ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 394 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 590,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 197

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 394 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 21,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.61%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.23% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 327 次浏览,首日通常累积 1 576 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 394
订阅者
+124 小时
+307
+2130
帖子存档
#_26_ለዓለም ብርሃን የሆኑ #ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተ_ማርያም፡፡ :: ፩ኛ. #መብረቅ፣ ፪ኛ. #ቸነፈር፣ ፫ኛ. #ረሃብ፣ ፬ኛ. #ወረርሽኝ፣ ፭ኛ. #የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሃብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) ክብርት በሆነችው ጸሎቱና ምልጃው ይማርን ይጠብቀን፡፡ #ሰላም_ለጽንሰትከ_እማኅፀነ_ቅድስት_ዮስቴና፤ #በብሥራተ_ጻድቅ_ባሕታዊ_ሠናየ_ዜና፡፡ #ሀብተማርያም_ጴጥሮስ_ሐዋርያ_ወልደ_ዮና፤ #መሐረኒ_ምግባረ_ጽድቅ_ወጸግወኒ_ልቡና፤ #አፍቅሮ_ቢጽ_እኅሥሥ_ዘምስለ_ፍጽመት_ትሕትና፡፡ https://youtu.be/GIzYreXgSOY

✤ጨነቅ ዋሻ መድኀኔዓለም፤ በቅዱስ ላሊበላ በዋሻ ውስጥ እንደገና ፎቅ ተደርጎ የተፈለፈለ፤ በሰሜን ተራሮች (በራስ ደጀን) እግር ሥር የሚገኝ፤ በፓርክ ክልል ውስጥ በመኾኑ በብዙ ኢትዮጵያውያን የማይታወቅ፤ ነገር ግን ብዙ ተዓምራትን እጅጉን ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበት፡፡ ✤መናገሻ ጋራ መድኀኔዓለም፤ ግማደ መስቀሉ ያረፈበት፤ ቀድሞ የቅዳሴ ቤቱን ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቀድሞ የልደታ ቤ.ክ) በአካል በመገኘት በመስቀሉ የባረከው፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተገለጸና ቅዱስ ራጕኤል የማይለየው፤ በአረማዊው ግራኝ ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ ካህናቱን መነኮሳቱንና ምዕመናኑን እንደያዘ በምድር ውስጥ ገብቶ የተሰወረበት በሥጋ ዕረፍተ ሞት ያልተገቱ ሥውራን ግሩማን አበው የሚኖሩበት "ዛቲ ይእቲ አምባ ማርያም መካነ ክብሮሙ ወጸሎቶሙ ለቅዱሳን ወለነገሥታተ ኢትዮጵያ በሐ በልዋ ተሳለምዋ ጊሱ ሐቤሃ ኢትርሐቁ እምኔሐ" ብለው አበው ያወደሷት የጸሎት የአርምሞና የትኅርምት ቦታ፡፡ . ✤ገዳመ አባ ጽጌ ድንግል (መድኀኔዓለም ቤ.ክ)፤ ማኅሌተ ጽጌ የተደረሰበት ወሎ፤ ወግዲ፤ ወለቃ ወንዝ አጠገብ፤ የበረሃው ዕንቊ ገዳም፤ አባ ጽጌ ድንግል የፈለፈሉት ባለ 3 መቅደስ እጅግ ሰፊ ዋሻ ቤ.ክ፡፡ . ✤ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤ.ክ፥ አዲስ አበባ፤ በአዲስ አበባ ከተመሠረተ ከ1826 ዓ.ም ጀምሮ ፍልሰት ሳያጋጥመው በመቆየቱ፤ የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ቤ.ክ፡፡ (ነገር ግን በመሃል ፍልሰት እያጋጠማቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከ1600 ዓመታት በፊት ደብረ ኤረር፣ የካ ዋሻ ተክለሃይማኖትና /ኋላ የካ ሚካኤል/ በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን፤ እንዲሁም እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት መመሥረታቸውን ልብ ይሏል) ✤ታላቁ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን፤ (ስብስ፤ # የ111 ዓመታት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ የኢያሱ ደብር፡፡ ‹‹በወርቅ ወበዕንቊ ሥርጉት ደብረ ሰላም፤ ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ›› ለዛቲ ቤት ሣረራ ኢያሱ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት፤ ወፈጸመታ ንግሥት ዘውዲቱ፡፡ (ይህችን ደብረ ሰላምን በመጀመሪያ አቤቶ ኢያሱ /አልጋ ወራሽ ልጅ ኢያሱ/ (ክፍለ ያዕቆብ) በሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. መሠረታት፤ ንግሥት ዘውዲቱ አሁን ያለውን ሕንፃው ቤ.ክ ጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም አስፈጸመች፡፡) የብዙ ሊቃውንት መፍለቂያ፤ የላይ ቤት አቋቋም፣ የተክሌ ዝማሜና የሸዋና የራሱ የደብሩ ቀለም እንደ ወንዝ የሚፈስባት፤ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ቤተ መዘክር (Museum)ና ቤተ መጻሕፍት የሚገኙበት፤ ደብሩን ምዕመናኑ በአጸዱና በግርማ ሞገሱ ኹሌም የሚደነቁበት፤ ስዕለት ሰሚ ታቦታት ያሉበት፤ 4ት የሚጠጉ ፈዋሽ ጠበሎች የሚገኙበት፡፡ ጽዶቹ ሳይቀሩ #በ72 አርድዕት ቅዱሳን አምሳያ የተተከሉበት፤ በቀድሞ ዘመን መዐዛ ቅዳሴ የተሰኘው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ቅዳሴ በወርኃ ጽጌ የሚቀድስበት፤ 3 ጳጳሳትን ያፈራ፣ ……. ደብር ነው፡፡ ✣ ለደብረ ሰላም ይደልዋ ስብሐት፤ እስመ በውስቴታ ኀደረ መድኀኔዓለም (በደብረ ሰላም በውስጧ መድኀኔዓለም ስላደረ ምስጋና ይገባታል፡፡) በዓሉ በዚሁ ደብር በታላቅ ድምቀት ይከብራል፡፡

እንኳን ለጥቅምት መድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት ጥቂቶቹ፤ ፤ ስብስብ 1፤ ✤መቅደላ መድኀኔዓለም ✤ባሕር ዳር ድባንቄ መድኄኔዓለም ✤አዴት መድኃኔዓለም ✤አዲስ አምባ መድኃኔዓለም ከ1600 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው በግብፃዊው ጻድቅ አቡነ ሙሴ የተፈለፈለ የዋሻ ገዳም ✤በቅሎ አግት / ዝንጀሮ አስጨብጭብ/ ጨጨሆ መድኃኔዓለም ገዳም ✤ወንጪት መድኃኔዓለም በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግስት ተመስርቶ እስካሁን ድረስ ነብር በቤተ መቅደሱ እየኖረ በሚጠብቀው በታላቁ ወይን እንጨት ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ውስጥ የተሰራ ✤መቀሌ መድኃኔዓለም ✤አድግራት መድኃኔዓለም ወቅድስት ሥላሴ ወቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ብዙ ድንቅ ታሪክ ያለው ✤ደባርቅ መድኃኔዓለም ✤የሽረት መድኃኔዓለም እጅግ ተደንቀውና ተደምመው ምስጋናዎ ኢምንት ሆናብዎት የሚመለሱበት ✤ኮሶ በር መድኃኔዓለም ✤ሐረር መድኃኔዓለም ✤ምስካበ ቅዱሳን ጻድቃኔ ዋሻ መድኃኔዓለም ገዳም ✤እመኪና መድኃኔዓለም ገዳም በመናኔው ጻድቅ ንጉሥ በአጼ ካሌብ ልጅ በጻድቁ ንጉሥ በአጼ ገብረ መስቀል በ6ኛው መ.ክ.ዘ. የተመሰረተ ታሪካዊ ገዳም ✤በሬ አገር መድኃኔዓለም ገዳም 1000 ሜትር ፍልፍል ዋሻ ገዳም ✤ደብረ ታቦር መድኃኔ ዓለም ✤ደብረ ዘይት መድኀኔ ዓለም ቤ.ክ፤ ደብረ ዘይት ከተማ፤ ባቦጋያ አጠገብ ✤ ናዝሬት መድኃኔዓለም ✤ተከዜ መድኃኔዓለም ገዳም በ11ኛው መ.ክ.ዘ. የላስታ ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያም /ታላቁ ሐርቤይ/ ደቀመዝሙር እንደነ ነቢዩ ኤልያስና ወንጌላዊው ቅ.ዮሐንስም ሞትን ሳያይ እስከ ምጽዓተ ሐሳዊ መሲህ /ዳግም ምጽአተ ክርስቶስ ዋዜማ/ ድረስ የተሰወረው ጻድቁ አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን ከሰማይ ተቀብሎ የመሰረተው ንዑድ ክቡር የሆነ መካነ ጸሎት ወአርምሞ ወትኅርምት ✤ሬማ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም፦ በ1414 በአባ ኖብ የተመሰረተና የብዙ ቅዱሳን መካነ ጸሎት የነበረ በዘመነ ሱስንዮስ ሰማእትነትን የተቀበለቺው ጻድቅት ወሰማእት ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ አጽሟ ያለበትና የከበረና የማይሻር ቃልኪዳኑን ከአምላከ ቅዱሳን የተቀበለችበት እፁብ ድንቅ ሥፍራ ሲሆን የሰማእቷን ጨምሮ በርካታ ቅዱሳን አጽማቸው የሚገኝበት ጥንታዊ ገዳም __________________ በኢትዮጵያ የሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት፤ ፤ 1. ✤ዋሻ መድኃኔ ዓለም አቡነ ሙሴ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም 2. ✤አርብዓሐራ ምስካበ ቅዱሳን መድኀኔዓለም ገዳም(ምስካበ ቅዱሳን መድኀኔዓለም ገዳም)፦ ደመ ክርስቶስን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል የተቀበለበትን የብርሃን ጽዋ የሚያጥኑና ሌሎችንም ቅዱሳንን አጽም በንሥር አሞራ የተመሰለ የጌታ መልአክ በቀስተ ደመና ተከብቦ በቀን የሚያመጣበት እልፍ ታሪክና ብዙ የብዙም ብዙ ገቢረ ተአምራት የሚፈጸሙበት ለተፈቀደላቸውና እንደሚገባ ሆነው በቦታው ላይ በበጎ ኅሊና ለሚጸልዩ ምዕመናን ሥውራኑ እየተገለጡ ጥያቄያቸውን የሚመልሱበት ግርማ ያለው ክቡር ንዑድ የ40ዎቹ ቅዱሳን ሰማእታት መካነ ጸሎት የአቡነ ሐራ ግብፃዊ የቃልኪዳን ሥፍራ 3. ✤ጨጨሆ መድኀኔዓለም፤ ወሎና ጎንደር ድንበር ላይ 4. ✤በደሌ ደብረ ሣህል መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ ከ100 ዓመት በላይን ያስቈጠረ ጥንታዊ ቤ.ክ. 5. ✤ደሴ መድኃኔዓለም 6. ✤ወዘም ባሕታዊ መድኃኔዓለም፣ ፍቼ አጠገብ ሰሜን ሸዋ ———————————— ✤ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤ.ክ ✤ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምወደ.ት. ቅ. ገብርኤል ቤ.ክ ✤ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም፤ (ታቦተ ሕጉ ባይወጣም በሰዐታትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡)፤ 6 ኪሎ ✤አቃቂ ጋራው መድኀኔዓለም፤ ✤ረጲ መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም፤ረጲ ✤መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም፤ አቃቂ ክ/ከተማ ✤ደብረ ቅዱስ ደብረ ቀራሜሎስ ካራአሎ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ፤ የካ ክ/ከተማ ✤መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም፤ የካ ክ/ከተማ ✤ቦሌ ቡልቡላ ደብረ ገነት መድኀኔ ዓለም፤ቦሌ ቡልቡላ ✤ድልበር መድኀኔዓለም፤ ጉለሌ (ቶታል) ✤ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ.ክ ልደታ ሜክሲኮ ✤ደብረ ሳሌም ቦሌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤተ ክርስቲያን (የመድኀኔዓም ታቦት በድርብነት ይገኛል)፤ ቦሌ ✤ምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኀኔዓም ቤተክርስቲያን፤ቀበና ✤አያት መድኃኔዓለም፤ አያት ✤ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔዓለም፤ደቡባዊ አ.አ ✤ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን፤ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፡፡ ✤ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል ፡፡ ጎተራ ✤የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ወኢሉጣ ቤ.ክ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፤ ለገሃር ✤ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ፤ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፡፡ ✤ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም ቤ.ክ (የመድኀኔዓለምና የመብዓ ጽዮን ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ ኮተቤ(ሲምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል) ---------------------------------- በኢትዮጵያና በአሜሪካ የሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት፤ የፎቶ ስብስብ 7፤ 1. ✤ላፍቶ ሌንቃ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ 2. ✤መድኃኔዓለም ቤ.ክ፤ ደብረ ሊባኖስ አጠገብ 3. ✤የቲሊሊ ደብረ ገነት መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን 4. ✤ሚዛን ተፈሪ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን 5. ✤ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም 6. ✤ኒውዮርክ መድኀኔ ዓለም ___________________________

መታሰቢያዩን እንደ አንተ የሚያደርግ ሁሉ በየወሩ አምስት ሺህ ነፍሳት በዓርብ ቀንም ሥስት መቶ አርባ ነፍሳትን አወጣለታለሁ አለው፡፡ለአንተ ግን ስለ ስቅለቴ የኃጥአንን እኩሌታ እሰጥካለሁ አለው ፡፡ስምህን የጠራና በአንተ የተማፀነ ውንም አንተ ከሞትክ በኃላ መታሰቢያህንም ያደረገውን አንተ ከምታደርገው ከሞቴ መታሰቢያም ቁራሽ የበላውንም ወሬም ስምቶ በልቡ ደስ ያለውና የወደደውን ከሞቴ መታሰቢያ መድረስ ባይቻለውም እምረዋለሁ አለው፡፡ ይህንን በቅዱስ ሥጋውና ደሙ ማለለት፡፡ ስለ እናቱ ስለ ማርያምም ( ስለ እኔ ምን ትሰጠዋለህ ብላ በጠየቀችው ጊዜ ) በበዓልሽ ቀን አምስት ሺህ ነፍስ እምርለታለሁ አላት ፡፡ የሞቱን መታሰቢያ ስለማድረግ በየቀኑ ለመባዓ ጽዮንም 600 አሥራትን ሠጣቸው፡፡ በዚህ መሰረት ጥቅምት ፳፯ ቀን ለአቡነ መባዓ ጽዮን ቃልኪዳን የገባበት ቀን በመሆኑ በየዓመቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱ ጋር ይከበራል፡፡ ጽድቁ ነፍሱንም ጥቅምት 27 ለጌታ ሰጥቷል ፡፡ ዕድሜውም 74 ዓመት ነበር ፡፡ በ47 ዓመቱ ዲ/ን ሆኗል በ56 ዓመቱ ምንኵስናን ተቀብሏል ዳግምኛም በ65 ዓመቱ ቄስ ሆኗል ቄስ በሆነ በዘጠኝ አመቱ ዓርፏል፡፡ የጻድቁ አቡነ መባዓ ጽዮን በረከትና ረድኤት ይደርብን ቃል ኪዳኑ አይለየን ሃገራችንን ይጠብቅልን ፡፡፡፡ የመድኀኔዓለም ይቅርታውና ቸርነቱ ሁላችንንም ይጠብቀን አሜን! /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like ------------

#እንኳን ለመድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 #ጥንተ_ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ #መባዓ_ጽዮን (ተክለ ማርያም )ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በዲሜጥሮስ ቀመር መሠረት አጽዋማትን በጠበቀ መልኩ ከትንሣኤ በዓል በፊት ያለውን ዓርብ “ስቅለት” ተብሎ እንዲከበር አባቶቻችን ሥርዓት ሠርተዋል፡፡መጋቢት ፳፯ ቀን በዓቢይ ጾም ስለሚውል በዓቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለ ፤ ወደ ጥቅምት ፳፯ ተዛውሮ በፍስሐ በሓሴት እንድናከብረው ቤተክርስቲያን ሥርዓት ሰርታለች ። ይህንን በዓል የሚያከበር በመስቀሉ የተደገፈ ይሁን! የቅዱሳንንም በዓል የሚያደረግ በቅድስት ደብረ ጽዮን ከአነርሱ ጋር እንደሚነግሥ አልሰማችሁምን! የመድኀኔዓለምንም መታሰቢያ የሚያደርጉ በመንግሥተ ሰማያት ባለሟልነት አላቸው በየወሩም አምስት ሺህ ነፍሳት ከደይን ይወጣላቸዋል በየሳምንቱ ዓርብም ስለ ስቅለቱ ሶስት መቶ አርባ ነፍስ ይሰጣቸዋል፤ የዕንቁ የወርቅ አክሊልም ይሰጣቸዋል ፡፡ --------------------------------------------- ቅዳሴ ዮሐንስ “ሊቃነ መላእክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤ ኃጢያትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፤ በመኳንንት በሚፈርደው በርሱ ፈረዱበት” ፡፡ እንዲል ክርስቶስን አይሁድ ስቀለው ብለው ፈረዱበት አክሊልን የሚያቀናጀውን የነገሥታት ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስን አነገስንህ ብለውታልና ጭፍሮች በፍና ተሣልቆ የእሾህ አክሊል ደፉለት “ወጸፈሩ ሐራ አክሊለ ዘሦክ ወአስተቀጸልዎ ዲበ ርእሱ” ዮሐ ፲፱፥፪ ። ኢየሱስ ክርስቶስ የእሾኽ አክሊል በመቀዳጀቱ ዕፀ በለስን በልቶ “ምድር እሾኽንና አሜከላን ታበቅልብኻለች” ዘፍ ፫፥፲፰ ብሎ የፈረደበትን አዳም ስለርሱ ክሶ መርገሙን ደምስሶለታል ። መጋቢት ፳፯ ቀን ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ፤ የተሰቀለው የክብር ባለቤት ሰማይን የፈጠረ ነውና ፀሐይ ጨልማለች፣ ጨረቃ ደም ሆኗል፣ ከዋክብት ረግፈዋል። የተሰቀለው የክብር ባለቤት ምድርንም የፈጠረ ነውና በምድር የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለኹለት ተቀዷል፤ ምድር ተናውጣ ዐለቶች ተሠንጥቀዋል፤ መቃብራት ተከፍተዋል፤ ከ፭፻ በላይ ሙታን ተነሥተዋል (ማቴ ፳፯ )፡፡ ስቅለቱን በዲሜጥሮስ ቀመር አውጥተን የጌታን መከራውን አስበን በስግደት ሕማማቱን እናስባለን በዝክረ ጥንተ ስቅለቱ በጥቅምት ፳፯ ደግሞ በመስቀል የተደረገልንን አስበን እናመሰግነዋለን፡፡ የመድኀኔዓለም ይቅርታውና ቸርነቱ ሁላችንንም ይጠብቀን አሜን! /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ————————————————————————- አቡነ መባዓ ጽዮን (ተክለ ማርያም ) ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ ጋር ቤተ ክርስቲያን በ15ኛው መ.ክ.ዘ የነበሩትን አቡነ መባዓ ጽዮንን ታስባለች፡፡ አቡነ መበዓ ጽ ዮን ከእናታቸው ከጽዮን ትኩና ከአባታቸው ከ ሀብተ ጽ ዮን ተወልደዋል :: በአንዲት ቀን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብሎ ከቤተክርስቲያን ወጥቶ ይሄድ የነበረ ሰው እግሩን እንቅፋት ተመቶ ደሙ ከመሬት ሲፈስስ በአየ ጊዜ እውቀት በልጅነቱ የሞላ መባዓ ጽዮን የደማው ጣቱ እስኪደርቅ ድረስ ጠባው፡፡ በመሬት የፈሰሰ ደሙን ከአፈሩ ጋር በላ፡፡ ለጌታ ሥጋ እና ደም ያለውን ክብር አሳይቷል፡፡ የመጽሐፍ ቃል ያፀናው ወጣቱ መባዓ ጽዮን ከቤተሰቡ የመጣለትን የጋብቻ ጥያቄ ሳይቀበል የምንኵስና ሕይወቱን ጀምሯል፡፡ መንኵስናው ተጋድሎ የነበረባት ነች ይኸውም ትልቅ ድንጋይ በደረቱ ተሸክሞ ከምድር ከአመድ በተቀመጠም ጊዜ በራሱ ተሸክሞ፣ በሚሰግድም ጊዜ በጀርባው አዝሎ ስለ ክርስቶስ መከራ ያስባል፡፡ ራሱን ይበድላል፣ ስጋውን ያደክማል፡፡ ይኸውም ያለሰንበት እና ያለበዓላት በቀር በዚህ ተጋድሎ የምንኩስና ሕይወቱን ቀጠለ፡፡ ከዛም ወደ ደብረ ሊባኖስ በመሄድ ከአቡነ ተክለሃይማኖት መቃብር በረከትን ተቀብሏል :: አቡነ መባዓ መባዓ ጽዮን ራሱን ለእግዚአብሔር በሰጠ ቁጥር መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋ ወደሙ እየተገለፀ፤ እመቤታችንም እየታየች ትመክረው ታስተምረው ነበር፡፡ ቅዱሳንን ማክበር በዓላቸውን መዘከር እንዲገባ ከምንማርባቸው ታሪኮች አንድ የአቡነ መባዓ ጽዮን ታሪክ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን እና የእናቱን የቅድስት ድንግል ማርያምን በዓል አብዝቶ ያከብር ነበር፡፡ በዚህም መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ እና ከቅድሳን ጋር መጥቶ ባርኮታል፡፡ የመለኮት ምሥጢርም ሥርዓትም በአካባቢው ላሉ ሠዎችም ተሠጥቷቸዋል፡፡ መታሰቢያዩንም ለሚያደርግ በእኔ በአባቴ በመንፈስ ቅዱስም በእናቴ ማርያምም ዘንድ ስለ ሰው ፍቅር ከሰማይ ስለወረድሁ ክብርና ባለሟልነትን ያገኛል ብሎ የማይታበይ ቃሉን ነግሮዋቸዋል፡፡ ስላደረገው መታሰቢያም አምላካችን ከገዳም ከዋሻ በደመና በነፋሳት ቅዱሳንን ሰብስቦ ፣ ባህሩን ለሁለት ከፈለው አንዱን እሣት አንዱም ውሃ ሆኖ ቀረ፤ በእሣቱ መባዓ ጽዮንን እና ከመጡት ውስጥ ሁለት ቅዱሳንን አጥምቋል፡፡ መድኃኔዓለምም እጁን በመባዓ ጽዮንን ጭኖ ሌሎቹን ቅዳሳን እንዲያጠምቅ አዞት እርሱም አጥምቋል፡፡ ከሲኦልም እጅግ በጣም ብዙ ነፍሳት ሄዶ እንዲያወጣ አድርጎታል:: መናፍቃን በዓል ማክበር አይገባም ቢሉ የበዓል ማክበር ውጤቱ እዚህ ድረስ መሆኑን እናያለን፡፡ ለማሰብ የሚከብደውን የመድኀኔዓለምን ሥቃይ በራሱ ላይ በፈጸሙ ጌታችን ወደ ሰማይ ውስዶት ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ቆመ ፡፡ ብዙ ሀገሮችንም አሳየው የሚያስፈራ እና ጨለማ ገደልም አየ በውስጡም ብዙ ሰዎች ይወድቁ ነበር መድኃኔዓለምንም በጠየቀው ጊዜ ዘርዓ ያዕቆብን ያሙት ስለሆነ ተፈረደባቸው አለ፡፡ ስለ ብዙ ነፍሳትም ምሕረትን ለሞኖ ከሲኦል አስወጥቷል፡፡ ሁለት ነጫጭ ፈረሶችም በደመና አምሳል አየ የማናቸው ብሎ ቢጠይቀው የአንተና የዘርዓ ያዕቆብ ናቸው ወደ መንግሥተ ሰማያት ስትሄዱ ትቀመጡበታላቹህ አለው፡፡ እንዴት ከዘርዓ ያዕቆብ ጋር ልትደመርኝ ይገባኛልም ብሎ መበዓ ጽዮን በመድኀኔዓለም እጅግ ተደስቷል፡፡ በፀሎቱም ኦ እግዚኦ አንተ ትብለኒ ሰአል ኩሎ ዘፈቀድከ ወአነ እሁበከ፣ ጌታ ሆይ አንተ የወደድከውን ሁሉ ለምን እኔ እሠጥሃለሁ አልከኝ፡፡ አሁንም የለመንኩን ግለጽልኝ በማለት የቀራንዮን መስቀል መከራውን ያሳየው ዘንድ ሁልጊዜ ይለምን ነበር፡፡ የለመኑትን የማይነሳ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን የሆኑ እጆቹን በመስቀሉ እንዲዘረጋ፣ እግሮቹም እንዲቸነከሩ፣ የሾህ አክሊልም በራሱ ተሸክሞ የጥቅምት 27 ቀን ታየው፡፡ ለሙሴ ሊታያቸው እንዳልቻለ አባ መባዓ ጽዮን ከመሬት ወደቀ፡፡ እንደ ሞተም ሆነ፡፡ ማንም የመስቀሉን መከራ ሕማሙን ማየት እንደማይችል ነገረው፣ በቸርነቱም አነሳው፡፡ የሞቱ ገናንነት የሚያስፈራ እና የሚያስደነግጥ መሆኑን አሳውቀው፡፡ መከራው ታላቅ ፣ በሰው አእምሮ አይታሰብምና ነው፡፡ የጌታችንን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ዘወትር ስለሚያለቅሱ ዐይናቸው ጠፍቶ ነበር፡፡ ነገር ግን እመቤታችንቅድስት ድንግል ማርያም የብርሃን ጽዋ ይዛ መጥታ ዐይናቸውን ቀብታ አድናቸዋለች፡፡ በዚህ የተነሳ ‹‹በትረ ማርያም›› እየተባሉ እንደሚጠሩ ገድላቸው ያስረዳል እኚህ ቅዱስ አባታችን ተክለ ማርያምም ይባላሉ ይህም በልጅነታቸም ስለ እመቤታችን ስዕል በነበራቸው ፍቅር ነው ፡፡

ለአባታችን ማስታወሻ ይሆን ዘንድ በሰ/ት/ቤቱ አዘጋጅነት እና በአጋፋራ ይሁኔ ቤተሰቦች ረዳትነት ያሳተምነው የጸሎት መጽሐፍ .
+1
ለአባታችን ማስታወሻ ይሆን ዘንድ በሰ/ት/ቤቱ አዘጋጅነት እና በአጋፋራ ይሁኔ ቤተሰቦች ረዳትነት ያሳተምነው የጸሎት መጽሐፍ .

#አባታችንን_ዓመት_እስከ_ዓመት_ስናስታውሳቸው_እንኖራልን ፡፡ አምላካችን መድኀኔዓለም ከደጋጎቹ አባት ከአብርሃም ከይስሐቅ ጋር ይደምርልን! አሜን!
+8
#አባታችንን_ዓመት_እስከ_ዓመት_ስናስታውሳቸው_እንኖራልን ፡፡ አምላካችን መድኀኔዓለም ከደጋጎቹ አባት ከአብርሃም ከይስሐቅ ጋር ይደምርልን! አሜን!