Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 408 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 577,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 192 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 408 名订阅者。
根据 12 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 76,过去 24 小时变化为 7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.12%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.38% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 871 次浏览,首日通常累积 1 446 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 13 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 408
订阅者
+724 小时
+347 天
+7630 天
帖子存档
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
በወርኃ ጥር ፭/፳፻፲፩ ዓ.ም. ጋብቻችሁን ለፈጸማችሁ የደብራችን የድጓ መምህር፤
* መምህር ጥበቡ ገበየሁ ከማንጠግቦሽ ቸኮል ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤
የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡
✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ
✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡
/ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/
በቅድስት ሥላሴ ከተሰየሙ በሃገራችን ከሚገኙ ገዳማትና አድባራት፤ የታሪክ አሻራቸው ያንጸባረቀ፥ አሻራቸው የላቀ፥ እድሜያቸው የጎላ፤ 7ቱ ዐበይት ገዳማት (ቤ.ክ)፤
1ኛ) #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ ከ2000ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ የብዙ ቅዱሳን (የአባ ዓምደ ሥላሴ፣ የአባ ክፍለ ማርያም፣ የ7ቱ ዘሥላሴ፣ የአባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ /የአርኬና የመልክዓ ቊርባን ደራሲ/፣ …….. ) መፍለቂያ፡፡
2ኛ) #አሰቦት_ቅድስት_ሥላሴ፣ በ13ኛው ክ/ዘመን በታላቁ ጻድቅ በአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተመሠረተ፡፡
3ኛ) #ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_ሰሜን_ሸዋ_ደብረ_ብርሃን_ከተማ፤ በ14ኛው ክፍለ ዘመን በዓፄ ዘርዓያዕቆብ ዘመን የተመሠረተ፡፡
4ኛ) #መካነ_ሥላሴ_ደቡብ_ወሎ_ወረኢሉ፤ በ1500ዓ.ም. በዓፄ ናዖድ የተመሠረተና በልጁ በዓፄ ልብነ ድንግል ሥራው የተጠናቀቀ፤ ባለ 16 መንበር በዕንቊና በወርቅ የታነጸ የነበረ፤ (ኋላ በግራኝ የፈረሰ፤ ጽላቱ በዓፄ ምኒልክ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ቀድሞ መካነ ሥላሴ አሁን 4 ኪሎ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል የሚጠራው)፤ ደቡብ ወሎ ያለው መካነ ሥላሴ ግን ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ነውና በቀድሞው ቅርጹ በባለ 16 መንበር ተደርጎ ካች አምና የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ በመገንባት ላይ ይገኛል፤ (ለሕንፀታ ቤቱ ኹላችንንም ያብቃን)፡፡
5ኛ) #ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_ጎንደር_ከተማ፤ በጥር 26 ቀን 1683 ዓ.ም. በዓፄ አድያም ሰገድ የታነጸ፤ በጎንደር ከተማና ዙሪያ ከሚገኙ 44ቱ ታቦታተ ጎንደር በአሠራሩ ልዩ የኾነ፤ በ1880ዎቹ ድርቡሽ ጎንደር ከተማን ሲያጠፋ አብረው ከጠፉት 44ት አብያተ ክርስቲያናት በተዓምራት ሳይቃጣል የቀረ፤ የታላላቅ ሊቃወንት (የእነ ሊቁ ክፍለ ማርያም) መፍለቂያ፡፡
6ኛ) #ናርጋ_ሥላሴ_ከጣና_ላይ_ገዳማት_አንዱና_ዋነኛው፡፡
7ኛ) #ጨለቆት_ሥላሴ_ትግራይ፤ መቀለ አጠገብ፡፡
……. ቤ.ክ አንዲት ናት፤ ሌሌች በቅድስት ሥላሴ የተሠየሙ የታሪክ ሙዳይ የኾኑ ብዙ አድባራትና ገዳማት ቢኖሩም እነዚህ ከላይ የጠቀስናቸው 7ቱ ግን ከዕድሜያቸው ብዛትና ከአመሠራረታቸው አንጻር በታሪክ አሻራ ላይ ያላቸው አስተዋጽዖ ከፍተኛ በመኾኑ ነው የዘገብናቸው፡፡
#ጥር_7_በዓለ_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈራረሱበትና_ቋንቋ_የደባለቁበት_ዕለት_ነው፡፡
#የመንበረ_ጸባዖት_ቅድስት_ሥላሴ_በልዩ_አሠራር_የተሠራው_የሕንፃ_ቤተ_ክርስቲያኑ_ቅዳሴ_ቤት_75ኛ_ ዓመት_የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ #በዓሉም_ከጥር_7_እስከ_11_ይቆያል_፡፡ በጃንሜዳ የጥምቀት በዓል ተረኛም ይህ ታላቅ ደብር ነው (በዘንድሮ በዓሉ በዩኔስኮ ድንቃ ድንቅ መዝገብም ይመዘገባል ተብሎ ይጠበቃል)፡፡
/ለሥላሴና ለከተራና ለጥምቀት ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስትመጡ እንደ መላእክት ቤተ ክርስቲያን የምታዘውን ነጭ ልብስ ለብሳችሁ እንድትመጡም ቤተ ክርስቲያኗ ጥሪዋን አስተላልፋለች፡፡
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
በወርኃ ጥር ፭/፳፻፲፩ ዓ.ም. ጋብቻችሁን ለፈጸማችሁ የሰ/ት/ቤታችን አገልጋይና የደብራችን አገልጋይ፤
* መስታወት ይጥና ከፈቃዱ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤
* ዲ.ን ዳንኤል እስጢፋኖስ ከሰላም ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤
የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡
✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ
✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡
/ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/
#ጥር 6 በዓለ ግዝረት ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ ልደተ ቅድስት አርሴማ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡ (በተለይ ይህ ክብረ በዓል በለብቃና በበልበሊት ኢየሱስ/ሰሜን ሸዋ/፣ በበለስ ዋሻ ኢየሱስ /ተጉለትና ቡልጋ/፥ በአ.አ ፈረንሳይ ኢየሱስና ገዳመ ኢየሱስ(መርካቶ አማኑኤል አጠገብ)ና በእንጦጦ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል በድምቀት ይከበራል፡፡
#ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ቅዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ቅዱስ ጳውሎስ/፡፡
የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡
እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡
#ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ (የዚህን ቅዱስ ነቢይ ታሪክ በደንብ ያንቡብት ብዙ ትምህርት ይቀስሙበታል)
በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡
✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ከእሱ በፊትም ኾነ በኋላ በተአምራት የተሞላ እሳት ለበስ ነቢይ እሱ ከመረጠው ከደቀ መዝሙሩ ከኤልሳዕ በቀር አልተነሳም፡፡
በ ነበር ቅዱስ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን የጠነቀቀ: የንጽሕናና የአምልኮ ሰው ነበር:: ከኢዮርብዓም እስከ እርሱ ድረስ ለአያሌ ዓመታት እስራኤላውያን በሰይጣን ግፊት በሰው ሠራሽ ጣዖት(በኢሎፍላውያን እጅ የነበሩት ጣዖታት ዳጐንና ቤል ወደ እስራኤል ገብተው) ተመረዙ፥ በኀጢአትም ረዘረዙ፡፡ ቅዱሱ ኤልያስም የግፈኛው አክአብና የዘማዊቷ ኤልዛቤልን መንግሥት በሦስት ዓመት ከመንፈቅ በከባድ ድርቅ በመናጥ፣ ሰማይን የለጐመ፥ እሳትን ያዘነመ፥ ፍጥረትንም በቃሉ ያዘዘ፤ እንዲሁም አፈር እንደበላው ብረት የዛገ አስተሳሰባቸውን በሰው ደምና በቅሚያ ገንዘብ የተሞላ ሰውነታቸውን በማን አለብኝነት ያበጠ ልባቸውን እንደሰም በማቅለጥ የሚይዙትንና የሚጨብጡትን ያሳጣ በፈጣሪው ለዚህ ሥራ የተመረጠ ሰመ ጥር ነቢይ ነው፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ነውና፡፡
ኤልያስ የከተማ ነቢይ ብቻ አይደለም ባሕታውያን ተብለው ከሚጠሩት ነቢያተ ጽድቅም አንዱ እንደነበር ሕልውናው ምስክር ነው፡፡ ኤልያስ ድንግል ባሕታዊም ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ መኖሪያውም በተራሮችና በዱር ነበነር በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ የእርሱ ቤቱ ነበር፡፡ በዚህም አኗኗሩ አሁን ላለው ምንኵስና በብሉይ መሠረት ከጣሉት ውስጥ ግንባር ቀደምና ዋናው ነው፡፡
(( ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡
✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን እንዳታጸድቅ የዘሩባትን እንዳታበቅል ለባለንብረቱ አመለከተ ይህም ጥያቄው ከእግዚአብሔር መልስ አግኝቷል፡፡ ነገሥ 17፥1፡፡ ከዚህ ላይ የሊቀ ነቢያት ሙሴንና የኢሳይያስን ቃል ያስጠቅሳል ዘዳ 32፥1-4፣ ኢሳ 1፥2-5፡፡ በእነዚህ እስከፊ ዓመታት ውስጥ በመሪዎች አመፅ በኤልያስ ተግሣጽ የሚመለከተውም የማይመለከተውም የሚልሰውና የሚቀምሰው አጥቶ በዋለበት እንደ ቅጠል ረገፈ፥ እንደሻሽ ተነጠፈ፡፡ የኀጥአን ፍዳ ጻድቅ ይደፋ ይሏል ይህ ነው፡፡
ዛሬም በአምስቱ ክፍለ ዓለም የብዙኃኑ እልቂት ሲፈጸም የሚታየው በጥቂት እግዚአብሔር የለሽ ሰይጣን ጁንታዎች ሽፍቶች መሆኑን ከአክአብና ኤልዛቤል ይማሯል፡፡
ይህን የኤልያስን ጠበቅ ያለ እገዳ ከስምንት መቶ አምሳው ነቢያተ ሐሰት ካህናተ ጣዖት አንዱም ወደ ሚመለከተው በጸሎቱም ሆነ በመሥዋዕቱ አመልክቶ ሊያስነሳ ወይም ለማስነሳት የቻለ የለም፡ ጠንቋዮችና አታላዮች በብሉይ ኪዳን ብዙ ጊዜ ከቤተ መንግሥት ተለይተው አይርቁም፡፡ 1ኛ ነገሥ 18፥22፣ዳን 2፥1-14፡፡
✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18፥41-46፣ ያዕ 5 17-18 እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የገባውን ቃል ኪዳን አያጥፍም አቁም ሲሉት ያቆማል፥ ስጥ ሲሉት ይሰጣል እንጂ ምን አገባቸው ብሎ እንደፈለገው አያደርግም፡፡
የእግዚአብሔር ሐዋርያ ስለ ኤልያስ ማንነት ሲያደንቅ ኤልያስ እንደኛ ሰው ነበር ዝናም እንዳይዘንም ከለከለ እንደገናም እንዲዘንም አደረገ በማለት በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖች ከቀና ክርስትናቸው ምን እንደሚጠበቅባቸው ከእምነታቸው ምን ማግኘት እንዳለባቸው ይጠይቃል ያዕ.5፥13-20፡፡ ዛሬስ ምን ይመስሎታል፡፡
ኤልያስ በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ነገር ግን በረዶ ያዘነመላቸው አንደኛ ሙሴ ዘፀ 9፥13-21 ሁለተኛ ኢያሱ 10፥9-12 ሦስተኛም ሳሙኤል 1ኛ ሳሙ 12፥1-19 ይመለከታል፡፡
✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡
✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡
✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ይህች ሴት በእምነቷ አርአያነት ያላት ደገኛ ሴት ናት፡፡ ኤልያስን የእግዚአብሔር ሰው ሆይ #ከአንተ_ጋር_ምን_አለኝ፣ ኀጢአቴንስ ታስብ ዘንድ ልጄንስ ትገድል ዘንድ ወደ እኔ መጥተሃልን ብላዋለች፡፡ ኤልያስም በእግዚአብሔር ኀይል ማንኛውንም ችግር ለመፍታት ሙሉ መብት ነበረውና ወዲያውኑ ወደ አምላኩ በመጸለይ የሞተውን ብላቴና ጠጋ ብሎ ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት አስነስቶ የብላቴናውን እናት አስደስቷል 1ኛ ነገሥ. 17 17-24
ሐዋርያው የእምነት ጀግኖችን በመዘገበበት አንቀጽ ይህችን ሴት ልብ ይሏል፤ ዕብ 11፥35፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ያሉ እናቶች ያስፈልቷል፡፡ ይህችን ሴት የሚመስሉ እናቶች 2ኛ ነገሥ. 4፥18-38 ፣ሉቃ 7፥11-17 ተመዝግበዋል፡፡ በሐዋርያት ሥራም ያሉት እናቶች ከእነዚህ ጋር ያነጻጽሯል የሐዋሥ 9 36-43፡፡
✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29፡፡ ሰይጣን በሰማርያ ምድር እንደዚያ ቀን ሰው መዘባበቻ በመሆን የውርደት ቀን ገጥሞት አያውቅም
#ጥር 6 በዓለ ግዝረት ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ ልደተ ቅድስት አርሴማ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡ (በተለይ ይህ ክብረ በዓል በለብቃ ኢየሱስ/ሰሜን ሸዋ/፣ በበለስ ዋሻ ኢየሱስ /ተጉለትና ቡልጋ/፥ በአ.አ እንጦጦ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል በድምቀት ይከበራል፡፡
#ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ቅዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ቅዱስ ጳውሎስ/፡፡
የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡
እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡
#ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ (የዚህን ቅዱስ ነቢይ ታሪክ በደንብ ያንቡብት ብዙ ትምህርት ይቀስሙበታል)
በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡
✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ከእሱ በፊትም ኾነ በኋላ በተአምራት የተሞላ እሳት ለበስ ነቢይ እሱ ከመረጠው ከደቀ መዝሙሩ ከኤልሳዕ በቀር አልተነሳም፡፡
በ ነበር ቅዱስ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን የጠነቀቀ: የንጽሕናና የአምልኮ ሰው ነበር:: ከኢዮርብዓም እስከ እርሱ ድረስ ለአያሌ ዓመታት እስራኤላውያን በሰይጣን ግፊት በሰው ሠራሽ ጣዖት(በኢሎፍላውያን እጅ የነበሩት ጣዖታት ዳጐንና ቤል ወደ እስራኤል ገብተው) ተመረዙ፥ በኀጢአትም ረዘረዙ፡፡ ቅዱሱ ኤልያስም የግፈኛው አክአብና የዘማዊቷ ኤልዛቤልን መንግሥት በሦስት ዓመት ከመንፈቅ በከባድ ድርቅ በመናጥ፣ ሰማይን የለጐመ፥ እሳትን ያዘነመ፥ ፍጥረትንም በቃሉ ያዘዘ፤ እንዲሁም አፈር እንደበላው ብረት የዛገ አስተሳሰባቸውን በሰው ደምና በቅሚያ ገንዘብ የተሞላ ሰውነታቸውን በማን አለብኝነት ያበጠ ልባቸውን እንደሰም በማቅለጥ የሚይዙትንና የሚጨብጡትን ያሳጣ በፈጣሪው ለዚህ ሥራ የተመረጠ ሰመ ጥር ነቢይ ነው፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ነውና፡፡
ኤልያስ የከተማ ነቢይ ብቻ አይደለም ባሕታውያን ተብለው ከሚጠሩት ነቢያተ ጽድቅም አንዱ እንደነበር ሕልውናው ምስክር ነው፡፡ ኤልያስ ድንግል ባሕታዊም ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ መኖሪያውም በተራሮችና በዱር ነበነር በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ የእርሱ ቤቱ ነበር፡፡ በዚህም አኗኗሩ አሁን ላለው ምንኵስና በብሉይ መሠረት ከጣሉት ውስጥ ግንባር ቀደምና ዋናው ነው፡፡
(( ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡
✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን እንዳታጸድቅ የዘሩባትን እንዳታበቅል ለባለንብረቱ አመለከተ ይህም ጥያቄው ከእግዚአብሔር መልስ አግኝቷል፡፡ ነገሥ 17፥1፡፡ ከዚህ ላይ የሊቀ ነቢያት ሙሴንና የኢሳይያስን ቃል ያስጠቅሳል ዘዳ 32፥1-4፣ ኢሳ 1፥2-5፡፡ በእነዚህ እስከፊ ዓመታት ውስጥ በመሪዎች አመፅ በኤልያስ ተግሣጽ የሚመለከተውም የማይመለከተውም የሚልሰውና የሚቀምሰው አጥቶ በዋለበት እንደ ቅጠል ረገፈ፥ እንደሻሽ ተነጠፈ፡፡ የኀጥአን ፍዳ ጻድቅ ይደፋ ይሏል ይህ ነው፡፡
ዛሬም በአምስቱ ክፍለ ዓለም የብዙኃኑ እልቂት ሲፈጸም የሚታየው በጥቂት እግዚአብሔር የለሽ ሰይጣን ጁንታዎች ሽፍቶች መሆኑን ከአክአብና ኤልዛቤል ይማሯል፡፡
ይህን የኤልያስን ጠበቅ ያለ እገዳ ከስምንት መቶ አምሳው ነቢያተ ሐሰት ካህናተ ጣዖት አንዱም ወደ ሚመለከተው በጸሎቱም ሆነ በመሥዋዕቱ አመልክቶ ሊያስነሳ ወይም ለማስነሳት የቻለ የለም፡ ጠንቋዮችና አታላዮች በብሉይ ኪዳን ብዙ ጊዜ ከቤተ መንግሥት ተለይተው አይርቁም፡፡ 1ኛ ነገሥ 18፥22፣ዳን 2፥1-14፡፡
✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18፥41-46፣ ያዕ 5 17-18 እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የገባውን ቃል ኪዳን አያጥፍም አቁም ሲሉት ያቆማል፥ ስጥ ሲሉት ይሰጣል እንጂ ምን አገባቸው ብሎ እንደፈለገው አያደርግም፡፡
የእግዚአብሔር ሐዋርያ ስለ ኤልያስ ማንነት ሲያደንቅ ኤልያስ እንደኛ ሰው ነበር ዝናም እንዳይዘንም ከለከለ እንደገናም እንዲዘንም አደረገ በማለት በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖች ከቀና ክርስትናቸው ምን እንደሚጠበቅባቸው ከእምነታቸው ምን ማግኘት እንዳለባቸው ይጠይቃል ያዕ.5፥13-20፡፡ ዛሬስ ምን ይመስሎታል፡፡
ኤልያስ በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ነገር ግን በረዶ ያዘነመላቸው አንደኛ ሙሴ ዘፀ 9፥13-21 ሁለተኛ ኢያሱ 10፥9-12 ሦስተኛም ሳሙኤል 1ኛ ሳሙ 12፥1-19 ይመለከታል፡፡
✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡
✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡
✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ይህች ሴት በእምነቷ አርአያነት ያላት ደገኛ ሴት ናት፡፡ ኤልያስን የእግዚአብሔር ሰው ሆይ #ከአንተ_ጋር_ምን_አለኝ፣ ኀጢአቴንስ ታስብ ዘንድ ልጄንስ ትገድል ዘንድ ወደ እኔ መጥተሃልን ብላዋለች፡፡ ኤልያስም በእግዚአብሔር ኀይል ማንኛውንም ችግር ለመፍታት ሙሉ መብት ነበረውና ወዲያውኑ ወደ አምላኩ በመጸለይ የሞተውን ብላቴና ጠጋ ብሎ ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት አስነስቶ የብላቴናውን እናት አስደስቷል 1ኛ ነገሥ. 17 17-24
ሐዋርያው የእምነት ጀግኖችን በመዘገበበት አንቀጽ ይህችን ሴት ልብ ይሏል፤ ዕብ 11፥35፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ያሉ እናቶች ያስፈልቷል፡፡ ይህችን ሴት የሚመስሉ እናቶች 2ኛ ነገሥ. 4፥18-38 ፣ሉቃ 7፥11-17 ተመዝግበዋል፡፡ በሐዋርያት ሥራም ያሉት እናቶች ከእነዚህ ጋር ያነጻጽሯል የሐዋሥ 9 36-43፡፡
✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29፡፡ ሰይጣን በሰማርያ ምድር እንደዚያ ቀን ሰው መዘባበቻ በመሆን የውርደት ቀን ገጥሞት አያውቅም፡፡ በገዛ አገሩና መንደሩ፡፡
✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበ
በአ.አ ብቸኛ በሆነው የወንጌላዊው ዮሐንስ ቤ.ክ በደብረ ነጎድጓድ ሥርዐተ ማኅሌቱ ይህን ይመስል ነበር፨
ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋና በሆነው ዘንስር ዮሐንስ ደብረ ተድላ ላይ ይደረግ የነበረውን ማኅሌተ ጽጌ መስሎ በዝማሬና በእልልታ ቦታው እስኪጠብ ድረስ እንዲሁ አደረ፨ ካህናትና ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በነጭ ልብስና በጥንግ ድርብ አሸብርቀው ነበር፨
ሥርዐተ ማኅሌቱንም በፀባቴ ገብረ ማርያምና በደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ሰሎሞን ሲመራ አድሯል፨
/ፈክር ለነ ወልደ ነጎድጓድ፤
ወልደ ነጎድጓድ ፈክር ለነ... የሚለውን ቸብቸቦም ለቆምሻ አቅርበንላችኀዋል/
/ከቦታው ድረስ ለዘገበልን ቅዱስ ዮሐንስ ይጠብቅልን/
በአ.አ ብቸኛ በሆነው የወንጌላዊው ዮሐንስ ቤ.ክ በደብረ ነጎድጓድ ሥርዐተ ማኅሌቱ ይህን ይመስል ነበር፨
ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋና በሆነው ዘንስር ዮሐንስ ደብረ ተድላ ላይ ይደረግ የነበረውን ማኅሌተ ጽጌ መስሎ በዝማሬና በእልልታ ቦታው እስኪጠብ ድረስ እንዲሁ አደረ፨ ካህናትና ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በነጭ ልብስና በጥንግ ድርብ አሸብርቀው ነበር፨
ሥርዐተ ማኅሌቱንም በፀባቴ ገብረ ማርያምና በደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ሰሎሞን ሲመራ አድሯል፨
/ፈክር ለነ ወልደ ነጎድጓድ፤
ወልደ ነጎድጓድ ፈክር ለነ... የሚለውን ቸብቸቦም ለቆምሻ አቅርበንላችኀዋል/
/ከቦታው ድረስ ለዘገበልን ቅዱስ ዮሐንስ ይጠብቅልን/
ጥር 4 የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡ (የአባ ናርዶስ ዘደብረ ቢዘን እረፍቱ ነው፡፡ የጊዮርጊስ፤ የሊቀ ጳጳሳት ማርቴና፤ የሰማዕት ታኦድራ፤ የአባ ሊቃኖስ፤ የቀውስጦስ መታሰቢያቸውም ነው፡፡)
፨ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ፤
#በተለያዩ_ቅጽል_ስሞች_የሚጠራ፤ (100 አካባቢ ከሚጠጉ ስሞቹ ጥቂቶቹን /21ዱን ስሞች ከጽሑፍ በስተመጨረሻ ይመልከቱ)
#ሰዓሊ_የኾነ፤ የጌታችንን ስነ ስቅለት የሳለ፡፡
#ከ81ዱ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_ክፍሎች_5ቱንና_ሌሎች_መጻሕፍትንም_(ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤
#ብዙ_ደቀ_መዛሙርትን_ያስተማረ፤
✤ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤
✤ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤
✤ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤)
✤ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤
✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /እመጽሐፈ ሰዐታት/
፨ ‹‹ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ፤
ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ›› /መልክአ ኢየሱስ/
፨ ሰላም ለሥዕልኪ ወለሥዕለ ወልድኪ ዘሰዓሞ፤
ዮሐንስ ርኄ ዮሐንስ ቀናንሞ፤
ለዝ ወልድኪ መሐሪ ኅሩመ በቀል ወተቀይሞ፤
ማርያም ሀብኒ በእዴኪ እንዘ ትጼውዒ ስሞ፤
ሥጋሁ ቅዱሰ ወክቡረ ደሞ፡፡ /መልክአ ሥዕል/
፨#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ፤
1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ)
2. ዮሐንስ ድንግል
3. #ዮሐንስ_ፍንው
4. #ዮሐንስ_ካህን
5. #ዮሐንስ_ኅሩይ
6. ዮሐንስ ሥርግው
7. #ዮሐንስ_ምዑዝ
8. ዮሐንስ ቅኑይ
9. #ዮሐንስ_ማኅቶት
10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ
11. #ዮሐንስ_ክቡር
12. ዮሐንስ ጻድቅ
13. #ዮሐንስ_ረድእ
14. ዮሐንስ ማኅቶት
15. #ዮሐንስ_ድንግል
16. ዮሐንስ ንጹሕ
17. #ዮሐንስ_ለባዊ
18. ዮሐንስ መረግድ
19. #ዮሐንስ_ዕንቈ
20. ዮሐንስ መልአክ
21. #ዮሐንስ_ኪሩብ
/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/
ልዩ የጥምቀት በዓል ጕባኤና ዝክረ ቅዱስ ያሬድ (፻፲፬ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) እንዳያመልጣችሁ፡፡ ዐርብ ጥር ፫፡፡ ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ በሰዐቱ ይገኙ!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡
