Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 382 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 582,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 195 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 382 名订阅者。
根据 07 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 40,过去 24 小时变化为 9,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.55%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 469 次浏览,首日通常累积 1 461 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 08 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 382
订阅者
+924 小时
-177 天
+4030 天
帖子存档
ዘምኵራብ፡፡
(መዝሙር፤ ምስባክ፣ ምንባባት፣ ወንጌል)
መዝሙር ዘምኲራብ፤ቦአ ኢየሱስ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ፤
ቦአ ኢየሱስ ምኲራበ አይሁድ
ወመሀረ ቃለ ሃይማኖት
ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት፤
አነ ውእቱ እግዚአ ለሰንበት
ወአቡሃ ለምሕረት
እግዚአ ውእቱ ለሰንበት
ወልደ እጓለ እመሕያው፤
ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምሥያጥ
ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ፤
ቦአ ምኲራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ፤
አንከሩ ምሕሮቶ ሞገሰ ቃሉ
ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ።
ትርጕም፤ ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገባ፤ የሃይማኖትን ቃል አስተማረ፡፡ ከመሥዋዕት ምጽዋትን እወዳለሁ አላቸው፡፡ የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባትዋ እኔ ነኝ አላቸው፡፡ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ፤ ቤቴ የጸሎት ቤት ነው (ይባላል)፡፡ ምኵራብ ገብቶ ተቆጣቸው፤ ዝም ይሉ ዘንድ ትምህርቱን የቃሉን መሰማት (ሞገስ) የነገሩን መወደድ የአፉን ለዛ አደነቁ፡፡
ምንባባት
ቈላስይስ ፪፥፲፮-ፍጻሜው
ያዕ. ፪፥፲፬-ፍጻሜው
የሐዋ. ፲፥፩-፱
ꕥꕥꕥ ፨፨፨ ꕥꕥꕥ
ምስባክ፤ መዝ. ፷፰፥፱
እስመ ቅንዓተ ቤትከ በልዓኒ፤
ትዕይርቶሙ ለእለ ይትኤየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፤
ወቀጻእክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡
(ትርጕም፤ የቤትህ ቅናት በልቶኛል፤ የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ላይ ወደቀ፤
ነፍሴን በጾም ቀጣኋት፡፡)
ꕥꕥꕥ ፨፨፨ ꕥꕥꕥ
ወንጌል፤
ዮሐ.፪፥፲፪-ፍጻሜው
ꕥꕥꕥ ፨፨፨ ꕥꕥꕥ
ቅዳሴ፤
ቅዳሴ እግዚእ (ነአኵተከ)
ꕥꕥꕥ ፨፨፨ ꕥꕥꕥ
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
ምኵራብ፤ ሦስተኛው ሳምንት
ሦስተኛ ሳምንት ምኵራብ ይባላል፡፡ ጌታ በምኵራብ ማስተማሩን የሚዘከርበት ሳምንት ሲሆን ‹‹ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ›› የሚልና ይህን የመሰለ ጌታ በምኩራብ ማስተማሩን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢሩሳሌም የአይሁድ ቤተመቅደስ ነበራቸው፡፡ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተመቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡንም ወደ ባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሰሩ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ ሐዋርያት በሚያስተምሩበት ወቅት ከአንዳንድ ቦታዎች በቀር በምኵራቦች ገብተው ወንጌልን አስተምረዋል፡፡
በብሉይ ዘመን ቢያንስ ዐስር የጎለመሱ ወንዶች (የቤተሰብ ኃላፊዎች) በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመስራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ዋናው ቤተ መቅደሱ ያለው በኢየሩሳሌም ብቻ ነበር፡፡
በምኵራብ ውስጥም የኦሪት የሕግ መጻሕፍትና በቅዱሳን ነቢያት የተጻፉ ጽሑፎች በብራና ጥቅልል ይገኛሉ፡፡ ምዕመኑ እንዲሰማቸው እንደ መድረክ ባለ ቦታ ላይ ካህናትና መምህራን ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም ያስተምሩ ነበር፡፡
በኦሪቱ ምኵራብን የሚመሩት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሲገኝ፤ በመግረፍ ወይም ከምኵራብ በማስወጣት ሊቀጡ ስልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር ጥቅሎችን በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትዕዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡
በየሰንበቱ ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስበው አምልኮታቸውን ይፈጸሙ ነበር፤ በአምልኮታቸው ውስጥም ጸሎት፤ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፤ ስብከትና ቡራኬ ነበር፡፡
በዚህ በምኩራብ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፤ ሕሙማንን ፋውሷል፡፡ የኢሳይያስን መጽሐፍ ምዕራፍ ፷፩ን አንብቧል፡፡ በዚህ በዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ምኵራብ) የሚታሰበውም ይህ ነው፡፡
፨ ‹‹ወደ አደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሳ፡፡›› ሉቃ. 4፥16
፨ ‹‹ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡›› ማቴ. 13፥52
፨ ‹‹ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፡፡››ማር 6፥1
፨ በዕለቱ ቅዳሴ ላይ የሚነበቡ ምንባባትም፤ ጌታችን ቤተ መቅደሱን የንግድ ማዕከል ያደረጉትን ዓይቶና አዝኖ ነጋዴዎቹን ከነመንጋቸው በጅራፍ እንዳስወጣቸውና ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን እኔ እሠራዋለሁ፡፡›› ብሎ ስለመ ሞቱና ስለ ትንሣኤው ማስተማሩን የሚገልጽ ነው፡፡
፨፨፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፨፨፨
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
*ለታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ የብር ጸናጽል፣ መቋሚያና መስቀል አበርክተዋል፤ እነዚህም ንዋያተ ቅድሳት በገዳሙ ቤተ መዘክር (Museum) ተቀምጠው በዕይታ ላይ ይገኛሉ፡፡
*ላደጉባት ለጋን ማርያም የተለያዩ ንዋየተ ቅድሳትን አበርክተዋል፤ እንዲሁም በአቅራቢያው ለሚገኘው የሰገን ሚካኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑን አሠርተዋል፡፡ አሁን እንኳን በቅርቡ በየካቲት ወር እንኳን መጎናጸፊያ፣ ሞጣሕት፣ ሽቱ፣ ከነሻንጣው ጭምር በስጦታ አበርክተዋል፡፡
*ለታላቁና ባለ 13ት ቤተ መቅደሱ ሞላሌ ዳግማዊ ቤተልሔም አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ገዳም የብራና ግብረ ሕማማትና የተለያዩ ንዋያተ ቅድሳት አብርክተዋል፡፡
*ለእንሳሮ የትኖራ ቅዱስ ሚካኤል የተለያዩ ንዋየተ ቅድሳት አበርክተዋል፡፡
አባታችን አባ ቆሞስ ተክለ ወልድ በዚህች ምድር ላይ ከልጅነት እስከ ዕርግና በቤተ ክርስቲያን አድገውና ኖረው፤ ተምረውና አገልግለው ያለደዌ ፥ ያለሕማም እኁድ የካቲት 22/2012 ዓ.ም. ጠዋት ቁርሳቸውን ዳቦ በሰሊጥና በማር አድርገው ተመግበው እንዳበቁ በተወለዱ በ83 ዓመታቸው በሰላም የቅዱሳንን ዓይነት ዕረፍት አረፉ፡፡ ሥርዐተ ግብዐተ መሬታቸው ደግሞ ከፍትሐት ጭምር በታላቁ ገዳም ዕፁብ በሚያሰኝ ሁኔታ በደብረ ደብረ ሊባኖስ የካቲት 23/2012 ዓ.ም. ተፈጽሟል፡፡
የቃል አስረጂዎች፤
*ቀሲስ ተስፋዬ፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም አገልጋይና የቆሞስ አባ ተክለ ወልድ የንስሐ አባት፡፡
*የአባ ተክለ ወልድ የእኅት ልጆች
*ወ/ሮ ዐሥራት (ፍሬሕይወት) ተክለ አረጋዊ፤ ኄኖክ ጌታቸው፤ ቄስ……. አብረው በአንድ ግቢ የሚኖሩ፡፡
*ዲያቆን ዮናስ፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም አገልጋይና ከቆሞስ አባ ተክለ ወልድ አንዳንድ ጥያቄዎችን የጠየቀ፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
‹‹#ያገለገለህን_ሰው_ሞት_ቸል_አትበል_፡፡›› ሲራክ 38፥26
(እያለቀስን ጻፍንላችሁ)
ደብራችንን ለ26 ዓመታት በነጻ በክህነት ያገለገሉን አባት #ቆሞስ_አባ_ተክለ_ወልድና በተለያዩ የማስተባበር አገልግሎቶች የሚያገለግለው ወንድማችንን #አቡዬን (#ዮሴፍ_አለምሸትን) በአንድ ቀን አጣች፡፡ የ2ቱንም አጭር ታሪክ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
#የቆሞስ_አባ_ተክለ_ወልድ_መኮንን_ታሪክ፤
፠ ‹‹ግርማት ኃይላ›› ብለው የሚጠሯት የእመቤታችን ስዕል ዘንድሮን እንዳማላፍ ነግራኛለች ብለው ተናግረው ያረፉ፤
፠ በታላቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም 3ት ስውራን አባቶች መኖራቸውን የተናሩና ደብሩን ለ26 ዓመታት በነጻ ያገለገሉ፤
፠ አኗኗራቸው ልክ እንደ ገዳም አባቶች የሆኑት፤
፠ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲሁም የሃገራችንንና የቅዱሳንን ታሪክ በቃላቸው የሚያውቁ፤
፠ ድምፃቸው እጅግ በጣም የሚማርከው፤…… አባታቸውን ቆሞስ አባ ተክለ ወልድ የካቲት 23 ዐረፉ፡፡ ሥርዐተ ግብዐተ መሬታቸውም በታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ተፈጸመ፡፡
ግንቦት 24/1929 ዓ.ም. በሰሜን ሸዋ እነዋሪ ሞረት አውራጃ ልዩ ስሙ ሰገድ ሚካኤል (ጋን ማርያም) አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ መኮንንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ተወለዱ፡፡
የተወለዱበት ወቅቱ ጣሊያን ኢትዮጵያን በጠላትነት የወረረችበት ወቅት በመሆኑ ገና ልጅ ሳሉ ቤተሰቦቻቸው ይዘዋቸው ወደ ዋሻ ገቡ፤ ቢሆንም ግን ጠላት ጣሊያን ደርሶ በአካላቸው ላይ ጉዳት አደረሰባቸው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በሞት ገና ብዙ ሥራን የሚሠራባቸው በመሆኑ ሕይወታቸው ተረፈ፡፡
ቤተ ሰቦቻቸውም ቤተ ክርስቲያንን እያገለገለ ይደግ ብለው በአቅራቢያቸው ለምትገኘው ጋን ማርያም ሰጧቸው፤ እርሳቸው በዚህችው ቤተ ክርስቲያን በልጅነታቸው እያገለገሉ ቆይተዋል፡፡ 7ት ዓመት ሲሞላቸው ወደ ታላቁ ገዳም ደብር ዜና ማርቆስ ገብተው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ከተለያዩ መምህራን በሚገባ ቀስመዋል፡፡
ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው ወደ አዲ አበባ ረጲ መድኀኔ ዓለም አምጥተዋቸው በዚሁ ደብር ከሚገኙ መምህራን ተጨማሪ ትምህርቶችን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ፡፡ እቴጌ መነን አ.አ. ኮልፌ ላይ የቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅን ከፍተው የሚማሩ ተማሪዎችን በሚያሰባስቡበት ጊዜ በቢትወደድ መኮንን እንዳልክቻው አቅራቢነት ወደ ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብተው ተምረዋል፡፡ ለተማሪነትም እንደተመረጡ ከገጠር ለብሰዋት የመጡት ነጠላ ነበረች፤ ይህች ነጠላ አልቃ ነበርና አውልቋት ተባሉ፤ እርሳቸው ግን ከገጠር ስወጣ ለብሼያት የወጣኋት የእናቴ ነጠላ ነችና አላወልቃትም አሉ፤ እቴጌ መነን ይህን ሲሰሙ ልባቸው ተነክቶ በነጠላቸው ላይ የሚለብሱትን ሌሎች ልብስ ወዲያውኑ ሰጥተው ትምህርታቸው እንዲማሩ አደረጓቸው፡፡
በዜማ ትምህርት የተደነቁ በመሆናቸው በሃገር ፍቅር በዜማ ክፍል ተቀጥረው ለመሥራት ፍላጎቱም ስለነበራቸው የመንፈሳዊ ኮሌጅ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁና የሃገር ፍቅር የዜማ ክፍል አስተባባሪ ኢዩኤል የተባሉ ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ለመቀጠር ተመዝገቡ፤ ነገር ግን ቀጠሮ ስለበዛባቸው፤ ወደ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተመልሰው ከቆዩ በኋላ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ገብተዋል፡፡
የ23 ዓመት ዕድሜ ላይ ሳሉም በታላቁ ገዳም በደብረ ሊባኖስ መንኵሰዋል፤ ኋላም ቆይተው በ1957 ዓ.ም. ቁምስና ተቀብለዋል፡፡
በቋንቋ በኩልም አማርኛ፣ ግእዝ፣ ዐረብኛና ሱዳንኛን አዋቂ ነበሩ፡፡
በጠቅላይ ቤተ ክህነትም የብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ረድዕ በመሆን ሲያገለግሉ ቆተዋል፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም እጅግ በጣም ይወዷቸው ስለነበር ኋላ አሜሪካ ከሄዱ በኋላ ልብስና ገንዘብ ይልኩላቸው ነበር፡፡ በደሴ ይኖሩ ከነበሩት ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ጋርም አብረው ኖረዋል፡፡
በመቀጠልም ወደ አሥመራና አሰብ ለአገልግሎት ተልከዋል፤ ምጽዋንና ደብረ ቢዘንንም አገልግለዋል፡፡ በመቀጠልም ግብጽ ለተወሰኑ ጊዜያት ከቆዩ በኋላ፤
የሱዳን ካርቱም ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሆነው ተመድበው በትጋት አገልግለዋል፡፡
ወደ ሃገራቸው ተመልሰው በጠቅላይ ቤተ ክህነትና በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስት ማርያም በተያዩ የአገልግሎት ዘርፎች እያገለገሉ መኖሪያቸውንም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ አድርገው ቆይተዋል፡፡
ከ26 ዓመታት በፊት በ1986 ዓ.ም. የመድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያንን በጣም ይወዱ ስለነበር ከጠቅላ ቤተ ክህነትና ከቅድስት ማርያም ወደ ታላቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም መጥተው አቶ አማረ የተባሉ አባት የመቃብር ቤት ሰጥተዋቸው ደብራችንን በቅስና አገልግሎት በነጻ ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ በመቃብር ቤት ሕይወታቸውም በቀጨኔ ደብ ሰላም 3ት ስውራን አባቶች (1ኛው መነኰስ ሺኖዳ ዘግብፅ የሚባሉ) መኖራቸ ተገልጾላቸዋል፤ ይህንንም ነገር በጣም የቅርብና የልብ ወዳጃቸው ለሆኑ ሰዎች ብቻ ተናግረዋል፡፡
በ2000 ዓ.ም. ላይም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉ በመቃብር ቤት የሚኖሩ አገልጋዮች ቤቶቹን እንዲለቁ በተደረገበት ወቅት ለደብራችን ብዙ ታላላቅ አስተዋጽዖ ካደረጉት ግንባር ቀደም የሆኑት የአቶ ደርቤ አበበ ባለቤት ወ/ሮ ዐሥራት (ፍሬሕይወት) ተክለ አረጋይ በመኖሪያ ቤታቸው ግቢ ውስጥ አንድ ክፍል ሰጥተዋቸዋል፡፡ እንዲያም ሁኖ የሚወዱት ደብራችንን ሌሊት፣ ጠዋትና ማታና ሳይለዩ፤ ሌሊት በሰዓታትና በኪዳን፤ ጠዋት(ከሰዐት) በቅዳሴ፣ ማታ በጸሎት አይለዩም ነበር፡፡
በሚሄዱበት ቦታ ሁሉ አብረው ይዘዋት የሚሄዷትና የማይለይዋት ስዕለ እግዝዕትነ ማርያም ‹‹ግርማት ኃይላ›› (ፎቶውን ይመልከቱ) ብለው የሰየሟት ዘንድሮ እንደማላልፍ ነግራኛለች ይሉ እንደነበር አብረው የሚኖሩ አባቶች ነግረውናል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን፣ ታሪክን በተለይም የሃገራችንንና የቅዱሳንን ታሪክ እጅግ በጣም ከማወቃቸው የተነሣ ለሚጠይቃቸው ሁሉ በቃላቸው አስፈላጊውን መልስ ይሰጡ ነበር፤ በዚህም ሊቅነታቸው የማይደነቅባቸው ሰው አልነበረም፡፡ በዜማ በኩልም ቅዳሴ በጣም አዋቂና ድምፃቸው እጅግ የሚመስጠው ቆሞስ አባ ተክለ ወልድ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው ድረስ ድምፃቸው ባለመለወጡና ቅዳሴ በጣም ስለሚወዱ የቅዳሴ አገልግሎት የሚያገለግሉት አብዛኛውን ጊዜ በዲቁና ነው፡፡
እኒህ አባት የማላስተምረውና የማልመክረው፤ የማልጠይቀውና የማልጎበኘውን የንስሐ ልጅ አልይዝም ብለው አንድም የንስሐ ልጅ አልያዙም ነበር፡፡
አኗኗራቸውም ልክ በገዳም እንዳሉ አባቶች ሲሆን፡፡ ይኸውም፤
*በአብዛኛው ጊዜ የሚለብሱት ወይባ (ቢጫ) ልብስ ነው፤
*የሚተኙት መሬት ላይ ያለምንም ፍራሽ ነው፤ (ፎቶውን ይመልከቱ)
*የሚበሉት ዳቦ በሰሊጥና በማር ነው፤
ምንም እንኳን ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስንም ጨምሮ ከውጭ ሃገር ጭምር የሚያውቋቸው ሰዎች ገንዘብ ቢልኳላቸውም እርሳቸው ግን በመጠን የሚኖሩ ስለሆነ፤ ገንዘቡን ለተለያዩ ገዳማትና አድባራት በጥሬ ገንዘብና አስፈላጊውን ንዋያተ ቅድሳት እየገዙ ይሰጡ ነበር፡፡ ለአብነትም ያህል፤
*ለደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም 4ት የእጅ መስቀሎች (1ዱ ከኢየሩሳሌም የመጣ)፣ 1ድ የአንገት መስቀል፣ ልዩ የሆነ ትልቅ መቁጠሪያ፣ ይታጠቁበት የነበሩ 2ት የመነኰሳት መታጠቂያዎች (1ዱ ከኢየሩሳሌም የመጣ ከቆዳ የተሠራና ስማቸው ያለበት ነው)፣ እንዲሁም 3ት የመነኰሳት ቀሚስ (1ዱ ላይ የእመቤታችን ስዕል በጥልፍ የተቀመጠበትን) አበርክተዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ ስጦታዎችም በቤተ መዘክር (Museum) ተቀምጠው ተቀምጠው በዕይታ ላይ ይገኛሉ፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ)
፠ #ዓድዋ፥ #ሶሎዳ(በፎቶ ላይ የምትመለከቱትና ከዓድዋ ተራሮች ዋነኛው)፡፡
#ዓድዋ #፬ት #ታላላቅ_ነገሮችን_አስተባብራ_የያዘች_የኢትዮጵያ_ሕያው_ምስክር።
1ኛ) ከ1500 ዓመትት በፊት ዓድዋ (ዖድዋ፥ ዖድዋ) ብለው የሰየምዋትንና ከተሰዐቱ ቅዱሳን በገቢረ ተአምራታቸው ገሪማ ገረምከኒ የተባለላቸውን #የእንዳአባ_ገሪማን ገዳም የያዘች፤
2ኛ) በዓለም #ከ1500 #ዓመታት_በላይ ረዥም ዕድሜን ያስቆጠረውን የእንዳአባ ገሪማን #የብራና_ወንጌል ጠብቃ ያቆየች፤
3ኛ) ከዓድዋ በፊት በጥር 1878 ጣሊያንን ዶጋሊ ላይ ጠላትን ድባቅ በመምታት ወደ ምጽዋ የመለሰው፡፡ የታላቁ አርበኛ #ራስ_አሉላ ነጋ (የዐፄ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና የሐማሴን ባላባት)፤ በክብር ያሸለበባት፤
4ኛ) ከጣሊያን ጋር የመጨረሻው ፍልሚያ የተደረገበትን #ሶሎዳ_ተራራና ሌሎችንም ተራሮች በጉያዋ ያቀፈች ናት፤ ዓድዋ።
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ #ዓድዋ፥ #ሶሎዳ (በፎቶ ላይ የምትመለከቱትና ከዓድዋ ተራሮች ዋነኛው)፡፡
#ዓድዋ #፬ት #ታላላቅ_ነገሮችን_አስተባብራ_የያዘች_የኢትዮጵያ_ሕያው_ምስክር።
1ኛ) ከ1500 ዓመትት በፊት ዓድዋ (ዖድዋ፥ ዖድዋ) ብለው የሰየምዋትንና ከተሰዐቱ ቅዱሳን በገቢረ ተአምራታቸው ገሪማ ገረምከኒ የተባለላቸውን የእንዳአባ ገሪማን ገዳም የያዘች፤
2ኛ) በዓለም ከ1500 ዓመታት በላይ ረዥም ዕድሜን ያስቆጠረውን የእንዳአባ ገሪማን የብራና ወንጌል ጠብቃ ያቆየች፤
3ኛ) ከዓድዋ በፊት በጥር 1878 ጣሊያንን #ዶጋሊ_ ላይ ጠላትን ድባቅ በመምታት ወደ ምጽዋ የመለሰው፡፡ የታላቁ አርበኛ ራስ አሉላ ነጋ (የዐፄ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና የሐማሴን ባላባት)፤ በክብር ያሸለበባት፤
4ኛ) ከጣሊያን ጋር የመጨረሻው ፍልሚያ የተደረገበትን ሶሎዳ ተራራና ሌሎችንም ተራሮች በጉያዋ ያቀፈች ናት፤ ዓድዋ።
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#ዜና_ዕረፍት
****ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል።
፠ ደብራችንን በተለያዩ አገልግሎቶች ለበርካታ ዘመናት ያገለገሉን #ቆሞስ_አባ_ተክለወልድ እና
፠ በመስቀል ደመራ፣ በጥምቀትና በተለያዩ የደብራችን አገልግሎት ግንባር ቀደም አገልጋያችን #ዮሴፍ_አለምሸት (#አቡዬ) በድንገት ስላረፉ፤ ሥርዐተ ግብዓተ መሬታቸው የሚፈጸመው፤
* ሰኞ የካቲት 23 ጠዋት የአባ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሽኝት
* የአቡዬ ደግሞ በ8 ሰዐት በደብራችን ላይ ይፈጸማል።
የዐድዋ ድል 124ኛ ዓመት መታሰቢያን በማስመልከት በአ.አ. ኤግዚብሽን ማዕከል ከቀረቡት ስዕሎች መካከል ሰዓሊ በድሉ ሞላ፤ የዐድዋ ድልን እንዲህ ገልጾታል፡፡
#፻፳፬ኛ #ዝክረ_ዐድዋን_በየት_ሊያከብሩ_አስበዋል??????፤
ከተለያዩ አኀት ሰ/ት/ቤቶች ድግሱን ደግሰው፥ ወጥተውና ወርደው ብለው ከሚጠብቋችሁ መካከል፤
የማኅበረ ቅዱሳ ጥናትና ምርምር፤ ሰኞ የካቲት 23፤ ከቀኑ 7፡ 30 - 11፡30 ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና የዐድዋ ድል›› በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ በዕውቁ ምሁር መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በ3ኛ ፎቅ ላይ አዘጋጅቼ እጠብቃችኋለሁ፤ በዕለቱ ሥራና ትምህርት ስለሚዘጋ ማንም ሰው ቢሆን ከድግሴ እንዳይቀር እኔ ሰፋ አድርጌ ደግሼ እጠብቃለሁ ብላችሁ ጥሪዬን አስተላልፉልኝ ብሏል፡፡
የመናገሻ ገነተ ጽጌ (አራዳ) ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት፤ እኁድ የካቲት 22-የካቲት 24 (ለ3ት ቀናት)፤ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በዐውደ ምሕረትና በሰ/ት/ቤቱ ሕንፃ ላይ ተጋበዙልን ብለዋል፡፡
የምስካየ ኅዙናን ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት፤ ቅዳሜ የካቲት 21 ከ11፡30 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ‹‹ዐድዋና ቤተ ክርስቲያን›› በሚል ሰፊ ድግስ ደግሼ እንደተለመደው በፋና ወጊነት እጠብቃችኋለሁ ብላለች፡፡
የደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም፤ ሰኞ የካቲት 23 ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ የጥበብ ምሽት አዘጋጅተን እንጠብቃችኋለን ብለው የግብዣ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ መሕረት ማርያምና ክርስቶስ ሠምራ የእውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት፤ እኁድ የካቲት 22 ጠዋት ከ3 ሰዐት ጀምሮ ‹‹ዝክረ አድዋ›› በሚል ርዕስ ልዩ የኪነ ጥበብ ጕባኤ ስላዘጋጀሁ ከቅዳሴ መልስ በጠዋቱ ወደየትም እንዳትሄዱ ቁርስን የሚያስንቅ ድግስ ደግሼ ፥ አሰናድቼ እጠብቃችኋለሁና በጠዋቱ እንድትገኙልኝ ብላ ጥሪዋን አስተላልፋለች፡፡
የደብረ ይባቤ ውሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት፤ እኁድ የካቲት 22 ከጠዋቱ 4፡30 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ‹‹ አድዋና ቤተ ክርስቲያን›› በሚል ርዕስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ሥርዐት፣ ትምህርተ አበውና በሌሎችም ስመ ጥርና ታዋቂውወ በሆነው በመምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል እንዲሁም መነባንብ፣ ግጥሞች፣ ጭውውትና ከአባታችን ከቅዱስ ያሬድ ዝማሬ ጋር አስተባበሮ ተሰናድቼ እጠብቃለሁና ማንም እንዳይቀርብኝ ብላ ጥሪዋን አስተላልፋለች፡፡
….. /ሌላ ያልዘገብነው ዝክረ አድዋ ካለ እንናተደግሞ ጨምሩበት
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ #የማንቂያ_ደወል_፤ (ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችንና የሃገራችንን ሁኔታ የምንማርበት፤ በቅርቡ ሰማዕታት የሆኑትን በብርሃን (በጧፍ የምናሰብበት)
አዲስ አበባ ላይ ቅዳሜና እኁድ መንገዶች ኹሉ ወደ፤ …….. ማንቂያው ደወል ያመራሉ፡፡
#ቅዳሜ_የካቲት_21/2012 ዓ.ም.፤ በገርጂ(ቦሌ) ማርያም፤
#እኁድ_የካቲት_22/2012 ዓ.ም. በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ፡፡
፠፠፠ የአቤልን የግፍ ሞት፤ የዘካርያስን በግፍ መገደል የተበቀለ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያናችንና በምዕመኗ ላይ የደረሰውን ግፍ፣ ቅትለት (ግድያ)፣ ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ሥልጣንን ተገን በማድረግ የሚሠራ ደባ፣ ሙስና፣ ……. እርሱ ይበቀልልን፤ እርሱ ፍርዱን ይስጥ፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#አድዋ፥ #ሶሎዳ፡፡ #9ኛው #የኢጣሊያና_የኢትዮጵያ_ጦርነት፡፡
9ኛ) #አድዋ፥ #ሶሎዳ፡፡
ዓድዋ የሚለውን ስም የሠየሙት ከተሰዐቱ ቅዱሳን በገቢረ ተአምራታቸው ገሪማ ገረምከኒ የተባለላቸው አባ ገሪማ ሲኾኑ፤ ዓድዋ ብዙ ተራሮችን የያዘች ሃገር ስትሆን፤ ከጣሊያን ጋር የመጨረሻው ፍልሚያ የተደረገው ከዓድዋ ተራሮች በግዙፉ #ሶሎዳ_ ተራራ ላይ ነው፡፡
#የኢጣሊያና_የኢትዮጵያ_ጦርነት_መነሻ
፠ ለአድዋ ጦርነት መነሻው፤ የአውሮፓ ኃያላን ሃገር ነን ብለው ራሳቸውን የሰየሙ አፍሪካን ሊቀራመቱ በተስማሙት መሠረት ጣሊያን ከሚስዮኖቿ አንዱና ተኩላ በሆነው አባ ማስያስ ሰላይነት ያጠኗትን ኢትዮጵያን ልትቀራመት መወሰኗ፡፡
፠ መጀመሪያ በ1861ዓ.ም. እግሯን ወደ ኢትዮጵያ በአሰብ በኩል አስገባች፤ በ17ዓመታት ቆይታ (እስከ 1878ዓ.ም.) ምጽዋን፣ የዳህላክ ደሴቶችንና የኤርትራን ቀይ ባሕር ያዘች፡፡ ምጽዋን በያዘች በ3ት ዓመታት ኤርትራን ያዘች፤ ኤርትራን በያዘች በ7 ዓመት መረብን ተሻግራ ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመግባት ጦርነት ከፈተች፡፡ ራስ አሉላ አባነጋም ድባቅ መትቶ መለሳቸው፡፡
፠ ይህ አልሆን ሲላቸው በተወካያቸው በአንቶኔሊ በሚያዝያ 25/1881ዓ.ም. በውጫሌ (ወሎ ቦሩ ሜዳ የምትገኝ) ላይ የተፈረመውን የውል ስምምንት አንቀጽ 17 በአማርኛና በጣሊያንኛ ቅጂው የተሳሰተ (የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከውጭ ሃገራት ጋር የሚያደርገውንግንኙነት በኢጣልያ በኩል ማድረግ ይገባዋል!!፡፡›› በሚል ሰበብ ሌሎች ጦርነቶች ተቀሰቀሱ፡፡
ኦ ፍጡነ ረድኤት … ብለው ኢትዮጵያውያን በእምነት ኾነው ሲጠሩት፤ ከዐይን ጥቅሻና ከዐውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የደረሰላቸው የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓሉ ነው፡፡
#ኮከበ ክብር፥
*ሊቀ ሰማዕታት፥
*መክብበ ሰማዕታት፥
*የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥
*የልዳ ፀሐይ፥
*የኢትዮጵያ ገበዝ፥
*ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥
*፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥
*በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥
*፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥
*፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤
*እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ ጋር፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር እንዲኾን ያደረገችለት፤
/የካቲት 23 ከዋይዜማው ጀምሮ በተለይም በአ.አ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. የሚቆመውን ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት አቅርበንላችኋል፡፡/
ከ1878-1888ዓ.ም. #ከዓድዋ_በፊት_የነበሩ_8ቱ_አድዋዎችና_የዓድዋ_ሶሎዳ_ውጊያ፤
1ኛ) ራስ አሉላ ነጋ (የዐፄ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና የሐማሴን ባላባት)፤ #ዶጋሊ_ ላይ ጠላትን ድባቅ በመምታት ወደ ምጽዋ የመለሰበት፡፡
2ኛ) ደጃች ደበብ፤ #ሰገነይቲ ላይ የተደረገ ውጊያ
3ኛ) ደጃች ባሕታ ሀጐስና ወንድማቸው አዝማች ሰንጋል፤ ከጄነራል ሳጎናይቲና ከተከታዩ ታንቲ ጋር ያደረጉት ውጊያ፡፡ ቀጥሎም ደጃች ባሕታና ዘመዳቸው ባሻይ ምስጉን የተሰዉበት #የሐላይ_መንደር_ ውጊያ፡፡
4ኛ) ራስ መንገሻ ዮሐንስ #በኰዓቲት_ ከጥር 13-15 የተዋጉበት፤ ጦርነቱ የተራዘመና በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሰዉበት፤ የሟች ቊጥር በመበርከቱ አሸናፊና ተሸናፊው ሳይለይ፤ የራስ መንገሻ ጦር ወደ ሰነዓፌ የተበተነበት፡፡
5ኛ) የራስ መንገሻ ዮሐንስ የጦር አዝማቾች (እነ ተስፋይ ህንጣሎ አጋሜ፥ ወልደ ማርያም፥ ቀኛዝማች ኃይለማርያም ወምበርታ፥ ቀኛዝማች አብርሃ፥ ደጃች ረዳ አባ ጉብራ /የራስ አርአያ ልጅ/) መሪያችንን ራስ መንገሻን አናስነካም ብለው #በደብረ_አላ_ ላይ የተዋጉት ውጊያ፡፡
6ኛ) ልዑል ራስ መኰንን (የኢትዮጵያ ጠቅላይ ጦር አዛዥና የሐረርጌ ገዥ /የአፄ ኃይለ ሥላሴ አባት/)፤ #አምባ_አላጌ ላይ ጣሊያንን እንደ ንብ ወረው ትልቅ ጀብድ የሠሩበትና ለአድዋውም ወኔ ቀስቃሽ ውጊያ፡፡
7ኛ) ልዑል ራስ መኰንን፤ መቀሌ #እንዳ_ኢየሱስ (ዛሬ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግ ግቢ የሚገኝበት) ላይ፤ ቀድሞ በቦታው ላይ ጠላት ሸምቆ ስለበረ ዙሪያውን ከበው ስንቅ በማሳጣት መሪው ማጆር ጋሊያኖ ማሩኝ ለጄነራሌ ለባራታሪ ሂጄ ዕርቅ ይሆናል አስማማለሁ፤ ብሎ በዕርቅ ያለቀበት፡፡ (ኋላ ግን ማጆር ጋሊያኖ ቃሉን በማጠፉና ጣሊያንን ለጦርነት በማነሳሳቱ የአድዋ ጦር ሁኗል፡፡)
8ኛ) ራስ ስብሐትና ደጃች ሐጐስ ተፈሪ (ቀድሞ ባንዳ ነበሩ) ማጆር ጋሊያኖ ለጄነራሉ ከማስማማት ይልቅ ጠብን በመምከሩና የጣሊያን ጦር በእንትጮ በኩል ከኢትዮጵያ ጋራ ሊዋጋ ሲገሰግስ የአካለ ጉዛይን ባላሃገር በማስተባበር #እንትጮ ላይ ደጀን ሁነው መክተው የተዋጉት ውጊያ፡፡
9ኛ) #አድዋ፥ #ሶሎዳ፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
