Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 382 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 582,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 195 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 382 名订阅者。
根据 07 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 40,过去 24 小时变化为 9,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.55%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 469 次浏览,首日通常累积 1 461 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 08 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 382
订阅者
+924 小时
-177 天
+4030 天
帖子存档
#በጣሊያን_ወረራ_ወቅት_አስተዋጽዖ_ካደረጉት_መካከል_ዐበይቶቹ_ገዳማትና_አድባራት፤ #ከካህናት፡፡
ፋሽስት ኢጣሊያ በ5ቱ ዓመት ወረራዋ ጀግኖች አርበኞችን ስላልቻለቻቸው ንጹሐን ዜጋዎችን በመግደል፤ እንዲሁም የተደበቁበትን ገድልና ዱር አላገኝ ስትል፤
ገዳማትንና አድባራትን አቃጥላለች፡፡
እንደ ተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት 460,770 (በጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፋቸው ደግሞ 746,800 ሰዎችን በግፍ ገድላለች፤
300ሺህ ሰዎች ደግሞ በስደት ሲንከራተቱ በረሃብ አልቀዋል፤
2,000 አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥላላች፣
በርካታ ንዋያተ ቅድሳትንም ዘርፋ ለካቶሊኳ ቫቲካን ሰጥታለች፡፡
፠ይህንን እኩይ ተግሯን በግንባር ቀደምትነት የተፋለሟት፤ ዐበይቶቹም፤
፠ የ፳ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕታት #ብፁዕ_አቡነ_ጴጥሮስ_(ሐምሌ 22/1929 ዓ.ም. መሐል አ.አ ላይ በስምንት ጥይት ያረፉት)ና #ብፁዕ_አቡነ_ሚካኤል_ (ኅዳር 24 ቀን 1929 ዓ.ም በኢሉባቦር ጎሬ ላይ በግፍ የተገደሉት)
፠ ጣሊያንን አውግዘው በታኅሣሥ 7/1928 ዓ.ም ሲሰየፉ፤ ከአንገታቸው ደም፥ ወተትና ውኃ የወጣው #ታላቁ_ሊቅ_አቡነ_ክፍሌ፡፡
፠ በግንቦት 28/1929 ዓ.ም. ቊጥራቸው 2,200 የሚሆኑ በግፍ የተጨፈጨፉ #የደብረ_ሊባኖስ_መነኰሳት፡፡
፠ በግንቦት 29/ 1929 ዓ.ም በቅዳሴ ላይ እንዳሉ የታረዱና ደመና የሸፈናቸው 43 #የአቡነ_ዜና_ማርቆስ_መነኰሳት፡፡
፠ በሰኔ 12/ 1929 ዓ.ም በማስታኮት ላይ እያሉ የተገደሉ አስከሬናቸውን ሳይቀር በአካፋ የተሰቃየው 211 #የዝቋላ_መነኰሳት፡፡
፠ በጥቅምት 17/1929 ዓ.ም የታረዱ 2116 የሆኑ #የደብረ_ዳሞ_መነኰሳት፡፡
፠ በሰኔ 3/1929 ዓ.ም 60 የታረዱ #የምድረ_ከብድ_መነኰሳት፡፡
፠ በሰኔ 15/ 1929 ዓ.ም የታረዱ፤ በዚህም አንበሶች ከጫካ ወጥተው ያለቀሱላቸው፤ 91 የሚሆኑ #የአሰቦት_መነኰሳት፡፡
፠ በኅዳር 25/ 1929 ዓ.ም የታረዱ፤ ሲታረዱም ብርሃንም የወረደላቸው፤ 143 #የአዲስ_ዓለም_ካህናትና_መነኰሳት፡፡
፠ በየካቲት 12/1929 ዓ.ም ከ30 ሺ በላይ በአካፋ ሳይቀር የተጨፈጨፉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፡፡
፠ በመጋቢት 16/1929 ዓ.ም. ከላይ በቦንብ የውሃ ገንዳውን ጭምር፣ ከታች በመትረየስ የተፈጁት 515 #የማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም መነኰሳት፡፡ የበቁ አባቶችም በጸሎታቸውም አውሮፕላኗን የከሰከሷት፡፡
፠ በመጋቢት 17/1929 ዓ.ም የታረዱ ብዛታቸው በውል ያልታወቁ #የደብረ_ዓባይ_ገዳም መነኰሳት፡፡
፠ በሚያዝያ 18 ና ሚያዝያ 20/1929 ዓ.ም የታረዱ 363 #የመርጦ_ለማርያምና_የተድባበ_ማርያም ካህናትና መነኰሳት፡፡
፠ በሐምሌ 29/1929 ዓ.ም. እየተለቀሙ እንዲታሰሩ ከተደረገ በኋላ ግማሾቹ የተሰፉትና ግማሾቹ ደግሞ በግዞት የተወሰዱት #የጎንደር_ሊቃውንት፡፡
፠ በየካቲት 18/1929 ዓ.ም. የተሠዉት የአዲስ አበባ #የካ_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና ካህናት አባቶች፡፡
፠ በየካቲት 20/1929 ዓ.ም #በአ.አ ከተማ ያሉ በተለያዩ ገዳማትና አድባራት የሚገኙ ታላላቅ ሊቃውንት ተለቅመው እንዲሰበሰቡ ከተደረገና ከተደበደቡ በኋላ እጅና እግራቸውን አስረው እሳት አጉርሰዋቸዋል፡፡
፠ የትግራይ #ጨለቆት_ሥላሴ አገልጋዮችና (ርዕሰ ደብር የነበሩትን አስተዳዳሪውን ጨምሮ) አስረው ‹‹በሮማ ካቶሊክ ታምናላችው ወይስ በረሃብ ትሞታላችሁ?›› እያሉ በረሃብ አሠቃይተዋቸዋል፡፡ እምቢ ቢሏቸው ጽኑ ግርፋት ገርፈው ከለቀቋቸው በኋላ በመኪና ገጭተው ገድለዋቸዋል፡፡
፠ #ይደመቆ_ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን /ሰሜን ሸዋ/
፠ #አፈር_ባይኔ_ተክለ_ሃይማኖት ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
፠ #አክርሚት_ቅዱስ_ሚካኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
፠ #ጎበጥ_አገር_ገብርኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ እመ ምሕረት/
፠ #አንኮበር_ቅድስት_ማርያም ቤ.ክ.
፠ #ደረፎ_ቅድስት_ማርያም ቤ.ክ. /ሰሜን ሸዋ ደረፎ/
፠ #ጎንቻ_መድኀኔ_ዓለም ገዳም /ምሥራቅ ጎጃም/
፠ #አንኮበር_ቅዱስ_ሚካኤል ቤ.ክ.፡፡
#ጀግናውና_የቅኔው_አዝመራ_አለቃ_መርሻ_ወልደ_ማርያም
ከዚህ በታች የቀረበውን ግጥማዊ ቅኔ ብዙዎቻችን እናውቀዋለን፡፡ ሊገድሏቸው የመጡትን ጣልያኖች አብዛኛውን ፈጅተው በሐምሌ 12/1928ዓ.ም. በሰማዕትነት ያረፉት የ70 አዛውንቱ ጀግናና የቅኔው አዝመራ አለቃ መርሻ ወልደ ማርያም ከመሞታቸው ከ8 ቀን ቀድመው እንዲህ ብለው ተቀኙ፡፡
ተምሮ ተምሮ ካልሰበሰቡት፤
እንዴት ያሳዝናል ሲባክን ዕውቀት፡፡
ሂጅ ተመለሽ ግቢ አገርሽ ቅኔ፤
ወንዶች ከዋሉበት መዋሌ ነው እኔ፡፡
ለጀግንነታቸውም መታሰቢያ ደግሞ የሚቀጥለው ግጥማዌ ቅኔ ቀረበላቸው፤
አለቃ መርሻ አይፈራም እጁ፤
ጠላት ሲጋበዝ እንደ ወዳጁ፤
ገሥግሠው ሄደው እንደ ጐመጁ፤
በሽጉጥ ጠርሙስ ፩ድ ፩ዱን ፈጁ፡፡
መርሻ ቢያጠጣው የሽጉጥ ጠላን፤
ወዲያው ወደቀ ግብዙ ጣሊያን፡፡
፠ ከ1927-1934 ዓ.ም. ለ7ት ዓመታት ጣሊያን በሀገራችን ላይ ያደረሰችው ጥፋት፤
*በኢትዮጵያ ሰሜንና ደቡብ በየቀለቡና በማደሪያው ከዘመተው የሞቱ፤
*ጠላት አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ዓረቦችና ዓርመኖች ግሪኮች ተዘርፈናል በማለታቸው ምክንያት የሞቱ፤
**የካቲት ሚካኤል (የካቲት 12) ዕለት በአካፋ በዱላ በእሳት ያለቁ ከ30,000 በላይ ሰማዕታት፤
*በአርበኝነት በየጊዜው በጠላት እጅ የሞቱ፤
*በደኅንነት አገር ቤት ላይ ሳሉ ሳያስቡት በጠላት እጅ የሞቱ፤
*ወደ ስደት ሲሄዱ በችግር ምክንያት በየመንገዱ የሞቱ፤
*በፌርማቶሪ አመልካችነት በየቀኑ የሞቱ፤
*ጠላት ከኢትዮጵያ ሊወጣ ሲል በተደረገው ጦርነት የሞቱ፤
*ከጠላት ወገን ሆነው (ባንዳዎች) ሆነው ከተዋጉ ባንዳ የሞቱ፡፡
*ሞሶሎኒ ባነሳው ጦርነት በየቀኑ በሚደረገው የግፍ ሥራ ያላግባብ የሞቱ (በሆለታ ተማሪ ቤት የነበሩ ወጣቶች፣
*350 የሚጠጉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ወደ ሮምና ሞቃድሾ እስር ቤት ተላኩ፤ ከ2500 በላይ ደግሞ በእስር ቤት ታጉረው እንዲማቅቁ ተደረጉ፡፡ በእስረኞችና በምርኮኞች ላይም አሰቃቂ ድርጊቶችን ፈጽማለች፡፡
**ኢጣሊያ ላደረሰችው ጥፋት 326 ቢሊዮን ሊሬ ቢወሰንባትም የሰጠችው ግን 105 ቢሊዮን ሊሬ ብቻ ነው፡፡ (እንደ ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ ዘገባ ደግሞ 175 ሚሊዮን ስተርሊንግ ተወስኖባት የከፈለችው 25 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው)፡፡ በከፈለችው ገንዘብም የቆቃ ግድብ ብቻ ተሠርቶበታል፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#የአዲስ_አበባው_ጦርነት (ሽብር ዘረፈና ግድያ፤ እምቢ ለሃገሬን ወለደ፡፡) (ከሚያዝያ 27/1928 - የካቲት 12/1929 ዓ.ም.)
/ከባለፈው ከየካቲት 12 የቀጠለ……/ #ክፍል #፮
#ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥
#ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥
#ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_
#የአዲስ_አበባው_ጦርነትና በሌላ በኩልም፤
#በጎጃም_ዱር_ቤቴና #ደጃዝማች_በላይ_ዘለቀ፤
በሸዋ #ጅሩ#ራስ_አበበ_አረጋይ፣ #ፊታውራሪ_ዘውዱ_አባ_ኮራን፣ #ደጃዝማች_ባልቻ_አባ_ነፍሶ፣ #ደጃዝማች_ፍቅረ_ማርያም_ናደው፣ #ፊታውራሪ_በለው_ቸርነት፣ #ልጅ_ኃይለ_ማርያም_ማሞ፣ #ግራዝማች_ዘውዱ_አስፋው፣ #ባሻ_ወልደ_ጻድቅ
#የሆለታ_የጦር_አካዳሚ_ምሩቃን (#ዶ.ር #የአለም_ወርቅ_በየነና በውጭ ሃገር የተሰማሩ ሲቪሎች የመሠረቱትና በ#ራስ_እምሩ የሚመራው ‹‹‹#ጥቁር_አንበሳ›› ቦንጋ ላይ ጣሊያንና ባንድና ጠራርጎ ያጠፋው፡፡
በአዲስ አበባ በ4ቱም አቅጣጭ ፋሺስትን መቆሚያ መቀመጫ ያሳጡትና የጉያ ረመጥ የሆኑበት #የሸዋ_አርበኞች ዐበይቶቹ፤
በሰሜን አዲስ አበባ #ወንድማማቾቹ_ደጃዝማች_አበራ_ካሣና_ወንድወሰን_ካሣ በውስጡ ሰማዕት የሆኑትን #ብፁዕ_አቡነ_ጴጥሮስን ያካተተ፡፡
**በሰሜን ምሥራቅ አዲስ አበባ፤ #በራስ_አበበ_አረጋይ የሚመራ፡፡
**በምሥራቅ አዲስ አበባ፤ #በደጃዝማች_ፍቅረ_ማርያም_ናደው (አባ ተጫን)ና #ነጋድራስ_ቦጋለ የሚመራ፡፡
**በደቡብ አዲስ አበባ፤ #በደጃዘማች_ባልቻ_አባ_ነፍሶ የሚመራ ሠራዊት፡፡
፠ በሚያዝያ 24/1928 ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ለተባበሩት መንግሥታት አቤቱታ ሊያቀርቡ ወደ ጄኔቫ ሄዱ፤ በሃገሪቱ ንጉሠ ነገሥቱ አለመኖሩን ጣሊያኖች ሲያውቁ በ3 ቀናት በመገስገስ #በሚያዝያ_27 አዲስ አበባን ተቈጣጠሩ፡፡ በእነዚህ 3ት ቀናት ውስጥም ሽብር ዘረፈና ግድያ #በአዲስ_አበባ እጅጉን በርቶቶ ነበር፡፡
፠ የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች የሆኑት አርበኞችም፤ ጎራዴ መዝዘው፥ ነፍጥ ይዘው፥ ጦር ሰብቀው፥ ዘገር ነቅንቀው በተለያዩ ቦታዎች እምቢ ለሃገሬ በማለት ሸፈቱ፤ #በጎጃም_ዱር_ቤቴ ያሉት ለጣሊያን ፋታ አልሰጥ አሉት፡፡ #ራስ_አበበ_አረጋይ ግንቦት 6/1928ዓ.ም. #ጅሩ ገብተው የአርበኝነት ተግባራቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ጀግኖች አርበኞችም እርስ በእርሳቸውም ተባበሩ፡፡ ለአብነትም ዋና ዋናዎቹ ከፊት መሪዎቹና አስተባባሪዎቹ #ፊታውራሪ_ዘውዱ_አባ_ኮራን፣ #ደጃዝማች_ባልቻ_አባ_ነፍሶ፣ #ደጃዝማች_ፍቅረ_ማርያም_ናደው፣ #ፊታውራሪ_በለው_ቸርነት፣ #ልጅ_ኃይለ_ማርያም_ማሞ፣ #ግራዝማች_ዘውዱ_አስፋው፣ #ባሻ_ወልደ_ጻድቅ ሲሆኑ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በጎጃም ታላላቅ የጀግንነት ጀብዱ ከፈጸመው #ደጃዝማች_በላይ_ዘለቀ ጋር ኅብረት ፈጠሩ፡፡ ይህ ኅብረትም ለጣሊያን ፋታ ሲያሳጣው፤ በሌሎች ቦታ ላሉ ኢትዮጵያውያን ፈር ቀዳጅ በመሆኑ ሁሉም ይተባባርና እምቢ ለሃገሬ ይል ጀመር፡፡
፠ ስለ ታላቁ አርበኛ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ እንዲሁም ለጃዝማች ኃይሉ እንዲህ ተብሎ ተገጥሞላቸዋል፤
**እውነተኛው ጀግና ኃይለ ማርያም፤
ስሙ እንዳይረሳ ጻፈልን በደም፡፡
እንዲህ ያለው ጀግና እንዲህ ያለ ወንድ፤
ጌጥ ይሆናቸዋል ለታሪኮች ዐምድ፡፡ የተባለለት
የደጃዝማች ኃይሉ እጁ ውድ ናት፤
የቀመሱ ሁሉ ሲያመሰግኗት፡፡ የተባለለት፡፡
፠ ለምሳሌም፤ ሰኔ 1928ዓ.ም. #የሆለታ_የጦር_አካዳሚ_ምሩቃን (#ዶ.ር #የአለም_ወርቅ_በየነን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጦ)ና በውጭ ሃገር የተሰማሩ ሲቪሎች በመተባበር የመሠረቱት ‹‹‹#ጥቁር_አንበሳ›› አንዱ ነው፡፡ ‹‹ጥቁር አንበሳ›› #ራስ_እምሩን መሪው በማድረግ ብዙ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፤ ጣሊያን ደቡብ ኢትዮጵያን ለመያዝ ካቶሊካዊውን ደጃዝማች ሀብተ ማርያምን በመጠቀም ቦንጋ አውሮፕላኖቿን ስታሳርፍ የጥቁር አንበሳ ማኅበርም በቦንጋ አውሮፕላን ማረፊያ የሰራው ጀብዱ ግን ከሁሉም የላቀና የማይረሳ ነው፡፡
፠ ሌላው ፋሽስትን በተባበረና ስልታዊ በሆነ መልኩ በሐምሌ 21/1928ዓ.ም. በአዲስ አበባ መቀመጫና መቆሚያ ያሳጡት #የሸዋ_አርበኞች ሲሆኑ አሰላለፋቸውም፤
በሰሜን አዲስ አበባ #ወንድማማቾቹ_ደጃዝማች_አበራ_ካሣና_ወንድወሰን_ካሣ የሚመሩት ሲሆን በውስጡ ሰማዕት የሆኑትን #ብፁዕ_አቡነ_ጴጥሮስን ያካተተ ነው፡፡
በሰሜን ምሥራቅ አዲስ አበባ፤ #በራስ_አበበ_አረጋይ የሚመራ፡፡
በምሥራቅ አዲስ አበባ፤ #በደጃዝማች_ፍቅረ_ማርያም_ናደው (አባ ተጫን)ና ነጋድራስ ቦጋለ የሚመራ፡፡
በደቡብ አዲስ አበባ፤ #በደጃዘማች_ባልቻ_አባ_ነፍሶ የሚመራ ሠራዊት ተጀምሯል፡፡ ነገር ግን ወቅቱ ክረምት በመሆኑና ወንዞች በመሙላታቸው አርበኞች ተቀናጅተው እንዳይዋጉና ሕዝቡንም እንዳይቀሰቅሱ ትልቅ እክል ሁኖባቸው ነበር፡፡ በዚህም ሙሉ አዲስ አበባ ላይ አደጋ ጥሎ ጣሊያንን የማስለቀቁ ተግባር የታለመለትን ያክል ባየሳካም በጥቂት አቅጣጫዎች ጀግኖች አርበኞች ተዋግተዋል፡፡ የተወሰኑትም ወደ ፍቼ ሸሽተዋል፤ ታላቁ አባት ብፁዕ ጴጥሮስም የታያዙት በዚሁ ወቅት ነበር፡፡ ጀግኖቹም ጣሊያንን እምቢ ለሃገገሬ በማለት እስከ የካቲት 12/1929 ዓ.ም. የጉያ ረመጥ ሁነውበታል፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
ሊያመልጥዎ የማይገባ የጥያቄና መልስ ልዩ ጕባኤ
#ዐርብ_የካቲት_20፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት #ጥያቄና መልስ #በሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ዙሪያ_ክፍል_፲፩፡፡ #የማጠቃለያ_ትምህርት
Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡
ለ11 ሳምንታት በሕይወት ፈተናና ምንጮቹ ዙሪያ ሲሰጡ በነበሩ ትምህርቶች ዙሪያ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር፡፡
(፻፷ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ)
#ዐርብ_የካቲት_፳፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት
አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች እንዲሁም ለ11 ተከታታይ ክፍል የተሰጡ ትምህረቶች በጥያቄና መልስ የሚዳሰሱበት ስለሆነ ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!!
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
መዝሙር ዘቅድስት.mp32.72 MB
#ዘቅድስት፡፡
(መዝሙር፤ ምስባክ፣ ምንባባት፣ ወንጌል)
#መዝሙር_ዘቅድስት፤ግነዩ ለእግዚአብሔር
ሃሌ ሉያ(፭) ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤
ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ /መዝ. ፻፬፥፩/
ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፡፡ /መዝ. ፷፭፥፪/
አክብሩ ሰንበተ ተገብሩ ጽድቀ፤
ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት፤
ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሠራቂ፤/ማቴ.፮፥፲፱
ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ሐልዩ፤
ኀበ ሀሎ ክርስቶስ፡፡ /ማቴ. ፳፬፥፵፬/
ትርጕም፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፤ ለአሕዛብም ሥራውን አውሩ፤ ለስሙም ክብር ስጡ፤ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፡፡ ብልና ዝገት በማያጠፉት፣ ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፡፡ ክርስቶስ በሚኖርበት ቦታ ያለውን ክብር እያሰባችሁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፡፡
#እስመ ለዓለም ምሕረቱ
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ …፤
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤
ነአኵተከ ወንሴብሐከ፤ ለዘዓቀብከነ ወአብጻሕከነ፤
/ግነዩ …/ ወወሀብከነ ጾመ ቅድስተ
ከመ ናግርሮ ለሥጋነ፤
/ግነዩ …/ ወከመ ንትፋቀር በበይናቲነ
ወንኅድግ አበሳ ለቢጽነ፤
/ግነዩ …/ ይእዜኒ እግዚኦ ተራድአነ ሀበነ
ንትቀነይ ለከ ለነ፤ ለአግብርቲከ ወለአዕማቲከ፤
/ግነዩ …/ አብ ቀደሳ ወአልዓላ ለዕለተ ሰንበት፤
/ግነዩ …/ ኅብስተ እምሰማይ ፈኖከ ሎሙ
ከመ ይብልዑ ወይጽገቡ፤
/ግነዩ …/ በ፪ኤ ዓሣ ወበ፭ቱ ኅብስት
አጽገቦሙ ኢየሱስ ለ፶፻ት፤
/ግነዩ …/ ወሠርዓ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ
ውብውህ ሎቱ ይኅድግ ኃጢአተ፤
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፨
#አራራይ፤
ሃሌ ሉያ፤ ለክርስቶስ ይደሉ ስብሐት፤
ለዘአብጽሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት፤
እግዚአ ለሰንበት ዘልማዱ ኂሩት፤
ሎቱ ስብሐት ለዘቀደሳ ለሰንበት፡፡
#ዕዝል፤
በወንጌል ኮነ ሕይወትነ፤
ሃሌ ሉያ(3)፤
ሰንበት ቅድስት ለውሉደ ሰብእ መድኀኒት፤
ለሙታን መንሥኢ፡፡
#ሰላም፤
ሰንበት ይእቲ ቅድስት ይእቲ፤
ሰንበት ተዓቢ እምኵሉ ዕለት እስመ ሰንበትሰ በእንተ ሰብእ ተፈጥረት፤
ሰንበተ ሰንበታቲሁ ለውሉደ ሰብእ መድኀኒት፤
ጽዮን ቅድስት ሰላማዊት፤
ታስተርኢ እምርኁቅ ከመ ማኅቶት፡፡
#ምንባባት
፩ኛ.ተሰ ፬÷፩-፲፫፤ እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኙ እንደሚገባችሁ እንመክራችኋለን፡፡/ቊ.1
፩ኛ.ጴጥ.፩÷፲፫፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጽ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡ /ቊ.13/
የሐዋ. ሥራ ፲፥፲፯-፴፤እግዚአብሔር ማንንም ሰው ርኵስና የሚያፀይፍ ነው እንዳልል አሳየኝ፡፡ /ቊ.28/
#ምስባክ፤ መዝ. ፺፭÷፭
እግዚአብሔርሰ ሰማያት ገብረ፤
አሚነ ወሠናይት ቅድሜሁ፤
ቅዳሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፡፡
(ትርጕም፤እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፤ እምነትና በጎ ምግባርም በፊቱ ነው፤ ቅድሳትና የምስጋና ገናናነትም በመቅደሱ ውስጥ ናቸው፡፡)
#ወንጌል፤
ማቴ. ፮÷፲፮-፳፭፤
ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፡፡ /ቊ. ፳/)
#ቅዳሴ፤
ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ ꕥꕥꕥ፨ꕥꕥꕥ
#ዘወረደ_መዝሙር፣ #ምንባባት፣ #ምስባክ፣ #ወንጌል በድምፅ ከፈለጉ በቴሌግራም አድራሻችን ያገኛሉ፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#ዘቅድስት፡፡
(መዝሙር፤ ምስባክ፣ ምንባባት፣ ወንጌል)
#መዝሙር_ዘቅድስት፤ግነዩ ለእግዚአብሔር
ሃሌ ሉያ(፭) ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤
ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ /መዝ. ፻፬፥፩/
ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፡፡ /መዝ. ፷፭፥፪/
አክብሩ ሰንበተ ተገብሩ ጽድቀ፤
ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት፤
ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሠራቂ፤/ማቴ.፮፥፲፱
ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ሐልዩ፤
ኀበ ሀሎ ክርስቶስ፡፡ /ማቴ. ፳፬፥፵፬/
ትርጕም፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፤ ለአሕዛብም ሥራውን አውሩ፤ ለስሙም ክብር ስጡ፤ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፡፡ ብልና ዝገት በማያጠፉት፣ ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፡፡ ክርስቶስ በሚኖርበት ቦታ ያለውን ክብር እያሰባችሁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፡፡
#እስመ ለዓለም ምሕረቱ
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ …፤
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤
ነአኵተከ ወንሴብሐከ፤ ለዘዓቀብከነ ወአብጻሕከነ፤
/ግነዩ …/ ወወሀብከነ ጾመ ቅድስተ
ከመ ናግርሮ ለሥጋነ፤
/ግነዩ …/ ወከመ ንትፋቀር በበይናቲነ
ወንኅድግ አበሳ ለቢጽነ፤
/ግነዩ …/ ይእዜኒ እግዚኦ ተራድአነ ሀበነ
ንትቀነይ ለከ ለነ፤ ለአግብርቲከ ወለአዕማቲከ፤
/ግነዩ …/ አብ ቀደሳ ወአልዓላ ለዕለተ ሰንበት፤
/ግነዩ …/ ኅብስተ እምሰማይ ፈኖከ ሎሙ
ከመ ይብልዑ ወይጽገቡ፤
/ግነዩ …/ በ፪ኤ ዓሣ ወበ፭ቱ ኅብስት
አጽገቦሙ ኢየሱስ ለ፶፻ት፤
/ግነዩ …/ ወሠርዓ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ
ውብውህ ሎቱ ይኅድግ ኃጢአተ፤
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፨
#አራራይ፤
ሃሌ ሉያ፤ ለክርስቶስ ይደሉ ስብሐት፤
ለዘአብጽሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት፤
እግዚአ ለሰንበት ዘልማዱ ኂሩት፤
ሎቱ ስብሐት ለዘቀደሳ ለሰንበት፡፡
#ዕዝል፤
በወንጌል ኮነ ሕይወትነ፤
ሃሌ ሉያ(3)፤
ሰንበት ቅድስት ለውሉደ ሰብእ መድኀኒት፤
ለሙታን መንሥኢ፡፡
#ሰላም፤
ሰንበት ይእቲ ቅድስት ይእቲ፤
ሰንበት ተዓቢ እምኵሉ ዕለት እስመ ሰንበትሰ በእንተ ሰብእ ተፈጥረት፤
ሰንበተ ሰንበታቲሁ ለውሉደ ሰብእ መድኀኒት፤
ጽዮን ቅድስት ሰላማዊት፤
ታስተርኢ እምርኁቅ ከመ ማኅቶት፡፡
#ምንባባት
፩ኛ.ተሰ ፬÷፩-፲፫፤ እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኙ እንደሚገባችሁ እንመክራችኋለን፡፡/ቊ.1
፩ኛ.ጴጥ.፩÷፲፫፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጽ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡ /ቊ.13/
የሐዋ. ሥራ ፲፥፲፯-፴፤እግዚአብሔር ማንንም ሰው ርኵስና የሚያፀይፍ ነው እንዳልል አሳየኝ፡፡ /ቊ.28/
#ምስባክ፤ መዝ. ፺፭÷፭
እግዚአብሔርሰ ሰማያት ገብረ፤
አሚነ ወሠናይት ቅድሜሁ፤
ቅዳሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፡፡
(ትርጕም፤እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፤ እምነትና በጎ ምግባርም በፊቱ ነው፤ ቅድሳትና የምስጋና ገናናነትም በመቅደሱ ውስጥ ናቸው፡፡)
#ወንጌል፤
ማቴ. ፮÷፲፮-፳፭፤
ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፡፡ /ቊ. ፳/)
#ቅዳሴ፤
ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ ꕥꕥꕥ፨ꕥꕥꕥ
#ዘወረደ_መዝሙር፣ #ምንባባት፣ #ምስባክ፣ #ወንጌል በድምፅ ከፈለጉ በቴሌግራም አድራሻችን ያገኛሉ፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
የዛሬ ወር #መጋቢት #20/2012 ዓ.ም. እኁድ ማንም ሰው ሊቀርበት የማይገባ ጕባኤ፡፡
፠ እንኳን ደስ አላችሁ፤ አባታችንን ቅዱስ ያሬድን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚዘክር ልዩ ጕባኤ (ዐበይት መምህራንና ሊቃውንት የተሳተፉበት ዘጋቢ ፊልም፤ ቅዱስ ያሬድ የተሰወረበትን ደብረ ሐዊ ገዳም ላይ ሊሠሩ የታሠቡ ሥራዎች የሚቀርቡበት) መጋቢት 20/2012 ዓ.ም. በሚሊንየም አዳራሽ ተዘጋጀ!!!
ከአሁኑ ቀጠሯችሁን እንድትይዙ ቀድመን አሳወቅናችሁ፡፡
የቀጠሮ ሰው ይበለን፡፡
ጥዑመ ስመ ፥ ወሠናየ ግእዝ፡፡
(ስሙ የሚጣፍጥ ፥ ምግባሩም የቀና)
(ቅዱስ ያሬድ ማሕሌታይን እንደምን ሰወረው፤
የሚፈራውን ሞት አዚሞ ገደለው፡፡)
/ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/
እኁድ #የካቲት 22/2012ዓ.ም. ከ7፡30 ጀምሮ፡፡
#ሱታፌ_አምላክ (#THEOSIS) #በቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ፡፡
(ጕባኤ ደቂቀ አበው፡፡)
ቦታ፤ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ፡፡
#ቅድስት፤ #ሁለተኛው_የዐቢይ_ጾም_ሳምንት
ሁለተኛው ሳምንት ቅድስት ይባላል፡፡
‹‹ሰንበትየ ቅድስት›› የሚልና ይህን የመሰለ የሰንበትን ቅድስና የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
በተጨማሪ ቅድስት የተባለበት ምክንያት ለ40 ቀን ጌታችን ጾም የጀመረበት ሳምንት ስለኾነም፤ ቅድስት ጾሙን ለማዘከር ቅድስት ተብሏል፡፡
፠ ‹‹የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ፡፡›› ዘዳ 20፥8 ይህን ቃል እግዚአብሔር በሊቀ ነቢያት ሙሴ ላይ አድሮ ተናግሮታል፡፡ ‹‹ዕረፍባት›› ያለው እግዚአብሔር የፍጥረቱን አቅም ስለሚያውቅ ነው፡፡ ስናከብር ለነፍስ ዕረፍትና ፍስሐን፤ ለሥጋ በረከት ሊያሰጡ የሚችሉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በመፈጸም የሚከበር ነው፡፡ በቤተክርስቲያን በመሰባሰብ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት /በመማር/፣ ንሰሐ ገብቶ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል፣ የተጣላ በማስታረቅ፣ ያዘነ የተከዘ በማረጋጋት በማጽናናት የታሰረን በመጠየቅ፣ በችግር የወደቁትን በመጎብኘት በአጠቃላይ በማቴ 25፥35-37 ላይ የተጠቀሱትን ምግባራት በመፈጸም ከተከበረ ከእግዚአብሔር ዘንድ የማያልቅ ዘላለማዊ በረከትን ያስገኛል፡፡ ኢሳ 56፡4-8 ይህችን ዕለት የናቁ ሰዎች በሞት ተቀጥተዋል፡፡ ዘኁ 15፡32-36፡፡
፠ ሰንበትን እንደምናከብረው ኹሉ በየ49 ዓመታት ደግሞ እንኳን ሰው መሬትም ከሚያርሱባት እንድታርፍ ኢዮቤልዩ አድርጎ ሰጥቶናል፤ መሬትን ያለ እረፍት ከዘራንባት ፍሬ አትሰጥምና፡፡
፠በተጨማሪም በዚህ ሳምንት ቅዱስ ኾኖ ቅዱሳን ኹኑ ብሎ ያስተማረው የጌታችን ትምህርት የሚታሰብበት ሳምንትም ነው፡፡
#የዕለተ_ሰንበት_ክብር፤
1. በብሉይ ኪዳን፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከስራው ኹሉ አርፎበታል፡፡ ዘፍ 2፥3፣ ዘጸ. 20፥8
2. በሐዲስ ኪዳን፤ ጌታችን የተጸነሰባት፣ ትንሣኤውን የገለጠባት፣ ለሐዋርያት ጸጋ መንፈስ ቅድስ የሰጠባት፣ ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣባት....ወዘተ ናት፡፡ በአጠቃላይ ታላላቅ ሥራዎችን የሰራበት በመሆኗ ከሌሎች ቀናት ለይተን እናከብራታለን፡፡
3. ከምጽአት በኋላ ሌሎች ቀናት ሲያልፉ ዕለተ ሰንበት ባለማለፏ ለዘለዓለም ጸንታ በመኖሯ ነው፡፡ /ድርሳነ ሰንበት/ ምዕ 18፥3-7 በዕለተ ምጽዓት ከማያልፉ ነገሮች መካከል ቃሉ፣ ዕለተ ሰንበት፣ የሰው ልጅ ናቸው፡፡
ዛሬ ዛሬ የኀጢአት ሥራ ኹሉ ቀን ተለይቶ የሚፈጸመው (ዝሙት፣ ሴሰኝነቱ፣ መዳራቱ፣ ዘፈኑ) ወዘተ በዚች ቅድስት ዕለት ነው፡፡ ‹‹ይህን ኀጢአት ቅድስት በምትኾን በእለተ ሰንበት፣ በሰሞነ ሕማማት፣ የሚፈታም ወዮለት›› ይላል፡፡ /መጽሐፈ ፍትሐ ነገሥት/፤ የባልና ሚስት ሩካቤ ኃጢአት ባይሆንም በማይገባ ወቅት ይልቁንም በዕለተ ስንበት በሰሞነ ሕማማት በረቡዕና ዐርብ ከተፈጸመ ኃጢአት ነው፡፡
ኢሳ 58፥13-14 ‹‹ፈቃድህን በተቀደሰው ቀን ከማድረግ እግርህን በሰንበት ብትመልስ፣ የሰንበትንም ደስታ እግዚአብሔር የቀደሰው ክቡር ብትለው፣ የገዛ መንገድህን ከማግኘት ከንቱ ነገርንም ከመናገር ተከልክለህ ብታከብረው፣ በዚህ ጊዜ በእግዚአብሔር አፍ ተናግሯልና››
ሮሜ 14፡16 ‹‹ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል›› በማክበራችን ከእግዚአብሔር የምንቀበለው ዘላለማዊ ዋጋ ክብር አለና፡፡ ባለ ማክበራችን ደግሞ ቅጣት ጉዳት አለና ነው፡፡ ሰንበትን በሚገባ ለማክበር ቸሩ አምላክ ይርዳን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#የወልወል_ጦርነት (ኅዳር 26/1927ዓ.ም.)
#ከአድዋ (1888ዓ.ም.) #በኋላ_የጣሊያን_ሁለተኛው_ወረራና_ጦርነት
/ከባለፈው ከየካቲት 12 የቀጠለ……/ #ክፍል_፭
#ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥
#ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥
#ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_
#ሁለተኛው_ወረራና_ጦርነት #የወልወል_ጦርነት
#ፋታውራሪ_ዓለማየሁና_107 #ኢትዮጵያውያን የጀግንነት ጀብድ የፈጸሙበት
#ኑር_ሑሴንና_ደጃዝማች_ዑመር_ሰመትር
#ደጃዝማች_ታደሰ_ይማም_ወንድይራድ (በባንዳነተ ተሰልፈው የነበሩትን 3ት ደጃዝማቾች ድባቅ የመቱ)
#ከራስ_ሙሉጌታ_
#በተንቤን፣ #በእንደርታ፣ #በሽሬ፣ #በአሸንጌ፤ ብዙ ኢትዮጵያውያን በቦንብ የተሰዉበት
#በማይጨው_ጦርነት፤ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን እንደ መነኮራኩር እየተገለባበጡ ጣሊያንንና ባንዳን አፈር ከድሜ ያበሉበት፡፡
#በአምባ_አራዶም፣ #በሽሬና_በተንቤን፤ ብዙ ኢትዮጵያውያን በቦንብ የተሰዉበት
፠ #ሁለተኛው_ጦርነት ከ1929ዓ.ም. – 1933ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ (ለዚህ ጦርነት ደግሞ መሠረቱ ጣሊያን የቀድሞ ሽንፈቷ ቂም በመያዟ ነው)፡፡ የተጀመረውም በኅዳር 26/1927ዓ.ም. #በወልወል_ (የኢትዮጵያ ሶማሌ ክፍለ ሃገር በኦጋዴን ውስጥ በዋርዴር አውራጃ አካባቢ የምትገኝ ወረዳ ስትሆን ንጹሕ የከርሠ ምድር ውኃ የሚገኝባትም ነች፤ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ 350 ጥልቅ የውኃ ጕድጓድ አስቆፍረውላታል) ላይ ሲሆን ጣሊያን ባንዲራዋን በመትከሏና በወቅቱ የሰሜን ሱማሊያ ቅኝ ገዥ ከነበረችዉ ብሪታኒያ የድንበር ማካለል ለማድረግ ኢትዮጵያን አላሳልፍ በማለቷ ነው፡፡ በዚሁም ምክንያት የአውራጃው ገዢ #ፋታውራሪ_ዓለማየሁ ከጣሊያኑ ጦር አዛዥ ካፒቴን ችማሩታ ጋር ጦርነት ገጠመዋል፤ በጦርነቱም ጀግናው ፊታውራሪ ዓለማየሁ በፋሽስታዊ ታንክ ነጂ በገዛ ታንኩ ላይ ላይ ተወርውረው በመውጣት ሰይፈውታል፤ ብዙ የጀግንንት ሥራንም አከናውነዋል፤ ቆይቶ ግን ለሃገራቸው በጀግንነት እየተዋጉ ሣለ ከሌሎች 107 ኢትዮጵያውያን ጋር አርፈዋል፡፡ በዚህ ውጊያ ላይ አብዛኞቹ ሙስሊሞች ባንዳ በመሆን ለሃገራችን ጠላት (ለምሳሌ ሡልጣን ኢብራሂም አሰብን ለሮማ ልዑካን ሸጥኩላቸው የሚለውና፣ የአዳል ባላባት የራሄታ ሡልጣን ሐሰን ሙሐመድ ለሮማ ሚስዮናውያን የኢትዮጵያን ወደቦች እንሸጣለን ብሎ የመከረ) የነበሩ ቢሆኑም፤ ለሃገራቸው ሲሉ የተዋጉ የሙስሊም አርበኞችም ነበሩ፤ ዋነኞቹም #ኑር_ሑሴንና_ደጃዝማች(#ኋላ_ፊታውራሪ)# _ዑመር_ሰመትር ይጠቀሳሉ፡፡
፠ #ደጃዝማች(#ኋላ_ፊታውራሪ)# _ዑመር_ሰመትር፤ ‹‹ከአገሬ አፈር የሚደባልቅ ቤልጅግ እና ጎራዴ ይዤ እንጂ ጫት ተሸክሜ የምመጣ እንዳይመስልህ!›› በማለት #በኤልቡሬን ጦርነት 6ት ባታሊዮን የጣሊያንን ጦር ከጥቅም ዉጪ ያደረገው፤ #በሸላቦ ጦርነት አይቀጡ ቅጣት የቀጣው፤ በሌሎች ታላላቅ ጦርነቶች (#በቆራሄ፣#በሃነሌ) ላይ ጣልያንን ከአፈር የደባለቀ ፥ ባንዳዎችን አፈር ከድሜ ያበላ ጀግና፡፡ #በገርለጉቤ ጦርነት ላይ በጥይት ተመትቶ ቢቆስልም እስከ መጨረሻው ድረስ በጀግንነት ተዋግቶ ሕክምና ተደርጎለት 9 ዓመታት በሰላም ኖሮ የኢትዮጵያን ነፃነትን አይቶ በመጋቢት 10 ቀን 1936 ዓ.ም. ብክብር ያረፈ የጀግኖች ጀግና ነው፡፡ ይህ እንደ ወንጭፍ እየተወነጨፈ ጣሊያንን ዶግ አመድ ያደረገው፤ እንደ ንብ እየነደፋ ባንዳን ትቢያ ያደረገው ጀግና ስመ አጠራሩ እንዳይዘነጋ፤
በመዲናችን አዲስ አበባ ፥ በመሃል መርካቶ በስሙ ትምህርት ቤት ተሠይሞለታል፡፡
ባላምባራስ አብዶ ሀይድ የተባሉ የትግል አጋራቸው በቀብራቸው ላይም ይህንን ቅኔ ተቀኙላቸው፤
ተገዳይ እወልወል እጠረፉ ዳር፤
ተጋዳይ አፍዱግ ላይ እጠረፉ ዳር፤
ተጋዳይ ቆራሄ እጠረፉ ዳር፤
ተጋዳይ ሀነሌ እጠረፉ ላይ፤
የመትረየሱ ሼክ የለበን መምህር፤
ሞት ጠራህ አንተንም ዑመር ስመጥር!!!
፠ በዚሁም ጣሊያን ‹‹ጅራፍ ረሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል›› እንደሚሉት በደጃዝማች ዑመር ስመተር በተደጋጋሚ ድባቅ በመመታቷ፤ ኢትዮጵያ ዜጎቼን ገድላብኛለችና 200 ሺህ ሊሬ ካሳ ትክፈለን ፤ ደጃች ዑመር ሰመትርም ተላልፎ ይሰጠን ብለው ለመንግሥታቱ ማኅበር ከሰሱ፡፡ ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በድርድር ያልቃል ብላ ስትጠብቅ በጎን ግን ኢጣሊያ ለጦርነት ስትዘጋጅ ቆየች፤ በኅዳር 1927 ዓ.ም. የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስቴር ፒየር ላቫል ኢጣሊያ ከጀርመን ሂትለር ጎን እንዳትሰለፍ በማሰብ ኢትዮጵያን ብትወርር እንደማትቃወም አሳወወቀች፤ ጦርነቱን የተቃመወችው ሩሲያ ብቻ ነበረች፡፡ በመስከረም 22/1928 ዓ.ም. ኢጣሊያ የመረብን ወንዝ ተሻግራ ጦሯን በ3ት መስመር አሰልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ገባች፡፡
፠ ያገኘችውንም እያጠፋች እንትጮንና አዲግራትን በመያዝ ዓድዋ ደረሰች፤ ለዚሁም አስተዋጽዖ ያደረጉላት ለግል ጥቅማቸው ያደሩ የኢትዮጵያ ጠላት የሆኑ ባንዳዎች ነበሩ ለአብነትም ዋነኞቹ (ባንዳ ደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ፣ ባንዳ ደጃዝማች ሀብተ ማርያም፣ ባንዳ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው) ናቸው፡፡ ባንዳ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው የጎንደርን ሕዝብ አሳምኖ ለኢጣሊያ ተገዢ ለማድረግ መንቀሳቀሱን ጀግናው አርበኛ #ደጃዝማች_ታደሰ_ይማም_ወንድይራድ ሲሰማ ያለበት ድረስ ደርሶ ድባቅ መትቶታል፤ ባንዳው እጅጉ በጣና ሐይቅ በታንኳ ተሻግሮ አምልጦ ወሎ ተደበቀ፤ ይህንንም ታላቁ አርበኛ #ደጃዝማች_ታደሰ ወሎ ድረስ ዘምቶና ከበባ አድርጎ ሃገሩን ለሸጠ ምሕረት አይገባውምና እንደ በግ አርደውታል፡፡
፠ ጣሊያኖች በባንዳዎች በመታገዝ ጭምር በመርዝ ጋዝ ታግዘው በየካቲት 27 #ከራስ_ሙሉጌታ_ ጋር በተደረገው ውጊያ የራስ ሙሉጌታ ጦርን በመደምሰሳቸው በሐበሾች ዘንድ የሞራል ውደቀት አስከትሏል፡፡ ነገር ግን ጀግኖች አርበኞች እምቢ ለሃገሬ በማለት #በተንቤን፣ #በእንደርታ፣ #በሽሬ፣ #በአሸንጌ ላይ ተዋጉ፡፡ በአሸንጌው ጦርነት ጠላት ጣሊያን ከላይ በአውሮፕላን ጠላት ባንዳ ደግሞ ከታች በመሆን 8ሺህ የሚጠጉ አርበኞቻችን ላይ ጉዳት አደረሱ፡፡ በመጋቢት 24 ለ13 ሰዐታት በተካሄደው #የማይጨው_ጦርነት ላይ ኢትዮጵያውያን ድል አድረገው ጦርነቱ ማብቂያ ላይ የመርዝ ጋዝና የቦንብ ውርጅብኝ ከአውሮፕላን ላይ በማዝነብ ጀግኖች አርበኞቻችን አብዛኞች አለቁ፤ ከማይጨው የተረፉና በአሸንጌ ላይ የነበሩትን ጀግኖች አርበኞችን 150 አውሮፕላን ደርሰው ደብደቡት በመትረየስም ፈጁት፡፡ (ጣሊያኖች በዚሁ ወረራቸው በሰሜን 300፣ በደቡብ 150 አውሮፕላን አዝምተዋል፡፡)
፠ #በአምባ_አራዶም 50 ሺህ፣ #በሽሬና_በተንቤን 15 ሺህ ሰው ሙቶ 200 ሺህ ሰው ቆስሏል፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_)፤ #ክፍል፪_
#ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ (ሳኦል የአማሌቃውያንን ምርኮ ባገኘበት ወቅት፣ ሐናንያ ገንዘብ በእጁ በገባበት ወቅት ሰይጣን እንደፈተናቸው ልብ ይሏል /ሐናንያ ሆይ መንፈስ ቅዱስን ታታልል ዘንድ ከመሬቱ ሽያጭ ታስቀር ዘንድ ሰይጣን በልብህ ስለምን ሞላ?፡፡›› ሐዋ. ፭፥፫/ እኛንም እንዲሁ እንደ ዘመናችን ሁኔታ መልኩን እየለዋወጠ ይፈትነናል፡፡ እርሱ የ7511 ዓመታት የመፈተን የሥራ ልምድ ያለው ነውና!!፡፡
##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣውና መጽሐፍ ቅዱስም የተጻፈበት ዐቢይ ጉዳይ ሰይጣን በሰው ልጆች ላይ እያደረሰ ካለው ጉዳትና ጥፋት ለመታደግና ችግሩንም በዝርዝር ለማሳወቅና ሰዎችም የሰይጣንን ክፉ ሥራ ዐውቀው እንዲርቁ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡›› ፩ዮሐ. ፫፥፰/ ‹‹በእኔም የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፡፡›› ዮሐ. ፲፪፥፵፮
***ነገር ግን ጌታችን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ፤ ሰው በመሆኑ ይህ የሕይወት ብርሃን ለዓለም ቢበራም፤ ሁሉም #ሰው ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከዲያብሎስ ሽንገላ ለመላቀቅ ፈቃደኛ አለመሆኑን ተመልክቶ /‹‹ወደ ሕይወት የሚወስደው በር የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚገቡትም ጥቂቶች ናቸው፡፡›› ብሏል ማቴ. ፯፥፲፬/ ጌታችን እንዲህ ያለው ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው የሰይጣንን ፈቃድ በመፈጸም በፈቃደ ሥጋቸው ስለሚመሩና የእርሱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ደስተኛና ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንጂ ወደ ሕይወት የሚወስደው መንገድ የሚጠብ ሁኖ አይደለም፡፡ ይህ የሕይወት መንገድ የሚሰፋው የራስ ፈቃደኝነት ሲታከልበት ነው፡፡
#ለሰው ልጅ ወደ ሕይወት ለመግባት ወሳኙ ነገር ፈቃደኝነት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ቢሆንም የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ነጻ ፈቃድ ያለው አድርጎ ስለፈጠረው መልካሙን ነገር ሊያደርግ በሚፈልግበት ጊዜ ፈቃደኝነታቸው ይጠይቃል፡፡ /ድውያንን ሲፈውስ ልትድን ትወዳለህን እያለ የሚጠይቃቸውን ልብ ይሏል፡፡ ዮሐ. ፭፥፮/
#የራስ ፈቃደኝነት ካለ ትእዛዛትን መጠበቅ ቀላል ይሆናል፡፡ /የዘለዓለምን ሕይወት እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ ብሎ ለጠየቀው ሀብታም ጎልማሳ ‹‹ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ትእዛዛትን ጠብቅ … ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂደህ ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፤ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፡፡›› ነገር ግን ሀብታሙ ጎልማሳ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ታላቅ ሐዘን ተሰምቶታል፡፡ ማቴ. ፲፱፥፳፩/
#ጽድቅ፣ ቅድስናና ሰይጣንን ማሸነፍ የሚመጣው በራስ ፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ #አንድ_ሰው_በፍጹም_ትሕትና_ትእዛዛትን_ለመጠበቅ_የራስ_ፈቃደኝነት_ካለውና_ንስሐ_ከገባ__በቀላሉ_ሰይጣንን_የሚያሸንፍበት_ኀይል_ከእግዚአብሔር_ያገኛል፡፡ ሰይጣንም የብዙ ዘመን ልምድ ስላለው ይህን ሁኔታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሰዎች፤
++ሰዎች ትእዛዛትን ለመጠበቅ የራስ ፈቃደኝነት እንዳይኖራቸው የተለያየ ምክንያት በመፍጠር አጥብቆ ይዋጋቸዋል፡፡
++ሰዎች ትእዛዛትን ሊጠብቁና ንስሐ ሊገቡ ሲያስቡ በታላቅ ፍርሃትና ስጋት እንዲያዙ ያደርጋቸዋል፡፡
++ሰዎችን ሕግና ትእዛዛትን መፈጸም ከባድና ጭንቅ፥ በሩም የጠበበ፥ ፈጽሞም የማያሳልፍ አድርጎ ያሳያቸዋል፡፡
++ሰዎች ትእዛዛትን የሚጠብቁና በቁርጠኝነት ንስሐ የሚገቡ ከሆነ በዚህ ምድር ላይ መኖር እንደማይችሉና ታላቅ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ደጋግሞ በማሳሰብና በማስፈራራት ያሳምናቸዋል፡፡
… ነገር ግን በፍጹም ትሕትናና በራስ ፈቃደኝነት ትእዛዙን በመጠበቅና ንስሐ በመግባት ከዚህ ሰይጣናዊ ውጊያ ነጻ ይወጣሉ፤ ነጻ ሲወጡም በሰይጣን አሳሳቢነትና ማስፈራርት ከባድ መስሎ ይታያቸው የነበረው ትእዛዛት ለእነርሱ የደስታና የሰላም ምንጭ ይሆንላቸዋል፡፡ /ይህንንም በሐዋርያትና በቅዱሳንና ቅዱሳት ሕይወት ታውቋል ማቴ. ፲፩፥፳፰/
ከእውነተኛ (መንፈሳዊ) ሕይወት ርቀው የሚኖሩ ሰዎች በጥቂት የፈተና ሰዐት ስንኳ መታገሥና መረጋጋትን፥ ሰላማዊነትንና አስተዋንትን አጥተውና ተስፋ ቆርጠው ለከፋ ችግር የሚጋለጡት አስቀድሞ የጠጠጋቸው ሰይጣናዊ መንፈስ ስለሚያስጨንቃቸውና ስለሚያስፈራራቸው ነው፡፡
#የሰው ልጅ በምድር ላይ እስካለ ድረስ በጥንተ ጠላቱ ሰይጣን በየጊዜው መፈተኑ አይቀሬ በመሆኑ /ዘፍ. ፫፥፲፭/ ውጊያውም ከደምና ከሥጋ ጋር ሳይሆን ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከአለቆችና ከሥልጣናት እንዲሁም ከረቂቃን ሰይጣናት ከዲያብሎስ ሠራዊት ጋር በመሆኑ፤ ፈተናውን ለማለፍ የሰይጣን መግቢያ የሆኑ ቀዳዳዎችን ለመድፈን እንዲያስችለው መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረግ አለበት፡፡ ከኃጢአት ንጹሕ ሁኖ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ ስለሰይጣን አስከፊነት በእጅጉ መማርና ማወቅ፥ መረዳትና ማስተዋል ይገባዋል፡፡
+‹‹ከሚመጣው ሁሉ መዳን ትችሉ ዘንድና በሰው ልጅ ፊትም ለመቆም እንድትችሉ ሁል ጊዜ በጸሎት ትጉ፡፡›› ሉቃ. ፳፩፥፮
+‹‹ለጸሎት ትተጉ ዘንድ … ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ፡፡›› ፩ቆሮ. ፯፥፭
+‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› ኤፌ. ፮፥፲፩
+‹‹በመጠን ኑሩ፥ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፡፡›› ፩ጴጥ. ፭፥፰
+‹‹በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፤ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት፡፡›› ኤፌ. ፬፥፳፯
#አንድ ሰው ካመነና ከተጠመቀ በኋላ ስለሰይጣን ክፋትና ተንኮል ጥልቅ እውቀት ከሌለውና በመንፈሳዊ ትሩፋት የማይተጋ ከሆነ በቀላሉ ተመልሶ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ይወድቃል፡፡ ከዚያ በኋላም ሕይወቱ በእጅጉ የከፋ ይሆንበታል፡፡ /‹‹ርኩስ መንፈስ ከሰው ከወጣ በኋላ ዕረፍት ለማድረግ ፈልጎ ውኃ ወደሌለበት ምድረ በዳ ይዞራል፤ አያገኝም፡፡ ከዚህም በኋላ እንግዲህስ ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፡፡ በመጣም ጊዜ ባዶ ሁኖ ተጠርጎና ተጊጦ ያገኘዋል፤ ከዚህም በኋላ ይሄዳል፤ ከእርሱም የሚከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትን ያመጣል፤ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው የኋላ ኑሮው ከፊተኛው የከፋ ይሆናል፡፡›› ማቴ. ፲፪፥፵፫ ‹‹በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርሷ ተጠልፈው ከተሸነፉ ከፊተኛው ኑሯቸው ይልቅ የኋለኛው ኑሯቸው የባሰና የከፋ ይሆንባዋቸዋል፡፡›› ፪ጴጥ. ፪፥፳/፡፡ ሰዎች ዳግመኛ በሰይጣን ሽንገላ ተታለው በዓለም ርኵሰት እንዳይወድቁ የሚረዳ እውቀት ማግኛ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብና ማወቅ እንዲረዳ መምህረ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ፲፭፥፬ ላይ .. መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፏልና ብሎ እንደተናገረው::
#ቀሲስ_ጳውሊ_ወደ_ጭፈራ_ቤት_የሚሄዱትን_ሰዎች_የሚያስተውን_ሰይጣን_በዙ_ጥያቄዎችን_ሊጠይቀው_እንደገዘተው፤ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_፤ #ክፍል_፫ _.… #ይቀጥላል_ይጠብቁን_/
#በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡
#በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
