Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 336 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 643,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 190 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 336 名订阅者。
根据 13 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -75,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.35%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.54% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 428 次浏览,首日通常累积 1 616 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 25。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 14 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 336
订阅者
+224 小时
-47 天
-7530 天
帖子存档
#መዝሙር_ዘሰንበት_ምኵራብ
" ታቦት አክባሪው ዘማች "
የሙሉ ሰዓት ተውኔት
📆 የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
⌚️ ከቀኑ 10:30 ሰዓት
⛪️ በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
💵 መግቢያ :– 100 ብር
VIP :– 300 ብር
ፍቁረ እግዚእ ሰ/ትቤት ከ ፍኖተ ህይወት ሰ/ት/ቤት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ
👉 ትኬቱን ባሉበት ቦታ በቴሌ ብር 09 01 04 44 44
👉 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000658449633 መቁረጥ ይችላሉ‼
🔔ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ
ትጣላኛለህ። አልተውህም።
ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም።🔔
#ምስባክ_ዘቅድስት_እምሐሙስ_እስከ_ቀዳሚት_ሰንበት
ሰላም ለከ
ገብርኤል በነደ እሳት ሥዑል :: ሰላም ለከ ገብርኤል በጌራ ብርሃን ክሉል። ሰላም ለከ ገብርኤል መልአከ መዊዕ ወኃይል ሰላም ላከ ገብርኤል እንተ ክንፍከ ቀሊል። ጸልለኒ በክንፍከ እመንሱት ወኅጉል ። መልክዐ ገብርኤል
#ምስባክ_ዘቅድስት_እምሰኑይ_እስከ_ረቡዕ
እንኳን ለእመቤታችን ኪዳነ ምሕረት ዓመታዊ ክብረ በዓል (ቃል ኪዳን ለተቀበለችበት) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡
ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ፤
ፈለገ እሳት ወደይን እምአስጠመ ኵሎ፡፡
(ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡)
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲዖልን ካየች በኋላ ስለኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች የካቲት አሥራ ስድስት ቀንም በጎልጎታ ቦታ ቆማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች፡፡
ጸሎትና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ አገልጋይህ የምለምንህን ይህ ነው፡፡ መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ አብያተ ክርስቲያኔን ለሚሠሩ፣ ወይም ለታረዙ ለሚያለብሱ፣ ለተራቡ ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም የሚያጠጡ(በስሜ ለድሆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጡ) ፣ የታመመውንም የሚጎበኝ፣ ያዘነውንም የሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ የሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ በዓይን ያልታየውን በጆሮ ያልተሰማውን በጎ ዋጋ ስጣቸው፡፡ በአማላጅነቴም የሚተማመኑትን ሁሉ ከሲዖል ነፃ አድርጋቸው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረሃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽን ቃልኪዳን እንዳይታበይ በራሴ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡
#ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘየካቲት_16፤ #በዓለ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡
በሃገራችን በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመው፤ የ3ት ዐበይት አድባራት አብነት ነው፡፡ እነዚህም፤
1ኛ) የላይ ቤት፤ የደብረ መድኀኒት ዐቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት
2ኛ) የታች ቤት አብነት፤ የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ
3ኛ) የደፈጫ ኪዳነ ምሕረት አብነት ናቸው፡፡
እኛም ከላይ ከተጠቀሱት ውስጥ የዐቢየ እግዚእንና የበዓታን ይትበሃል አንድ ላይ በቅደም ተከተል አድረገን አዘጋጅተንላችኋል፤ የደፈጫ ከላይ ከተጠቀሱት ከ2ቱ በጥቂት ቀለም ብቻ የሚለይ በመኾኑ አላካተትነውም፡፡ ስለዚህ እንደ የደብራችሁ ይተበሃል የላይ ቤት ከኾነ ‹‹ዘዐቢየ እግዚእ›› የሚለውን፤ የታች ቤት ከኾነ ‹‹ዘበዓታ) የሚለውን እንድትጠቀሙ እናሳስባልን፡፡
መልካም ማኅሌት፡፡
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
ቅድስት፤ የዐቢይ ጾም ሁለተኛው ሳምንት ቅድስት ይባላል፡፡
‹‹ሰንበትየ ቅድስት›› የሚልና ይህን የመሰለ የሰንበትን ቅድስና የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በተጨማሪ ቅድስት የተባለበት ምክንያት ለ40 ቀን ጌታችን ጾም የጀመረበት ሳምንት ስለኾነም፤ ቅድስት ጾሙን ለማዘከር ቅድስት ተብሏል፡፡
‹‹የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ፡፡›› ዘዳ 20፥8 ይህን ቃል እግዚአብሔር በሊቀ ነቢያት ሙሴ ላይ አድሮ ተናግሮታል፡፡ ‹‹ዕረፍባት›› ያለው እግዚአብሔር የፍጥረቱን አቅም ስለሚያውቅ ነው፡፡ ስናከብር ለነፍስ ዕረፍትና ፍስሐን፤ ለሥጋ በረከት ሊያሰጡ የሚችሉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በመፈጸም የሚከበር ነው፡፡ በቤተክርስቲያን በመሰባሰብ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት /በመማር/፣ ንሰሐ ገብቶ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል፣ የተጣላ በማስታረቅ፣ ያዘነ የተከዘ በማረጋጋት በማጽናናት የታሰረን በመጠየቅ፣ በችግር የወደቁትን በመጎብኘት በአጠቃላይ በማቴ 25፥35-37 ላይ የተጠቀሱትን ምግባራት በመፈጸም ከተከበረ ከእግዚአብሔር ዘንድ የማያልቅ ዘላለማዊ በረከትን ያስገኛል፡፡ ኢሳ 56፡4-8 ይህችን ዕለት የናቁ ሰዎች በሞት ተቀጥተዋል፡፡ ዘኁ 15፡32-36፡፡
ሰንበትን እንደምናከብረው ኹሉ በየ49 ዓመታት ደግሞ እንኳን ሰው መሬትም ከሚያርሱባት እንድታርፍ ኢዮቤልዩ አድርጎ ሰጥቶናል፤ መሬትን ያለ እረፍት ከዘራንባት ፍሬ አትሰጥምና፡፡
በተጨማሪም በዚህ ሳምንት ቅዱስ ኾኖ ቅዱሳን ኹኑ ብሎ ያስተማረው የጌታችን ትምህርት የሚታሰብበት ሳምንትም ነው፡፡
፨ የዕለተ ሰንበት ክብር፤
በብሉይ ኪዳን፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከስራው ኹሉ አርፎበታል፡፡ ዘፍ 2፥3፣ ዘጸ. 20፥8
በሐዲስ ኪዳን፤ ጌታችን የተጸነሰባት፣ ትንሣኤውን የገለጠባት፣ ለሐዋርያት ጸጋ መንፈስ ቅድስ የሰጠባት፣ ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣባት....ወዘተ ናት፡፡ በአጠቃላይ ታላላቅ ሥራዎችን የሰራበት በመሆኗ ከሌሎች ቀናት ለይተን እናከብራታለን፡፡
ከምጽአት በኋላ ሌሎች ቀናት ሲያልፉ ዕለተ ሰንበት ባለማለፏ ለዘለዓለም ጸንታ በመኖሯ ነው፡፡ /ድርሳነ ሰንበት/ ምዕ 18፥3-7 በዕለተ ምጽዓት ከማያልፉ ነገሮች መካከል ቃሉ፣ ዕለተ ሰንበት፣ የሰው ልጅ ናቸው፡፡
ዛሬ ዛሬ የኀጢአት ሥራ ኹሉ ቀን ተለይቶ የሚፈጸመው (ዝሙት፣ ሴሰኝነቱ፣ መዳራቱ፣ ዘፈኑ) ወዘተ በዚች ቅድስት ዕለት ነው፡፡ ‹‹ይህን ኀጢአት ቅድስት በምትኾን በእለተ ሰንበት፣ በሰሞነ ሕማማት፣ የሚፈታም ወዮለት›› ይላል፡፡ /መጽሐፈ ፍትሐ ነገሥት/፤ የባልና ሚስት ሩካቤ ኃጢአት ባይሆንም በማይገባ ወቅት ይልቁንም በዕለተ ስንበት በሰሞነ ሕማማት በረቡዕና ዐርብ ከተፈጸመ ኃጢአት ነው፡፡
ኢሳ 58፥13-14 ‹‹ፈቃድህን በተቀደሰው ቀን ከማድረግ እግርህን በሰንበት ብትመልስ፣ የሰንበትንም ደስታ እግዚአብሔር የቀደሰው ክቡር ብትለው፣ የገዛ መንገድህን ከማግኘት ከንቱ ነገርንም ከመናገር ተከልክለህ ብታከብረው፣ በዚህ ጊዜ በእግዚአብሔር አፍ ተናግሯልና››
ሮሜ 14፡16 ‹‹ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል›› በማክበራችን ከእግዚአብሔር የምንቀበለው ዘላለማዊ ዋጋ ክብር አለና፡፡ ባለ ማክበራችን ደግሞ ቅጣት ጉዳት አለና ነው፡፡ ሰንበትን በሚገባ ለማክበር ቸሩ አምላክ ይርዳን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
#መዝሙር_ዘሰንበት_ቅድስት
#ምስባክ ዘዘወረደ እምሐሙስ እስከ ቀዳሚት ሰንበት
ዐጤ ኃይለ ሥላሴም ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ በኋላ በ6 ኪሎ ለሰማዕታቱ ሐውልት ቆመ መጀመሪያ የተሠራው አነስተኛ በመሆኑ ኋላ አሁን ያለው ትልቅ ተደርጎ ተሠርቷል፡፡ ቀኑ እንዳይረሳም ቤተ ሳይዳ ተብሎ ይጠራ የነበረው የካቲት 12 ሆስፒታል ተባለ፡፡ ከ8 ዓመት በኋላም የሰማዕታቱንም ዐፅም ሰብሰብሰበውና አፍልሰው በ4ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክብር እንዲያርፍና መቃብር ቤት እንዲሠራለት ተደረገ፡፡ በሐውልቱ ላይ ያለው ጽሑፍና ግጥም እንዲህ ይነበባል፤
#‹‹ዝንቱ ውእቱ ምዕራፈ አዕጽምቲሆሙ ለብዙኃን ኢትዮጵያውያን እለ ተቀትሉ በግፍዕ በእደዊሆሙ ለሕዝበ ኢጣሊያ ፋሽስታውያን አመ ፲ወ፪ ለየካቲት በ፲ወ፱፻፳ወ፱ ዓ.ም.፤ ወተቀትሎቶሙኒ ኮኑ በውግረተ አእባን ወበአብትር፥ በመክርይ ወበመስኤ፥ በመሕፄ ወበዕፀው፥ በመብረቀ ሐፂን ወበፀዓዕ፥ ወበውዕየተ እሳት ውስተ ቤቶሙ፡፡ ወበራብዕ ዓመት እምዘኮነ ዝንቱ ነገረ ግፍዕ ተመይጠ እግዚእነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እም ሀገረ ብሪታንያ በግርማ መዊዕ፤ ወአቲዎ ብሔሮሙ ሠረዎሙ ለጸላእትነ ወአቀመ ትእምርተ ግዕዛንነ፡፡ ወእምድኅረዝ አዘዞሙ ለኅሩያኒሁ ከመ ያስተጋብኡ አዕጽምቲሆሙ ለእሉ እለ ተቀትሉ በግፍዕ ወያንብርዎሙ ውስተ ዝንቱ መካን ቅዱስ ዘሕኑፅ ለዝክረ ነገር ወለዝክረ ስሙ፤ ወኮነ በዓለ ፍልሰቶሙ ወተጋብኦቶሙ ለእሙንቱ አዕጽምተ ምውታን በ፲ወ፬ ዓመተ በዓለ ንግሡ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትየጵያ አመ ፳ወ፫ ለጥቅምት በዕለተ ኀሙስ በ፲ወ፱፻፴ወ፯ዓ.ም.፡፡››
#ራስን ካንገት ላይ ቈራርጦ እየጣለ፤
በችንካር ቸንክሮ ሰው እየገደለ፤
ሰውን ከነቤቱ አብሮ እያቃጠለ፤
ማነው እንደ ፋሽስት በሰው ግፍ የዋለ?፡፡
ሥጋችንን ገድለው ሳይቀብሩ እየጣሉ፤
ስማችንን ገድለው ሊቀብሩት ከጀሉ፡፡
በዚህ ያልነበሩ ሐሰት እንዳይሉ፤
እሊህ አስከሬኖች ይመሰክራሉ፡፡
ይህን ታላቅ ስቃይ መከራና ግፍ፤
ሲያስታውስ ይኖራል የታሪክ መጽሐፍ፡፡
አትርሱት አንርሳው ያስታውሰው ዘራችን፤
ኢጣሊያ መሆኗን መርዛም ጠላታችን፡፡
እናንት አእጽምቶች ዕድለኞች ናችሁ፤
በኃይለ ሥላሴ ትንሣኤ አገኛችሁ፡፡
በአምባ አራዶም 50 ሺህ፣ በሽሬና በተንቤን 15 ሺህ ሰው ሙቶ 200 ሺህ ሰው ቆስሏል፡፡
በሚያዝያ 24/1928 ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ለተባበሩት መንግሥታት አቤቱታ ሊያቀርቡ ወደ ጄኔቫ ሄዱ፤ በሃገሪቱ ንጉሠ ነገሥቱ አለመኖሩን ጣሊያኖ ሲያውቁ በ3 ቀናት በመገስገስ በሚያዝያ 27 አዲስ አበባን ተቈጣጠሩ፡፡ በእነዚህ 3ት ቀናት ውስጥም ሽብር ዘረፈና ግድያ በአዲስ አበባ እጅጉን በርቶቶ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች የሆኑት አርበኞችም፤ ጎራዴ መዝዘው ነፍጥ ይዘው በተለያዩ ቦታዎች እምቢ ለሃገሬ በማለት ሸፈቱ፤ በጎጃም ዱር ቤቴ ያሉት ለጣሊያን ፋታ አልሰጥ አሉት፡፡ ራስ አበበ አረጋይ ግንቦት 6/1928ዓ.ም. ጅሩ ገብተው የአርበኝነት ተግባራቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ጀግኖች አርበኞችም እርስ በእርሳቸውም ተባበሩ፡፡ ለአብነትም ዋና ዋናዎቹ ከፊት መሪዎቹና አስተባባሪዎቹ ፊታውራሪ ዘውዱ አባ ኮራን፣ ዳዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ፣ ደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው፣ ፊታውራሪ በለው ቸርነት፣ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ፣ ግራዝማች ዘውዱ አስፋው፣ ባሻ ወልደ ጻድቅ ሲሆኑ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በጎጃም ታላቁቅ የጅግንነት ጀብዱ ከፈጸመው ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ጋር ሕብረት ፈጠሩ፡፡ ይህ ሕብረትም ለጣሊያን ፋታ ሲያሳጣው፤ በሌሎች ቦታ ላሉ ኢትዮጵያውያኝ ፈር ቀዳጅ በመሆኑ ሁሉም ይተባባርና እምቢ ለሃገሬ ይል ጀመር፡፡
ለምሳሌም፤ ሰኔ 1928ዓ.ም. የሆለታ የጦር አካዳሚ ምሩቃን(ዶ.ር ያለም ወርቅ በየነን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጦ)ና በውጭ ሃገር የተሰማሪ ሲቪሎች በመተባበር የመሠረቱት ‹‹‹ጥቁር አንበሳ›› አንዱ ነው፡፡ ‹‹ጥቁር አንበሳ›› ራስ እምሩን መሪው በማድረግ ብዙ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፤ ጣሊያን ደቡብ ኢትዮጵያን ለመያዝ ካቶሊካዊውን ደጃዝማች ሀብተ ማርያምን በመጠቀም ቦንጋ አውሮፕላኖቿን ስታሳርፍ የጥቁር አንበሳ ማኅበርም በቦንጋ አውሮፕላን ማረፊያ የሰራው ጀብዱ ግን ከሁሉም የላቀና የማይረሳ ነው፡፡
ስለ ታላቁ አርበኛ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ እንዲሁም ለጃዝማች ኃይሉ እንዲህ ተብሎ ተገጥሞላቸዋል፤
እውነተኛው ጀግና ኃይለ ማርያም፤
ስሙ እንዳይረሳ ጻፈልን በደም፡፡
እንዲህ ያለው ጀግና እንዲህ ያለ ወንድ፤
ጌጥ ይሆናቸዋል ለታሪኮች ዐምድ፡፡ የተባለለት
የደጃዝማች ኃይሉ እጁ ውድ ናት፤
የቀመሱ ሁሉ ሲያመሰግኗት፡፡
ሌላው ፋሽስትን በተባበረና ስልታዊ በሆነ መልኩ በሐምሌ 21/1928ዓ.ም. በአዲስ አበባ መቀመጫና መቆሚያ ያሳጡት የሸዋ አርበኞች ሲሆኑ አሰላለፋቸውም፤
በሰሜን አዲስ አበባ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች አበራ ካሣና ወንድወሰን ካሣ የሚመሩት ሲሆን በውስጡ ሰማዕት የሆኑትን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ያካተተ ነው፡፡
በሰሜን ምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በራስ አበበ አረጋይ የሚመራ፡፡
በምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው (አባ ተጫን)ና ነጋድራስ ቦጋለ የሚመራ፡፡
በደቡብ አዲስ አበባ፤ በደጃዘማች ባልቻ አባ ነፍሶ የሚመራ ሠራዊት ተጀምሯል፡፡ነገር ግን ወቅቱ ክረምት በመሆኑና ወንዞች በመሙላታቸው አርበኞች ተቀናጅተው እንዳይዋጉና ሕዝቡንም እንዳይቀሰቅሱ ትልቅ እክል ሁኖባቸው ነበር፡፡ በዚህም ሙሉ አዲስ አበባ ላይ አደጋ ጥሎ ጣሊያንን የማስለቀቁ ተግባር የታለመለትን ያክል ባየሳካም በጠቂት አቅጣጫዎች ጀግኖች አርበኞች ተዋግተዋል፡፡ የተወሰኑትም ወደ ፍቼ ሸሽተዋል፤ ታላቁ አባት ብፁዕ ጴጥሮስም የታያዙት በዚሁ ወቅት ነበር፡፡ ጀግኖቹም ጣሊያንን እምቢ ለሃገገሬ በማለት እስከ የካቲት 12/1929ዓ.ም. የጉያ ረመጥ ሁነውበታል፡፡
ከ1927-1934 ዓ.ም. ለ7ት ዓመታት ጣሊያን በሀጋረችን ላይ ያደረሰችው ጥፋት፤
*በኢትዮጵያ ሰሜንና ደቡብ በየቀለቡና በማደሪያው ከዘመተው የሞቱ፤
*ጠላት አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ዓረቦችና ዓርመኖች ግሪኮች ተዘርፈናል በማለታቸው ምክንያት የሞቱ፤
**የካቲት ሚካኤል (የካቲት 12) ዕለት በአካፋ በዱላ በእሳት ያለቁ የሞቱ፤
*በአርበኝነት በየጊዜው በጠላት እጅ የሞቱ፤
*በደኅንነት አገር ቤት ላይ ሳሉ ሳያስቡት በጠላት እጅ የሞቱ፤
*ወደ ስደት ሲሄዱ በችግር ምክንያት በየመንገዱ የሞቱ፤
*በፌርማቶሪ አመልካችነት በየቀኑ የሞቱ፤
*ጠላት ከኢትዮጵያ ሊወጣ ሲል በተደረገው ጦርነት የሞቱ፤
*ከጠላት ወገን ሆነው (ባንዳዎች) ሆነው ከተዋጉ ባንዳ የሞቱ፡፡
*ሞሶሎኒ ባነሳው ጦርነት በየቀኑ በሚደረገው የግፍ ሥራ ያላግባብ የሞቱ (በሆለታ ተማሪ ቤት የነበሩ ወጣቶች፣
#የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን)
ግራዚያኒ በናፖሊ መስፍን አልጋ ወራሹ ኡምቤርቶ ወራሽ በማግኘቱ ምክንያት ዐርብ የካቲት 12/1929ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚገኙ ድሃዎችንና ነዳያንን እንዲሰበሰቡ አደረገ፡፡ በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ቀትር ላይም ንግግር ማድረግ ሲጀምር በወቅቱ የተገኙትና የጣሊያን ፋሽስትነት ያንገፈገፋቸው አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ሰባት ቦንብ በግራዚያኑ ላይ ወረወሩ፤ በጥቃቱም ግራዚያኑ 365 ቦታዎች ላይ ቆሰለ /በይበልጥ እግሩ ቆሰለ/፣ 3ት ኢጣሊያናውያን ሞቱ፣ 50 ቆሰሉ፣ በተለይም የጦር አዛዡ አውራሊያ ሊአታ ከን ዓይኑ ጠፋ፡፡ በዚህም አንድም ኢትዮጵያዊ እንዳያመልጥህ ግደል በመታዘዙ በፋሽስት ኢጣሊያ በመትረየስ፣ .... በአካፋ ጭምር ሊረዳ የመጣውን ድሃና ነዳይን ጨምሮ 30 ሺህ የአዲስ አበባ ነዋሪ በሰዕትነት አረፈ፡፡ ይህ ግድያ ወደ ታላላቆቹ ገዳማትና አድባራትም በመዛመት በደብረ ሊባኖስ ያሉ 2200፤በዝቋላ ገዳምም 120 መነኰሳትና ምዕመናን ተረሸኑ፡፡ አስከሬናቸውንም ክብር ባለመስጠት በአካፋ በማንሳት አሰቃዩት፡፡ እንዲሁም 350 የሚጠጉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ወደ ሮምና ሞቃድሾ እስር ቤት ተላኩ፤ ከ2500 በላይ ደግሞ በእስር ቤት ታጉረው እንዲማቅቁ ተደረጉ፡፡ በእስረኞችና በምርኮኞች ላይም አሰቃቂ ድርጊቶችን ፈጽማለች፡፡
ፋሽስት ኢጣሊያ በ5ቱ ዓመት ወረራዋ ጀግኖች አርበኞችን ስላልቻለቻቸው ንጹሐን ዜጋዎችን በመግደል፤ እንዲሁም የተደበቁበትን ገድልና ዱር አላገኝ ስትል ገዳማትንና አድባራትን አቃጥላለች፡፡ እንደ ተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት 460 770 (በጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፋቸው ደግሞ 746 800 ሰዎችን በግፍ ገድላለች፤ 300ሺህ ሰዎች ደግሞ በስደት ሲንከራተቱ በረሃብ አልቀዋል፤ 2000 አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥላላች፣ በርካታ ንዋያተ ቅድሳትንም ዘርፋ ለካቶሊኳ ቫቲካን ሰጥታለች፡፡ ለአብነትም ካቃጠለቻቸው ገዳማትና አድባራት መካከል፤
*ይደመቆ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን /ሰሜን ሸዋ/
*አፈር ባይኔ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
*አክርሚት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
*ጎበጥ አገር ገብርኤል ቤ.ክ ሰሜን ሸዋ እም ምሕረት/
*አንኮበር ቅድስት ማርያም ቤ.ክ.
*ደረፎ ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. /ሰሜን ሸዋ ደረፎ/
*ጎንቻ መድኃኔ ዓለም ገዳም /ምሥራቅ ጎጃም/
*አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. ይገኙበታል፡፡ (ምንም እንኳን አልፎ አልፎ እንደ ማኅበረ ሥላሴ ያሉ ገዳማት አባቶች በጸሎታቸው አውሮፕላናቸውን እንዲከሰከሱ ቢያደርጉባቸውም)
ኢጣሊያ ላደረሰችው ጥፋት 326 ቢሊዮን ሊሬ ቢወሰንባትም የሰጠችው ግን 105 ቢሊዮን ሊሬ ብቻ ነው፡፡ (እንደ ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ ዘገባ ደግሞ 175 ሚሊዮን ስተርሊንግ ተወስኖባት የከፈለችው 25 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው)፡፡ በከፈለችው ገንዘብም የቆቃ ግድብ ብቻ ተሠርቶበታል፡፡
#ለየካቲት_12_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_ማስታወሻ
የአውሮፓ ኃያላን ሃገር ነን ብለው ራሳቸውን የሰየሙ አፍሪካን ሊቀራመቱ በተስማሙት መሠረት ጣሊያን ኢትዮጵያን ልትቀራመት ወሰኑ፡፡ ለዚህም ውሳኔ ያደረሳቸው ከሚስዮኖቿ አንዱና ተኩላው አባ ማስያስን(የጣሊያ ንጉሥ የቪክቶሪ ንስሐ አባትን ቀድሞ በትንሹ ራስ ዐሊ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የገባው) በአፄ ቴዎድሮስ ተባሮ፤ እንደገና በአፄ ዮሐንስ ዘመን ወደ ሃገራችን ገብቶ ነበር፤ አሁንም መልሰው አፄ ዮሐንስ ሲያብርሩት ለጣሊያን መንግሥት የኢትዮጵያን ልዩ መልክአ ምድሮችና በዓለም ላይ ልዩ ሃገር መሆኗን 2ት መጻሕፍት ጽፎ ለጣሊያን መንግሥት በማስረከቡ በዚሁ መሠረት ጣሊያኖች በመቋመጣቸው ነው፡፡
#የመጀመሪያው_ወረራና_ጦርነት
መጀመሪያ በ1861ዓ.ም. እግሯን ወደ ኢትዮጵያ በአሰብ በኩል አስገባች፤ በ17ዓመታት ቆይታ(እስከ 1878ዓ.ም.) ምጽዋን፣ የዳህላክ ደሴቶችንና የኤርትራን ቀይ ባሕር ያዘች፡፡ ምጽዋን በያዘ በ3ት ዓመታት ኤርትራን ያዘች፤ ኤርትራን በያዘች በ7 ዓመት መረብን ተሻግራ ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመግባት ጦርነት ከፈተች፡፡
ከኤርትራ ሲሻገሩ መጀመሪያ ጦርነት ያደረጉት በ1887ዓ.ም. በወርኃ ጥር በዶጋሊ ከአጼ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና ከሐማሴኑ ባላባት ከጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋ ጋር ነው፡፡ ጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋም ጠላትን ድል በማድረግ ወደ ምጽዋ መልሰውታል፡፡
ለራስ አሉላ አባ ነጋም እንዲህ ተብሎ ተግጠሞላቸዋል፡፡
‹‹የአሉላ ፈረስ የረገጣቸው፤
እስካሁን ድረስ አለ ቊስላቸው፡፡
የአሉላ ፈረስ ተስቦ ወርዶ፤
ያንን ነጭ ገብስ አረገው ነዶ፡፡››
ይህ አልሆን ሲላቸው በተወካያቸው በአንቶኔሊ በሚያዝያ 25/1881ዓ.ም. በውጫሌ (ወሎ ቦሩ ሜዳ የምትገኝ) ላይ የተፈረመውን የውል ስምምንት አንቀጽ 17 በአማርኛና በጣሊያንኛ ቅጂው የተሳሰተ (የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከውጭ ሃገራት ጋር የሚያደርገውንግንኙነት በኢጣልያ በኩል ማድረግ ይገባዋል!!፡፡›› በማድረግ
በየካቲት 1885ዓ.ም. ዐጤ ምኒልክ የውጫሌ ውል እንደማይሠራ ለአውሮፓ መንግሥታት ደብዳቤ ጻፉ፡፡ በዶጋሊ የተሸነፉትና በውጫሌ ውል አልሆን ያላቸው ጣሊያን በኅዳር 29/1888ዓ.ም. ጦርነት ከፈቱ ጀግኖች ኢትዮጵያኖችም ሻለቃ ቶዘሊንና ሌሎች ፋሽስቶችን እንደ ነፋስ ትቢያ አድርጎ በተናቸው፡፡ ቀጥለውም በየካቲት 23/1888ዓ.ም. ጠዋት 12 ሰዐት አመሻሽ 12 ሰዐት ባለቀው፤ እንኳን ለኢትዮጵያውይን ይቅርና ለአፍሪካውያን ኩራትና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የአድዋ /የሶሎዳ ተራራ/ ጦርነት በጀግናው መሪ በዐጤ ምኒልክ ድል አድራጊት ተጠናቀቀ፤ ጣሊያንም የሽነፈት ጽዋዋን ጠጥታ ተመለሰች፡፡፡ዐጤ ምኒልክም ሚያዝያ 15/1889ዓ.ም. ወደ መናገሻ ከተማቸው ሲመለሱ የማረኳቸወን ጣሊያኖች ዛሬ ‹‹ጣሊያን ሰፈር›› በሚባለው ቦታ አኖሯቸው፡፡ ‹‹የአዲስ አበባ ውል›› ተብሎ በሚጠራው በኢትዮጵያና በጣሊያን በተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ ምርኮኞቹን እንድትፈታ፤ የውጫሌ ውል መሠረዙና፣ ኢጣሊያ በኢትዮጵያ ላይ ጣልቅ እንዳትገባ፤ የኤርትራ ድበር እስኪከለል ጣሊያን ከጦርነቱ በፊት ባለችበት እንድትረጋ በሚል ተከናወነ፡፡
#ሁለተኛው_ወረራና_ጦርነት
ሁለተኛው ጦርነት ከ1929ዓ.ም.-1933ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ (ለዚህ ጦርነት ደግሞ መሠረቱ ጣሊያን የቀድሞ ሽንፈቷ ቂም በመያዟ ነው)፡፡ የተጀመረውም በኅዳር 26/1927ዓ.ም. በወልወል (የኢትዮጵያ ሶማሌ ክፍለ ሃገር በኦጋዴን ውስጥ በዋርዴር አውራጃ አካባቢ የምትገኝ ወረዳ ስትሆን ንጹሕ የከርሠ ምድር ውኃ የሚገኝባትም ነች፤ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ 350 ጥልቅ የውኃ ጕድጓድ አስቆፍረውላታል) ላይ ጣሊያን ባንዲራዋን በመትከሏ ምክንያት ነው፡፡ በዚሁም ምክንያጥ የአውራጃው ገዢ ፋውራሪ ዓለማየሁ ከጣሊያኑ ጦር አዛዥ ካፒቴን ችማሩታ ጋር ጦርነት ገጠመዋል፤ በጦርነቱም ጀግናው ፊታውራሪ ዓለማየሁ በፋሽስታዊ ታንክ ነጂ በገዛ ታንኩ ላይ ላይ ተወርውረው በመውጣት ሰይፈውታል፤ ብዙ የጀግንንት ሥራንም አከናውነዋል፤ ቆይቶ ግን ለሃገራቸው በጀግንነት እየተዋጉ ሣለ ከሌሎች 107 ኢትዮጵያውያን ጋር አርፈዋል፡፡ በዚህ ውጊያ ላይ አብዛኞቹ ሙስሊሞች ባንዳ በመሆን ለሃገራችን ጠላት ቢሆኑም (ለምሳሌ ሡልጣን ኢብራሂም አሰብን ለሮማ ልዑካን ሸጥኩላቸው የሚለውና፣ የአዳል ባላባት የራሄታ ሡልጣን ሐሰን ሙሐመድለሮማ ሚስዮናውያን የኢትዮጵያን ወደቦች እነሸጣለን ብሎ የመከረ)፤ ለሃገራቸው ሲሉ የተዋጉ የሙስሊም አርበኞችም ነበሩ፤ ዋነኞቹም ኑር ሑሴንና ደጃዝማች ዑመር ሰመትር ይጠቀሳሉ፡፡
በዚሁም ጣሊያን ‹‹ጅራፍ ረሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል›› እንደሚሉት ኢትዮጵያ ዜጎቹን ገድላብኛለችና 200 ሺህ ሊሬ ካሳ ትክፈለን ብለው ለመንግሥታቱ ማኅበር ከሰሱ፡፡ ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በድርድር ያልቃል ብላ ስትጠብቅ በጎን ግን ኢጣሊያ ለጦርነት ስትዘጋጅ ቆየች፤ በኅዳር 1927ዓ.ም የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስቴር ፒየር ላቫል ኢጣሊያ ከጀርመን ሂትለር ጎን እንዳትሰለፍ በማሰብ ኢትዮጵያን ብትወርር እንደማትቃወም አሳወቅ፤ ጦርነቱን የተቃመወችው ሩሲያ ብቻ ነበረች፡፡በመስከረም 22/1928ዓ.ም. ኢጣሊያ የመረብን ወንዝ ተሸግራ ጦሯን በ3ት መስመር አሰልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ገባች፡፡ ያገኘችውንም እያጠፋች እንትጮንና አዲግራትን በያዝ ዓድዋ ደረሰች፤ ለዚሁም አስተዋጽዖ ያደረጉላት ለግል ጥቅማቸው ያደሩ የኢትዮጵያ ጠላት የሆኑ ባንዳዎች ነበሩ ለአብነትም ዋነኞቹ (ደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ፣ ደጃዝማች ሀብተ ማርያም፣ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው) ናቸው፡፡ ባንዳ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው የጎንደርን ሕዝብ አሳምኖ ለኢጣሊያ ተገዢ ለማድረግ መንቀሳቀሱን ጀግናው አርበኛ ደጃዝማች ታደሰ ይማም ወንድይራድ ሲሰማ ያለበት ድረስ ደርሶ ድባቅ መትቶታል፤ ባንዳው እጅጉ በጣና ሐይቅ በታንኳ ተሸግሮ አምልጦ ወሎ ተደበቀ፤ ይህንንም ታላቁ አርበኛ ደጃዝማች ታደሰ ወሎ ድረስ ዘምቶና ከበባ አድርጎ ሃገሩን ለሸጠ ምሕረት አይገባውምና እንደ በግ አርደውታል፡፡
ጣሊያኖች በባንዳዎች በመታገዝ ጭምር በመርዝ ጋዝ ታግዘው በየካቲት 27 ከራስ ሙሉጌታ ጋር በተደረገው ውጊያ የራስ ሙሉጌታ ጦርን በመደምሰሳቸው በሐበሾች ዘንድ የሞራል ውደቀት አስከትሏል፡፡ ነገር ግን ጀግኖች አርበኞች እምቢ ለሃገሬ በማለት በተንቤን፣ በእንደርታ፣ በሽሬ፣ በአሸንጌ ላይ ተዋጉ፡፡ በአሸንጌው ጦርነት ጠላት ጣሊያን ከላይ በአውሮፕላን ጠላት ባንዳ ደግሞ ከታች በመሆን 8ሺህ የሚጠጉ አርበኞቻችን ላይ ጉዳት አደረሱ፡፡ በመጋቢት 24 ለ13 ሰዐታት በተካሄደው የማይቸው ጦርነት ላይ ኢትዮጵያውያን ድል አድረገው ጦርነቱ ማብቂያ ላይ የመርዝ ጋዝና የቦንብ ውርጅብኝ ከአውሮፕላን ላይ በማዝነብ ጀግኖች አርበኞቻችን አብዛኞች አለቁ፤ ከማይጨው የተረፉና በአሸንጌ ላይ የነበሩትን ጀግኖች አርበኞችን 150አውሮፕላን ደርሰው ደብደቡት በመትረየስም ፈጁት፡፡ (ጣሊያኖች ዚሁ ወረራቸው በሰሜን 300፣ በደቡብ 150 አውሮፕላን አዝምተዋል፡፡)
+4
‹‹የአካፋው ሚካኤል››፤ የካቲት_12
ለሁለተኛ ጊዜ ሃገራችንን ልትወር በመጣችው የጣሊያን የጦር ሹም የነበረውን ግራዚያኒን ለመግደል ጀግኖቹ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በጣሉት አደጋ ግራዚያኒ በመቁሰሉና አመራሮቹ በመሞታቸው የተቆጣው የጣሊያን ጦር በአዲስ አባባ በየካቲት 12/1929ዓ.ም. ለቅዱስ ሚካኤል ወርኋዊ በዓል በየቤተ ክርስቲያኑ የተገኙትን (ለምጽዋት የተሰበሰቡትን ጨምሮ)ና በየቤቱ በመግባት 30 ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ በአካፋ ጭምር እንደ ቅጠል አረገፏቸው፤ 30ሺህ ሰማዕታት በመባልም ይታወቃሉ፡፡ ከጥቂት ናት በኋላም የደብረ ሊባኖስ ገዳም መነኰሳትን አርበኞችን ደብቃችኋል በሚል በተቀደሰው ስፍራ ተረሸኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ጣሊያን ይህን አሰቃቂ ግፍ ስትሠራና የሰማዕታቱን የከበረ አካል በአካፋ በመሰብሰቧ ‹‹የአካፋው ሚካኤል›› በሚል መጠሪያ ይጠራል፡፡ በተለይም በ6 ኪሎ በመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ የቅዱስ ሚካኤል ታቦተ ሕግ ወጥቶ በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ (እናት ቤተ ክርስቲያን መቼውንም ቢሆን የሃገርና የቤተ ክርስቲያን ባለውለታዎችን አትዘነጋምና!!!!)
(እናቶቻችንና አባቶቻችን እንደነገሩን በቀጨኔ የሚገኙ አያቶቻችን የተሠዉና ግማሾቹም ይህንን ዜና ሲሰሙ ወደ 6 ኪሎ ከመሄድ የተመለሱ እንዳሉ ልብ ይሏል)፡፡
+4
‹‹የአካፋው ሚካኤል››፤ የካቲት_12
ለሁለተኛ ጊዜ ሃገራችንን ልትወር በመጣችው የጣሊያን የጦር ሹም የነበረውን ግራዚያኒን ለመግደል ጀግኖቹ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በጣሉት አደጋ ግራዚያኒ በመቁሰሉና አመራሮቹ በመሞታቸው የተቆጣው የጣሊያን ጦር በአዲስ አባባ በየካቲት 12/1929ዓ.ም. ለቅዱስ ሚካኤል ወርኋዊ በዓል በየቤተ ክርስቲያኑ የተገኙትን (ለምጽዋት የተሰበሰቡትን ጨምሮ)ና በየቤቱ በመግባት 30 ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ በአካፋ ጭምር እንደ ቅጠል አረገፏቸው፤ 30ሺህ ሰማዕታት በመባልም ይታወቃሉ፡፡ ከጥቂት ናት በኋላም የደብረ ሊባኖስ ገዳም መነኰሳትን አርበኞችን ደብቃችኋል በሚል በተቀደሰው ስፍራ ተረሸኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ጣሊያን ይህን አሰቃቂ ግፍ ስትሠራና የሰማዕታቱን የከበረ አካል በአካፋ በመሰብሰቧ ‹‹የአካፋው ሚካኤል›› በሚል መጠሪያ ይጠራል፡፡ በተለይም በ6 ኪሎ በመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ የቅዱስ ሚካኤል ታቦተ ሕግ ወጥቶ በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ (እናት ቤተ ክርስቲያን መቼውንም ቢሆን የሃገርና የቤተ ክርስቲያን ባለውለታዎችን አትዘነጋምና!!!!)
(እናቶቻችንና አባቶቻችን እንደነገሩን በቀጨኔ የሚገኙ አያቶቻችን የተሠዉና ግማሾቹም ይህንን ዜና ሲሰሙ ወደ 6 ኪሎ ከመሄድ የተመለሱ እንዳሉ ልብ ይሏል)፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
