ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 399 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 564,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 183

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 399 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 21,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.61%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.23% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 327 次浏览,首日通常累积 1 576 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 399
订阅者
+124 小时
+307
+2130
帖子存档
ቅድመ ዘመን ሥላሴ ዓለምን ሳይፈጥሩ በዚህ ጊዜ ተገኙ ባይባልም ጥንት በሌለው ዘመናቸው በአንድነትና በሦስትነት ነበሩ። አለምንም ከፊጠሩ በኋላ በአንድነት በሦስትነት ጸንተው ይኖራሉ።አንድነት ያለሦስትነት ሦስትነትም ያለአንድነት አይገኝም፡፡ ለዘላለም ሶስት ለዘላለም አንድ ናቸው አንድነታቸው ሦስትነታቸውን አይጠቀልለውም! ሦስትነታቸውም አንድነታቸውን አይከፋፍለውም (ሶስት አያደርገውም) l ሶስት አካላት ማለትን የሚያፈርስብን አይደለም ሶስት አካላት ማለታችንም አንድ መለኮትን ከሶስት የሚከፍልብን አይደለም! ሶስቱ አካላት አንዱም አንዱ በየአካላቸው ጸንተው የሚኖሩ ናቸው አንጂ መለኮትም ሦሥት ወደ መሆን አይከፈልም እንዳለ ሃይማኖተ አበው ሶስትነታቸው በስም! በግብር (በሥራ)፣ በመልክ በገጽ ነው የስም ሶስትነታቸው መጠሪያቸው አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ የሚለው ነው። አብ የወልድ አባት የመንፈስ ቅዱስ አስራጺ ነው፡ አብ ማለት ጥንት መሠረት መገኛ ማለት ነው፡ ጥንት መሠረት መገኛ መሆነ ወላዲ አሥራጺ ይባላል አንጂ ወላዲ አሥራጺ በመሆኑ አብ ወይም አባት የተባለ አይደለም፡ ይህም ማለት ርብቃ ስለሳቀች ይሥሐቅ እንደተባለ ያዕቆብም የወንድሙን ሰኮና ይዞ ተወልዶ አሰናካይ እንደተባላ አይደለም ማለት ነው፡ አብ ወልድን ሲወልደው ከሙሉ አካሉ ከሙሉ ባህርይው ነው የፀሐይ ክበቡ ከሙሉ አካሉ ከሙሉ ባህርይው ሙቀትና ብርሃንን እንደሚልክ አብም ሙሉ አካሉ ወላዲ ስራጺም ነው። ወልድም ሙሉ አካሉ ተወላዲ ነው መንፈስ ቅዱስም ሙሉ አካሉ - ሰራጺ ነው ወልድ አባት ከመሆን በቀር (ከአባትነት በቀር) / አባቱ ያለው ሥልጣን ወዘተ ሁሉ አለው ፀሐይ ግን በአስጎኙ ክበብ ይልቅ የተገኘ ሙቀትና ብርሃን ይረቃል። አብ ግን ከወልድ አይረቅም ወልድም ከአብ እያንስም አይገዝፍም፡ አርአያ ገጹ ለእግዚአብሔር እግዚአብሔርን በመልክ የሚመስለው በባህርይ እንደሚተካከለው እንዲል እብ1። እሪናቸው በአካል : መመሳሰላቸው በህብረ _ መልክ አንድነታቸው በመለኮትት ተዋህዷቸው በኩነት ወይም በመሆን ነው፡ ሲወልደዉ በዘመን አይቀድመውም ምክንያቱም አብ (አባት) የሚለው ስም የአካሉ ስም ስለሆነ ልጅ ከሌለ አባት ተብሎ ይጠራም። አብ በልብ ይመሰላል፣ ከሀሳብ ከቃል ቀድሞ የሚገኝ ልብ የለም፡ ሲገኙ ሁለቱም በአንድ ጊዜ ነው አንድ የጠፋ እሳት ቢነድ ነዲዱም ብርሃኑም መቀቱም በአንድ ጊዜ ይገኛሉ። ብርሃንና ሙቀቱ ከነዲዱ መገኘታቸው ግን የማይካድ ሀቅ ነው፡ እንደዚሁም ሁሉ አብ ወልድን ሲወልደውና መንፈሰ ቅዱስን ሲያሰርጸው (ያወጣው) ሳይቀዳደሙ ነው። ነገር ግን በወንጌል እምሀበ እግዚአብሔር ወጻእኩ ወመጻዕኩ እኔ ከእግዚአብሔር ወጣሁ ወደዚህ አለም መጣሁ ብሉ ጌታ ስለራሱ ልደት' መንፈሰ ጽድቅ ዘይወጽዕ እምሀበ አብ ውእቱ ሰማዕትየ፤ ከአብ የሚወጣው የዕውነት መንፈስ እርሱም ምስክሬ ነው ብሎ ስለመንፈስ ቅዱስ መውጣት እንደተናገረ የወልድ መወለዱ የመንፈስ ቅዱስ መስረጹ ከአብ መውጣቱ እንጂ ነው፡ አዎ የሁለቱስ መውጣት ከሆነ ወልድን ሠረጸ መንፈስ ቅዱስን ተወለደ ማለት ይገባልን ቢሉ አይገባም ለምን ያሉ አንደ ሆነ እነሆ ከልብ ቃልና እስትንፋስ ይወጣሉ መውጣት ስላስተባበራቸው ቃልን ተነፈሰ እስትንፋስን ተናገረ እንዳይሉ ወልድን ሰረጸ መንፈስ ቅዱስን ተወለደ ይሉ ዘንድ አይገባም፡ : የቅድስት ሥላሴ የምሕረት ባህር አይለየን ! አሜን /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፋል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

እመቤታች ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇ ወዳጇ አማኑኤል፣ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊና ቅድስት ሰሎሜ በስደት ላይ ሳሉ ውሃ ቢጠማቸው ቸሩ መድኃኔዓለም ውሃ ያፈለቀላቸውና የጠጡበት ጉድጓድ: (ፎቶዎች በመ/ር ልዋ
+3
እመቤታች ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇ ወዳጇ አማኑኤል፣ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊና ቅድስት ሰሎሜ በስደት ላይ ሳሉ ውሃ ቢጠማቸው ቸሩ መድኃኔዓለም ውሃ ያፈለቀላቸውና የጠጡበት ጉድጓድ: (ፎቶዎች በመ/ር ልዋም ሃብቴ ከ አብርሃም ቆሎ ተማሪው ገጸ ላይ የተወሰደ)

#ፎቶዎቹ ፤ እመቤታችን ከልጇ ጋር ያረፈችበት ገዳመ ቊስቋም ማርያም ገጽታ የሚያሳዩ (ፎቶዎች በመ/ር ልዋም ሃብቴ ከ አብርሃም ቆሎ ተማሪው ገጸ ላይ የተወሰደ)
+9
#ፎቶዎቹ ፤ እመቤታችን ከልጇ ጋር ያረፈችበት ገዳመ ቊስቋም ማርያም ገጽታ የሚያሳዩ (ፎቶዎች በመ/ር ልዋም ሃብቴ ከ አብርሃም ቆሎ ተማሪው ገጸ ላይ የተወሰደ)

#ፎቶዎቹ ፤ እመቤታችን ከልጇ ጋር ያረፈችበት ገዳመ ቊስቋም ማርያም ገጽታ የሚያሳዩ (ፎቶዎች በመ/ር ልዋም ሃብቴ ከ አብርሃም ቆሎ ተማሪው ገጸ ላይ የተወሰደ) _______________________________ ደብረ ቁስቋም በደቡብ ግብፅ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ደብረ ቁስቋም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲሁም ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን ይዛ ከስደት ሲመለሱ ያረፉበት ቦታ ነው፡፡ ይህም ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭) የክርስቶስ ስደቱ ቀድሞ በነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹. . . እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተቀምጦ ወደ ግብፅ ይመጣል፡፡ የግብፅም ጣዖታት በፊቱ ይዋረዳሉ›› ተብሎ በተነገረው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ ነቢዩ ፈጣን ደመና ያለው ጌታችን በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ጀርባ ላይ ሆኖ ወደ ግብፅ መውረዱን ለመግለጽ ነው፡፡ ፈጣን ደመና የተባለችውም እመቤታችን ነች፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩) በስደቱም ጣዖታተ ግብፅ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፡፡ ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቦና አውጥቶ አሳደደ፡፡ እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከስደት ስትመለስ ያረፈችበትን ተራራ ደብረ ቁስቋምን ባረከችው ቀደሰችውም፤ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም እንዲህ አለ፤ ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት፤ የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡›› ‹‹አንተ ተራራ ሆይ የእግዚአብሔር ማደሪያ በሆንህ ጊዜ በኪሩቤልና በሱራፌል መካከል ፍጹም ደስታ ተደረገ፡፡ የመላእክት ሠራዊት ቅዱስ የሆነ ፈጣሪያቸውንና ጌታቸውን ይታዘዙ (ያገለግሉ) ነበር፡፡ አንተ ተራራ ሆይ ያደረብህ ጌታችን ስለሆነ ከተራሮች ሁሉ ከደብረ ሲናም ይልቅ ከፍ ከፍ አልህ፤ ጌታችን በደብረ ሲና ባረፈ ጊዜ ፍጹም ደስታ፣ ታላቅ ብርሃንም በሆነ ጊዜ መቅረብና መመልከት ከሙሴ በቀር የቻለ የለም፡፡ እርሱም ቢሆን ፊቱን ማየት አልቻለም፡፡ ሥጋ ለባሽ ሁሉ እርሱን ዐይቶ በሕይወት መኖር የሚቻለው የለምና፡፡ እኛ ግን አየን፤ ከዚህ ማደሩንም ተረዳን፤ ዳግመኛም ንጽሕት በሆነች በማርያም ዘንድ አየነው፡፡ ቅድስት ከሆነች ከእመቤታችን ማርያም ዘንድ በቤተልሔም ስለ እኛ በተዋሐደው ሥጋ በጨለማና በሞት ጥላ ሥር ያለን እኛን ከቸርነቱና ሰውን ከመውደዱ የተነሣ መጥቶ አዳነን፤ ከዓለም ሁሉ ይልቅ ጣዖትን በማምለክ ሲበድሉም ወደ ግብፅ ሀገር ወርዶ በእነርሱ ላይ የመለኮትነት ብርሃኑን በማብራት ታላቅ የሆነ ክብሩን ገለጠ››፡፡ (ድርሳነ ማርያም) ኅዳር ፮ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛም በኋላ ዘመን ሐዋርያትን በደብረ ቁስቋም ሰብስቦ፤ ታቦትንና ቤተ ክርስቲያኑን አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙን እንደ ሰጣቸው፤ እኛንም ለዚህ ክብር የበቃን እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን፤ አሜን፡ ፍቶዎች በመ/ር ልዋም ሃብቴ ከ አብርሃም ቆሎ ተማሪው ገጽ ላይ የተወሰዱ የቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት :: #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ኅዳር 7 ( ፯ ) የሊቀ ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው :: መክብበ ሰማዕት ፥ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኰከበ ልዳ፥ ፀሐየ ፋርስ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ የኢትዮጵያ ገበዝ፤ ከአውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስ ፈጥኖ ደራሽ ሰማዕት፤ እንደ እናቱ (እኅቱ) ቅድስት ማርያም ርኁሩህ የኾነ፡፡ ኅዳር 7 ቅዳሴ ቤቱ (ለመጀመሪያ ጊዜ የተሠራው ቤ.ክ የተመረቀበትና ቅዳሴ የተከናወነበት ክብረ በዓል) ነው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሚያዚያ 23 ቀን በሰማዕትነት ከሞተ በኃላ አጋልጋዮቹ እጅግ የከበሩ ልብሶችና ያማሩ ሽቶዎች አዘጋጁ በከበረ አገናነዝም ገነዙት በመርከብም ጭነው ወደ ትውልድ አገሩ ልዳ አመጡት ነገር ግን ቤተሰቦቹ በሙሉ ማለትም አባቱ ዘሮንቶስ እናቱ ቴዎብስታ እህቶቹ ማርታና እስያ እንዲሁም አጭተውለት የነበረች እጮኛው ሁሉም ሞተው አገኙዋቸው፤ እንድርያስ የሚባል አጎት ነበረው ስጋውን ተቀበላቸው አገሬው ተሰበሰበ የእየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳስ አባ ቴዎድሮስ ተጠርቶ መጣ ቤተክርስቲያኑን አነጹለት ስጋውንም በዚያ በክብር አኖሩት፤ በዚህች ቀን እጅግ ብዙ የሆነ ድንቅ ታአምራትና ታላላቅ ኃይላት ተደረጉ፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቤተክርስቲያን ይህንን ቀን ታከብረዋለች። ታላቁ ንጉሳችን እምዬ ምኒሊክ አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ሲሰሩ ከዚሁ ከልዳ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ካለበት አፈሩን በመርከብ ከዚያም በበቅሎ አስጭነው አምጥተው ለቤተክርስቲያኑ መሰረት እንዳደረጉት እና ቅጥሩን ዙርያውንም እንደነሰነሱት መጻሕፍት ይናገራሉ ፡፡ ፠ ፠ በዓሉ በድምቀት በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ (በአራዳ ጊዮርጊስ) ይከበራል ———- ፨ ኅዳር ፯፤ (የአቡነ ገብረ እንድያስ በዓለ ዕረፍትና ነው)፨ ፠ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ተዓምራትን የሚሠሩት እንጨቱ ጸበላቸው_=ውስጥ ሲገባ መቊጠሪያ የሚያደርጉት ፤ (በፎቶ የምታዩት)፤ ፠ በጠበላቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተዓምራትን የሚያደርጉት ፠ ፻ ትውልድ የሚያስምሩት፤ ፠ በደንጊያ ሠረገላነት የሚጓጓዙት፤ ፠ ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨ ቦታቸውን ክርስቲያን የኾነ ኹሉ ሊያየው የሚገባ የተዓምራት ቦታ ነው፤ ✤✣✤ #ጻድቁ_አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_ዘወለቃ_ወዘደብረ_ቆዘት_፤ ✤አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ፥ እናታቸው አርሴማ ሲባሉ፥ የትውልድ ሀገራቸው ወሎ፥ ቦረና፥ ጋሥጫ ሲኾን፤ የቀድሞ ስማቸው ንፍታሊም ይባል ነበር። ✤ ለትምህርት ሲሄዱ መምህራቸው ብዙኃኑን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት የተናገሩላቸው ሲኾን፤ የመጻሕፍትን ትርጓሜ በደንብ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሊም ይባል የነበረውን የቀድሞ ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው። ✤ ጻድቁ በአቡነ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል፤ ብዙ አባቶች ሱባኤ በሚይዙበት በስኮሩ ሥላሴ ቤተክርስትያን ጸሎት ሲያደርጉ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል በወርቅ ጽዋ ማየ ሕይወት አጠጥቷቸዋል። ✤ ጻድቁ አባታችን ሙታንን በማስነሳትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። ✤ ጻድቁ ዐርብ ፥ ዐርብ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውን ና ክቡር ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበረው በአየር ላይ ድንጋዩን እንደ ሰረገላ ፥ ዋርካውን እንደ ጥላ እየተጠቀሙበት ነበር። ይህ ሰረገላ የሆነው ድንጋይ በገዳማቸው ዛሬ ድረስ ይገኛል። (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ጻድቁ አባታችን እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ርቀት ወንዝ ከተሰኘው ቦታ በአንገታቸው ላይ በጣም ትልቅ ድንጋይ እየተሽከሙ ይጸልዩ ነበር። በዚህም ይጸልዩበት በነበረው ወንዝ ውስጥ በተአምራት መቊጠርያ የሚሰራ ጸበል ፈለቀላቸው፤ ጠበላቸው ውስጥም እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት መቊጠርያ ሆኖ ይወጣል፤ ይኸውም መቊጠሪያ ለብዙ ሕመሞች መድኀኒት ነው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ✤ ✤ አቡነ ገብረ እንድርያስና ሊቀ ሰማዕቱ ስለ ሃገራችን በተቀበሉት ቃል ኪዳን ሰላምና ጤና ያውርዱልን፤ ጠላታችንን ከሃገራችን ያባርሩልን፨ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ኅዳር ፮፤ በግብፅ ሀገር ባለች ደብረ ቊስቋም ዋሻ ከ፫ ዓመት ከ፮ ወር ስደቷ ያረፈችበት፡፡ የቊስቋም ክብረ በዓል የሚከበርባቸው #ገዳማትና_አድባራት የተወሰኑት ፨ መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም_ቤ/ክ_፤ ዓመቱን ሙሉ ዝክር በማኅበረ_ሰላም መድኀኔዓለም የሚዘከርባት ቤ/ክ) 📍 ሽሮሜዳ (መነን) ቊስቋም፤ ፨ቃሊቲደብረ_ገነት_ቅዱስ_ሚካኤልና_ደብረ_ቊስቋም_ማርያም_ቤ/ክ፤ (ቃሊቲ ቊስቋም) 📍 ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፨ ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤ/ክ፤ 📍 /በቀለበት መንገድ.../ _____________ ፨ ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 አጣና ተራ ..ጠሮ ፨ ጉለሌ ሸጎሌ ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 ሸጎሌ ፨ ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 (መርካቶ) → የሺ ደበሌ፡፡ ፨ ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 ላፍቶ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ኅዳር ፮፤ በግብፅ ሀገር ባለች ደብረ ቊስቋም ዋሻ ከ፫ ዓመት ከ፮ ወር ስደቷ ያረፈችበት፡፡ የቊስቋም ክብረ በዓል የሚከበርባቸው #ገዳማትና_አድባራት የተወሰኑት ፨ መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም_ቤ/ክ_፤ ዓመቱን ሙሉ ዝክር በማኅበረ_ሰላም መድኀኔዓለም የሚዘከርባት ቤ/ክ) 📍 ሽሮሜዳ (መነን) ቊስቋም፤ ፨ቃሊቲደብረ_ገነት_ቅዱስ_ሚካኤልና_ደብረ_ቊስቋም_ማርያም_ቤ/ክ፤ (ቃሊቲ ቊስቋም) 📍 ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፨ ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤ/ክ፤ 📍 /በቀለበት መንገድ.../ _________________ ፨ ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 አጣና ተራ ..ጠሮ ፨ ጉለሌ ሸጎሌ ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 ሸጎሌ ፨ ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 (መርካቶ) → የሺ ደበሌ፡፡ ፨ ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤በድርብነት፤ 📍 ላፍቶ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like