ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 368 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 616 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 192 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 368 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 25 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -4، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 20.07‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.16‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 085 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 254 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 368
المشتركون
-124 ساعات
+357 أيام
-430 أيام
أرشيف المشاركات
ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ የሚቆይ የጸሎት መርኀ-ግብር ። #ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የሚቆይ #ጸሎት_አወጀች፡፡ በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን
ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ የሚቆይ የጸሎት መርኀ-ግብር ። #ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የሚቆይ #ጸሎት_አወጀች፡፡ በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ቅድስት ማርያም ገዳም ከተጠናቀቀነ በኋላ ሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሦስት ቀናት የጸሎትና የሱባኤ ጊዜ እንዲሆን አዋጅ መታወጁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል፡፡ #_#_#_#_#_#_#_ #በዚህም መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤታችን ከነገ #ሐሙስ (18/05/2015) ጀምሮ እስከ #ቅዳሜ(20/05/2015) የሚቆይ #የመሐረነ_አብ የጸሎት መርኀ-ግብር ስላዘጋጀ ሁላችንም #ከ11:30 ጀምሮ በመገኘት የጸሎቱ ተሣታፊ እንድሆን ይሁን ።

ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ የሚቆይ የጸሎት መርኀ-ግብር ። #ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የሚቆይ #ጸሎት_አወጀች፡፡ በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ቅድስት ማርያም ገዳም ከተጠናቀቀነ በኋላ ሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሦስት ቀናት የጸሎትና የሱባኤ ጊዜ እንዲሆን አዋጅ መታወጁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል፡፡ #_#_#_#_#_#_#_ #በዚህም መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤታችን ከነገ #ሐሙስ (18/05/2015) ጀምሮ እስከ #ቅዳሜ(20/05/2015) የሚቆይ #የመሐረነ_አብ የጸሎት መርኀ-ግብር ስላዘጋጀ ሁላችንም #ከ11:30 ጀምሮ በመገኘት የጸሎቱ ተሣታፊ እንድሆን ይሁን ።

ሰበር ዜና መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ በሕገ ወጥ መንገድ በተከናወነው "ሢመተ ጳጳሳት" በመሳተፋቸው በመጸጸት ይቅርታ ጠየቁ ! ተ.ሚ.ማ መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ በሕገ ወጥ መንገድ በተከናወነው "ሢመተ ጳጳሳት" በመሳተፋቸው በመጸጸት ይቅርታ ጠየቁ ! ጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ በሕገ ወጥ መንገድ በተከናወነው "ሢመተ ጳጳሳት" በመሳተፋቸው በመጸጸት ይቅርታ ጠየቁ። መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ የይቅርታ ደብዳቤያቸውን ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው የይቅርታ ደብዳቤያቸውን የተቀበሉ ሲሆን የቅዱስ ሲኖዶስን ምላሽ እንዲጠብቁ ምክር ለግሰዋል።

እንኳን ለቅድሱ ጊዮርጊስ ስባረ ዓፅሙ (ዝርወተ አጽሙ ) በሰላም አደረሳቹሁ ፠ ዐላውያን ነገሥታት በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የሊቀ ሰማዕቱን ሥጋውንና አጥንቱ በመንኰራኵር ፈጭተው በነፋስ ለበተኑበት፤ ነገር ግን ለአምላካችን የታመነ ሰማዕት በመሆኑ ያረፈበት መሬትና ዕፅዋት ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር እያሉ ያመሰገኑበት ነው፡፡ ------------ ....ነገሥታቱም ጊዮርጊስን ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡ ※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡ ※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡ ሙሉውን ታሪክ እዚህ ያንብቡ ----> https://t.me/medihanaelem/6273 ፠ እንደ ጎንደር አበራ ጊዮርጊስ ባሉት ክብረ በዓሉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርዶና አድሮ ነው በዓሉ የሚከበረው፡፡ በጎንደር በጥር ወር የሚከበሩ በዓላት ወደ ጥምቀተ ባሕር በመውጣት የሚከበሩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ጥር 18 አበራ ጊዮርጊስ፤ ጥር 21 ሎዛ ማርያም፣ ጥር 22 ቅዱስ ዑራኤል (በዓታ ያለው)፤ ጥር 25 ቅዱስ መርቆሬዎስ (በተለይ በገጠሩ አካባቢ፡፡) እርሱ እንደ ንብ አውራ ፈረሱ እንደ አሞራ፤ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያን አደራ፡፡ ሰአል ለነ ጊዮርጊስ፤ ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ ዘሐረፀከ ዱድያኖስ፤ ወወገረከ ደብረ ይድራስ፤ ዘዘረወከ በነፋስ፡፡

ዛሬ ከምሽት ጀምሮ ! በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዙሪያ የተመደቡት የመንግሥት ጥበቃዎች ተነሥተዋል። [ ትእዛዙ የማን እንደሆነ ባልታወቀ ሁኔታ ዛሬ ምሽት ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዙሪያ ጥበቃ ሲያደርጉ የቆዩ የመንግሥት የጥበቃ አካላት እንዲነሱ መደረጋቸውን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ገልጸዋል።

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የ"አባ" ሳዊሮስ ፣ የ"አባ" ኤዎስጣቴዎስን እና የ"አባ" ዜና ማርቆስን ማረፊያ ቤት አሸገ ! የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የ"አባ" ሳዊሮስ ፣ የ"አባ" ኤዎስጣቴዎስን እና የ"አባ" ዜና ማርቆስን ማረፊያ ቤት አሽጓል። በትናንትናው ዕለት 3ቱ አባቶች ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለመናድ እና ሲኖዶሳዊ አንድነትን ለመከፋፈል በማቀድ 26 መነኮሳትን ሾመናል በማለት መግለጫ መስጠታቸው ይታወሳል። ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

ጉባኤ ከለባቶቹ #የተመደቡበት_ሀገረ_ስብከት_እና_ስማቸው 1.አባ ገ/ማርያም ነጋሳ - አባ ገብርኤል - ምዕራብ ወለጋ 2.አባ ተ/ሃይማኖት ወልዱ - አባ ባስልዮስ - ድሬዳዋ 3.አባ ገብርኤል ወ/ዮሐንስ - አባ ጢሞቴዎስ -ጉራጌ ሶዶ 4.አባ ገ/እግዚአብሔር ታደለ - አባ ጳውሎስ - ምዕራብ አርሲ 5.አባ ሚካኤል ገ/ማርያም - አባ ኤልሳዕ - ከምባታ 6.አባ ኃይሉ እንዳለ - አባ ገሪማ - ምሥራቅ ሐረርጌ 7.አባ ተ/ማርያም ስሜ - አባ ተ/ሃይማኖት - ጉጂ ሊበን 8.አባ ኃ/ኢየሱስ መንግስቱ - አባ ዕዝራ - ከፋ 9.አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ - አባ ኢያሱ - ቄለም ወለጋ 10.አባ ጳውሎስ ከበደ - አባ ዳንኤል - ሀዲያ 11.አባ ኃ/ኢየሱስ ተስፋዬ - አባ በርሱማ - ምሥራቅ ወለጋ 12.አባ ገ/ኢየሱስ ገለታ - አባ ሚናስ - ሆሮ ጉዱሩ 13.አባ ጸጋዘአብ አዱኛ - አባ ኤጲፋንዮስ - ምሁር ገዳም የበላይ ኃላፊ 14.አባ ኃ/ማርያም ጌታቸው - አባ አቤል - ምዕራብ ሐረርጌ 15.አባ ወ/ጊዮርጊስ ኃ/ሚካኤል - በርተሎሚዎስ - ከሚሴ 16.አባ እስጢፋኖስ ገብሬ - አባ ራጉኤል - ባሌ ረዳት ጳጳስ 17.አባ ገ/መድኅን ገ/ማርያም - አባ ዑራኤል - ጎፋ ባስኬቶ 18.አባ ኃ/ሚካኤል ንጉሤ - አባ አኖሬዎስ - ጊኒር 19.አባ አብርሃም መስቀሌ - አባ ኒቆዲሞስ - ዳውሮ,ኮንታ 20.አባ ንዋየ ሥላሴ አክሊሉ - አባ ሀ/ማርያም - ምዕራብ ጉጂ 21.አባ ኪ/ማርያም ቶሎሳ - አባ ተ/ሃዋርያት - ጅማና የም 22.አባ ወ/ማርያም ጸጋ - አባ አብሳዲ - ቦረና 23.አባ አምደሚካኤል ኃይሌ - አባ መርቆሬዎስ - አሩሲ 24.አባ መርሐጽድቅ ኃ/ማርያም - አባ ደቅስዮስ - ጌዴኦ,ቡርጁ,አማሮ 25.አባ ሞገስ ኃ/ማርያም - አባ ኤፍሬም - መናገሻ.ጋራ መ/ዓለምና ,ደ/ፀሐይ ቅ ጊዮርጊስ የበላይ ኃላፊ 26.አባ ገ/ኢየሱስ ንጉሤ - አባ አልዓዛር - ቡኖ በደሌ