ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 406 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 570,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 189

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 406 名订阅者。

根据 12 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 76,过去 24 小时变化为 7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.12%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.38% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 871 次浏览,首日通常累积 1 446 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 13 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 406
订阅者
+724 小时
+347
+7630
帖子存档
(ሃገረ ስብከቱ ደብዳቤውን ለሚመለከታቸው አካላት (ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት፣ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ ለሀገረ ስበከቱ የተለያዩ ክፍሎች፣ ለወረዳውና ለክልሉ አስተዳደር አካላት፣ ጸጥታ አካላትና ለሚዲያ አካላት) ግልባጭ ድርጎ ጽፏል፡፡) (የለጠፍናቸው ደብዳቤዎች፤ ሀገረ ስብከቱ የገዳሙን ሀብትና ንብረት በአግባቡ መዝግበው ሪፖርት እንዲያደርጉ ለአባ ዮሐንስ የጻፈውን፤ ሀገረ ስብከቱ ለፀረ ሙስና ኮሚሽን የጻፈውንና አባ ዮሐንስን ያገደበት ደብዳቤዎች ናቸው፡፡)

#እንወያይበት፡፡ #በእንተ_አባ_ዮሐንስ_ተስፋ_ማርያም_ /ጽሑፉን ሳታነቡ አስተያየት ባትሰጡ ይመከራል፡፡/ ያያችሁትን፥ የሰማችሁትንና የምታውቁትን ብትጽፉም እንዲሁ ይመከራል፥ ውይይታችን ሁሉ እውነቱን እውነት፥ ሐሰቱን ሐሰት በማለት ይሁን እንጂ፤ በጭፍን ድጋፍና ጥላቻ አይሁን!!!፡፡/ እኛ ግን ባየነው ደብዳቤ (የደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት የደራ ወረዳ ቤተ ክህነትን የጻፈለትንና መነሻ በማድረግና ራሱ ሀገረ ስብከቱም የጻፋቸውን ደብዳቤዎች)፤ እንዲሁም በሰመናውና ባየነው ቪዲዮ (አባ ዮሐንስ በታጣቂ ገበሬዎች ታጅበው የሰጡትን የቪዲዮ ንግግር) መነሻ አድርገን ይሄን ጽፈናል፡፡ #ጥር_3/2011ዓ.ም. #የደቡብ_ጎንደር_ሃገረ_ስብከት_በጻፈው_ደብዳቤ፤ *ገዳሙ የሚገኝበት የደራ ሐሙሲትና የአፈር ውኃ እናት ወረዳ ቤተ ክህነት ጥምር ኮሚቴ በነሐሴ 18/2010ዓ.ም. በቊጥር ደ/ወ/ቤ/ክ/340/2010 ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እንዲከበርና የገዳሙ ሀብት ንብረት እንዲመለስ መመሪያ ቢሰጥም ምላሽ ባለመሰጠቱና ከ2004ዓ.ም. ጀምሮ ሃገረ ስብከቱ ለአባ ዮሐንስ በሥርዐተ ገዳም እንዲመሩ በተደጋጋሚ መመሪያ ቢሰጣቸውም እርሳቸው ግን በዚሁ በአበው ሥርዐተ ገዳም ሊመሩ ባለመፈለጋቸውና ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምሕሮና ከሥርዐተ ገዳም ውጭ ራሳቸውን ከቅዱሳን በላይ በማድረጋቸው ደብዳቤውን እንደጻፈ ይገልጻል፤ *ሃገረ ስብከቱም በኅዳር 7/2011ዓ.ም. በቊጥር ደጎ/ሀስ/464/2011 የገዳሙን ሀብት ንብረት እንዲያስመዘግቡ ቢታዘዙም ማንም አያዘኝም በማለት ሪፖርት ሳያደርጉ ቆይተዋል፡፡ ይህንንም ለማስተካከል ይቻል ዘንድ በታኅሣሥ 17/2011ዓ.ም. ወደ ሃገረ ስብከቱ ሲጠሩ ጠበልተኞችን ሰብስቦ በማምጣት የሰላም ችግር በመፍጠርና፤ የሃገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል የሚመሩትን ስብሰባ በመርገጣቸው፤ የሃገረ ስብከቱ የአስተዳደር ጕባኤ በታኅሣሥ 24/2011ዓ.ም. ተሰብስቦ ባጠፉት የዶግማና ቀኖና ጥሰት እንዲሁም የገዳሙን ሀብትና ንብረት በግለሰቦች ስም በማድረጋቸው እንዲጠየቁ ወስኗል፡፡ አስተዳዳር ጕባኤውም ይህንን ለሚመለከታቸው አካላት፣ ለአባ ዮሐንስና ለገዳሙ በደብዳቤ አሳውቋል፤ ነገር ግን አሁንም አባ ዮሐንስ በሀገረ ስብከቱ ላይ በመዛትና በማስፈራራት ሁከት እየፈጠሩ እንዲሁም አንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ሽፋን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በአባ ዮሐንስ ላይ እንዲጣራባቸው የአስተዳደር ጕባኤው የወሰናቸው ጉዳዮችም የሚከተሉት ናቸው፤ #በመስቀል ላይ ከሚቀረጸው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ(ኢ.ና.ን.አ) ስም ይልቅ የአባ ዮሐንስ ስም እየተቀረጸበት እየተሸጠ በመገኘቱ፤ (የጽሑፉ አዘጋጆች ልዩ ምልከታ፤ ማንኛውም ምዕመን የአንገት መስቀሉ ላይ /በተለይ ወደ አኵሱም የሚሄድ ምዕመን/ የራሱን ስም ማስቀረጽ ሥርዐተ ቤ.ክ. አይደለም!!! መስቀል ላይ ሊጻፍ የሚገባው ስም ኢ.ና.ን.አ. የሚለው የአምላካችን ስም ነው፡፡!!) #በስዕለ አድኅኖ ፈንታ የአባ ዮሐንስ ፎቶ ግራፍ የገዳሙ ማኅተም እየታተመበት በ50 ብር እየተሸጠ መገኘቱ፤ #ሥርዐተ ገዳም በማይፈቅደው ሁኔታ በገዳሙ ውስጥ መኖር የማይገባቸውን ሰዎች እንዲኖሩ በማድረጋቸው፡፡ #ቅዱስ ጊዮርጊስ የተጋደለው 7 ዓመታት ነው፤ እኔ የገተጋደልኩት 30 ዓመት ነው፡፡ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ያጠመቀው ጌታችንን ብቻ ነው፤ እኔ ግን ያጠመኩት ዓለምን ሁሉ ነው፡፡ ስለዚህ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፥ ከቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ እኔ እበልጣለሁ በማለት እያስተማሩ መሆናቸው፡፡ #ስግደት የሚገባው ለቅዱሳን ስዕላትና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቢሆንም በቤተ ክርስቲያኑ በር ላይ የአባ ዮሐንስ ፎቶ ተደርጎ እየተሰገደለት በመሆኑ፡፡ #መስከረም 1 ቀን የአባ ዮሐንስ ልደት በሚል ሰበብ ከ5ት በላይ በሬ እየታረደ የገዳሙ ሀብትና ንብረት እየባከነ መሆኑ፡፡ (የጽሑፉ አዘጋጆች ልዩ ምልከታ፤ ሲጀመር ልደትን ያለቅጥ ማክበር የክርስቲያን ወይስ የአሕዛብ ጠባይ ነው!!!????) #በቤተ ክርስቲያን ሁል ቀንም፥ ሁል ጊዜም፤ የፈውስ ቀን፥ የበረከት ቀን ቢሆንም፤ የፈውስ ቀን በሚል የቤተ ክርስቲያንን የፈውስ ቀን በጥቂት ቀናት እንዲወሰኑ ማድረጋቸው፡፡ #የገዳሙ ጥሬ ገንዘብ በማን ስም እንዳለና ንብረቶቹ በዝርዝር የማይታወቁ በመሆናቸው #በሃገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅና ሠራተኞች ላይ ማስፈራሪያና ዛቻ እያደረሱ በመሆናቸው ምክንያት ሃገረ ስብከቱ ደብዳቤውን ለሚመለከታቸው አካላት (ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት፣ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ ለወረዳውና ለክልሉ ጸጥታ አካላትና ለሚዲያ አካላት) ግልባጭ አድርጎ ጽፏል፨ #ስለ_አባ_ዮሐንስ_መታገድና_ከአስተዳዳሪነት_መነሣትን_በተመለከተ #የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በየካቲት 07/2011ዓ.ም. ባካሄደው የአስተዳደር ጠቅላላ ጕባኤ የደራ ወረዳ ቤተ ክህነት አባ ዮሐንስን አግዶ እገዳው ይጽናልኝ ሲል የጻፈውን የይታገድልኝ ደብዳቤ በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ አጽድቋል፡፡ የማገጃ ደብዳቤውም የሚከተሉትን ነጥቦች አካቷል፤ **የከተማውን ሕዝበ ክርስቲያን በመከፋፈል ከፍተኛ የሆነ ችግር እየፈጠሩ ስለሚገኙ፤ **በቅዳሴ ጊዜ ጠቅጥቀው(ረግጠው) በመግባት ለምዕመናን እንቅፋት በመሆንና ራስዎትን እንደ መላእክት በመቊጠር ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በማፍለስ፤ ከቅዱሳን በላይ ነኝ እያሉ ሕዝበ ክርስቲያኑን በማደናገርዎ፤ **እኔ ከቅዱሳን እበልጣለሁ እያሉ ለምሳሌ ‹‹መጥምቁ ዮሐንስ ያጠመቀው ጌታን ብቻ በዮርዳኖስ /ነው/፤ እኔ ግን ዓለም ዞሬ አጠመኩ፤ ስለዚህ እኔ እበልጣለሁ በማለት ከሥርዐተ ቤተ ክርቲያን ውጭ ትምህርት በማስተላለፍዎ፤ **ከሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ውጭ የፈውስ ሥርዐት በማለት ምዕመናኑን እያደናገሩና ግራ እያጋቡ መሆንዎት፤ **መስቀል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሁኖ ያዳነበት ሲሆን፤ እርስዎ ግን ከክርስቶስ መስቀል ላይ ስምዎትን በማስቀረጽና የእርስዎን ፎቶ እንደ ስዕለ አድኅኖ በገዳሙ ማኅተም በማስደገፍ እየሸጡ ምዕመናንንበማደናገርና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እያፋለሱ በመገኘትዎ፡፡ **ቃለ ዐዋዲው ከሚያዘው ሥርዐት ውጭ በመሆን የቤተ ክርስቲያኒቱን ሀብትና ንብረት ጉዳዩ የማይመለከታቸውን ግለሰቦች በመሰብሰብ ንብረቱን እያባከኑና አላግባብ የልደት ቀን በማለት ገንዘቡን እያባከኑ መገኘትዎ፤ **የቤተ ክርስቲያኒቱ ቃለ ዐዋዲ ከመቶ ሃያ ፐርሰንት ለወረዳ ቤተ ክህነት እንዲከፈል ቢያዝም፤ እርስዎ ግን ከቃለ ዐዋዲው መመሪያ ውጭ በመሆንዎና በአጠቃላይ በቤተ ክርስቲያኗ መንፈሳዊም ሆነ ማኅበራዊ አገልግሎት ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩ መሆኑን ጠቅሶ የደራ ወረዳ ቤተ ክህነት በቊጥር 62/20011ዓ.ም. በቀን 03/04/2011ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ መሠረት ሃገረ ስብከቱ እርስዎ እየፈጸሙ ያሉት ድርጊት የሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ጥሰት፣ የገዳመ ሀብትና ንብረት ብክነትና ለማይመለከታቸው የገዳሙን ቋሚ ሀብትና ንብረትን መስጠት #ካጣራ_በኋላ_የአስተዳደር_ጕባኤው_ባደረገው_ስብሰባ_በሙሉ_ድምፅ_እግዳውን_አጽንቷል፤ ስለዚህ በእጅዎ ያሉትን የገዳሙን ማንኛውም ንብረት እንዲያስረከቡ በጥብቅ እየገለጽን፤ የደራ ወረዳ ቤተ ክህነት ርክክቡን እንዲያስፈጽም፤ /በሀገረ ስብከቱ/ ሊቀ ጳጳስ ደብሩን በቋሚነት የሚመራ አስተዳዳሪ እስኪመደብ ድረስ፤ ደብሩን በአግባቡ የሚመራ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ወክሎ እንዲያቀርብ በዚህ ደብዳቤ (በየካቲት 07/2011ዓ.ም. በቊጥር ደጎ/ሀስ/831/2011) የታዘዘ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

#ጀግናውና_የቅኔው_አዝመራ_አለቃ_መርሻ_ወልደ_ማርያም ከዚህ በታች የቀረበውን ግጥማዊ ቅኔ ብዙዎቻችን እናውቀዋለን፡፡ ሊገድሏቸው የመጡትን ጣልያኖች አብዛኛውን ፈጅተው በሐምሌ 12/1928ዓ.ም. በሰማዕትነት ያረፉት የ70 አዛውንቱ ጀግናና የቅኔው አዝመራ አለቃ መርሻ ወልደ ማርያም ከመሞታቸው ከ8 ቀን ቀድመው እንዲህ ብለው ተቀኙ፡፡ ተምሮ ተምሮ ካልሰበሰቡት፤ እንዴት ያሳዝናል ሲባክን ዕውቀት፡፡ ሂጅ ተመለሽ ግቢ አገርሽ ቅኔ፤ ወንዶች ከዋሉበት መዋሌ ነው እኔ፡፡ ለጀግንነታቸውም መታሰቢያ የሚቀጥለው ግጥማዌ ቅኔ ቀረበላቸው፤ አለቃ መርሻ አይፈራም እጁ፤ ጠላት ሲጋበዝ እንደ ወዳጁ፤ ገሥግሠው ሄደው እንደ ጐመጁ፤ በሽጉጥ ጠርሙስ ፩ድ ፩ዱን ፈጁ፡፡ መርሻ ቢያጠጣው የሽጉጥ ጠላን፤ ወዲያው ወደቀ ግብዙ ጣሊያን፡፡ /ቢያነቧቸው ስለ የካቲት 12ና ስለ 5ቱ ዓመት የመከራ ዘመን በርካታ ቁም ነገርን ያስጨብትዎታል፤/ #አምስቱ የመከራ ዘመናት፣ ቅጽ 1፤ 44 የተመዘበሩ. የተቃጠሉና የጠፉ አብያተ ክርስቲያናት ታሪክ፣ እርቅይሁን በላይ፣ 2007 #“The Massacre of Debre Libanos, Ethiopia 1937” (“የደብረ ሊባኖስ እልቂት)፣ ኢያን ካምፕቤል፣ # "ሕይወቴ(ግለ ታሪክ)" ተመስገን ገብሬ፤ #የሸንቁጥ ልጆች፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ #"Yekatit" 12 Revisited: new light on the strike against Graziani Author(s): Ian Campbell Source: Journal of Ethiopian Studies, Vol. 40, No. 1/2, Festschrift Dedicated in Honour of Prof. Richard Pankhurst & Mrs. Rita Pankhurst (June-December 2007), pp. 135-154 /ታሪኩን ከመጻሕፍት አገላብጦና ምሁራንን ጠይቆ ላቀረበልን አምላከ ኢትዮጵያ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በእድሜ በጤና ይጠብቅልን፡፡/

ዐጤ ኀይለ ሥላሴም ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ በኋላ በ6 ኪሎ ለሰማዕታቱ ሐውልት ቆመ መጀመሪያ የተሠራው አነስተኛ በመሆኑ ኋላ አሁን ያለው ትልቅ ተደርጎ ተሠርቷል፡፡ ቀኑ እንዳይረሳም ቤተ ሳይዳ ተብሎ ይጠራ የነበረው የካቲት 12 ሆስፒታል ተባለ፡፡ ከ8 ዓመት በኋላም የሰማዕታቱንም ዐፅም ሰብሰብሰበውና አፍልሰው በ4ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክብር እንዲያርፍና መቃብር ቤት እንዲሠራለት ተደረገ፡፡ በሐውልቱ ላይ ያለው ጽሑፍና ግጥም እንዲህ ይነበባል፤ #‹‹ዝንቱ ውእቱ ምዕራፈ አዕጽምቲሆሙ ለብዙኃን ኢትዮጵያውያን እለ ተቀትሉ በግፍዕ በእደዊሆሙ ለሕዝበ ኢጣሊያ ፋሽስታውያን አመ ፲ወ፪ ለየካቲት በ፲ወ፱፻፳ወ፱ ዓ.ም.፤ ወተቀትሎቶሙኒ ኮኑ በውግረተ አእባን ወበአብትር፥ በመክርይ ወበመስኤ፥ በመሕፄ ወበዕፀው፥ በመብረቀ ሐፂን ወበፀዓዕ፥ ወበውዕየተ እሳት ውስተ ቤቶሙ፡፡ ወበራብዕ ዓመት እምዘኮነ ዝንቱ ነገረ ግፍዕ ተመይጠ እግዚእነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እም ሀገረ ብሪታንያ በግርማ መዊዕ፤ ወአቲዎ ብሔሮሙ ሠረዎሙ ለጸላእትነ ወአቀመ ትእምርተ ግዕዛንነ፡፡ ወእምድኅረዝ አዘዞሙ ለኅሩያኒሁ ከመ ያስተጋብኡ አዕጽምቲሆሙ ለእሉ እለ ተቀትሉ በግፍዕ ወያንብርዎሙ ውስተ ዝንቱ መካን ቅዱስ ዘሕኑፅ ለዝክረ ነገር ወለዝክረ ስሙ፤ ወኮነ በዓለ ፍልሰቶሙ ወተጋብኦቶሙ ለእሙንቱ አዕጽምተ ምውታን በ፲ወ፬ ዓመተ በዓለ ንግሡ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትየጵያ አመ ፳ወ፫ ለጥቅምት በዕለተ ኀሙስ በ፲ወ፱፻፴ወ፯ዓ.ም.፡፡›› #ራስን ካንገት ላይ ቈራርጦ እየጣለ፤ በችንካር ቸንክሮ ሰው እየገደለ፤ ሰውን ከነቤቱ አብሮ እያቃጠለ፤ ማነው እንደ ፋሽስት በሰው ግፍ የዋለ?፡፡ ሥጋችንን ገድለው ሳይቀብሩ እየጣሉ፤ ስማችንን ገድለው ሊቀብሩት ከጀሉ፡፡ በዚህ ያልነበሩ ሐሰት እንዳይሉ፤ እሊህ አስከሬኖች ይመሰክራሉ፡፡ ይህን ታላቅ ስቃይ መከራና ግፍ፤ ሲያስታውስ ይኖራል የታሪክ መጽሐፍ፡፡ አትርሱት አንርሳው ያስታውሰው ዘራችን፤ ኢጣሊያ መሆኗን መርዛም ጠላታችን፡፡ እናንት አእጽምቶች ዕድለኞች ናችሁ፤ በኃይለ ሥላሴ ትንሣኤ አገኛችሁ፡፡

የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች የሆኑት አርበኞችም፤ ጎራዴ መዝዘው ነፍጥ ይዘው በተለያዩ ቦታዎች እምቢ ለሃገሬ በማለት ሸፈቱ፤ በጎጃም ዱር ቤቴ ያሉት ለጣሊያን ፋታ አልሰጥ አሉት፡፡ ራስ አበበ አረጋይ ግንቦት 6/1928ዓ.ም. ጅሩ ገብተው የአርበኝነት ተግባራቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ጀግኖች አርበኞችም እርስ በእርሳቸውም ተባበሩ፡፡ ለአብነትም ዋና ዋናዎቹ ከፊት መሪዎቹና አስተባባሪዎቹ ፊታውራሪ ዘውዱ አባ ኮራን፣ ዳዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ፣ ደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው፣ ፊታውራሪ በለው ቸርነት፣ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ፣ ግራዝማች ዘውዱ አስፋው፣ ባሻ ወልደ ጻድቅ ሲሆኑ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በጎጃም ታላቁቅ የጅግንነት ጀብዱ ከፈጸመው ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ጋር ሕብረት ፈጠሩ፡፡ ይህ ሕብረትም ለጣሊያን ፋታ ሲያሳጣው፤ በሌሎች ቦታ ላሉ ኢትዮጵያውያኝ ፈር ቀዳጅ በመሆኑ ሁሉም ይተባባርና እምቢ ለሃገሬ ይል ጀመር፡፡ ለምሳሌም፤ ሰኔ 1928ዓ.ም. የሆለታ የጦር አካዳሚ ምሩቃን(ዶ.ር ያለም ወርቅ በየነን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጦ)ና በውጭ ሃገር የተሰማሪ ሲቪሎች በመተባበር የመሠረቱት ‹‹‹ጥቁር አንበሳ›› አንዱ ነው፡፡ ‹‹ጥቁር አንበሳ›› ራስ እምሩን መሪው በማድረግ ብዙ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፤ ጣሊያን ደቡብ ኢትዮጵያን ለመያዝ ካቶሊካዊውን ደጃዝማች ሀብተ ማርያምን በመጠቀም ቦንጋ አውሮፕላኖቿን ስታሳርፍ የጥቁር አንበሳ ማኅበርም በቦንጋ አውሮፕላን ማረፊያ የሰራው ጀብዱ ግን ከሁሉም የላቀና የማይረሳ ነው፡፡ ስለ ታላቁ አርበኛ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ እንዲሁም ለጃዝማች ኃይሉ እንዲህ ተብሎ ተገጥሞላቸዋል፤ እውነተኛው ጀግና ኃይለ ማርያም፤ ስሙ እንዳይረሳ ጻፈልን በደም፡፡ እንዲህ ያለው ጀግና እንዲህ ያለ ወንድ፤ ጌጥ ይሆናቸዋል ለታሪኮች ዐምድ፡፡ የተባለለት የደጃዝማች ኃይሉ እጁ ውድ ናት፤ የቀመሱ ሁሉ ሲያመሰግኗት፡፡ ሌላው ፋሽስትን በተባበረና ስልታዊ በሆነ መልኩ በሐምሌ 21/1928ዓ.ም. በአዲስ አበባ መቀመጫና መቆሚያ ያሳጡት የሸዋ አርበኞች ሲሆኑ አሰላለፋቸውም፤ በሰሜን አዲስ አበባ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች አበራ ካሣና ወንድወሰን ካሣ የሚመሩት ሲሆን በውስጡ ሰማዕት የሆኑትን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ያካተተ ነው፡፡ በሰሜን ምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በራስ አበበ አረጋይ የሚመራ፡፡ በምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው (አባ ተጫን)ና ነጋድራስ ቦጋለ የሚመራ፡፡ በደቡብ አዲስ አበባ፤ በደጃዘማች ባልቻ አባ ነፍሶ የሚመራ ሠራዊት ተጀምሯል፡፡ነገር ግን ወቅቱ ክረምት በመሆኑና ወንዞች በመሙላታቸው አርበኞች ተቀናጅተው እንዳይዋጉና ሕዝቡንም እንዳይቀሰቅሱ ትልቅ እክል ሁኖባቸው ነበር፡፡ በዚህም ሙሉ አዲስ አበባ ላይ አደጋ ጥሎ ጣሊያንን የማስለቀቁ ተግባር የታለመለትን ያክል ባየሳካም በጠቂት አቅጣጫዎች ጀግኖች አርበኞች ተዋግተዋል፡፡ የተወሰኑትም ወደ ፍቼ ሸሽተዋል፤ ታላቁ አባት ብፁዕ ጴጥሮስም የታያዙት በዚሁ ወቅት ነበር፡፡ ጀግኖቹም ጣሊያንን እምቢ ለሃገገሬ በማለት እስከ የካቲት 12/1929ዓ.ም. የጉያ ረመጥ ሁነውበታል፡፡ ከ1927-1934 ዓ.ም. ለ7ት ዓመታት ጣሊያን በሀጋረችን ላይ ያደረሰችው ጥፋት፤ *በኢትዮጵያ ሰሜንና ደቡብ በየቀለቡና በማደሪያው ከዘመተው የሞቱ፤ *ጠላት አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ዓረቦችና ዓርመኖች ግሪኮች ተዘርፈናል በማለታቸው ምክንያት የሞቱ፤ **የካቲት ሚካኤል (የካቲት 12) ዕለት በአካፋ በዱላ በእሳት ያለቁ የሞቱ፤ *በአርበኝነት በየጊዜው በጠላት እጅ የሞቱ፤ *በደኅንነት አገር ቤት ላይ ሳሉ ሳያስቡት በጠላት እጅ የሞቱ፤ *ወደ ስደት ሲሄዱ በችግር ምክንያት በየመንገዱ የሞቱ፤ *በፌርማቶሪ አመልካችነት በየቀኑ የሞቱ፤ *ጠላት ከኢትዮጵያ ሊወጣ ሲል በተደረገው ጦርነት የሞቱ፤ *ከጠላት ወገን ሆነው (ባንዳዎች) ሆነው ከተዋጉ ባንዳ የሞቱ፡፡ *ሞሶሎኒ ባነሳው ጦርነት በየቀኑ በሚደረገው የግፍ ሥራ ያላግባብ የሞቱ (በሆለታ ተማሪ ቤት የነበሩ ወጣቶች፣ #የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን) ግራዚያኒ በናፖሊ መስፍን አልጋ ወራሹ ኡምቤርቶ ወራሽ በማግኘቱ ምክንያት ዐርብ የካቲት 12/1929ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚገኙ ድሃዎችንና ነዳያንን እንዲሰበሰቡ አደረገ፡፡ በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ቀትር ላይም ንግግር ማድረግ ሲጀምር በወቅቱ የተገኙትና የጣሊያን ፋሽስትነት ያንገፈገፋቸው አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ሰባት ቦንብ በግራዚያኑ ላይ ወረወሩ፤ በጥቃቱም ግራዚያኑ 365 ቦታዎች ላይ ቆሰለ /በይበልጥ እግሩ ቆሰለ/፣ 3ት ኢጣሊያናውያን ሞቱ፣ 50 ቆሰሉ፣ በተለይም የጦር አዛዡ አውራሊያ ሊአታ ከን ዓይኑ ጠፋ፡፡ በዚህም አንድም ኢትዮጵያዊ እንዳያመልጥህ ግደል በመታዘዙ በፋሽስት ኢጣሊያ በመትረየስ፣ .... በአካፋ ጭምር ሊረዳ የመጣውን ድሃና ነዳይን ጨምሮ 30 ሺህ የአዲስ አበባ ነዋሪ በሰዕትነት አረፈ፡፡ ይህ ግድያ ወደ ታላላቆቹ ገዳማትና አድባራትም በመዛመት በደብረ ሊባኖስ ያሉ 2200፤በዝቋላ ገዳምም 120 መነኰሳትና ምዕመናን ተረሸኑ፡፡ አስከሬናቸውንም ክብር ባለመስጠት በአካፋ በማንሳት አሰቃዩት፡፡ እንዲሁም 350 የሚጠጉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ወደ ሮምና ሞቃድሾ እስር ቤት ተላኩ፤ ከ2500 በላይ ደግሞ በእስር ቤት ታጉረው እንዲማቅቁ ተደረጉ፡፡ በእስረኞችና በምርኮኞች ላይም አሰቃቂ ድርጊቶችን ፈጽማለች፡፡ ፋሽስት ኢጣሊያ በ5ቱ ዓመት ወረራዋ ጀግኖች አርበኞችን ስላልቻለቻቸው ንጹሐን ዜጋዎችን በመግደል፤ እንዲሁም የተደበቁበትን ገድልና ዱር አላገኝ ስትል ገዳማትንና አድባራትን አቃጥላለች፡፡ እንደ ተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት 460 770 (በጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፋቸው ደግሞ 746 800 ሰዎችን በግፍ ገድላለች፤ 300ሺህ ሰዎች ደግሞ በስደት ሲንከራተቱ በረሃብ አልቀዋል፤ 2000 አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥላላች፣ በርካታ ንዋያተ ቅድሳትንም ዘርፋ ለካቶሊኳ ቫቲካን ሰጥታለች፡፡ ለአብነትም ካቃጠለቻቸው ገዳማትና አድባራት መካከል፤ *ይደመቆ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን /ሰሜን ሸዋ/ *አፈር ባይኔ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/ *አክርሚት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/ *ጎበጥ አገር ገብርኤል ቤ.ክ ሰሜን ሸዋ እም ምሕረት/ *አንኮበር ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. *ደረፎ ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. /ሰሜን ሸዋ ደረፎ/ *ጎንቻ መድኃኔ ዓለም ገዳም /ምሥራቅ ጎጃም/ *አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. ይገኙበታል፡፡ (ምንም እንኳን አልፎ አልፎ እንደ ማኅበረ ሥላሴ ያሉ ገዳማት አባቶች በጸሎታቸው አውሮፕላናቸውን እንዲከሰከሱ ቢያደርጉባቸውም) ኢጣሊያ ላደረሰችው ጥፋት 326 ቢሊዮን ሊሬ ቢወሰንባትም የሰጠችው ግን 105 ቢሊዮን ሊሬ ብቻ ነው፡፡ (እንደ ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ ዘገባ ደግሞ 175 ሚሊዮን ስተርሊንግ ተወስኖባት የከፈለችው 25 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው)፡፡ በከፈለችው ገንዘብም የቆቃ ግድብ ብቻ ተሠርቶበታል፡፡

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ለየካቲት_12_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_ማስታወሻ የአውሮፓ ኃያላን ሃገር ነን ብለው ራሳቸውን የሰየሙ አፍሪካን ሊቀራመቱ በተስማሙት መሠረት ጣሊያን ኢትዮጵያን ልትቀራመት ወሰኑ፡፡ ለዚህም ውሳኔ ያደረሳቸው ከሚስዮኖቿ አንዱና ተኩላው አባ ማስያስን(የጣሊያ ንጉሥ የቪክቶሪ ንስሐ አባትን ቀድሞ በትንሹ ራስ ዐሊ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የገባው) በአፄ ቴዎድሮስ ተባሮ፤ እንደገና በአፄ ዮሐንስ ዘመን ወደ ሃገራችን ገብቶ ነበር፤ አሁንም መልሰው አፄ ዮሐንስ ሲያብርሩት ለጣሊያን መንግሥት የኢትዮጵያን ልዩ መልክአ ምድሮችና በዓለም ላይ ልዩ ሃገር መሆኗን 2ት መጻሕፍት ጽፎ ለጣሊያን መንግሥት በማስረከቡ በዚሁ መሠረት ጣሊያኖች በመቋመጣቸው ነው፡፡ #የመጀመሪያው_ወረራና_ጦርነት መጀመሪያ በ1861ዓ.ም. እግሯን ወደ ኢትዮጵያ በአሰብ በኩል አስገባች፤ በ17ዓመታት ቆይታ(እስከ 1878ዓ.ም.) ምጽዋን፣ የዳህላክ ደሴቶችንና የኤርትራን ቀይ ባሕር ያዘች፡፡ ምጽዋን በያዘ በ3ት ዓመታት ኤርትራን ያዘች፤ ኤርትራን በያዘች በ7 ዓመት መረብን ተሻግራ ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመግባት ጦርነት ከፈተች፡፡ ከኤርትራ ሲሻገሩ መጀመሪያ ጦርነት ያደረጉት በ1887ዓ.ም. በወርኃ ጥር በዶጋሊ ከአጼ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና ከሐማሴኑ ባላባት ከጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋ ጋር ነው፡፡ ጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋም ጠላትን ድል በማድረግ ወደ ምጽዋ መልሰውታል፡፡ ለራስ አሉላ አባ ነጋም እንዲህ ተብሎ ተግጠሞላቸዋል፡፡ ‹‹የአሉላ ፈረስ የረገጣቸው፤ እስካሁን ድረስ አለ ቊስላቸው፡፡ የአሉላ ፈረስ ተስቦ ወርዶ፤ ያንን ነጭ ገብስ አረገው ነዶ፡፡›› ይህ አልሆን ሲላቸው በተወካያቸው በአንቶኔሊ በሚያዝያ 25/1881ዓ.ም. በውጫሌ (ወሎ ቦሩ ሜዳ የምትገኝ) ላይ የተፈረመውን የውል ስምምንት አንቀጽ 17 በአማርኛና በጣሊያንኛ ቅጂው የተሳሰተ (የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከውጭ ሃገራት ጋር የሚያደርገውንግንኙነት በኢጣልያ በኩል ማድረግ ይገባዋል!!፡፡›› በማድረግ በየካቲት 1885ዓ.ም. ዐጤ ምኒልክ የውጫሌ ውል እንደማይሠራ ለአውሮፓ መንግሥታት ደብዳቤ ጻፉ፡፡ በዶጋሊ የተሸነፉትና በውጫሌ ውል አልሆን ያላቸው ጣሊያን በኅዳር 29/1888ዓ.ም. ጦርነት ከፈቱ ጀግኖች ኢትዮጵያኖችም ሻለቃ ቶዘሊንና ሌሎች ፋሽስቶችን እንደ ነፋስ ትቢያ አድርጎ በተናቸው፡፡ ቀጥለውም በየካቲት 23/1888ዓ.ም. ጠዋት 12 ሰዐት አመሻሽ 12 ሰዐት ባለቀው፤ እንኳን ለኢትዮጵያውይን ይቅርና ለአፍሪካውያን ኩራትና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የአድዋ /የሶሎዳ ተራራ/ ጦርነት በጀግናው መሪ በዐጤ ምኒልክ ድል አድራጊት ተጠናቀቀ፤ ጣሊያንም የሽነፈት ጽዋዋን ጠጥታ ተመለሰች፡፡፡ዐጤ ምኒልክም ሚያዝያ 15/1889ዓ.ም. ወደ መናገሻ ከተማቸው ሲመለሱ የማረኳቸወን ጣሊያኖች ዛሬ ‹‹ጣሊያን ሰፈር›› በሚባለው ቦታ አኖሯቸው፡፡ ‹‹የአዲስ አበባ ውል›› ተብሎ በሚጠራው በኢትዮጵያና በጣሊያን በተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ ምርኮኞቹን እንድትፈታ፤ የውጫሌ ውል መሠረዙና፣ ኢጣሊያ በኢትዮጵያ ላይ ጣልቅ እንዳትገባ፤ የኤርትራ ድበር እስኪከለል ጣሊያን ከጦርነቱ በፊት ባለችበት እንድትረጋ በሚል ተከናወነ፡፡ #ሁለተኛው_ወረራና_ጦርነት ሁለተኛው ጦርነት ከ1929ዓ.ም.-1933ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ (ለዚህ ጦርነት ደግሞ መሠረቱ ጣሊያን የቀድሞ ሽንፈቷ ቂም በመያዟ ነው)፡፡ የተጀመረውም በኅዳር 26/1927ዓ.ም. በወልወል (የኢትዮጵያ ሶማሌ ክፍለ ሃገር በኦጋዴን ውስጥ በዋርዴር አውራጃ አካባቢ የምትገኝ ወረዳ ስትሆን ንጹሕ የከርሠ ምድር ውኃ የሚገኝባትም ነች፤ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ 350 ጥልቅ የውኃ ጕድጓድ አስቆፍረውላታል) ላይ ጣሊያን ባንዲራዋን በመትከሏ ምክንያት ነው፡፡ በዚሁም ምክንያጥ የአውራጃው ገዢ ፋውራሪ ዓለማየሁ ከጣሊያኑ ጦር አዛዥ ካፒቴን ችማሩታ ጋር ጦርነት ገጠመዋል፤ በጦርነቱም ጀግናው ፊታውራሪ ዓለማየሁ በፋሽስታዊ ታንክ ነጂ በገዛ ታንኩ ላይ ላይ ተወርውረው በመውጣት ሰይፈውታል፤ ብዙ የጀግንንት ሥራንም አከናውነዋል፤ ቆይቶ ግን ለሃገራቸው በጀግንነት እየተዋጉ ሣለ ከሌሎች 107 ኢትዮጵያውያን ጋር አርፈዋል፡፡ በዚህ ውጊያ ላይ አብዛኞቹ ሙስሊሞች ባንዳ በመሆን ለሃገራችን ጠላት ቢሆኑም (ለምሳሌ ሡልጣን ኢብራሂም አሰብን ለሮማ ልዑካን ሸጥኩላቸው የሚለውና፣ የአዳል ባላባት የራሄታ ሡልጣን ሐሰን ሙሐመድለሮማ ሚስዮናውያን የኢትዮጵያን ወደቦች እነሸጣለን ብሎ የመከረ)፤ ለሃገራቸው ሲሉ የተዋጉ የሙስሊም አርበኞችም ነበሩ፤ ዋነኞቹም ኑር ሑሴንና ደጃዝማች ዑመር ሰመትር ይጠቀሳሉ፡፡ በዚሁም ጣሊያን ‹‹ጅራፍ ረሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል›› እንደሚሉት ኢትዮጵያ ዜጎቹን ገድላብኛለችና 200 ሺህ ሊሬ ካሳ ትክፈለን ብለው ለመንግሥታቱ ማኅበር ከሰሱ፡፡ ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በድርድር ያልቃል ብላ ስትጠብቅ በጎን ግን ኢጣሊያ ለጦርነት ስትዘጋጅ ቆየች፤ በኅዳር 1927ዓ.ም የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስቴር ፒየር ላቫል ኢጣሊያ ከጀርመን ሂትለር ጎን እንዳትሰለፍ በማሰብ ኢትዮጵያን ብትወርር እንደማትቃወም አሳወቅ፤ ጦርነቱን የተቃመወችው ሩሲያ ብቻ ነበረች፡፡በመስከረም 22/1928ዓ.ም. ኢጣሊያ የመረብን ወንዝ ተሸግራ ጦሯን በ3ት መስመር አሰልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ገባች፡፡ ያገኘችውንም እያጠፋች እንትጮንና አዲግራትን በያዝ ዓድዋ ደረሰች፤ ለዚሁም አስተዋጽዖ ያደረጉላት ለግል ጥቅማቸው ያደሩ የኢትዮጵያ ጠላት የሆኑ ባንዳዎች ነበሩ ለአብነትም ዋነኞቹ (ደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ፣ ደጃዝማች ሀብተ ማርያም፣ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው) ናቸው፡፡ ባንዳ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው የጎንደርን ሕዝብ አሳምኖ ለኢጣሊያ ተገዢ ለማድረግ መንቀሳቀሱን ጀግናው አርበኛ ደጃዝማች ታደሰ ይማም ወንድይራድ ሲሰማ ያለበት ድረስ ደርሶ ድባቅ መትቶታል፤ ባንዳው እጅጉ በጣና ሐይቅ በታንኳ ተሸግሮ አምልጦ ወሎ ተደበቀ፤ ይህንንም ታላቁ አርበኛ ደጃዝማች ታደሰ ወሎ ድረስ ዘምቶና ከበባ አድርጎ ሃገሩን ለሸጠ ምሕረት አይገባውምና እንደ በግ አርደውታል፡፡ ጣሊያኖች በባንዳዎች በመታገዝ ጭምር በመርዝ ጋዝ ታግዘው በየካቲት 27 ከራስ ሙሉጌታ ጋር በተደረገው ውጊያ የራስ ሙሉጌታ ጦርን በመደምሰሳቸው በሐበሾች ዘንድ የሞራል ውደቀት አስከትሏል፡፡ ነገር ግን ጀግኖች አርበኞች እምቢ ለሃገሬ በማለት በተንቤን፣ በእንደርታ፣ በሽሬ፣ በአሸንጌ ላይ ተዋጉ፡፡ በአሸንጌው ጦርነት ጠላት ጣሊያን ከላይ በአውሮፕላን ጠላት ባንዳ ደግሞ ከታች በመሆን 8ሺህ የሚጠጉ አርበኞቻችን ላይ ጉዳት አደረሱ፡፡ በመጋቢት 24 ለ13 ሰዐታት በተካሄደው የማይቸው ጦርነት ላይ ኢትዮጵያውያን ድል አድረገው ጦርነቱ ማብቂያ ላይ የመርዝ ጋዝና የቦንብ ውርጅብኝ ከአውሮፕላን ላይ በማዝነብ ጀግኖች አርበኞቻችን አብዛኞች አለቁ፤ ከማይጨው የተረፉና በአሸንጌ ላይ የነበሩትን ጀግኖች አርበኞችን 150አውሮፕላን ደርሰው ደብደቡት በመትረየስም ፈጁት፡፡ (ጣሊያኖች ዚሁ ወረራቸው በሰሜን 300፣ በደቡብ 150 አውሮፕላን አዝምተዋል፡፡) በአምባ አራዶም 50 ሺህ፣ በሽሬና በተንቤን 15 ሺህ ሰው ሙቶ 200 ሺህ ሰው ቆስሏል፡፡ በሚያዝያ 24/1928 ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ለተባበሩት መንግሥታት አቤቱታ ሊያቀርቡ ወደ ጄኔቫ ሄዱ፤ በሃገሪቱ ንጉሠ ነገሥቱ አለመኖሩን ጣሊያኖ ሲያውቁ በ3 ቀናት በመገስገስ በሚያዝያ 27 አዲስ አበባን ተቈጣጠሩ፡፡ በእነዚህ 3ት ቀናት ውስጥም ሽብር ዘረፈና ግድያ በአዲስ አበባ እጅጉን በርቶቶ ነበር፡፡

‹‹#የአካፋው_ሚካኤል››፤ #የካቲት_12 ለሁለተኛ ጊዜ ሃገራችንን ልተውርር በመጣችው የጣሊያን የጦር ሹም የነበረውን ብራዚያኒን ለመግደል ጀግኖቹ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በጣሉት አደጋ ግራዚያኒ በመቁሰሉና አመራሮቹ በመሞታቸው የተቆጣው የጣሊያን ጦር በአዲስ አባባ በየካቲት 12/1929ዓ.ም. ለቅዱስ ሚካኤል ወርኋዊ በዓል በየቤተ ክርስቲያኑ የተገኙትን (ለምጽዋት የተሰበሰቡትን ጨምሮ)ና በየቤቱ በመግባት 30 ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ በአካፋ ጭምር እንደ ቅጠል አረገፏቸው፤ 30ሺህ ሰማዕታት በመባልም ይታወቃሉ፡፡ ከጥቂት ናት በኋላም የደብረ ሊባኖስ ገዳም መነኰሳትን አርበኞችን ደብቃችኋል በሚል በተቀደሰው ስፍራ ተረሸኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ጣሊያን ይህን አሰቃቂ ግፍ ስትሠራና የሰማዕታቱን የከበረ አካል በአካፋ በመሰብሰቧ ‹‹የአካፋው ሚካኤል›› በሚል መጠሪያ ይጠራል፡፡ በተለይም በ6 ኪሎ በመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ የቅዱስ ሚካኤል ታቦተ ሕግ ወጥቶ በልዩ ጁኔታ ይከበራል፡፡ (እናት ቤተ ክርስቲያን መቼውንም ቢሆን የሃገርና የቤተ ክርስቲያን ባለውለታዎችን አትዘነጋምና!!!!) (እናቶቻችንና አባቶቻችን እንደነገሩን በቀጨኔ የሚገኙ አያቶቻችን የተሠዉና ግማሾቹም ይህንን ዜና ሲሰሙ ወደ 6 ኪሎ ከመኄድ ተመለሱ እንዳሉ ልብ ይሏል፡፡) /ክፍል ሁለትን ለነገ ይጠብቁ፡፡/

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን)፤ #ክፍል#፭_ ++አባ ጳውሊ፤ የወገኖችህ ቊጥራቸውና ስማቸው እንዲሁም በዚህ ዓለም የምትታዩት ብዛታችሁ ምን ያህል እንደሆነ እውነቱን ትነግረኝ ዘንድ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ባየኸው በፈጣሪ ስም አምልሐለው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ነገዳችን ብቻ ነው እንጂ ቊጥራችን አይታወቅም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ በአኗኗራችሁ ከእናንተ የበላይ አለቃ አለን አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለ ፤ ታላቁ አለቃ እኔ ነኝ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ከእናንተ ወገን በክፋትና በማሳት ከወገን ወገን፥ ከሰይጣን ሰይጣን የሚበላለጥ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ከሰው ወገን ዘመድ ወዳጅ አለህን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለኝ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ የረከስክ ነህና ወዳጅህ ማነው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #የእግዚአብሔርን ሕግ ትቶ ኃጢአትን የሚሠራ ነው አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ስለምጠይቅህ ነገር ምንም እንዳትሸሽገኝ በመስቀል ላይ በተሰቀለው በጌታ ስም አምዬሃለው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተ ክፉ ሽማግሌ ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ ፤ ከሥራዬ ምንም የምደብቅህ የለኝምና በዚህ ቅዱስ ስም አታቃጥለኝ ዝም በል አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ከክብርህ የተዋረድክና የተረገምህ! #ክፉ ሥራህን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው እስኪ ንገረኝ አለው፡፡ ሰይጣን፤ አንተ ሽማግሌ ብዙዎች እኔ እንደማስታቸውና እንደማልጠቅማቸው አያውቁምና ሥራዬን አትነግርብኝምን? አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የምጠይቅህን ክፉ ሥራህን ንገረኝ እንጂ እኔ እንዳልናገር የማዘዝ ሥልጣን የለህም አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከቸርነቱ ያርቃቸው ዘንድ አምላካቸውን ሐሰተኛ አድርገው እስኪያዩትና ፣ እስኪነቅፉት እስኪሰድቡትም ድረስ ሐሰትን እናስተምራቸዋለን፡፡ ዳግመኛም የማስተዋል አእምሮን በመንሳት የነቀፋና የስድብ መንፈስ ከልባቸውና ከአፋቸው እንዳይጠፋ እናደርጋለን አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምክ እንዲህ በማድረግህ #ምን ትጠቀማለህ? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ እናንተን ከዘለዓለም ሕይወት ማጥፋትና በገሃነም እሳት ማቃጠል ነው እንጂ የምጠቀመው ጥቅም የለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ በውኑ ገሃነም የሚባል ቦታ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ ገሃነመ እሳት አለ፡፡ በዚያ መጽናናት የሌለው ልቅሶ፥ ጥርስ ማፋጨት እንዲሁም የማያንቀላፋ ትል፥ ታላቅ ስቃይና የማይቋረጥ ልቅሶ ድቅድቅ ጨለማ አለ፡፡ ኑሯችን በዚያ ነው አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ከክብርህ የተዋረድክ፤ በገሃነመ እሳት እንደምትቀጣ የምታውቅ ከሆነ ለምን ንስሐ አትገባም!? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ንስሐ እንዳልገባ #የሚጸጸት ልብ የለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ እግዚአብሔር መሐሪና ይቅር ባይ ነውና ከለመንከው ይሰጥሃል!! አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ለዚህ ሥራ ዕድል የለንም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከእናንተ በዚህ በክፉ ሥራችሁ የበላይ አለቃ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለ፤ በጨለማ ሠራዊት ላይ ታላቁ አለቃ እኔ ነኝ፡፡ እኔ ሰይጣናትን ሁሉ ሰውን ለማሳት በየቦታው እልካቸዋለሁ፡፡ ከአጋንንት ጭፍራና ከወገኖቼ መካከል ከእኔ የሚከፋ የለም፡፡ ከእኛ መካከል ሰዎች ዝሙትንና ስርቆትን፥ ቂምና ስካርን ይህን የመሰለ ኃጢአት እንዲሠሩ የሚያደርጉ እጅግ የከፉ ጨካኝ አጋንንት አሉ አለው፡፡ #የሰይጣን ኀይል በምን እንደሚደክም፤ ሰው በሰራው ኀጢአት ተጠያቂው ራሱ እንደሆነ፤ ሰይጣን ሰዎችን ፈጣሪያቸውን እንዴት ባለ መንገድ እንደሚያስክዳቸው፤ አንድን ኀጢአት ያለፈን ሰው በሌላ ኀጢአት እንደሚፈትኑት፤ ለሰው በሚፈልገው ተመስለው በምትሐት እንደሚገለጹ … ክፍል ፮.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

#ዝክረ_ቅዱስ_ያሬድና_የነነዌ_ሱባዔ_መርሐ_ግብር፡፡ #ከዛሬ ሰኞ-ረቡዕ ማታ ማታ ትምህርት #ከሰኞ - ዐርብ ጠዋት ጠዋት ደግሞ ጸሎት አለ፡፡ ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ካህን ምኑን ካህን ኾነ? ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ሰንበት ተማሪ ምኑን ሰንበት ተማሪ ኾነ? ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ክርስቲያን ምኑን ክርስቲያን ኾነ? ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ኢትዮጵያዊ ምኑን ኢትዮጵያዊ ኾነ? ‹‹ያሬድ ካህን ጥዑመ ልሳን፤ መዘምር ዘበድርሳን፤ ዕንዚራሃ ለቤተ ክርስቲያን፡፡ /መጽሐፈ ሰዐታት፥ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫ/ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ትቤት፡፡

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፬_ (#ሰይጣን_የቅዱሳን_መላእክትን_ቃል_ምሥጢር_እንደሚሰማና_ #የሰማው_ከመደረጉ_በፊት_ለሰዎች_በመናገር_እንደሚያስት፤ #ሰይጣን_ከተፈጠረ_ጀምሮ_በዘመን_ብዛት_ሰውን_ያሚያስትበት_ብዙ_ጥበብ_እንዳለው፤ #የክርስቶስ_ሰው_መሆን_ከሰይጣን_የተሰወረ_እንደነበር) +አባ ጳውሊ፤ ወደ ሰማይ ወጥታችሁ የመላእክትን ቃል ትሰማላችሁን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ፈጽመን አንወጣም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ስለምንድነው የማትወጡት? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከክብራችን ከተዋረድን በኋላ በቧለሟልነት ሥልጣን ወደዚያ እንቀርብ ዘንድ አይፈቀድልንም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰዎች እናንተ ወደ ሰማይ እንደምትወጡና ከመላእክት ጋር እንደምትነጋገሩ የሚናገሩት ዋሽተው ነውን? አለው፡፡ ሰይጣን፤ መላእክት ከምስጋና በቀር አይናገሩምና አዎን ዋሽተው ነው አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ እንግዲያ ከመደረጉ በፊት አስቀድመህ ለሳኦል ምሥጢር የገለጥክለት በምን አውቀህ ነው? አለው፡፡ /፩ሳሙ.፳፰፥፲፯/ ዲያብሎስ፤ እግዚአብሔር ለሳሙኤል ሲነግረው ሰምቼ ነው አለው፡፡ /፩ሳሙ.፲፮፥፩) እግዚአብሔር ለመላእክቶቹ ምሥጢር ሲነግራቸው እኛም ባለንበት ሆነን እንሰማለን፡፡ ያን ጊዜ ፈጥነን ሄደን ከመደረጉ በፊት ለሰዎች እንነግራቸዋለን፡፡ ሰዎች ሁሉ በየሀገሩ እኛ የነገርናቸውንና በሕልም ያሳየናቸውን ይናገራሉ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ነገርህን እንደምን አምነው ይቀበሉሃል? የመልክህን ክፋት የመዓዛህን ክርፋት አያውቁምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ሰዎች ሁሉ እንደ አንተ ክፉ መሰሉህ? ለአንተ ክፉ መስዬ እታይሃለሁ እንጂ በዚህ ዓለም መዓዛዬን ለማሽተትና መልኬን ለማየት እኔን የሚሹ ብዙ ሰዎች እንዳሉ እነግርሃለሁ፡፡ እነርሱ ወደ እኔ መጥተው እገለጽላቸው ዘንድ ይለምኑኛል እንጂ እኔ ወደ እነርሱ አልሔድም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ስለምን ይወዱሃል? ይህ የሚሆነው ለምንድን ነው? ዲያብሎስ፤ እኔን ለማየት በሚፈልጉት መልክ ተመስዬ በመገለጽ ስለማስደስታቸው ነው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ መልክህን መለወጥ እንደምን ይቻልሃል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ይህ የሚያስደንቅ አይደለም ሰይጣን የብርሃን መልአክን ይመስላል ብሎ ጳውሎስ የተናገረውን አልሰማህምን፡፡ /፪ቆሮ.፲፩፥፲፬/ ++አባ ጳውሊ፤ የማታውቀውን ምሥጢር ማስመሰል እንደምን ይቻልሃል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በዘመን ብዛት የሰበሰብኩትና የማውቀው ብዙ ጥበብ አለኝ፡፡ #ነገር ግን የክርስቶስ ሰው መሆን ብቻ ተሰወረብኝ እንጂ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የክርስቶስ ሰው መሆን ስለምን ተሰወረብህ? ዲያብሎስ፤ ከእኔ የተሰወረበትን ምክንያት አላውቅም፡፡ ነገር ግን አውቄስ ቢሆን ክፉና በጎ ለይተው ያላወቁ ብዙ ሕፃናትን በሄሮድስ አድሬ ባላስገደልኩም ነበር አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ አንተ ፈትነኸዋልና አላውቅም አትበል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በሰውነቱ ስለሚሠራው ሥራ እንደ ነቢይ፥ እንደ ንጉሥ ይመስለኝ ነበርና ባውቅም እጠራጠር ነበር፡፡ ስለዚህ እፈትነው ዘንድ በእርሱ ላይ ተነሳሁ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ እርሱ በእውነት አምላክ መሆኑን ያወቅኸው መቼ ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ኃይሌን እስከሚያደክመው ድረስ አላወቅሁም ነበር፡፡ መላእክት ሲያመሰግኑት፥ ሙታን ሲነሡ፥ ምድር ሲነዋወጥ፥ ፀሐይ ሲጨልም አየሁ፤ ያን ጊዜ የዓለም ብርሃን፥ የፍጥረታት ፈጣሪ እርሱ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ አወቅሁ አለው፡፡ #የሰይጣናት_አለቃና_ታዛዥ_እንዳላቸው፤ #ገሃነም_ስለመኖሩና_ዲያብሎስ_ለምን_ንስሐ_እንደማይገባ) #ክፍል_፭.… #ይቀጥላል_ነገ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

‹‹ሊቃውንትን ጠይቅ ያስታውቁህማል፤ አባትህን ጠይቅ ይነግርሃል፡፡›› (ተሰአሎ ለአቡከ ወይነግረከ፤ ወለሊቃውንቲከ ይዜንዉከ፡፡›› /ዘዳ. ፴፪፥፯/ ልዩ ዓመታዊ ጕባኤ በጾመ ነነዌ (#ከየካቲት 11-13) ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ፤ እንደ አምላክ ፈቃድ ዐበይት ሊቃውንት መምህራን የሚገኙበት እንደ አምናው ተዘጋጅቷል፡፡ በጽርሐ ጽዮን ጰራቅሊጦስ ቤ.ክ. (ኋላ ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ በሚገኘው) ቦታው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ፡፡