Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 389 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 582,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 199 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 389 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 23,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.38%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.20% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 290 次浏览,首日通常累积 1 569 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 389
订阅者
-324 小时
+207 天
+2330 天
帖子存档
#ዕርገተ_እግዚእነ
እንኳን ለጌታችን በዓለ ዕርገት፤ ኀሙስ ሰኔ 4/2013 ዓ.ም. አደረሳችሁ፥ አደረሰን፤
‹‹አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው፤ ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡›› እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ዮሐ.3፥13
ꔰ የሰውን ልጅ በመውደዱ ልዑል ባሕርዩን ዝቅ አድርጎ ከሰማይ ወረደ፥ ሥጋ ለበሰ፥ በምድር ላይ ተመላለሰ፥ ምድርን በኪደተ እግሩ ቀደሰ፥ ድውያንን ፈወሰ፡፡
ꔰ ፍጹም ሰው እንደ መሆኑ ተራበ፥ ተጠማ፤ ፍጹም አምላክ መሆኑንም ያስረዳ ዘንድ አምስት ገበያ ሕዝብ በአምስት እንጀራ በሁለት ዓሣ አጠገበ .ማቴ.14፥19፡፡
ꔰ መምህረ ትሕትና ነውና ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በዚህ ዓለም ኖረ ለሐዋርያት ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን አስተማረ፤ ትምህርት በሚገባ ከተረዳለት በኋላ ለድኅነተ ዓለም በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ተሰቀለ፡፡#ወገብረ_መድኀኒተ_በማዕከለ_ምድር_በምድር_መካከል_መድኀኒትን_አደረገ_እንዲል _መዝ.73፥12
ꔰነቢያት እንደተናገሩ በሞቱ ዓለምን አድኖ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሮ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ብርሃነ መለኮቱን ገልጾ ተነሣ፡፡ የተተነበየውን ትንቢት ፈጽሞ ተነሣ፡፡
ꔰ በሞቱ ሞታችንን ሻረልን፤ ‹‹በሞቱ ሞትን አጠፋው›› እንዲል መጽሐፈ ኪዳን፡፡ ሕንፃ መነኰሳት ‹እርሱ በሁሉ ምሉዕ ሲሆን በመቃብር ለመቀበር ዮሴፍ ኒቆዲሞስ ገንዘውት ታየ፡፡ ከመሬት ውስጥ በመቀበሩም ሙስና መቃብርን አጠፋ፤ ከሥሩም ነቀለው ከተነሣ በኋላ ትንሣኤውን መጀመሪያ ለማርያም መግደላዊት ገለጸ ማር.16፥9፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ትንሣኤው ሲመሰክር ‹‹ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረም፤ መጽሐፍ እንደሚል፤ በሦስተኛው ቀን ተነሣ፡፡ ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፡፡ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ›› 1ቆሮ.15፥3-8 ብሎ ክርስቶስ ትንሣኤውን ለተከታዮቹ በሙሉ የገለጠ መሆኑን መስክሯል፡፡
ꔰ የሚያምኑ ፈሪሳውያንም ‹‹ትንሣኤው ምትሐት ነው›› እንዳይሉ እየታየ እያስተማረ እስከ 40 ቀን ድረስ መቆየቱን ይገልጽልና፡፡ በዚህም ከትንሣኤ በኋላ የአርባ ቀን ቆይታው ሦስት ቀን ጉባኤ አድርጎ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ ቅዱስ ወንጌል ይነግረናል፡፡ ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛ ጊዜ ነበረ እንዲል ዮሐ.21፥14 ይህንም ሊቃውንት አባቶቻችን፡-
1ኛ) *የትንሣኤ
2ኛ) *የአግብኦተ ግብር /ዳግም ትንሣኤ/
3ኛ) *የጥብርያዶስ፡፡
#በዚህ_40_ቀን_ቆይታ_መጽሐፈ_ኪዳንን_ለደቀ_መዛሙርቱ_አስተምሯል፡፡
ꔰ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም ዕርገቱን ለመናገር ከሰማየ ሰማያት መውረዱን አስቀድሞ ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ማንም ወደ ሰማይ የወጣ የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው ብሎ ከዕርገቱ በኋላ በየማነ አብ፥ በዘባነ ኪሩብ ፥ ወደ ሰማይ የወጣ ከእርሱ በቀር ሌላ እንደሌለ አስረግጦ ነገረን፡፡ ሲጀምር ከሰማይ መውረዱን ማስቀደሙ ወረደ ብሎ ዐረገ ለማለት ይመቻል፡፡ ተጸነሰ ተወለደ ለማለት ጥንቱ ከሰማያት ወረደ ማለት እንደሆነ ሁሉ፤ ‹‹ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ ተነሣ›› ለማለት ‹‹ጥንቱ፤ ተጸነሰ፥ ተወለደ፥ አደገ፥ ተመላለሰ፥ ሠላሳ ዓመት ኖረ›› የሚለው ነው፡፡ ስለሆነም ቅዱስ ዮሐንስ ጠርዝና ጠርዙን ይዞ ተናገረ፡፡
ꔰ ‹‹ወረደ ዐረገ›› የሚሉት ሁለት ቃላት የዓለም ድኅነት መነሻና መድረሻ ናቸው፤ እነዚህን ሁለት ቃላት ስናይ በሁለቱ መካከል የተፈጸሙትን የአምላክ ሥራዎች ልብ ማለት ይገባል፡፡ ቤት በመሠረት ይጀመራል በጣሪያ ይፈጸማል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ይህን የቤዛነት ሥራ ሲያስረዳ በዮሐ.1፥14 ‹‹ቃል ሥጋ ኮነ፤�ቃል ሥጋ ሆነ›› ብሎ ጀምሯል፤ ይህንንም ቃል ‹‹ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም›› በማለት ሰው መሆኑን ብቻ ሳይሆን በአርያም የሚኖር መሆኑን አስተማረን፡፡ እንግዲህ ጌታችን ዕርገት እንዲሁ እንደ እንግዳ ደራሽ ፥ እንደ ውኃ ፈሳሽ አለመሆኑን ቀድሞ በነቢያት የተነገረ፤ ኋላም በሐዋርያት የተመሰከረ መሆኑን ማወቅ ያስፈለጋል፡፡
#የክርስቶስ_ዕርገት_በትንቢተ_ነቢያት
፠ ‹‹ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አደረገ ወረደም ጨለማ /ዲያብሎስ/ ከእግሩ በታች ነበር በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ በነፍሳትም ክንፍ በረረ፡፡›› መዝ.17፥9
፠ ‹‹አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ መዝ.46፥5
ወደላይ ዐረግህ፥ ምርኮን ማረክህ ፥ ስጦታንም ለሰዎች ሰጠህ›› መዝ.67፥18፡፡
፠ ‹‹ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ፤ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ›› መዝ.67፥33፡፡
#የክርስቶስ_ዕርገት_በትምህርተ_ሐዋርያት
፠ ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ማር.16፥19
፠ ‹‹እስከ ቢታንያ አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ፡፡››�ሉቃ.24፥50
፠ ‹‹ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ ደመናም ከዐይናቸው ሰውራ ተቀበለችው፤ እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ ለብሰው ሁለት ሰዎች /መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ ደግሞም ‹‹የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት ዳግመኛ ይመጣል፡፡›› አሏቸው››� ሐዋ.1፥9-12
በማለት ሐዋርያት የክርስቶስን ዕርገት ከመላእክት ጋር ሆነው እንደተመለከቱ ደስታውን እንደተካፈሉ ቅዱስ ሉቃስ ጽፎልናል፡፡ በትንሣኤው ነጭ ልብስ ለብሰው የታዩ መላእክት የደስታ ዘመን ነው ሲሉ በዕርገቱም ነጭ ልብስ ለብሰው የዕርገቱን የምሥራች ለሐዋርያት አብስረዋል፡፡
ተዛጋጅቶ የነበርው የእንኳን አደረሳቹህ ፓስት ካርድ
መድኀኔዓለም አምላክነ ባርክ ለቤተ ትምሕርትነ ፍኖተ ሕይወት ወዕቀባ ለደብርነ ደበረሰላም ወደብረ ትጉሃን::
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ.
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
ꔰየ55ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል መክፈቻ መርኀ ግብር ሚያዝያ 16 ማስታወሻዎች
ꔰቀጣይ መርኀ ግብራችንን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል ፡፡
ꔰꔰꔰየፍቶ ስብስብ 1
ꔰየሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ
ꔰየሰንበት ት/ቤቶች ማደረጃ ተጋባ እናግዶች አና ሌሎችም ተጋባ እንግዶች
ꔰ55ኛ ዓመት ኮሚቴዎች
ꔰ1962 የተነሣን ፎቶ ለመድገም የተደረገ ሙከራ
እና የመሳሰሉት …….
#የአቡነ ሀብተማርያም ወረብ በደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ሊቃውንት ፤ ከሠተ አፉሁ፡፡
#ግንቦት 26 ፤ 2013 ዓ.ም ገዳም
#ከሠተ አፉሁ ወልሳኑ ነበበለ አእቶ ወባረኮ ለእግዚአብሔር
መልዐ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሀብተማርያም
#ይህንን ሊንክ በመጫን ይመልከቱ
https://youtu.be/GIzYreXgSOY
#ተቋርጦ_የነበረው_የሰበካ_ጉባኤ_መምረጫ_ካርድ
#ሰበካ_ጉባኤ_ምንድን_ነው?
#ተቋርጦ_የነበረው የሰበካ ጉባኤ መምረጫ ካርድ ለምእመናን መስጠት ተጀምሯል
ከግንቦት 9/2013 ዓ.ም - ግንቦት 25 ድረስ ሳይሰጥ የቆየው ካርድ በዛሬው እለት መስጠት ተጀምሯል ሁላችንም ምእመናን ግንቦት 29/2013 ዓ.ም ለሚደረገው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ባሉት 3 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የምርጫ ካርድ መውሰድ ይኖርብናል::
ውድ የገፃችን ተከታታዮች “ሰበካ ጉባኤ”፣ “የሰበካ ጉባኤ ምርጫ” ወይም “የሰበካ ጉባኤ ውሳኔ” ወዘተረፈ ሲባል ሰምታችሁ ታውቃላችሁ ብለን እንገምታለን፡፡ በእኛም አጥቢያ ነባሩ ሰበካ ጉባኤ ከፈረሰ በኋላ አዲስ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አባላት ለመምረጥ እሑድ ግንቦት 29/2013 ዓ.ም ቀን ተቆርጦ ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ #ሰበካ_ጉባኤ_ምንድን_ነው? ከእኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡
በ2009 ዓ.ም ለአራተኛ ጊዜ ተሻሽሎ የወጣው ቃለ ዐዋዲ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤን “በአጥቢያ ለሚቋቋመውና ለተቋቋመው የቤ/ክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ (የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ) የሚያስፈልጉትን አባላት ለመምረጥ እና በአባልነትም ለመመረጥ የሚችሉ ቤ/ክርስቲያንን በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸው፣ በሀብታቸውና በአገልግሎታቸው የሚረዱ ካህናት፣ ምዕመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የሚገኙበት የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ፣ ስብስብ ነው፡፡” በማለት በአንቀጽ 2/1/ሀ ትርጉም ይሰጠዋል፡፡
በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኝ የሆነ ሁሉ የአጥቢያው ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አባል ሲሆን በቃለ ዐዋዲው የሚዘረዘሩ ቅድመ ሁኔታዎች እንዳሉ ሆነው የመምረጥም ሆነ የመመረጥ መብት አለው ማለት ነው፡፡
#ለመሆኑ_የአጥቢያ_ሰበካ_መንፈሳዊ_ጉባኤ_ዐላማ_ምንድን_ነው?
ቅድስት ቤ/ክርስቲያንን መጠበቅና አገልግሎቷም የተሟላ እንዲሆን ማድረግ
የቤ/ክርስቲያንን አገልጋዮች በሐዋርያዊ ተግባር ማደራጀት፣ችሎታቸውን እና ኑሮአቸውን ማሻሻል፣
ምዕመናን በመንፈሳዊ ዕውቀት ጎልምሰው በምግባርና በሃይማኖት ጸንተው በክርስቲያናዊ ሕይወት እንዲኖሩ ማድረግ
የቤ/ክርስቲያንን አስተዳደር ማጠናከር እና በገቢ ራሷን ማስቻል /ቃለ ዐዋዲ አንቀጽ 5/1-4/
የአጥቢያው ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከላይ የተዘረዘሩትን ዓላማዎች መሠረት አድርጎ የሚቋቋም ከሆነ የሚያከናውናቸው ተግባራት ምንድን ናቸው የሚል ጠያቂ ቢኖር ቃለ ዐዋዲው በዝርዝር ገልጦታል፡፡ የቃለ ዐዋዲውን የአጥቢያ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዝርዝር ተግባራት ከማየታችን በፊት እስኪ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራሳችንን እንጠይቅ፡፡
በአጥቢያችሁ የእግዚአብሔር ወንጌለ መንግሥት እንደሚገባው ይሰበካል? የሠርክ ጉባኤው እንዴት ነው? በአጥቢያችሁ ቋሚ ሣምንታዊ፣ ወርሃዊና ዓመታዊ ልዩ ጉባኤያት ይደረጋሉ? በጉባኤያቱ የሚሰጡት ትምህርቶች ምን ያህል ዘመኑን የዋጁና ምዕመናንን መሠረታዊ የሆነውን የቤ/ክርስቲያኒቱን ትምሀርት በማስጨበጥ ከመናፍቃን ንጥቂያ ይጠብቃል? ምን ያህልስ ምዕመናንን ወደ ንስሐ እና ወደ ቅዱስ ቁርባን በአጠቃላይ የምስጢራት ተካፋይ እንዲሆኑ ያደርጋል?
#በአጥቢያችሁ_ያለው_ሰንበት_ት/ቤትስ_ጠንካራ ነው?
የአጥቢያ ቤ/ክርስቲያናችሁ ሀብት #በአግባቡ_ይመዘገባል፣ ይጠበቃል፣ በአግባቡስ ይለማል? ወይስ የአለቃ፣ የጸሐፊ፣ የሒሳብ ሹም እና የቁጥጥር እንዲሁም የመሳሰሉት እንደፈለጉ ይጫወቱበታል?
ከላይ ለተዘረዘሩት ጥያቄዎች መልስዎ አዎንታዊ ከሆነ እርሶ ዕድለኛ ኖት አጥቢያዎ ላይ ጠንካራ ሰበካ ጉባኤ አለ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በሚችሉት ሁሉ ይህን ሰበካ ጉባኤ ይደግፉ፡፡
ለጥያቄዎቹ መልስዎ አሉታዊ ከሆነ ግን አጥቢያዎት በእርሶ ግዴለሽነት የግለሰቦች መጫወቻ ሆኗል ማለት፡፡ የቤ/ክርስቲያን #ቁስል ከተሰማዎ ቀረብ ብለው ሰበካ ጉባኤ ሥራውን በአግባቡ እንዲሠራ ይጠይቁ አቅም ከሌለው በሌላ እንዲተካ ያድርጉ፡፡ ሰበካ ጉባኤው በተለያዩ ማነቆዎች ተተብትቦ ከሆነ ማነቆዎቹን በማስወገድ ለሰበካ ጉባኤ አባላት ደጀን መሆኖትን ያሳዩ፡፡ በቤ/ክርስቲያን የሚፈጸሙ አግባብነት የሌላቸው ድርጊቶችን አይቶ እንዳላየ ማለፍ ቤ/ክርስቲያንን እያደማት ነውና ለቤ/ክርስቲያን ከለላ ይሁኗት፡፡
ቤተ ክርስቲያንን መጠበቅ የርሶም ድርሻ ነውና ነቃ ይበሉ ከዛሬ ጀምሮ ባሉት #3 ተከታታይ ቀናት የሰበካ ጉባኤ ካርዶን ይዘው ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ የምርጫ ካርድ ይውሰዱ::
ꔰ ተከታታይ መንፈሣዊ የክርምት ኮርስ በተጠቀሱት አማራጮች ይመዝገቡ
ꔰ በድረ ገጻችን ለመመዝገብ ይህን መጠቆሚያ ይጫኑ https://finotehiwotsundayschool.com/#Register/
ꔰ ሰኔ 14 በልዩ መክፈቻ መርኀ ግብር ይጀምራል!
#በስም_መመሳሰል_ለተወዛገቡ_የተሰጠ_መልስ
መምህራችን መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ካወገዛቸው ሶስቱ የሀሰት ጳጳሳት መካከል ከአንዳቸው ጋር ስማቸው ተመሳስሎ ብዙኃን ላይ ጥያቄ እያስነሳ ነው፡፡ ስለሆም የመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ የአባት ስም ፈንቴ ሲሆን የተወጉዙት ጳጳስ ስም ደግም ፈንታ መሆኑንና የተወገዙትም ሰመ ጳጳስ መምህራችን ደግሞ የልጆች አባት መሆቸውን እንድናስተውል እና አገልግሎታቸው ላይ አለመግባባት እንዳይፈጠር በፈጣሪ ስም እንጠይቃልን፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
