ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 371 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 616,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 192

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 371 名订阅者。

根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -4,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 20.07%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.16% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 085 次浏览,首日通常累积 1 254 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 371
订阅者
-124 小时
+357
-430
帖子存档
እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሳችኁ የቀደሙ የታኅሣሥ 19 አገልግሎቶች ። https://youtu.be/p3H4kxjbnM8

#ታኅሣሥ_12_የአቡነ_ሳሙኤል_በዓለ_ዕረፍት ✤✤ #ፀሐይ_ማር_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_(#ዘገዳመ_ዋሊ_) ✤✤ ፠ በሃገራችን በኢትዮጵያ በብቸኝነት በጌታችን የተመሠረተው ገዳመ ዋልድባ፤ ኋላ በአሕዛብ ጠፍቶ ነበርና በ13ኛው ክፍል ዘመን እንደ መሶብ ከፍ አድርገው በ4ቱም አቅጣጭ በ4 ወንዞች (በሰሜን ተከዜ፥ በምስራቅ እንስያ፥ በምዕራብ ዛሪማ ፥ በደቡብ እንዞና ወይቦ) ዙሪያውን ከልለውና አጥረው ያስባረኩ አባት ናቸው፡፡ ፠ አዲስ አበባና አካባቢውን ከ700ዓመታት በፊት በአንበሳ እየተጓጓዙ በስብከተ ወንጌል እርሻነት፥ በሥነ ምግባር ማለስለሻነት ያረሱ አባት ናቸው፡፡ ፠ ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን፣ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት የኾኑ ናቸው፤ ይህንንም ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ40ቀን ዕረፍታቸው በመካነ መቃብራቸው ተገኝተው መልክዓቸውን ደርሰውላቸዋ፤ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው አውስተዋቸዋል፤ እንዲሁም በርካታ ቅዱሳን ደራስያን በየድርሰታቸው አንስተዋቸዋል፡፡ #ክቡር_መምህር፥ #የከበረ_መምህር፤ #መልአክ_ዘበምድር፥ #የምድር_መልአክ፤ #ካህን_ወድንግል፥ #ካህንና_ድንግል፤ #ፍጹም_ንጹሕ_ወልዑል፥ #ፍጹም_ንጹሕና_ልዑል፤ #ትጉህ_ወኅሩይ፥ #ትጉህና_ኅሩይ_የተመረጠ)፤ #ብእሴ_እግዚአብሔር፥ #የእግዚአብሔር_ሰው፤ #ለባሴ_ንጽሕና፥ #ንጽሕናን_የተላበሰ፤ #ወለብሰ_ብርሃናዌ፥ #ብርሃንን_የለበሰ፤ #ዘፈጸመ_ገድሎ_በሠናይ፨ #ገድሉን_በመልካም_ተጋድሎ የፈጸመ፨/ገድለ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ/ ፠ ከረድአቸው አባ ብንያሚና፤ ከጓደኞቻቸው ከአባ አንበስ ዘሐዘሎና ከአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ጋር በመኾን በወቅቱ ከነበሩት ርዕሰ አበው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘንድ ለመባረክ ወደ ዝቋላና ምድረ ከብድ የመጡና በረከትን የተቀበሉ ከሰሜን እስከ ደቡብ ኢትዮጵያ ያስተማሩ ናቸው፡፡ ፠ አናታቸው በሥጋ ሞት በሕፃንንታቸው ቢለይዋቸውም፤ በሕፃንነታቸው ጌታችን አውራ ጣቱን አትብቷቸዋል፡፡ ‹‹እንዘ ይተግህ ለጸልዮ ወያስተበርክ ለስኢል፤ መንኰብያቲሁ አጠበዎ ወልደ ማርያም ድንግል፡፡ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል ዘዋልድባ መነኮስ ኀያል፡፡›› /እንዲል ነግሥ/ ፠ የተከዜ ወንዝ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትዕምርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ ፥ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ወደ ወንዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉም ሳይበላሽ ተሸግረዋል፡፡ ፠ ገባሬ ተዓምራት ወመንክራት የኾኑ፤ ⴲ ዝናብ በኾነ ጊዜ ዝሆኖች መጥተው እንደ ጥላ የሚያስጠልሉት፤ ‹‹ሳሙኤል አቡነ ሠረገላ ጸሎት፤ ጊዜ ርደቶሙ ለዝናማት፤ ዘከለሉከ ነጌያት፡፡›› እንዳለ መጽሐፈ ሰዐታት፤ ⴲ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ (ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት) ጋር መንበረ ጸባዖትን ለ12 ዓመታት አጥነዋል፤ በዚህም በጎንደር ደባርቅ አካባቢ የመሠረቱት ገዳማቸው አብ ጠራ(ህ) በሚል ተሰይሟል፡፡ ......................................የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ‹‹ሳሙኤል አቡነ ትሩፈ ምግባር፤ ዐምድ ጽኑዕ ፀወነ ሃገር፤ ወመልአክ ዘበምድር፡፡›› እንዲል መጽሐፈ ሰዐታት፣ ⴲ በዋልድባ ምድር ላይ ቀድሞ ውኃ የለም ነበርና፤ ፸ የሚጠጉ ምንጮችን በተለያዩ ቦታዎች አፍልቀዋል፡፡ ⴲ ቅዳሴ ማርያምን ወደ መሃል ሃገር ያመጡ፤ ⴲ ቅዳሴ ወውዳሴ ማርያምን ሲደግሙ ከመሬት ክንድ ከስንዝር ያህል ከፍ የሚሉ፡፡ ⴲ በአናብስት ዘባን ላይ የሚጫኑ፤ መጻሕፍቶቻችውንም በአናብስት ላይ የሚጭኑ፡፡ ⴲ እመቤታችን ነጭ ዕጣን (ስለ ምዑዝ ክህነታቸው) እንዲሁም ዕንቊ (ስለ ንጽህናቸው፣ ቅድስናቸውና ድንግልናቸው) የሰጠቻቸው። ⴲ በሰኔ 21 ቀን በቀደሱበት ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ አንድ ክንድ ከስንዝር ከምድር ለቆ እንደ ደመና በአየር ላይ ቆሞ የታየላቸው፡፡ ⴲ ውኃውን ወደ ኀብስት የቀየሩና ከነ ደቀመዛሙርቶቻቸው የተመገቡ፤ ‹‹ሶበ አተቦ ለማይ በቅዳሴኪ እንዘ ይጼሊ፤ ረሰዮ ኅብስተ ጽጌ ሃይማኖት ሳሙኤል ዘሐቅለ ዋሊ፡፡ ምሕረተ ወፍትሐ ለተአምርኪ እኅሊ፤ ሥረዪ ኀጢአትየ ወዕፀብየ አቅልሊ፤ አስመ ኵሎ ገቢረ ማርያም ትክሊ፡፡›› /ማኅሌተ ጽጌ/ ‹‹ …አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኀይላተ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በኀበ ተአኵተ፥ ወለማይኒ ረሰዮ ኅብስተ፡፡›› /ማኅሌተ ጽጌ/ የምንኵስና ተወረዱም፤ አባት አባትን ሲወልድ፤ መምህር መምህርን ሲተካ፥ ቅዱስ ቅዱስን ሲያፈራ፥ ገዳም ገዳምን ሲወልድ ነውና ቅሉ፤ የምንኵስና ተዋረዱም፤ ፠ ….. ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ መድኃኒነ እግዚእን፤ ፠ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ 7ቱን ከዋክብት /ፀሐይ አቡነ ሳሙኤልንና ሌሎች ቅዱሳንን/፤ ፠ ከ7ቱ ከዋክብት አንዱ ፀሐይ አቡነ ሳሙኤል ደግሞ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን (አባ ተሥፋ ሐዋርያትን፥ አባ ዘሩፋኤልን፥ አባ ብንያሚን፥ አባ በኪሞስን፥ …… ሌሎች እልፍ አእላፋት መነኰሳትን አምንኵሰዋል፣ ሊቃውንትን አስተምረዋል፤ መምህራንና ደራስያንን ተክተዋል ….፤ በዚህም ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ፥ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት አባ ሳሙኤል በመባልም ይታወቃሉ፡፡ #አቡነ_ሳሙኤል_፤ በአኵስም ከተማ አካባቢ በ1295 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው ዓመተ ማርያም ይባላሉ፡፡ በአኵስም ጽዮን ከነበሩት መምህራን ከፊደል ጀምረው የቅዱስ ያሬድን ጸዋትወ ዜማና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን ተምረዋል፡፡ ወላጆቻቸው በልጅነታቸው በሞት ተለይተዋቸዋል፡፡ ከወላጆቻቸው ሞት በኋላ ወደ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘንድ ሔደው ደብረ በንኰል ገዳም ገቡ፡፡ በዚህም ገዳም እያገለገሉ በወቅቱ ከነበሩት ሊቃውንት የብሉያትና የሐዲሳትን ትርጓሜ እንዲሁም ሥርዐተ ምንኵስናን ተምረው ከገዳሙ አባት በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ ከሌሎች 11ድ ወንድሞቻቸው ጋር አብረው መነኰሱ፤ ቆባቸውም እንደ አቡነ አረጋዊ የድንጋይ ቆብ ነበር፡፡ በዚህም ገዳም እህል ሳይበሉ ቅጠል ብቻ እየተመገቡ ይኖሩ ነበር፡፡ እግራቸው እስኪያብጥም ድረስ ይሰግዱ ነበር፡፡ **ኋላ ወደ ጣና ገብተው ከቆብ ወንድማቸው ከአቡነ ያሳይ ጋር ለ12 ዓመታት በሱባኤ ቆዩ፤ **በስተመጨረሻም ጌታችን ወደ መሠረተውና በመሃልም ጠፍ ሆኖ ወደ ነበረው ብዙ ቅዱንን፣ መምህራንን፣ ሊቃውንትንና መናንያንን ወደ ወለዱበት ዋልድባ ገዳም ገብተው ለ70 ዓመታት ያህል ከዚህ ዓለም በምናኔ ተለይተው፣ ግርማ ሌሊቱን፥ ፀብአ አጋንንቱን ፥ ድምፀ አራዊቱን፥ የሌሊቱን ቊር፥ የቀኑን ሐሩር ታግሠው፣ ረሃቡንና ጽሙን ችለው፣ መላ ዘመናቸውን በጽድቅ ጎዳና ተጕዘው በ1395ዓ.ም ታኅሣሥ 12 ቀን በዋልድባ አቴና ገዳም ዐርፈዋል፡፡ #ባርከኒ አባ እንሣእ ጸሎተከ፤ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ አባ ሳሙኤል ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፨ /ጸሎተ መሐረነ አብ/ #በታኅሣሥ ፲፪ በበዓለ ዕረፍታቸው ጊዜም፤ ሮም በጴጥሮስና በጳውሎስ ዕረፍት እንዳለቀሰች፤ ቅድስት ገዳማቸው ገዳመ ዋልድባ (ዋሊ) አልቅሳለች፨ ‹‹በከየት ወለሀወት ገዳምከ በሞትከ ዮም፤ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፤ ምድረ ዋልድባ ቅድስት ሰሚዓ ዜና ሞትከ፤ እንዘ አንተ ሰብእ ምድራዊ ወመልአክ ተሠመይከ፤ ካህነ አርያም ሳሙኤል መንበረ ሥላሴ ዘአጠንከ፤ አንበሳ ወነምር ይሰግዱ ለከ፤ ወይልህሱ ጸበለ እግርከ፤ ዕንቈ ወዕጣነ ማርያም አምጽአት ለከ፤ በቅዳሴሃ ሶበ ጸለይከ፤ በከየት ወለሐወት ገዳምከ።>> እንዲል ዚቅ፨ #ታኅሣሥ #፲፪ ፤ #በዓለ_ዕረፍቱ_ለአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_፡፡

ታኅሣሥ 7 ፤ በዚህችም ዕለት ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዱስ ያሬድ ዜማ በቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎት ጀመረች፤ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ የታኀሣስ 7 ክብረ በዓል ወድ ታኅሣሥ 11 ዞሮ ክብረ በዓሉ ታቦቱ ወጥቶ ይከበራል ፡፡ (አድራሻ፤ ጎተራ ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል ፍላወር በሚወስደው መንገድ፡፡) ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከቅዱስ ያሬድ በፊት ከሕገ ኦሪት በፊት በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በዜማ ማመስገን ነበር፡፡ ይህም በማሕዝኒና በበገና ብቻ እንደነበር መጻሕፍት ይናገራሉ ፡፡ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን የምንሰማው ውርድና ቁም ንባብ የዘመነ ብሉይ ውጤቶች ናቸው ፡፡ለምሳሌ ‹‹ መልዕክተ ዮሐንስ ሐዋርያ ወልደ ዘብዴዎስ ›› እይ ፡፡ የዜማ መሣሪያዎችንም ከዘመነ ኦሪት ጀምሮ ስትገለገለበት ቆይታለች ( ከበሮ ፣ መሰንቆ ፣ በገና ፣ መለከት )‹‹መዝ 8››፡፡ ቅዱስ ያሬድ ከተሰወረ በኃላ ደቀ መዛሙርቶቹ በእርሱ እግር ተተክተው ዜማውን ማስተማር ቀጠሉ፡፡ አክሱም ጽዮን ማርያምንም ጽርሐ አርያም አስመስለዋት ነበር፡፡ በአባ ገሪማ ገዳም ውስጥ እና ደብረ ዳሞ ድረስ በመሄድም ጕባዔ እየዘረጉ ማስተማሩን እና ማስፋፋቱን ቀጥለው ነበር፡፡ ደቁ መዛሙርቶቹም ትምህርቱን አስተምረው በተለያየ ተጋድሎ ከአረፉ በኃላ ፡፡ የዜማው ትምሕርት ትግራይ ውስጥ በሚገኙ ታላላቅ ገዳማትና አድባራት ፣ በጣና ቂርቆስ ፣ በጎሐ ጽዮን ፣ በተድባበ ማርያም ፣ በመርጡለ ማርያም በዙር አባ ሁሉ ተዳረሰ ፡፡ በሒደትም የቅዱስ ያሬድ ጣዕመ ዜማ ተስፋፋ ፡፡ ተጨማሪ እዚህ አንብብ---›https://t.me/medihanaelem/6363 የቅዱስ ያሬድ ሌሎች መጠሪያ ስሞች ፠ ጥዑመ ልሳን፤ ፠ የሱራፌል አምሳያ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤ ፠ መዓርዒረ ዜማ፤ ፠ ዓርከ ሊቃውንት፤ ፠ ደራሲ፤ ፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ) ፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤ ፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ ፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ፤ …… ማን እንደርሱ:: …... ተጨማሪ እዚህ አንብብ---›https://t.me/medihanaelem/6363 /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ኢትዮጵያውያን_ቅዱሳን #Ethiopian_Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts

ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ (ሜክሲኮ) (ጦር ኀይሎች) → አለም ባንክ፡፡ ፳፱. ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፊሊዶሮ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ → ፊሊዶሮ፡፡ ፴. ቃሊቲ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሲሪቲ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → አቃቂ → ሲሪቲ፡፡ ፴፩. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ\ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ሐና ማንጎ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ሐና ማንጎ ሰፈር፡፡ ፴፪. መንበረ ልዑል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት ድንግል ማርያም ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ 58 ማዞርያ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → 58 ማዞርያ፡፡ ፴፫. ቀበና ቤዛዊተ ዓለም ኪዳነ ምሕረት ቤ/ን፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ቀበና ደልድዩ ጋር፥ ከኮከበ ጽባሕ ት.ቤት ፊት ለፊት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቀበና፡፡ ፴፬. ኮተቤ ሀገረ ገነት ጊዮርጊስ፥ ድንግል ማርያምና መግደላዊት ማርያምቤ/ን፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ጊዮርጊስ) (4/6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → አንቆርጫ፡፡ ፴፭. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ መስቀል ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቦሌ (መስቀል ዐደባባይ/እስጢፋኖስ)፡፡ #ቅድስት_አርሴማ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_በዓሏ_የሚከበርባቸው_ #፳፬ ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ሲሪንቃ ቅድስት አርሴማ ገዳም አድራሻው፤ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ወልዲያ፥ ሲሪንቃ፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ወልዲያ → ሲሪንቃ፡፡ ፪. ጅሩ ሰንከታ ደብረ ልዕልና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ጅሩ፤ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጅሩ፤ ወይም፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ጅሩ፡፡ ፫. ይርጋለም ጋኔ ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻው፤ ሲዳማ አማሮና ቡርጂ ሀገረ ስብከት፥ ይርጋለም፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ይርጋለም፡፡ ፬. ደብረ ሲና ሳር አምባ ቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ሲና፥ ሳር አምባ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ሲና፡፡ ፭. ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ ወቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ የምሥራች፤ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ከተማ → የምሥራች፡፡ ፮. ደብረ ታቦር ሎሚ ዱር ምዕራፈ ቅዱሳን አርሴማ፤ አድራሻው፤ ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ታቦር፤ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር → ሎሚ ዱር፡፡ ፯. ጂንካ በዓታ ለማርያምና ቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ አርባ ምንጭ ሀገረ ስብከት፥ ጂንካ፤ ትራንስፖርት፤ ከአየር ጤና አውቶቡስ ተራ → አርባ ምንጭ → ጂንካ፡፡ ፰. አካኩ ምዕራፈ ቅዱሳን ዳግማዊት ሲሪንቃ ቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ እንጦጦ፥ ከሽንቁሩ ሚካኤል አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ጊዮርጊስ) (4 ኪሎ) → ሽሮ ሜዳ → ቊስቋም → አካኩ አርሴማ፡፡ ፱. ኵሉ ወይን አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ጫጫ፥ ፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጫጫ → ኵሉ ወይን፡፡ ፲. ደብረ ብርሃን ቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን፡፡ ፲፩. ወይንየ ጌቴ ሴማኒ ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ግዳን ወረዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ግዳን፡፡ ፲፪. ቅበት ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ (አሕዛብ ቤ/ኗን አቃጥለዋት የነበረችው) አድራሻ፤ ሃድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት፥ ቅበት፤ ትራንስፖርት፤ ከአየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ስልጢ፡፡ ፲፫. ባሌ ጋሰራ በኔባ አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ባሌ ሀገረ ስብከት፥ ባሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ባሌ፡፡ ፲፬. ናዝሬት ቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ናዝሬት (አዳማ)፤ ትራንስፖርት፤ ከቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ናዝሬት (አዳማ)፡፡ ፲፭. ደብረ ናዝሬት ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን፤ (በድርብነት) አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ናዝሬት (አዳማ)፤ ትራንስፖርት፤ ከቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ናዝሬት (አዳማ)፡፡ ፲፮. ቦንጋ ዋቻ ኦቤራ ጌቴ ሴማኔ ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ጂማ ሀገረ ስብከት፥ ቦንጋ፥ ዋቻ ኦቤራ ፤ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጂማ → ቦንጋ፡፡ ፲፯. ዋሻ መድኃኔ ዓለም አቡነ ሙሴ ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ዳውንት፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ወልዲያ → ዳውንት፡፡ ፲፰. ቱሉ አርቦ ሾላ ገነት ቀስተ ደመና ቅድስት አርሴማ ወአቡነ ዘርዓ ቡሩክ ወመስቀለ ክርስቶስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ወልመራ ወረዳ፥ ቱሉ አርቦ፤ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ወልመራ → ቱሉ አርቦ፡፡ ፲፱. አሸተን ማርያና አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ላስታ ላሊበላ ሀገረ ስብከት፥ ላበላ ከተማ፥ አሸተን፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → አሸተን፡፡ ፳. ሜሪላንድ ጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስና ምዕራፈ ቅዱሳን ቅድስት አርሴማ፤ አድራሻ፤ ሰሜን አሜሪካ ሜሪላንድ ሀገረ ስብከት፥ አሜሪካ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ → ሜሪ ላንድ፡፡ ፳፩. ባሌ ጎባ ቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ባሌ ሀገረ ስብከት፥ ጎባ፤ ትራንስፖርት፤ ከቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ባሌ ጎባ፡፡ ፳፪. ባህር ዳር ቅድስት አርሴማ፤ ፳፫. ገደቢዬ አርሴማ፤ (ደባርቅ አጠገብ) ፳፬. ደባርቅ አርሴማ፤ (ሰሜን ጎንደር) የአድራሻ ምንጭ ---› ክብረ በዓላት /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like ሰላም ለዘአዕረፉ ምስሌኪ ፳ወ፯ቱ ሰማዕታት፤ ረድኤቶሙ ትረድ ላዕሌየ ዘምስለ ብዙኅ ምሕረት፡፡ ወኀበ ሀለወ ስሞሙ ምስለ ስምኪ ቅድስት፤ ዓዲ ኢይቅረብ አርሴማ ሕማመ ብድብድ ወሞት፤ በኵሉ አዝማን ወበኵሉ ዓመታት፡፡

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - Telegram 频道 @finotehiwott 的统计与分析