት ይህ ሕፃን በእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾማል እርሱ ለእግዚአብሔር የተመረጠ መሣሪያ ይሆናልና። የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ጽሕፈትን አስተማሩት ወላጆቹንም ትቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በአበምኔቱ በአባ ዘካርያስም ዘንድ መንኩሶ በገድል ተጠመደ።
በአንዲትም ዕለት አንድ ጻድቅ ሰው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አየው በእርሱም ላይ ይስሐቅ በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾም ዘንድ አለው ብሎ ትንቢት ተናገረ። ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ ጸሐፊ የሚሆነውና የሚረዳው ብልህ ሰው ፈለገ ስለ አባ ይስሐቅም ነገሩት እሱንም አስመጣው ይጽፍለትም ዘንድ ደብዳቤ ሰጠው እርሱ ግን አባ ይስሐቅ እያወቀ ጽሕፈቱን አበላሽ ሊቀ ጳጳሳቱ እንዲተወውና ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመለስ ነበር የዚህን ዓለም ክብር ይጠላልና።
ሊቀ ጳጳሳቱም እንዲተወውና እንዲአሰናብተው አውቆ ማበላሸቱን በአወቀ ጊዜ በጥሩ ጽፈሃል እንድትሔድም እኔ አልተውህም አለው ከወራትም በኋላ አባ ይስሐቅ ወደ አስቄጥስ ገዳም ተመለሰ አባ ዮሐንስም የሚያርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔርን በራእይ ከአንተ በኋላ ለዚች ሹመት የሚጠቅም ረዳትህ ይስሐቅ ነው አለው። አባ ዮሐንስ በአረፈ ጊዜ ይህን ቅዱስ አባት ይስሐቅን ይዘው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ :- መጽሐፈ ስንክሳር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
#_ታላቅ_የንግስ_በዓል_እና_የዝክር_በረከት_ጥሪ!
#_በንቡ_ቅዱስ_ሚካኤል_ቤተ_ክርስቲያን!
ሼር በማድረግ ለቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች አዳርሱ!
የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች የፊታችን አርብ ህዳር 12 ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ታላቅ ክብረ በዓሉ ነው። ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አርብ ህዳር 12 በተአምረኛው በንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ይከብራል።
በእለቱም ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ሕዝቡን ይባርካል። ታቦተ ሕጉ ወደ መንበረ ክብሩ ከተመለሰ በኋላ፣ ከቅዳሴ መልስ ተአምረኛውና ብዙ ሰው የተፈወሰበት የቅዱስ ሚካኤል ማር ይታደላል፣ የቅዱስ ሚካኤል የዝክር በረከትም በሰፊው ይዘከራል።
ስለዚህ ህዳር 12 አርብ ተአምረኛው ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን መጥታችሁ ቅዱስ ሚካኤል እንድታከብሩ እንዲሁም የቅዱስ ሚካኤልን የዝክር በረከት እንድትቀምሱ፣ ተአምረኛውን ማር እንድትቋደሱ ቤተ ክርስቲያኗ ጥሪዋን ታስተላልፋለች!
#_አድራሻ :-
መገናኛ ከመጣችሁ በኋላ በቦሌ አራብሳ ታክሲ ተሳፍራችሁ ንቡ ሚካኤል አደባባይ ጋር ወርዳችሁ አጠገቡ ቤተ ክርስቲያኑ ይገኛል። ወይም አያት ሰንሻይን አፓርታማ ዝቅ ብሎ ይገኛል!
ከየትኛውም አቅጣጫ በመኪና እና በራይድ የምትመጡ አያት ሰንሻይን አፖርታማ ዝቅ ስትሉ ንቡ ሚካኤል አደባባይ አለ አጠገቡ ቤተ ክርስቲያኑ ይገኛል!
ቅዱስ ሚካኤል በእለተ ቀኑ በደጁ ለበረከት ያገናኘን!
ህዳር 8-3-2018 ዓ.ም
አዲስ ዝማሬ ''የፈቀድከው ይሁን'' #Hersolan#HeranandMenfesawi https://youtu.be/04gO-b0gyLI?list=RD04gO-b0gyLI
3ቱ ሁላችንም ማወቅ የሚገባን የአይነጥላ ክፉ መንፈስ ልዩ ልዩ ባሕሪና መገለጫዎች!! የአይነጥላ መንፈስን ለማሸነፍ እንዴት እንጸልይ? #አጋንንት #መናፍስት https://youtu.be/r2nGdmIWxo0
አርባዕቱ እንስሳ ህዳር_8 በዓላቸው መንፈሳውያን አመስጋኞችና መዘምራን የምትሆኑ አራቱ እንስሳት ስለ አኛ ለምኑ፤ አርባዕቱ እንስሳ መንፈሳውያን ሰባሕያን ወመዘምራን
ሰዐሉ በእንቲአነ
(አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ሰዓታት )
#_ኪሩቤል
🔥 ገጸ ሰብዕ
🔥 ገጸ አንበሳ
#_ሱራፌል
💥 ገጸ ላህም
💥 ገጸ ንስር
👉 ገጸ ሰብዕ ፦ ስለ ሰው ልጆች ይለምናል
ገጸ አንበሳ ፦ ስለ አራዊት ይለምናል
ገጸ ላህም ፦ ስለ እንስሳት ይለምናል
ገጸ ንሥር ፦ ስለ አዕዋፍ ይለምናል
( ሥንክሳር ኅዳር 8 ፥ ቁጥር 17 )
ቅዱስ ጄሮም እንዲህ አለ ፦
አርባዕቱ እንስሳት የድኅነታችን ምሥጢር የሆኑትን አራት ደረጀዋች ያስረዳሉ ።
ገጸ ሰብእ ፦ ሥጋዌውን ( ቃል ስጋ መሆኑን )
ገጸ አንበሳ ፦ ትንሣኤውን
ገጸ ላህም ፦ ንጹሕ መሥዋዕት ( ቤዛ ) መሆኑን
ገጸ ንሥር ፦ ዕርገቱን
አርባዕቱ አንስሳት
የጳጳሳት
የቀሳውስት
የዲያቆናት
የምዕመናን
( የቤተ ክርስቲያን አምድ እኚህ ናቸውና )
የእግዚአብሔርን ባሕርያት ያመለክታሉ።
ገጸ ሰብእ ፦ ጥበቡንና ዕውቀቱን
ገጸ አንበሳ ፦ ግርማውንና ኃይሉን
ገጸ ላህም ፦ ትዕግስቱን ፈታሒነቱን
ገጸ ንሥር ፦ ክብሩን ልዕልናውን
አንድም አርባዕቱ እንስሳት በአራቱ ወንጌላውያን ይመሰላሉ። “አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ክንፎች አሉአቸው፥ በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዓይኖች ሞልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም።” (ራእይ 4፥8)
አርባዕቱ_እንስሳት በእመቤታችን ድንግል ማርያም ይመሰላሉ። እነሱ መንበሩን ለመሸከም እንደተመረጡ፤ ሰማይና ምድር የማይችሉትን አምላክ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀኗ ተሸክማዋለችና።
ወርኃዊ መታሰቢያ በዓላቸው በ 8 ነው።
🙏🏽 በረከት ረድኤታቸው አይለየን 🙏🏽
(ዕብ.11፡33-38)
👉 እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ፥ የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥ ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ። ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤ ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤ በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።
+1
አባቶቼ እግዚአብሔር አምላካችን ረጅም ዕድሜን ይስጣችሁ። ከዚህ በላይ የምታገለግሉበትን ዘመን እግዚአብሔር ያድላችሁ። 🙏🙏🙏
ለጸሎታችን ምላሽ የማናገኘው ይኼንን ባለማድረጋችን ነው!! የስግደት መንፈሳዊ በረከቶችና ማወቅ የሚገቡን ነጥቦች!! ኃጢአተኝነት ክፋቱ ፈራጆች ያደርገናል!! https://youtu.be/c7WBnfNyaMQ
በመተትና በዛር አጋንንት መታደስ መከራ የምናየው ለዚህ ነው እንንቃ! አብሾ የአባቶቻችን ጥበብ እንጂ ጥንቆላ አይደለም! መናፍስትን ለማስወጣት እንዲህ ማድረግ! https://youtu.be/t2wl336zuRc
እጅግ አስደንጋጭ መረጃ በሴቶች እግር ኳስ ውስጥ ተጋለጠ እንጠንቀቅ! የእህቱን ድንግልና የወሰደው ወጣት አሳዛኝ ታርክ! የይቅርታ ልብ ያለው ሰው የታደለ ነው! https://youtu.be/aiW2ArzeH9c
3ቱ በጸሎት መዛልን ለማቆም የሚረዱ መምህር ተስፋዬ የራሱን ተሞክሮ ያጋራናል!! ያበዱና የአዕምሮ ዘገምተኛ ሰዎችን የሚፈውሱ ድንቅ አባት!! #ጸሎት #አጋንንት https://youtu.be/FM5y_G5dUvU
ኅዳር ፭/5/በዚች ቀን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ ጐኑን የወጋ የቅዱስ ለንጊኖስ ራሱ የታየችበት ነው:: ይህም ቅዱስ በጌታችን ካመነ በኋላ በቀጰዶቅያ አገር ወንጌልን የሚሰብክ ሆነ ከሀድያን አይሁድም በላዩ ተነሡበት በመኳንንት ዘንድ በሐሰት ወንጅለው በቀጰዶቅያ አገር ራሱን አስቆረጡት ራሱንም ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱዋት። በኢየሩሳሌም የሚኖሩም አይሁድ በአዩዋት ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ከዚህም በኋላ ከኢየሩሳሌም ከተማ ውጭ በአንድ ኮረብታ ላይ ቀበሩዋት። በቅዱሱ ስብከት ያመነች አንዲት ሴት በቀጰዶቅያ አገር ነበረች ራሱን ከቆረጡበት ጊዜ ጀምራ በተቆረጠበት ቦታ በመቆም ስለርሱ ታለቅስ ነበር የዚያች ሴት ዐይኖቿ ታወሩ። ከዚህም በኋላ ምናልባት ዐይኖቿ ቢገለጡላት በማሰብ ከከበሩ ቦታዎችና ክብር ይግባውና ከጌታችን መቃብር ለመባረክና ለመለመን ተነሥታ ልጅዋን ይዛ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች። ኢየሩሳሌምም በደረሰች ጊዜ በዚያ ልጅዋ ሞተ ኀዘንም ተጨመረባት ስለዚህም የመረረ ልቅሶን አለቀሰች ከኀዘኗም ብዛት የተነሣ ተኛች። ከዚህም በኋላ ቅዱስ ለንጊኖስን ከሞተው ልጅዋ ጋር በሕልሟ አየችው። ዕገሌ ከሚባልም ቦታ ሒደሽ ራሴን ከዚያ ውሰጂ አላት። ከእንቅልፍዋም በነቃች ጊዜ ስለዚያ ቦታ ጠየቀች ሰዎችም ወደርሱ አደረሱዋት። ያንንም ቦታ በቆፈረች ጊዜ መዓዛው እጅግ ጣፋጭ የሆነ የሽቱ መዓዛ ወጣ። ራሱ ወደአለችበትም ስትደርስ ታላቅ ብርሃን ተገለጠላትና ዐይኖቿም በዚያን ጊዜ ተገለጡላት እግዚአብሔርንም አመሰገነችው። ከዚህም በኋላ ከልጅዋ ሥጋ ጋር የቅዱስ ለንጊኖስን ራስ ወደ አገርዋ ወሰደቻት በታላቅ ክብርም ባማረ ቦታ አኖረቻት። #Subscribe #Like 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
ጸሎት እና የማይመች ሁኔታችን!
በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
ሼር በማድረግ ለሌሎች አጋሩ!
ተወዳጆች ሆይ ጸሎት ስትችሉ ሳይሆን ሳትችሉም ጸልዩ። ሲያማችሁ ብቻ ሳይሆን ጤነኛም ሆናችሁ ጸልዩ። ጸሎትን ሕመማችሁን ችግራችሁን ምክንያት አድርጋችሁ መተው ሳይሆን እንደአቅማችሁ ጸልዩ።
ጸሎት ሲመቻችሁ ሳይሆን ሳይመቻችሁም የምትጸልዩት ነው። ብዙ ሰዎች ቢዚ ነኝ አይመቸኝም እያሉ አይጸልዩም። ጸሎት ጊዜ ሲኖራችሁ ብቻ የምትጸልዩት ሳይሆን ጊዜም ሳይኖራችሁ ጊዜያችሁን አጣባችሁ የምትጸልዩት ነው። ለመብላት ጊዜ እንደማናጣ ለጸሎትም ጊዜ አናጣም።
በማይመች ሁኔታ ውስጥ፣ በሕመም ጊዜ፣ በተጣበበ ጊዜ፣ የሚጸለይ ጸሎት ጸሎት ብቻ ሳይሆን መስዋእትም ነው። ገድልም ነው!
አቡነ ኪሮስ ታመው ደም እየመታቸው ሕመማቸውን ችለው ይጸልዩ ነበር። በሕመም በስቃይ ውስጥ ሆነው ጸሎታቸውን አላቋረጡም ነበር።
አቡነ ተክለ ሃይማኖት እግራቸው ተቆርጦ፣ አጥንታቸው ተሰብሮ ደም እየፈሰሳቸው ይጸልዩ ነበር። ችግር ሕመም ፈተና የማይበግረው ጸሎት ትልቅ እና ጉልበት ያለው ጸሎት ነው። ስለዚህ እንዳቅማችሁ እና እንደ ሁኔታችሁ ጸልዩ!
"የባርያህን ጸሎትና ልመናውን ስማ" ት.ዳን 9፥17
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
** "መንፈሳዊ ውጊያችን መጀመሪያ የሚካሄደው በልባችን ቅጥር ውስጥ ነው። ቅዱስ እንጦንስ (St. Anthony the Great) 'የሰው ልጅ ሀሳቡን ቀድሞ ካልገዛው፣ በኀጢአት ይወድቃል' በማለት ይመክራል። እንደ ንቁ ጠባቂ ሁን፤ እያንዳንዱን ወደ ልብህ የሚገባን ሃሳብ መርምር። ክፉ ሃሳብ እንደ እባብ ጭንቅላቱ ሲነሳ በጸሎትና በእምነት ወዲያውኑ ደምስሰው። በንቃትህና በልብህ ንጽሕና ዘወትር ጠንክር።"
** "ትዕቢት ከሁሉ ቀድሞ በነፍስህ ውስጥ የሚነሳ ገዳይ በሽታ ነው። የሌላውን ሰው ጉድለት ለመፈተሽ አትጣር፤ ይልቁንስ የራስህን የነፍስ ቁስል መመልከት ይበልጣል። ቅዱስ ዮሐንስ መምህሩ (St. John Climacus) 'ትሑት የሌላውን ሰው ስህተት አያይም' ይላል። ራስህን ዝቅ ባደረግህ መጠን፣ ከእግዚአብሔር የሚመጣው ጸጋ ከፍ ያደርግሃል። የራስህ ነፍስ ፈራጅ ሁን፤ የሌላው ሰው አትሁን፤ በዚህም የውስጥ ሰላምህን አግኝ።"
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
