ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 399 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 564,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 183

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 399 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 21,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.61%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.23% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 327 次浏览,首日通常累积 1 576 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 399
订阅者
+124 小时
+307
+2130
帖子存档
በጉባኤው መጨረሻም:- 1.አልመለስም በማለቱ አርዮስን አወገዙ:: 2.ጸሎተ ሃይማኖትን "ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም" እስከሚለው ድረስ ተናገሩ:: 3.ፍትሐ ነገሥትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብለው አዘጋጁ፡፡ 4.ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንደሚገባ አደራጁ፡፡ 5.በስማቸው የሚጠራ አንድ ቅዳሴን ደረሱ፡፡ ፠ይህ ሁሉ ሲሆን መድኃኒታችን ክርስቶስ 319ኛ ሆኖ እና ገሊላዊ ዻዻስን መስሎ ሁሉን አከናውኖላቸዋል:: አባቶችም ሥራቸውን ከጨረሱ በሁዋላ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስን ባርከው ወደየ ሃገረ ስብከታቸው ተመልሰዋል፡፡ ፠በየዘመኑም ዐርፈው ለክብረ መንግስተ ሰማያት በቅተዋል:: እኛም እነሆ "አባቶቻችን: መምሕሮቻችን: መሠረቶቻችን: ብርሃኖቻችን: ምሰሶዎቻችን" እያልን እናከብራቸዋለን:: =>318ቱ ቅዱሳን ሊቃውንት በጸሎታቸው እኛንም: ቤተ ክርስቲያናችንንም ከክፉ ጠላት ይጠብቁልን:፡፡ በረከታችው ምልጃቸው አይለየን ፡፡ ------------------------------- የቤተ ክርስቲያኑ ፎቶ፤ ሐመረ ኖኅ ሠለስቱ ምዕት ቤ.ክ፤ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና በአሁኑ ሰዐት ከ4ቱ የመጻሕፍት ጕበኤያት በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ የሆነ ነው፡፡ ፠ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና ከ1700-1701 ዓመታት በፊት በአፄ ቴዎፍሎስ (ስመ መንግሥት አጽራር ሰገድ) ታንጾ የነበረ ሲኾን ንጉሡ ሲያንጹትም የሠለስቱ ምዕት የአእላፍ መላእክትና የነቢያት ቤተ ከርስቲያን አድርገው ነው፤ ድርቡሽ ጎንደርን በ1880 በወረረ ጊዜ ጠፍ ኹኖ ቆይቶ በ2007 ዓ.ም. ቤተ ክርስቲያኑ ድጋሚ ተሠርቷል፤ ፠ ይህ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ጕባኤ ቤትም ሲኖረው፤ ቀድሞ የ4ቱ ጕባኤያት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ቆይቷል፤ ከአፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ይገኛል፡፡ እጅግ የሚገረመው ደግሞ ደብረ ሲመሠረት ያገለግሉ የነበሩት ካህናት 318 መሆናቸው ነው እኚህም በሥነ መለኮትን ት/ት እጅግ ሊቅ የሆኑ ሲሆን መጻሕፍትን በመተርጕም እና ምሥጢር በመግለጥ አገልግለዋል በዙ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል ፡፡ ፠ በ900 ዓ.ዓ አካባቢ ከቀዳማዊ ምኒልክ ጋር የመጡት የብሉይ ኪዳን መምህራን ቁጥር 318 መሆኑን መጻሕፍት ይናገራሉ ፡፡እነዚህም ወንጌል እና ግዕዝ ቋንቋን ያስፋፉ ናቸው፡፡ ኦሪትም በሕዝቡ ልቡና እንዲቀር ያደረጉ ፣ መጻሓፍትንም ( ከዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ )በመተርጐም አስተዋጾ ያደረጉ ናቸው ፡፡፡፡የኦሪቶቹ 318 ሊቃውንት ከአዲስ ኪዳኖቹ ሊቃውንት ቁጥር ጋር እኩል መሆናቸው እጅግ የሚያስገርም ታሪክ ነው ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like Facebook (https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool)

ኅዳር ፱ 9፤ የሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ክብረ በዓል ነው፡፡ በዚህችም ቀም ዳግመኛ የሦስት መቶ ዐሥራ ስምነት ኤጲስ ቆጶሳት ሊቃውንት ስብሰባ በኒቅያ ከተማ በጻድቅ ንጉሥ በቈስጠንጢኖስ ዘመን ሆነ ፡፡ " ፠የተሰበሰቡበትም ምክንያት የሊብያው ሰው አርዮስ በእስክንድርያ በቄስነት ሲያገለግል ጌትነት ገንዘቡ የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን‹‹ወልድ በመለኮቱ ፍጡር ነው ብሎ ›› ክዷል ከዚያም: በጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጥሪ: 2348 ምሑራን ከመላው ዓለም ተሰበሰቡ:: ፠ጥሪው የተላለፈው በወርኀ ሚያዝያ ሲሆን በመንገድ ችግር ሁሉም ተጠቃለው ኒቅያ የገቡት መስከረም 21 ቀን ነበር (በዚችም ዕለት በዓላቸው ይታሰበል ) :: ከተሰበሰበው ብዙ ሰው መካከል የአበውን ደቀ መዛሙርት ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና: ምግባራቸው የጸና 318ቱ አበው ሊቃውንት ተገኙ:: ፠እነዚህ አባቶች 'ሊቃውንት' ሲባሉ እንዲሁ በእውቀት ብቻ የበሰሉ እንዳይመስሉን:: 318ቱ አበው እኩሎቹ በዘመነ ሰማዕታት እጅና እግራቸውን የተቆረጡና ለሃይማኖታቸው ብዙ ዋጋ የከፈሉ ናቸው:: ፠እኩሎቹ ደግሞ በገዳማዊ ሕይወት ያጌጡ: ፍቅረ ክርስቶስ በውስጣቸው የሚነድ: የመንፈስ ቅዱስ ቤት ናቸው:: የጥቂቶቹ 1.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ (በዓሉ በደብራችን ደብረሰላም የሚከበር(ነሐሴ 24) (በዘመነ ሰማዕታት ለ22 ዓመት ሲቆራርጡት ኖረው በጉባኤው ላይ የተገኘው ያለ እጅ: እግር: ጀሮ: ከንፈር: ቅንድብ ነው) ስለ ቅዱስ ቶማስ እዚህ አነብብ https://t.me/medihanaelem/6993 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool/posts/2985127341805344 2.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ (ስለ ቀናች እምነት ለ50 ዓመታት የተጋደለና ለ15 ዓመታት በስደት የኖረ ነው) 3.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ሊቅ (ከሰማይ ብርሃን ይወርድለት የነበረ አባት ነው) 4.ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ (በጸሎቱ አጋንንትን ያንቀጠቀጠ: ነፍሳትን ከሲዖል የቀማና ከከዊነ እሳት የደረሰ አባት ነው) 5.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ (ስለ ቀናች እምነት መጸዳጃ ጉድጉዋድ ውስጥ ለ15 ዓመታት ተጥሎ የኖረ ሰማዕት ነው) 6.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሜራ (ከሕጻንነቱ የተቀደሰ: በበርሃ የተጋደለ: በዘመነ ሰማዕታት ብዙ መከራን የተቀበለ አባት ነው) 7.ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን (በደግነቱ ሙታንን ያስነሳ: ወንዝን በጸሎቱ ያቆመ: በንጽሕና የተጋደለ አባት ነው) 8.ቅዱስ ሶል ዼጥሮስ (ቅዱሱን ንጉሥ ያጠመቀ: ቁስጥንጥንያን በወንጌል ያበራ ሊቅ ነው) 9.ቅዱስ ኤዎስጣቴዎስ (ስለ ቀናች እምነቱ ብዙ ግፍ የደረሰበትና በስደት ያረፈ አባት ነው) ፠ለአብነት እንዲሆኑን እነዚህን አነሳን እንጂ 318ቱም ሊቃውንት ስለ ቤተ ክርስቲያን ተግተው የተጋደሉ: ብዙ ዋጋም የከፈሉ አባቶች ናቸው:: ፠በወቅቱ ታዲያ ቤተ ክርስቲያንን የበጠበጡ ብዙ መናፍቃን ቢኖሩም የአርዮስ ግን ከመጠኑ አለፈ:: የእርሱ ኑፋቄ (ፈጣሪያችንን ፍጡር ነው ማለቱ) መነሻው ከእርሱ በፊት ነው:: መናፍቃን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ቤተ ክርስቲያንን ሲያውኩ መኖራቸው ግልጽ ነው:: ፠በተለይ ደግሞ ቢጽ ሐሳውያንና ግኖስቲኮች የወለዷቸው እሾሆች አባቶቻችንን እንቅልፍ ነስተው ነበር:: የሚገርመው በዘመኑ እንደ ነበሩ መናፍቃን ኃይለኝነት የእኞቹ ከዋክብት ሊቃውንት ባይኖሩ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ያሳስብ ነበር:: ፠ግን እግዚአብሔር ለሁሉ እንደሚገባ ያዘጋጃልና አበው ብርቱ መናፍቃንን በብርቱ መንፈሳዊ ክንድ እያደቀቁ ከጐዳና አስወገዷቸው:: የዛሬውን ደካማ ትውልድ ደግሞ የአርዮስ ልጆች 2 (3) ጥቅስ ይዘው ሲያደናብሩት ይውላሉ:: ፠ሐረገ መናፍቃን በርጉም ሳምሳጢ ዻውሎስ: በመርቅያንና በማኒ ይጀምራል:: በእርግጥ አርጌንስ እና የግብጹ ቀሌምንጦስም ተቀላቅለዋቸዋል:: ርጉም ሳምሳጢ ድያድርስን በኑፋቄ ወልዶታል:: ድያድርስ ሉቅያኖስን: ሉቅያኖስ ደግሞ አርዮስን ወልደዋል:: ፠ይህ አርዮስ እጅግ ተንኮለኛ በመሆኑ ልክ እንደ ዘመኑ መሰሎቹ ግጥምና ዜማ እየጻፈ በየመንገዱ እያደለ: በየቤቱ እየሰበከ ብዙዎችን በኑፋቄው በከለ:: በመጀመሪያ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ዼጥሮስ (አስተማሪው) መከረው:: ባይሰማው ከአንዴም ሁለት ጊዜ አወገዘው:: ፠ቆይቶ ሰነፉ ዻዻስ አኪላስ ቢፈታውም ሊቁ ቅዱስ እለእስክንድሮስ እንደ ገና አወገዘው:: እንደ አርዮስ ሐሳብ መድኃኒታችን ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ አይደለም (ሎቱ ስብሐት!!!) ማለት ክርስትናን ከሥሩ ፈንቅሎ መጣል ነው:: ፠ስለ ክርስቶስ እግዚአብሔርነት ብሉይም ሐዲስም እየመሰከሩ (ኢሳ. 9:6, መዝ. 46:5, 77:65, ዘካ. 14:4, ዮሐ. 1:1, 10:30, ራዕይ. 1:8, ሮሜ. 9:5) አርዮስና የዛሬ መሰሎቹ አንዲት ጥቅስ ይዘው ክርስትናን ከመሠረቱ ለመናድ መሞከራቸው በእርግጥም ከሰይጣን መላካቸውን ያሳያል:: ፠በወቅቱም በመወገዙ 'ተበደልኩ' ብሎ የጮኸው አርዮስ ከ2ቱ አውሳብዮሶች ባልንጀሮቹ (ዘቂሣርያና ዘኒቆምድያ) ጋር ሆኖ ወደ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሔዶ ከሰሰ:: ቅዱሱ ንጉሥም የጉዳዩን ክብደት ተመልክቶ የዓለም ሊቃውነት ይሰበሰቡ ዘንድ አዘዘ:: ፠ከሚያዝያ 21 እስከ መስከረም 21 ተጠቃለው ገቡ:: በ325 ዓ/ም (በእኛው በ318 ዓ/ም) ለ40 ቀናት የሚቆይ ሱባኤን ያዙ:: ሱባኤውን ሲጨርሱም በ4ቱ ፓትርያርኮች (እለእስክንድሮስ: ሶል ዼጥሮስ: ዮናክንዲኖስና ኤዎስጣቴዎስ) መሪነት: በእለእስክንድሮስ ሊቀ መንበርነት: በአትናቴዎስ ጸሐፊነት ጉባኤው ተጀመረ:: ፠በጉባኤው ሙሉ ስልጣን በሰማይ ከፈጣሪ: በምድር ከንጉሡ የተሰጣቸው አበው አርዮስን ተከራክረው ከነ ጀሌዎቹ ምላሽ አሳጡት:: ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ሥግው ቃል: ራሱም እግዚአብሔር መሆኑን አስረዱት::

:በኢትዮጵያ ሀገራችን የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበሩባቸው አድባራትና ገዳማት በጥቂቱ:- 1.#ቤተ ፬ቱ(አርባዕቱ) እንስሳ (ማዕከላዊ ትግራይ አክሱም ጽዮን አጠገብ) 2.#ደብረ ዓሣ አርባዕቱ እንስሳ (ማእከላዊ ትግራይ ተምቤን) 3.#አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ሰሜን ጎንደር፤ጎንደር ከተማ) 4.#ቤተ አርባዕቱ እንስሳ አለት ፍልፍል (ሰሜን ወሎ አንጎት አካባቢ) 5.#መካነ ትጉሐን አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ደቡብ ጎንደር ደብረ ታቦር) 6.#ደብረ ኪሩብ አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ምዕራብ ሐርጌ መኢሶ አካባቢ) 7.#ዝቋላ አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ምሥራቅ ሸዋ ዝቋላ) *በኤርትራ* 8.#አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስቲያን (ሃዞሞ የሚባል አካባቢ) 9.#ራቂት(ዓዲ ናላ) አርባዕቱ እንስሳ ቤተክርስትያን (በራቂት/ዓዲ ናላ) ****በደባልነት ያለ በአዲስ አበባ የሚከበርባቸው ቦታዎች*** 9.#ደብረ ጽጌ ቅድስት ማርያም (አዲስ አበባ፣ አደይ አበባ) 10.#ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን (አዲስ አበባ፣አራት ኪሎ) የአቅጣ። ጫ ምንጭ የአብርሃም ቆሎ ተማራው ገጽ

በዓለ ኪሩቤል (አርባዕቱ እንሣሳ ) በቅዱስ በዓለ ወልድ (8/03/2014 ዓ.ም ) ሰላም ለክሙ አርባዕቱ እነስሳሁ ፡፡ ለእግዚአብሔር መናብርቲኁሁ ፡፡ እሳታውያን ናሁ ሠረገላሁ ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱ
+5
በዓለ ኪሩቤል (አርባዕቱ እንሣሳ ) በቅዱስ በዓለ ወልድ (8/03/2014 ዓ.ም ) ሰላም ለክሙ አርባዕቱ እነስሳሁ ፡፡ ለእግዚአብሔር መናብርቲኁሁ ፡፡ እሳታውያን ናሁ ሠረገላሁ ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እንዘ ይብሉ ይሄልሑ፡፡ አሐተ ሰዓተ እንበለ አጽርዖ በጽርሑ ፡፡ ሰአሉ ለነ ትጉሃን ሐራሁ ፡፡ **መልክአ አርባዕቱ እንስሳ፡፡

እንኳን ለበዓለ ‹‹ኪሩቤል›› አርባዕቱ እንስሳ በሰላም አደረሳቹህ:: ኅዳር ፰፤ አርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) share ያድርጉ ከእግዚአብሔር በቀር የሚቆጥራቸው የሌለ የብዙ ሠራዊተ መላእክት በሰማይ ያሉ ሲሆን በዙውን አንድ እያልን በነገዳቸው እንቆጥራል፡፡ ስንቆጥርም የመጀሪያዎቹ ኪሩቤል (አርባዕቱ እንሳሣ )ናቸው ፨ ኪሩቤል ቃሉ ከአካድ/ጥንት ባቢሎናውያን ቋንቋ / የተወረሰ ሲሆን ትርጉሙም አማላጅ፣ኃያል፣ታላቅ ማለት ነው፡፡በአራቱ እንስሣ አምሳል የተገለጹ ጸውርተ መንበሩ ኪሩቤል ናቸው ፡፡ #ኪሩቤል የብዙ ቁጥር ሲሆን በነጠላ #ኪሩብ ይባላል፡፡ ፨ መላእክት ሆነው ሳለ ‹‹አርባዕቱ እንስሳ›› የተባሉበት ምክንያት ለቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በእንስሳት አምሳል በመገለጻቸው ነው፡፡ ፨ ኪሩቤል ከመቶው ነገድ መላእክት የአስሩ ነገድ መጠሪያ ስም ነው ፨ ከ3ቱም ሰማየ መላእክት በመጀመሪያይቱ በኢዮር ላይ ከአጋዕዝት በታች በ2ኛይቱ ከተማ የሰፈሩ ናቸው፡፡ ፨ ከእግር እስከ ራሳቸው በዓይን ተሸልመዋል - ዓይናቸውን እንደ ነብር ለምድ ዥንጉርጉር ነው፤አንድም እንደ መስታወት ስድ ነው ፤ ይኸውም ኪሩቤል ኃላፊያትንና መጻእያትን የማወቅ ክሂል ከልዑል አምላክ መቸራቸውን ያሳየናል ፤ ይህም የእግዚአብሔር ስራ ገደብ የማይጣልለት የቸርነት ሥራ ነው፡፡ መዝ 87፥ 35 ፨ነቢዩ ሕዝቅኤል እንደተመለከታቸወ ‹‹ ኪሩባውያን አፍራሱ ፤ ፈረሶቹ ናቸው ሲል ይገልጻቸዋል፡፡ ግብራቸውም ዙፋኑን ተሸክመው ሥላሴ ለወደዱት መገለጽ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ዙፋኑን ተሸክመው ይዘዋወራሉ ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር መገለጽ ሲፈልግ ዙፋኑን በዘፈቀደ ተሸክመው ስለሚታዩ ነው ፡፡ ፨ከአራቱ ኪሩቤል አንዱ ‹‹ ባራ ማራ ›› የሚባል ነው አንደኛነቱ የቁጥር እንጂ የክብር መበላለጥ አይደልም፡፡ ትርጕሙም ባራ ማለት በራ ማለት ነው ፡፡ በተፈጥሮ በራነት እንዳለ በመሸከምም በራነት ይኖራል ፡፡ ጸዋሬ መንበርነቱን ሲመለከትም ‹‹ ባራ ማራ መሊጦን ›› ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በምድራዊ ግሥ ገልጾታል፡፡ ፊቱም በአንበሣ ምስል ይገለጻል፤ ‹‹ ወቀዳሚ ይመስል አንበሳ ፤ የመጀመሪያው አንበሣን ይመስላል ›› እንዲል ራዕ 4፡፡ አንበሣ የአራዊት ንጉሥ ነውና በአለቃቸው ተመሰለ፡፡በአንበሣ መገለጹ ኃያልነቱን ሲያሳይ ነው ፍጻሜው ግን ‹‹ ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ›› የተበላው ክርስቶስ ይገለጣል ነው፡፡ ግብሩ ለአራዊት መለመን ሲሆን በሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ መመሰሉም የጌታን ሃያልነት ገልጾ ከማስተማሩ ጋር እና በአምሳለ አንበሳ የተሰሩ የግብፅ ጣዖታትን ቀጥቅጦ በማጥፋቱ ነው ፡፡ ፨‹‹መሊጦን መልአክ ›› ይህ ደሞ ሁለተኛው ሲሆን ሁለተኝነቱ የቁጥር እንጂ የክብረ መበላለጥ አይደልም፡፡ ትርጉሙም ዓምዳዊ ዘዐምድ እንደማለት ነው ዙፋኑን ተሸክሞ ‹‹ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ›› ብሎ ማመስገኑን ያሳያል ይህም መላእክት የሰማይ አምድ ናቸው ማለት ሳይሆን ግብራቸውን ያሳያል ፡፡ ቅዱስ ያሬድም ባራ ማራ .. መሊጦን ሲል ያዜማል፡፡‹‹ወካልዑ ይመስል ከመ ላሕም ››ሁለተኛውም ላም ይመስላል እንዲል ›› ራዕ እንዲል በላሕም ተመስሏል፡፡ በዚህም የተመሰለው ሉቃስ ሲጽፍ ‹ ‹ያን ላም አምጡት አርደን አወራርደን እንብላው ›› ሉቃ 15 ሲል ምሥጢረ ቁርባንን ጸፏል ፤ መሰየሙም ለዚህ ምክንያት ነው ፡፡ ፨‹‹እግረ ማጣ›› መልአክ ደግሞ አንዱ ነው ፡፡ቅዱስ ያሬድ ጸወርተ መንበር ብሎ በአንድነት ገልጻቸዋል፡፡ አምላካችንን በንጉሥ ፣ መንበረ ምንግሥቱን በኮር ፣ ሰማይ ውዱድን በአልጋ ፣ ኪሩቤልን በአራቱ እግሮቹ መስሎ ነው ፡፡ ይህ ከኪሩቤል አንዱ የሆነው መልአከ ፊቱ የሰው ልጅን ይመስላል ‹‹ወሣልሱ ይመስል ከመ ገጸ እጓለ እመ ሕያው ›› እንዲል ራእ 4 ፡፡ ይህ የሰው ፊት ያለው በማቴዎስ ይመሰላል ማቴዎስ ከአብርሃም ጀመሮ እስከ እመቤታችን ድረስ ልደተ አበውን ጸፏልና ፡፡ ፨‹‹ሱርትዮን መልአክ›› ይህ ደግሞ ትርጓሜው አገልጋይ ማለት ነው ፡፡ እሱም ዙፋኑን ተሸክሞ ሲያመሰግን ይኖራል ፡፡ገጹም ገጸ ንሥር ነው፤፤ ‹‹ወራቡዑ ይመስል ከመ ገጸ ንሥር›› እንዲል ራዕ 4፡፡ይህም ወንጌላዊውን ዮሐንስ የሚመስል ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሲጽፍ አመሣጥሮ ስለሚጽፍ ንሥር ደግሞ ከፍ ብላ ሌሎች አዕዋፍ የማይደርሱበትን ሰለምታይ እሱም እንዲሁ በ ንሥር ተመስሏል ፡፡ ፨ኪሩቤል (4ቱ እንሰሳ ) ለተወከሉበት መልክእ ቅድም እግዚአብሔር ጸሎት ያደርጋሉ #የሰው መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹እግረ ማጣ›› #ለሰው ልጅ፣ #የአንበሳ መልክ ያለው ኪሩብ‹‹ ባራ ማራ ››#ለአራዊት፣ #የላሕም መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹መሊጦን መልአክ ›› #ለቤት እንስሳት፣#የንስር መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹ሱርትዮን›› ደግሞ #ለአእዋፍ ሁሉ እየጸለየ ሲጠብቃቸው ይኖራል፡፡ ይህ ማለት ግን ምልጃቸው ገደብ አለው ማለት አይደለም አንዱ ለሌላኛው አንዱም ለሌላው መጸለይ መለመን ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ፨የሰው ፊት ያለው ዕውቀታቸውን ፣ የአንበሣ ፊት ያለው ግርማ ሞገሳቸውን ፣ የንስር ፊት ያለው ተመሥአቸውን ( ሲመሰጡ ሰማየ ሰማያት ይደርሳሉ )፡፡ ትህትናቸው የፍርሃት ምልክት ሲሆን ምድር ምድር የመለከታሉ ይህም ፊቱን ማየት ባሕርዩን መመርመር አይቻለንም ሲሉ ነው ፡፡ ግርማቸው ነበልባል ሲሆን እንደ እሳት ለተልእኮ ይፋጠናሉ ፡፡ አእምሮአቸው ግሩም ሲሆን በእውቀት ከሁሉ በላይ ናቸው ፡፡ አራት ፊትም ስላላቸው ለተልዕኮ አቅጣጫ አይቀይሩም ያለምንም ተፋልሶ ባለቡት ይቀጥላሉ እንጂ ‹‹ ሕዝ 1›› ለእያንዳንዳቸው አራት ክንፍ አላቸው ይህም በአጠቃላይ 16 ይሆናል ፡፡ ክንፋቸውስ 6 ነበር ነገር ግን በሰው አምሳል ስለተገለጡ ሁሉቱ እጃቸው ነበር ፡፡ እንጂ ያው ስድስት ክንፍ ነው ያላቸው ፡፡ ሁለቱ ክንፋቸውን ፊታቸውን ይሸፍኑበታል( ባህሪያን መመርምር አይቻለንም ሲሉ ) ሁለቱን ደግሞ እግራቸውን ይሸፍኑበታል( ከፊትህ ጸንቶ መቆም አይቻለንም ሲሉ ) ፣ ሁለቱን ደግሞ አንዱን ወደ ታች አንዱን ወደ ላይ ይዘረጋሉ( ቢወጡ ቢወረዱ አትመረመርም ሲሉ ) ፡፡ ፨የክንፋቸውም ጅግጅታ እንደ ፏፏቴ ከሩቅ ይሰማል ፡፡ ለመላእክት 6 ክንፍ ሲኖራቸው ለእንያንዳንዳቸው ኪሩቤል 16 ክንፍ በጠቅላላው 64 ክንፍ አላቸው ፡፡ ከዚኅ ጋርም ተያይዞ ‹‹ ከኪሩቤል እና ከሱራፌልም እሳ ትበልጣለች ›› የተባለቸው እመቤታችን እንዲዚህ መባሏ አንድም ኪሩቤል በክንፋቸው ጋርደው አምላከ ምሕረት ክርስቶስን ሲያመሰግኑባት አይቶ ነው ፡፡ ምልጃቸው አይለየን ፡፡ አሜን ! ፨፨፨፨፨፨፨፨፨በዓሉ የሚከበሩባቸውአድባራትን ኮሜንት ላይ ያጋሩን ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like