ch
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

前往频道在 Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

显示更多
2 280
订阅者
无数据24 小时
+77
+3930
帖子存档
መንፈሳዊ ውጊያን ከጀመርን በኋላ ወጣ ገባ ማለትን እንዴት እናስቀር? || ጸሎትና ስግደትን ጀምሮ ማቆም || የመንፈስ ዝለትን እንዴት እንከላከል? #ebs 💥🚩 https://youtu.be/CwxHqcY-7Ww

«እግዚአብሔር ያልተቀየማቸው ተጠራጣሪዎች» ◈ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ አለ አረጋዊው ስምዖን "እነሆ ድንግል ትጸንሳለች" የሚለውን ትንቢት ተጠራጠረ፤ ይህ ጥርጣሬው ግን በደል ሆኖ አልተቆጠረበትም ይልቁንም ስሙ አማኑኤል የተባለውን ሕፃን ለማቀፍ አበቃው እንጂ፡፡ "ወኢተኈልቈ ሎቱ ኑፋቄሁ ኀበ ጌጋይ አላ አብጽሖ ኀበ ሑቃፌ ሕፃን ዘስሙ አማኑኤል" ◈ ቶማስም የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠረ፤ ትንሣኤውን መጠራጠሩ ግን የጌታን ጎን ለመዳሰስ በችንካሩ እጁን ለማስገባት አበቃው፡፡ => "ወአብጽሖ ኑፋቄሁ ኀበ ገሢሠ አጽልእቲሁ ለመድኃኔ ዓለም" => በእውነት "መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው" እግዚአብሔር የወደደው ሰው ቍስሉ አይመረቅዝም በደሉም አይታሰብም፡፡ (መዝ 32፥1) ◈ ጌታ ሆይ እኔንም ስለ መጠራጠሬ አትቀየመኝ ልደትህን የተጠራጠረው ስምዖንን እንዲያቅፍህ ፈቀድክለት፤ ትንሣኤህን የተጠራጠረውን ቶማስ ጎንህን አስነካኸው፤ ያኛው "ዓይኖቼ ማዳንህን አዩ" ብሎ ዘመረልህ ይኼኛው ደግሞ "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ መሰከረልህ፡፡ ጌታ ሆይ እኔ እምነተ ቢሱንም መጠራጠሬን አትመልከትብኝ፤ የሚዋዥቅ ሕሊናዬን አጽናልኝ እንደዚያ የልጅ አባት "አለማመኔን እርዳው" እንደ ጴጥሮስ "ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ" በመጠራጠሬ አትቀየመኝ፡፡ ◈ መጠራጠሬን አይተህ አትቀየመኝ፤ አንድ ትቢያ ቢጠራጠርህ እንደማይጎድልብህ አውቃለሁ፤ ስለዚህ ራርተህ እምነትን አድለኝ፤ ምናለ ለእኔም ማዳንህን አይቼ እስካምን እንደ ስምዖን ዕድሜ ብትጨምርልኝ? መቼም ላንተ ዘመን አይቸግርህም፤ ሺህ ዓመት ለአንተ አንድ ቀን አይደለች? ቢያንስ አምኜ አሰናብተኝ እስክልህ እስከ ቀትር አቆየኝ፡፡ አንተን በእምነት እንዳቅፍህ እርዳኝ እንጂ ስምዖን አሰናብተኝ እንዳለህ እኔም ደስ ብሎኝ አርፋለሁ፤ ማዳንህን ሳልረዳ፣ አንተን በእምነት መዳፍ ሳላቅፍህ መሞትን ግን እፈራለሁ፡፡ ◈ "አምላኬ ጌታዬ" ብዬ ብዘምርም እንደ ቶማስ ካልዳሰስሁህ ሰውነቴ በእምነት አይኮማተርም፤ ተጠራጣሪውን የማትንቀው ሆይ ጥያቄው የማያባራ ልቤን ጥርጣሬው የማያልቅ ከንቱ ሕሊናዬን እንደ ቶማስ ራራለት፤ ለእኔ የቆሰልከውን ቁስል በእምነት መዳፍ ካልነካሁ ፤ እጄን ከችንካርህ ካላገባሁ የፍቅርህ ጥልቀት አይሰማኝምና እባክህን "ና ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን" በለኝ፡፡ ◈ ሳላውቅህ የኖርኩት ጌታዬ ሆይ እንደዚያ መቶ አለቃ "ለካስ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ" ብዬ ሳልመሰክርልህ አልሙት፤ እንደ ሌንጊኖስ ወግቼህ በፈሰሰው በጎንህ ውኃ ዓይኔን አብርተህ ካለማመን ብታወጣኝ ምናለ? ያላመኑትን የማትንቀው ሆይ ተጠራጣሪዎችን ያልተቀየምከው ሆይ የሚጠራጠርህን ልቤን አትቀየምብኝ፤ የሚያስብ የሚጠይቅ አእምሮ ሠጥተህ ለምን ተጠቀምክበት ብለህ አትቀየምምና ስምዖን አቀፈህ ቶማስም ዳሰሰህ። ◈ ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።" (ኤፌ 4፥29) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የለቅሶ ሥርዓታችንና ማወቅ ያለብን ነገሮች || ጠበል ተጠሚቀ ዳንኩ ስትሉ ያሾፋሉ || መተትና አጋንንት በእኛ ኑሮ || የአቡነ ናትናኤል መልዕክት #ebs 💥🚩 https://youtu.be/ZLXbat2kbrM

«ይኼ የሁላችን ጥያቄ አይመስላችሁም!» ◈ ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ ያቃተው አንድ ደቀ መዝሙር አረጋዊውን አባት እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል => "አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፤ አፌ ቢያነበውም ልቡናዬ ግን ይበታተናል፤ እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው ቅዱሳን በፍጹም ሐሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የጻፉትን እኔ በልቤ ሌላ እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደ ገደል ማሚቶ ፊደሉ አፌ ላይ እየነጠረ ይሄዳል እንጅ ጸሎትም አይሆንልኝም፤ ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?" ብሎ ጠየቃቸው። ◈ አረጋዊው አባትም እንዲህ ሲሉ አስረዱት => "አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምጽ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጅ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም፤ ስለዚህ አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ ያለው የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው፤ አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና፤ ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች። ◈ እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ይህንንም እንዳታቆመው፤ አሁን አንዱን ይዘህ ወደፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማገናኘት መጣር ይኖርብሃል እንጅ አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫወቻ እንዳትሆን። ስለዚህ ሁላችንም ለጸሎት መትጋት አለብን ማለት ነው። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ለኩነኔ የማያበቃ የኃጢአት ትንሽ ባይኖረውም መሠረትነታቸውን ለመናገር ያህል አበው ሦስቱ አርእስተ ኃጣውኡ (የኃጢአት ታላላቆች) ሲሉ የሚጠሯቸው አበይት የሰይጣን ፈተናዎች አሉ። ስስት፣ ትዕብትና ም
«ለኩነኔ የማያበቃ የኃጢአት ትንሽ ባይኖረውም መሠረትነታቸውን ለመናገር ያህል አበው ሦስቱ አርእስተ ኃጣውኡ (የኃጢአት ታላላቆች) ሲሉ የሚጠሯቸው አበይት የሰይጣን ፈተናዎች አሉ። ስስት፣ ትዕብትና ምቾት (ፍቅረ ንዋይ) ይባላሉ። ዓይነተ ብዙ የዲያብሎስ ውጊያዎችን ሰብስበን ብንደምር ብንቀንስ ከነዚህ ከሦስቱ አይወጡም። በዚህ የተነሣ በነዚህ ፈተናዎች ድል የተነሣ የተቀሩትንም ማሸነፍ እንደማይቻለው ይነገራል። ስግብግብነት ያስቸገረው፣ ትሕትና የጎደለው፣ ድሎት ደስ የሚለው ሌሎች ጥፋቶችን ማጥፋት አይሆንለትም ነው ብሂሉ። ለምሳሌ ዝሙትና ቅንጦት ይዋደዳሉ፤ የስንፍና እጮኛ ሆድ ናት፤ ዕብሪትና ንስሐ ተግባብተው አያውቁም። አንቺ ማስተዋል የሚሉሽ ሆይ፥ አንዴ ነይማ እዚህ ትፈለጊያለሽ!። በማለዳ ንቁ! እንንቃ!» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በትዳራችሁ ሰላም ያጣችሁ አዳምጡ! || 3ቱ የዛር መንፈስ መግቢያ መንገዶች | ትዳርን በመስተፋቅር ለመያዝ መሞከር | አደገኛው የሰይጣን መንገድ #ebs 🚩💥😱 https://youtu.be/l45FG06STW0

«በጠባብ በር ለመግባት እንታገል፣ ዛፎች በክረምቱ የዝናም ውሽንፍር ውስጥ ጸንተው ካላለፉ በስተቀር ፍሬ ሊያፈሩ እንደማይችሉ ሁሉ፣ በእኛም እንዲሁ ነው፣ ይህ የአሁኑ ዘመናችን የውሽንፍርና የማዕበል ጊዜ ነው፤ ስለዚህም መንግሥተ ሰማይን ለመውረስ የምንችለውን በብዙ ፈተናዎችና ውጣ ውረዶች በኩል በማለፍ ነው።» (እማሆይ ቴዎድራ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የዲያብሎስ 3ቱ ዋና ዋና ተንኮሎች || በፓርስ የታየው አጋንንታዊ ሴራ || አስቀዳሽ ነን ግን ያልተቀደስን || መጋኛ ወይም ልክፍት ምንድነው? #ebs 💥🚩😱😭 https://youtu.be/3y6UwdUVFdg

ለጸሎት ከመቆማችን በፍት ማድረግ ያለብን ነገሮች በጸሎት ሰዓት የዲያብሎስ ውጊያ መስተፋቅርና የትዳር ጣጣ || የቅዱስ ገብርኤል ተዓምር #ebs 😱💥🚩 https://youtu.be/q4UsH8yXJxo

✨ ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት የስሙ ትርጓሜ ☀️ አግዚአብሔር ብርሃኔ ነው ። ☀️ የእግዚአብሔር ብርሃን ማለት ነው። "ጌታ ስለ ሰማይ ሠራዊት ለእኔ ያዘዘልኝ መልአኩ ዑርኤል ስለ ብርሃናት እና ወሮ
✨ ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት የስሙ ትርጓሜ ☀️ አግዚአብሔር ብርሃኔ ነው ። ☀️ የእግዚአብሔር ብርሃን ማለት ነው። "ጌታ ስለ ሰማይ ሠራዊት ለእኔ ያዘዘልኝ መልአኩ ዑርኤል ስለ ብርሃናት እና ወሮች ፣ስለ በዓላት ፣ ስለ ዓራቱ ክፍለ ዘመኖች እና ዓመታት ፤ ስለ ቀኖችም አሳየኝ ፤ እውቀትንም አሳደረብኝ ፤ 🙏🏽 እርሱም በሰዎች ላይ በሰማይ የፀሐይን እና የጨረቃን ፤ የከዋክብትንም በክበባቸው የሚመላለሱ የሰማይ ሠራዊትንም ሁሉ ብርሃን ያሳይ ዘንድ ፤ በመዓልት እና በሌሊት ሥልጣን አለው " ☀️ (መጽሐፈ ሄኖክ 28 ፥ 12 13 ) ☀️ ༺◉❖═─◉●◉ ✨ ◉●◉──═❖◉༻ 🍂 " #ሊቀ_መላዕክት_ዑራኤል_አባት ፀበልህም ያድናል በእውነት በምልጃህ ያመኑ በሙሉ ባንተ ይድናሉ..." + #ዑራኤል ሆይ ለእጆችህ ጣት ሰላም እላለሁ + በጣጦችህ ጫፍ ላይ ለሚያንጸባርቁ ጽፍሮችህም ሰላም እላለሁ ። + + + + + #ዑራኤል ሆይ የምስጋና ለውዝ ገውዝ የያዝህ ነበልባለዊ ሙሽራ እንደመሆንህ #ከአንተ_ዘንድ_ከሚመነጭ_ዕዝራ_ከጠጣው_ጽዋ ለእኛም የጥበብ የማስተዋልን የሰላም የአንድነትን የፍቅር የመተሳሰብን ጽዋ አጠጣን 🙏 + + + #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የእምነት ኃይል ሲገለጥ ክፉው ትውልድ ተንጫጫ ቅዳሴ የክርስትያኖች ደስታ ነው ክፉኛ መጨነቅና ፈተናዎቹ #ebs #ethiopia መምህር ግርማ 😱💥🔥🚩🚩 https://youtu.be/Vy1NGcsY8X8?si=s6AqON7aAZwgMRqm

የሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ድንቅ ተዓምርና ምስክርነት 🙏 Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! https://youtube.com/live/MHry8Vr6NIQ?feature=share

በጸሎት፣ በጾም፣ በስግደት መወሰንና አጋንንትን መቃወም መናፍስት አዕምሮአችንን ስቆጣጠር ሦስቱ የደፈረሱ ምንጮች | መምህር ግርማ ተስፋዬ አበራ 💥🔥🚩 https://youtu.be/DnbTxdpn6OA?si=4T7NEfAsxApFHNRD

«ወንድሜ እኔ ደና ነኝ አሁን ላይ ቀልቤን እየሰበሰብኩ ነው፡ ከልቤ አመሰግናለው፡ ንስሃ ገብቻለው የረሳኋቸውን ሃጥያቴን እያሰብኩ ለመጻፍና ለነብስ አባቴ መናዘዝ እንዳለብኝ በጣም ገብቶኛል፡ ብዙ ዘመኔን በሃጥያት ተዘፍቄ ሃጥያት ኖርማል ህይወቴ ሆኖ የኖርኩ ሰው ነኝ እናም የትኛው ትክክል የትኛው ደግሞ ሃጥያት እንደሆነ እንኳን ተስኖኛል፡ ለእኔ ሃጥያት ሰው መግደል ወይም መስረቅ ብቻ ነበር የሚመስለኝ ግን ተሳስቻለው ክርስቶስ የሚጠላውን ስፈጽም ነበር የከረምኩት፡ ዛሬ ግን ክርስቶስ በምህረቱ እኔ አስቦኝ ይህው ንስሃ አባትም ይዣለው፡ ይሄ ክብር ለእኔ የሚገባኝ ሆኖ አይደለም ግን በቃ ክርስቶስ ስለሚወደኝ ብቻ ነው፡፡ ወንድሜ እንዳንተ መልካም ልብ ያላቸውን ወንድሞችና እህቴች ባርኮኛል ሲጨንቀኝ የምሄድባቸው እናም ክርስቶስን አመሰግነዋለው እናንተንም ከልቤ አመሰግናለው ምንም ክፉ አይንካችሁ፡ ወንድሜ የተቸገሩትን መርዳት ያልከው ነገር ትክክል ነው እንደውም ፈተናው የሚበዛብኝ ልክ የሆነ የበረከት ስራ ላይ ስሳተፍ በቃ ከ4ቱም ማዕዘን ይላክብኛል፡ በፊት በፊት አለቅስ ነበር ለምን ብዬ ዛሬ ላይ ግን የነብስ አባቴ ስለድያብሎስ ክፉ ስራ በደንብ ስላስረዱኝ ነቅቻለው፡፡ ታውቃለህ ወንድሜ እኔ ብዙ አልጸልይም ግን ጸሎት ስጀምር ከየት አባቱ እንደሚመጣ አልውቅም ማልቀስ ብቻ ይሄ ነገር ግራ ገብቶኝ ለነብስ አባቴ ነገርኳቸው፡ ገና ግንባሬ መሬቱን ሲነካ በቃ እዬዬዬዬዬ ነው፡ ወንድሜ በጸሎትህ አኑረኝ፡ አንዳንድ ሊጠቅሙኝ የሚችሉ መጻህፍቶችን ጠቁመኝ፡ አንድ መልካም በክርስቶስ ያገኘሁት ወንድም የመምህር መጽሃፍ እንድገዛ ነገረኝ እናም አስመጣሁ፡ የሚገርም ነገር ነው ውስጡ ያለው በእውነት የኢትዮጵያ ወላጆችና ወጣቶች ሊያነቡት የሚገባ መጽሃፍ ነው፡ ይሄንን ነገር ከ10አመት በፊት ተምረን ወይም አውቀነው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ላይ የልጅነታችንን ክብር አናጣውም ነበር ህይወታችንም አይመሰቃቀልም ነበር። ወንድሜ እስኪ አንተ ለጸሎት የምትጠቀማቸውን ወይም አጋዥ የምትላቸውን መጻህፍቶች አጋራኝ።»

◈ ወጣቶች ባለ አቅማችሁ ሁሉ ቤተክርስትያንን ማገልገል አለባችሁ፤ ቤተክርስቲያን እናታችሁ ናት በመሆኑም በተለየ ሁኔታ ልትንከባከቡአትና ልታከብሯት ይገባል፤ ቤተክርስቲያናችሁን ትናንት የነበሩ፣ ያሉ
◈ ወጣቶች ባለ አቅማችሁ ሁሉ ቤተክርስትያንን ማገልገል አለባችሁ፤ ቤተክርስቲያን እናታችሁ ናት በመሆኑም በተለየ ሁኔታ ልትንከባከቡአትና ልታከብሯት ይገባል፤ ቤተክርስቲያናችሁን ትናንት የነበሩ፣ ያሉ አባቶቻችን ውደዱ ፈፅሞ አትርሷቸው። ወጣቶች የቤተክርስቲያን የጀርባ አጥንቶች ናቸው፤ ትውፊታዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የሕይወት መንገድ ሲያያዝ የመጣ የወንጌል መገለጫ ነው፤ ሃይማኖታችሁ በደማችሁ ውስጥ ናት፤ ለሃይማኖታችሁ ብርቱ ጥንቃቄ ልታደርጉና ለቀጣዩ ትውልድ ልታሸጋግሩአት ይገባል። መንፈሳዊ ተልእኮአችሁን ከዕለት ተግባራችሁ ጋር ልታጣጥሙና ትጋትያላችሁ የቤተክርስቲያን አባላት ልትሆኑ ይገባል፤ ክርስትና ከቃላት ይልቅ በተግባር መገለጽ አለበት፤ ይህም ማለት ከመናገር ይልቅ ማድረግ መሥራት ማለት ነው፤ ሰዎች ሥራችሁን አይተው በምሳሌነት እንዲከተሉአችሁ የክርስቲያ አርአያ ሁኑ፤ ሀብታሞች ይሁኑ ድሆች ለሰዎች ክብር ስጡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ራሱን የሚገልጠው በእነርሱ ውስጥ ነው። በረከታቸው ይደርብን እውነት! #ሸር አድርጉ! (ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በረከትን ለማግኘት አጋንንትን ለማራቅ ማድረግ ያለብን | የክፉ መናፍስት ውጊያ ያለባችሁ | አብሮን ተወልዶ ያደገ አጋንንት! የስፓርተኞች የአጋንንቱ ዓለም 🔥💥 https://youtu.be/M5L_znvrd_k

"በሕይወትህ በረከት እንዲበዛልህ አመስጋኝ ሁን" ◈ በሕይወታችን ብዙ ልናሟላቸው የምንፈልጋቸው ነገሮች ይኖራሉ፤ ጠቢቡ ሰለሞን  መጽሐፈ መክብብ ላይ ሲናገር => "ፈሳሾች ሁሉ ወደ ባሕሩ ይሄዳሉ ባሕሩ ግን አይሞላም" ይላል። (መክ 1፥7) ይህም ምን ቢሰጠው የትኛውም ያህል ቢትረፈረፍለት የሰው ልጅ ምኞትና ፍላጎት ማለቂያ የለውምና፤ እኛም ገንዘብ፤ ስራ፤ ፍቅር፤ ዝና፤ ስልጣን፤ በምኞት ቋጠሯችን ውስጥ ካካበትናቸው ጥቂቶቹ ናቸው። መመኘቱ ባልከፋ ነገር ግን ብዙዎቻችን የሌለንን ስንመለከት ያሉንን ነገሮች ዓይን እንነፍጋቸዋለን ስለዚህ መጠየቅ እንጂ ማመስገን ይሳነናል፤ በዚህም ሁልግዜ ጠያቂዎች እንጂ አመስጋኞች አይደለንም። ልብ በሉ ምኞቶቻችን ሁሉ ሊሳኩ የሚችሉት ባለን ነገሮች መጀመሪያ መደሰት እና ማመስገን ስንጀምር ነው። ◈ ለምሳሌ፦ አንድ ወዳጃችን በችግራችን ደርሶ ረዳን እንበል፤ ላደረገልን እርዳታ ምስጋና ካልሰጠነው እንዴት ብሎ በሌላ ችግራችን ይደርስልናል፤ አምላካችን እግዚአብሔርም ላደረገልን ነገር ባመሰገንነው ቁጥር ሌሎች ልመናችንን ሰምቶ በበረከት ላይ በረከት ያትረፈርፍልናል። ስለዚህ ሁልግዜ አመስጋኝ አንደበት ሊኖረን ይገባል፤ ነገር ግን በምስጋና ፈንታ “በቂ ገንዘብ አላገኝም”፤ “ኑሮዬ ምስቅልቅሉ የወጣ ነው” ፤ “መልካም የትዳር አጋር አላገኘሁም”፤ “ስኬታማ አይደለሁም” "እግዚአብሔር አይሰማኝም" የምንልና የምንማረር ከሆነ ያለንን ነገሮች እንዳናይ ከማድረጋቸውም በላይ በረከታችንን የማራቅና ያለንም በረከት ልናጣና ልንነጠቅ እንችላለን። ◈ ብዙዎቻችን ግን ይህንን አንረዳም፤ ለደቂቃ ልቦናችንን ሰብስበን ካስተዋልነው እያንዳንዶቻችን በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እንኳን፤ ልናመሰግን የምንችልበት ብዙ ምክንያቶች አሉን፣ እንደው ዋጋቸውን እያራከስን ነው እንጂ እያንዳንዶቻችን ሌሎች የሚመኟቸው ነገሮች እኛ ጋር ዋጋ አጥተው ተቀምጠዋል። ለምሳሌ፦ የአልጋ ቁራኛ የሆነ ሰው በህይወቱ የሚመኘው ነገር ሙሉ ጤንነትን ሆኖ ሳለ፤ ጤነኛው ሰው ግን ስላለው ጤና አለማመስገኑ አይገርምም፤ ካስተዋልነው አንዲት ቃል ህይወታችንን በርግጥም ትለውጣለች። ◈ "ለጠቢብ ሰው አንዲት ቃል ይበቃዋል ይባል የለ" (ማቴ 25፥29) => "ላለው ሁሉ ይሰጠዋል ይበዛለትማል…. ለሌለው ግን ያው ያለውም እንኳን ይወሰድበታል” የሚለው ቃል የሚያስረዳን ሁላችንም ለተሰጠን ማንኛውም መክሊት መጀመሪያ ምስጋና እናቅርብ ያኔ…ሌሎች በረከቶቻችንን፣ ይመጣሉ።" እግዚአብሔርንም ስለሰጠን ነገር ሁሉ ካመሰገንነው ባለን ላይ ሁሉ ለመጨመር አያመነታም። ልዑለ ባህሪ ህያው እግዚአብሔር በያላችሁበት ይጠብቃችሁ፤ ይጠብቀን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መሻታችሁን፣ አሳባችሁን፣ አላማችሁን፣ ዕቅዳችሁን ይሙላላችሁ። እግዚአብሔር አምላካችን ስለ ቅዱስ ገብርኤል ብሎ በእውነት ይማረን፣ ይቅር ይበለን። እንኳን አደረሳችሁ ቤተሰቦቼ።
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መሻታችሁን፣ አሳባችሁን፣ አላማችሁን፣ ዕቅዳችሁን ይሙላላችሁ። እግዚአብሔር አምላካችን ስለ ቅዱስ ገብርኤል ብሎ በእውነት ይማረን፣ ይቅር ይበለን። እንኳን አደረሳችሁ ቤተሰቦቼ። ሐምሌ 19 🙏🙏