ch
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

前往频道在 Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

显示更多
2 639
订阅者
-224 小时
+87
+5630
帖子存档
ከሲውም እንዲህ አለ በዚህ ቦታ አንጻር መልከ መልካም ሴት ነበረች እኔ የምወዳት ናት ይህም ጐልማሳ ሲስማት አየሁት በሰንበት ቀንም ከርሷ ጋር አደረ ስለዚህም ነክሼ በመርዝ ገደልኩት ሐዋርያውም መርዝህን ከሱ ትወስድ ዘንድ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝዤሃለሁ አለው። ሔዶም ከዚያ ከሞተው መርዙን መጠጠና ወሰደ ወዲያውኑ ተነፍቶ አበጠ ተሠንጥቆም ሞተ የሞተውም ሰው ድኖ ተነሣ። ስለዚች ምልክትም ብዙዎች በክብር ባለቤት ጌታችን አመኑ እርሱም ሃይማኖትን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

ያን ጊዜ እግዚአብሔር ተቆጥቶ ይፈርዳል የማያስተውሉ ሕግ የሌላቸው አረማውያንም ተነሥተው ገዳማቱንና አድባራቱን ያጠፋሉ ብዙ ዘመናትም ምድረ በዳ ይሆናሉ የቅዱሳን መታሰቢያቸው አይጠፋም እግዚአብሔርም በሌሎች ሰዎች ልቡና ይቅርታውን ያሳድርባቸዋል እነርሱም ወደ ገዳማቱና ወደ አድባራቱ በመሔድ በውስጣቸው ዳግመኛ ይኖራሉ ሰይጣንም ወደ ገዳማት ሔዶ በመካከላቸው ጸብን ይዘራል እነርሱም የእግዚአብሔርን ፍቅር ገንዘብ በማድረግ ጨክነው አልታገሡባትምና ምንኵስናቸውን አስኬማቸውን ትተው ወደ ዓለም ይወርዳሉ በትዕግሥታችሁ ነፍሳችሁን ገንዘብ ታደርጓታላችሁ የሚለውን ጽሑፍ አላስተዋሉምና። እንጦንዮስም የከበርክ አባቴ ጳውሊ ሆይ ፊትህን አይ ዘንድ የታደልኩባት ሰዓት የተባረከች ናት አለ። የከበረ አባ ጳውሊም አሁን ወደ ማደሪያህ ሒድ ቈስጠንጢኖስ ለሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስ የሰጠውን ልብስ እርሱም አንተን ያለበሳትን ያቺን ከአንተ ጋር ይዘሃት ና ሥጋዬን በርሷ ትገንዝ ዘንድ ብሎ ተናገረው የተሠወረውን በማወቁ እጅግ አደነቀ የተነበየለትንም ትንቢት ሁሉ አመነ። ዳግመኛም እንዲህ አለው በሰው ሁሉ ላይ እንደተሠራ ከዓለም የምወጣበት ጊዜዬ ቀርቧልና ፈጥነህ ሒድና ተመለስ እርሱም ከአባ ጳውሊ ዘንድ ወጥቶ ወደ በዓቱ እስኪደርስ የሁለት ቀን ጎዳና ተጓዘ ያቺንም ልብስ ይዞ ተመለሰ በመንገድም እየተጓዘ ሳለ በአየር ውስጥ አባ ቡላን የመላእክትንም ማኅበር አየ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ይሉ ነበር። ሁለተኛም እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የመረጠህ ሰላምታ ፍቅር አንድነት ይገባሃል የእግዚአብሔር ሰው አንተ ጳውሊ የተመሰገንክ ነህ እንግዲህስ በሰማያዊ መንግሥት ከመላእክት ጋር ደስ ይበልህ የጨለማውን ዓለም ትተህ የብርሃን ሀገርን አግኝተሃልና ወደ ዘላለማዊ ተድላ ደስታ ይወስዱሃልና የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆንክ አንተ ገዳማዊ ጳውሎስ በትውልድህ የከበርክና የተመሰገንክ ነህ እንዲህ እያሉ ተሠወሩ። የከበረ እንጦኒም ይህች ወደ ሰማይ የሚያሳርጓት የአባቴ የጳውሊ ነፍስ ናት አለ ወደ በዓቱም በገባ ጊዜ እንደ ሰገደ ሁኖ እጆቹም በመስቀል ምልክት ተዘርግተው አገኘው አንሥቶም ሸፈነው አባቴ ሆይ በሰማያዊ ማደሪያህ ሁነህ አስበኝ ብሎ በላዩ አለቀሰ። ከዚህም በኋላ ተነሥቶ በዚያች ልብስ ሥጋውን ገነዘና በላዩ የቤተ ክርስቲያንን የጸሎት ሥርዓት ፈጸመ አደረሰም ከዚህም ቀጥሎ ከእርሱ ጋር የተማከርኩት ነገር የለም ምን ላድርግ ብሎ አሰበ በዚያንም ጊዜ አንበሶች መጡ እጅ ነሡትም ቀድሞ እንደሚያውቁትም ዘንበል ብለው የእግሩን ትቢያ ላሱ መቃብሩን በየት ቦታ እንቆፍርለት እንደሚሉ አመለከቱት እርሱም ምልክታቸውን አውቆ በቁመቱ ልክ ለክቶ ሰጣቸው አንዱ በራስጌ አንዱ በግርጌ ሁነው ቆፈሩ በአደረሱም ጊዜ በቃችሁ ብሎ አመለከታቸው እሊህ አንበሶችም ወጥተው ሰገዱለት። እርሱም ባረካቸውና ወደ ቦታቸው ሔዱ የከበረ እንጦኒ ወደ መቃብር አስገብቶ ዘጋው። ከሰኔል ቅጠልም የተሠራች ዐጽፉን ወሰደ የአባቱን ገንዘብ እንደሚወርስ ልጅ ነውና ወደ እስክንድርያም ሔደ፡፡ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም ገብቶ ከከበረ አባ ጳውሊ የሆነውን ሁሉ ነገረውና ያቺን ከሰኔል የተሠራች ዐጽፍ ሰጠው። ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም የከበረ ጳውሊን ዜና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ያቺንም ዐጽፍ ተቀብሎ በእርሱ ዘንድ አኖራት በየዓመቱም በከበረ በልደት በዓል በጥምቀትም በዓል በመድኃኒታችን ክርስቶስ ትንሣኤ በዓልም ሦስት ጊዜ ይለብሳት ነበር። ጌታችንም የቅዱስ ጳውሊን የልብሱን ክብር ሊገልጥ ወደደ በዚያችም ወቅት አንድ ወጣት ልጅ ሞተ አባ አትናቴዎስም ያቺን ልብስ በሞተው ላይ አኖራት ወዲያውኑ ተነሣ ይህንንም ያየ ኤጲስቆጶስ አባ ኤስድሮስ ምስክር ሆነ ይችም ተአምር በአገሮች ሁሉ ተሰማች። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አባ_ለንጊኖስ_ደብረ_ዝጋግ በዚህች ቀን ከእስክንድርያ ውጭ የደብረ ዝጋግ ገዳም አበ ምኔት የከበረ አባት ለንጊኖስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከኪልቅያ አገር ነው በዚያም መነኰሰ መምህሩም ክርስቶስን የሚወድ ሰው ከሚሰጠውም ክብር የሚሸሽ ነበር። በዚያንም ጊዜ የገዳማቸው አበ ምኔት አረፈ ይህንንም ስሙ ሉክያኖስ የተባለ አረጋዊ መምህሩን አበ ምኔትነት ሊሾሙት መነኰሳቱ ወደዱ እርሱም ደቀ መዝሙሩን ለንጊኖስን ይዞ በጭልታ ከኪልቅያ ወጥቶ ወደ ሶርያ አገር ሔደ በአንዲት ቤተ ክርስቲያንም ግቢ በአንድነት ተቀመጡ በእጆቻቸውም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር ወደደ ከሰዎችም ዘንድ ከንቱ ውዳሴና ክብር ሆነባቸው። አባ ለንጊኖስም በመምህሩ ምክር ወጥቶ ወደ ግብጽ አገር ሔደ ወደ ደብረ ዝጋግ ገዳምም በገባ ጊዜ በደስታ ተቀበሉትና ከእሳቸው ጋራ ኖረ ከዚህም በኋላ አበ ምኔቱ አረፈ ተጋድሎውን ትሩፋቱንና ደግነቱን ስለ አወቁ በደብረ ዝጋግ ገዳም ላይ አባ ለንጊኖስን አበ ምኔት አድርገው ሾሙት። ከጥቂትም ወራት በኋላ መምህሩ አባ ሉክያኖስ መጣ የመርከቦችን ጣሪያዎች እየሠሩ በእጆቻቸውም ከሚሠሩት እየተመገቡ በአንድ ልብ በመሆንም በአንድነት ኖሩ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ከዚህም በኋላ አባ ሉክያኖስ አረፈ። የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ በከሀዲው መርቅያኖስም ዘመን ወደ ሀገሮችም ሁሉ መልእክተኞችን ላከ ከእርሳቸውም ጋር አንዱን ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የምትከፍል የረከሰች የሃይማኖቱ ደብዳቤ አለች። ከንጉሥ መልእክተኞች ሦስቱ ወደ ደብረ ዝጋግ በደረሱ ጊዜ ያንን ደብዳቤ ለአባ ለንጊኖስ ሰጡት በዚህ ጽሑፍ እንድታምኑ በውስጡም እንድትፈርሙ ንጉሥ መርቅያኖስ አዝዞአል አሉት። አባ ለንጊኖስም ከቅዱሳን አባቶቼ ጋር ሳልማከር እኔ ምንም ምን መሥራት አልችልም እንድንማከርም እናንተም ከእኔ ጋር ኑ አላቸውና የቅዱሳን በድኖች ወደ አሉበት ዋሻ ውስጥ አስገባቸውና የከበራችሁ አባቶቼ ሆይ እናንተ ዐርፈን ተኝተናል አትበሉ እነሆ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ የሚያደርግ በውስጡ የተጻፈበትን ይህን ደብዳቤ አምጥተዋልና በቃሉ አምን ዘንድ በውስጡም እፈርም ዘንድ ታዙኛላችሁን ወይም አታዙኝም የምሠራውንም ካልነገራችሁኝ ሕያው እግዚአብሔርን ዐፅሞቻችሁን ከዚህ ቦታ አወጣለሁ አላቸው። ያን ጊዜ ሰዎች ሁሉም እየሰሙ ከአሰከሬናቸው የአባቶቻችንን የሐዋርያትንና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የቀናች ሃይማኖትን አትተው ይህንንም የረከሰ ደብዳቤ አትከተል ከአስከሬናችን ቦታ አርቀው እንጂ የሚል ቃል ወጣ የንጉሥ መልእክተኞችም ይህን ነገር ሰምተው እጅግ አደነቁ በላያቸውም ታላቅ ፍርሀት አደረባቸው ወደ ንጉሥም አልተመለሱም ራሳቸውን ተላጭተው መነኰሱ እንጂ እስከ አረፉም ድረስ ብዙ ዘመን እየተጋደሉ ኖሩ። የከበረ አባ ለንጊኖስም ያማረ ተጋድሎውን ጨርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ የሕይወት አክሊልንም ተቀበለ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቶማስ_ሐዋርያ በዚህችም ዕለት የከበረ ሐዋርያ ቶማስ ተአምራትን አደረገ፡፡ ጌታችን ወደ አዘዘው ሊአስተምር በወጣ ጊዜ ከመንገድ ጥቂት ፈቀቅ አለ ድንገትም የሞተ ጐልማሳ አየ መልኩ እጅግ የሚያምር ነበር ሐዋርያውም አቤቱ ይህን ጥፋት አይ ዘንድ ወደዚህ አመጣህኝን ነገር ግን ፈቃድህ ይሁን አለ። ከዚህም በኋላ ስለሞተው ሰው ጸለየ ያን ጊዜ ታላቅ ከይሲ ከደንጊያዎች ውስጥ ወጥቶ በጅራቱ ምድሩን እየደበደበ መጣ የክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ እኔ ካንተ ጋር ምን አለኝ ሥራዬን ልትዘልፍ መጣህን ብሎ በታላቅ ድምጽ ጮኸ ሐዋርያውም አዎን ሥራህን ተናገር አለው።

🔴#ስንክሳር የካቲት_2 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሁለት በዚህች ዕለት የትጉሃን መላእክት ወገን የሆነ የገዳማውያን ሁሉ አለቃ የከበረ #ታላቁ_ቅዱስ_ጳውሊ አረፈ፣ የደብረ ዝጋግ ገዳም አበ ምኔት የከበረ አባት #ቅዱስ_ለንጊኖስ አረፈ፣ የከበረ #ሐዋርያ_ቅዱስ_ቶማስ ተአምራትን አደረገ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አባ_ዻውሊ_ገዳማዊ (የበረሃው ኮከብ) የካቲት ሁለት በዚህች ዕለት የትጉሃን መላእክት ወገን የሆነ የገዳማውያን ሁሉ አለቃ የከበረ ታላቁ ጳውሊ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከእስክንድርያ አገር ጴጥሮስ የሚባል ወንድም አለው አባታቸውም የገንዘቡ ብዛት ሊቈጠር የማይቻል እጅግ ባለጸጋ ነበር በአረፈም ጊዜ የኀዘናቸው ቀን ሲፈጸም ርስቱንና ገንዘቡን ሊካፈሉ ጀመሩ ጴጥሮስም ታላቁን ክፍል ወደራሱ በመውሰድ የሚያንሰውን ለጳውሊ የሚሰጠው ሆነ። ስለዚህም ጳውሊ አዘነና ከአባቴ ርስት በትክክል ለምን አትሰጠኝም አለው እርሱም አንተ ወጣት ስለሆንክ ታባክነዋለህ እስከ ምታድግ እኔ እጠብቅልሃለሁ ብሎ መለሰለት። ስለዚህም ጳውሊ ተቆጣና እርስ በርሳቸው ተጣሉ ይፈርድላቸውም ዘንድ ወደ ዳኛ ሔዱ እነርሱም ወደ ዳኛ ሲሔዱ ሰዎች ተሸክመውት ወደ ሚቀብሩበት ሲወስዱት ብዙዎችም የተከተሉትን የሞተ ሰውን አገኙ ጳውሊም ከተከተሉት አንዱን ሰው ዛሬ የሞተው ማን ነው ብሎ ጠየቀው። ያም ሰው እንዲህ ብሎ መለሰለት ልጄ ሆይ ዕወቅ አስተውል ይህ የሞተ ሰው በወርቅ በብር እጅግ ባለጸጋ የሆነ ሁል ጊዜ ደስ የሚለው ነበር አሁንም እነሆ ይህን ሁሉ ትቶ ራቁቱን ወደ መቃብር ወደማይመለስበት መንገድ ይሔዳል በኃጢአት ማዕበል ውስጥ እያለ ሙቷልና። አሁንም ልጄ ሆይ ስለ ነፍሳችን ድኅነት ልንታገል ይገባናል እኛ መቼ እንደምንሞት አናውቅምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ውስጥ ገንዘብ ኑሮት ሥልጣንም ኑሮት ሳለ ይህን ሁሉ የተወ የተመሰገነ ነው እርሱ የቅዱሳን ሀገር በሆነች በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ታላቅ ክብርን ይቀበላልና። የከበረ ጳውሊም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ከልቡ አዘነ እንዲህም አለ የዚህ የኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምኔ ነው ምን ይጠቅመኛል ከጥቂት ቀኖች በኋላ ትቼው ራቁቴን የምሔድ አይደለሁምን አለ። ከዚህም በኋላ ወደ ወንድሙ ተመልሶ ወንድሜ ሆይ ወደ ቤታችን እንመለስ ከእንግዲህ ስለ ገንዘብ ምንም ምን ከአንተ ጋር አልነጋገርም አለው። ከዚህም በኋላ ከወንድሙ ሸሽቶ ከሀገሩ ወጣ ከመቃብር ቤት ውስጥም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት መንገዱን ይመራው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እየጸለየና እየማለደ ኖረ። ወንድሙ ጴጥሮስም በሀገር ውስጥ እየዞረ ሲፈልገው ሰነበተ ግን አላገኘውም ታላቅ ኃዘንንም አዘነ። የተመሰገነ ጳውሊ ግን ሦስት ቀኖች ያህል በዚያች መቃብር ቤት ሲኖር መብልና መጠጥን አላሰበም ፍርሀትና ድንጋፄም አልደረሰበትም አምላካዊ ኃይል ትጠብቀው ነበርና። በአራተኛዪቱም ዕለት እግዚአብሔር ወደርሱ መልአኩን ላከ ከዚያም ነጥቆ ወሰደው በምሥራቅ በኵል በምትገኝ በረሀ ውስጥ አኖረው በዚያም የውኃ ምንጭ አለ መልአኩም ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ የከበረ ጳውሊም አራዊት የሚኖሩበትን ጒድጓዶች አግኝቶ ወደ አንዲቱ ፍርኩታ ገባ ልብሱንም ሰኔል ሠርቶ ለበሰ። እንዲህም ብሎ ጸለየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርኀራኄ ከሌለው ጠላት እጅ ጠብቀኝ አድነኝም ተጋድሎዬን እስከምፈጽም ተጸናኝ ዘንድ ቸርነትህ ወደእኔ ትምጣ የትውልድ ሁሉ ንጉሥ ሆይ ኃይል ጌትነት ክብር ገንዘብህ ነውና ለዘላለሙ። በዚያችም ዋሻ ውስጥ ሰማንያ ዓመት ኖረ ከሰውም ከቶ ማንንም አላየም ልብሱም ከሰኔል ቅጠል የተሠራ ነው እግዚአብሔር ወደ ማታ ሁል ጊዜ ወደርሱ ቁራን ይልክለታል ከርሱም ጋራ ግማሽ እንጀራ አለ ያንን ለከበረው ጳውሊ ይሰጠዋል። የክብር ባለቤት እግዚአብሔርም ቅድስናውንና ጽድቁን ይገልጥ ዘንድ በወደደ ጊዜ መልአኩን ወደ ታለቅ አባት ወደ እንጦንዮስ ላከ ይህም እንጦንዮስ በበረሀ ውስጥ መኖርን የጀመረ እርሱ እንደሆነ በልቡ ያስብ ነበር መልአኩም እንዲህ አለው እንጦንዮስ ሆይ ከአንተ የሁለት ቀን ጎዳና ርቆ በበረሀ ውስጥ ሰው አለ የዓለም ሰዎች ከሚረግጥባቸው የእግሩ ጫማዎች እንደ አንዲቱ ሊሆኑ የማይገባቸው ስለ ርሱም ጸሎት ዓለም ተጠብቆ የሚኖር ምድርም ፍሬዋን የምትሰጥ ጠል በምድር ላይ የሚወርድ በምድር በሚኖሩ ኃጢአተኞች ሁሉ ላይ ፀሐይ የሚወጣ የሰውም ፍጥረት በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ተጠብቆ የሚኖር። አባ እንጦንዮስም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ተነሥቶ ወደ በረሀው መካከል ተጓዘ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ሁኖ ጎዳናውንም እንደሚጠርግለት አምኖ ሲጓዝ የሰውና የአራዊትን ፍለጋ አገኘ ያንንም ፍለጋ ተከትሎ ከቅዱስ ጳውሊ በዓት ደረሰ በሩንም አንኳኳ የከበረ አባ ጳውሊ ግን ከሰይጣን ሥራ እንደሆነ አስቦ ታላቅ ደንጊያ ወስዶ ከመዝጊያው ጀርባ አኖረ አባ እንጦንዮስም ይሰጠኝ ዘንድ ፈለግሁ አገኝ ዘንድ ለመንኩ ይከፈትልኝም ዘንድ ቡሩን አንኳኳሁ ብሎ አሰምቶ ተናገረ። በዚያንም ጊዜ ከፈተለትና ገባ እርስ በርሳቸውም በመንፈሳዊ ሰላምታ አጅ ተነሣሥተው በአንድነትም ጸልየው ተቀመጡ። አባ እንጦንዮስም አባቴ ሆይ ስምህ ማነው አለው አባ ጳውሊም አንተ ስሜን ካላወቅህ እስከዚች ቦታ ለምን ተጓዝክ ብሎ መለሰለት በዚያችም ሰዓት እግዚአብሔር የእንጦንዮስን ልቡን ገለጠለትና ገዳማዊ ጳውሎስን አየው ዘንድ ስለተገባኝ እኔ ብፁዕ ነኝ አለ ከዚህም በኋላ እርስ በእርሳቸው የእግዚአብሔርን ልዕልናውን ቸርነቱን ይነጋገሩ ጀመር በመሸም ጊዜ ቍራ መጥቶ አንዲት ሙሉ እንጀራ ጣለለት አባ ጳውሊም አባ እንጦኒን አንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደሆንክ አሁን አወቅሁ እስከ ዛሬ ሰማንያ ዓመት በዚህ በረሀ ስኖር እግዚአብሔር ሁልጊዜ የሚልክልኝ ግማሽ እንጀራ ነበር እነሆ አሁን ምግብህን ላከልህ አለው። ከዚህም በኋላ ተነሥተው የማዕድ ጸሎት ጸለዩ በልተውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት መላ ሌሊቱንም ሲጸልዩ አደሩ። ነግቶ ፀሐይ በወጣ ጊዜም እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ እንጦኒም አባቴ ሆይ በዚህ ሁሉ ዘመን ሥጋውንና ደሙን ከወዴት ትቀበላለህ አለው የከበረ ጳውሊም እግዚአብሔር መልአኩን ይልክልኛል በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ሰንበት በየሳምንቱ ከሥጋውና ከደሙ ያቀብለኛል በዘመኑም ሁሉ እንዲህ ያደርግልኛል ብሎ መለሰለት። ከዚህም በኋላ አባ እንጦኒ አባ ጳውሊን አባቴ ሆይ ይህ አስኬማ በምድር ላይ ይበዛ እንደሆነ ወይም አለመብዛቱን ትነግረኝ ዘንድ እሻለሁ አለው። የከበረ ጳውሊም ወደ ሰማይ ተመለከተና ፈገግ አለ። ከዚህም በኋላ አዘነ ጩኾም አለቀሰ አባ እንጦንዮስም ፈገግ ስትል በአየውህ ጊዜ ደስ አለኝ በአዘንክም ጊዜ አዘንኩ አለው። የከበረ ጳውሊም እንዲህ ብሎ መለሰለት እሊህ ተራሮችና በረሐዎች እግዚአብሔር ከሁሉ አገሮች መርጦ ለሚሰበስባቸው ንጹሐን ርግቦች ማደሪያዎች ይሆናሉ። ዳግመኛም ይህ ስም ያልፋል ስማቸውም መነኰሳት ይባላሉ እነርሱም ብዙ ዘመናት ደስ ይላቸዋል እግዚአብሔርም ከቁጣው ቀን አስቀድሞ ከዚያ ያፈልሳቸዋል። ከእነርሱም በኋላ ሰምተው ለመምህሮቻቸው የማይታዘዙ ትውልድ ይነሣሉ ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት በቀንና በሌሊት የማይተጉና የማይጸልዩ ናቸው።

በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የነነዌ ጉባኤ 30/05/2015
+9
በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የነነዌ ጉባኤ 30/05/2015

ኤርትራ አዲ ሞገስ ወደሚባል አካባቢ ሲደርሱ አንድ ታምነ በእግዚእ የሚባል ገበሬ "አባቴ የንስሐ አባት ሁኑኝ" አላቸው። አባታችን "በአገራችሁ ካህን የለም እንዴ? አሉት እርሱም "አዋ የለም" አላቸው አባታችንም ሕዝቡ አስተምረው አጥምቀው ጉዞ ወደ ኢየሩሳሌም ጀመሩ። ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ሲደርሱ ጌታ ተገልጾ,"ይህን ቦታ ዳግማዊ፡ ኢየሩሳሌም አድርጌልሀለው ውሃውም የዮርዳኖስ ውሃ ይሆንልሃል እና ከዚህ አትህድ" አላቸው። አባታችንን አቡነ እንድርያስ ተከትለው ወደዚህ ገዳም ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ተማሪዎች ወደ እሳቸው መጡ፡እነዚህ ልጆቻቸውን አመነኰሷቸው። ለእነዚህ ልጆቻቸው፡ ቀድሞ በመንገድ ላይ አስተምረው ካጠመቁት ገበሬው ከታምነ በእግዚእ እንደ ሰው እየተላላከ እህል የሚጭልላቸው የሚያገለግላቸው ገብረኄር የሚባል አህያ ነበራቸው ሰይጣንም ቀንቶ ይህንን አህያ ብገለው ልጆቹ በርሃብ ምክንያት ይበተናሉ ብሎ አስቦ በአንበሳ አድሮ ገደለው። አንበሳው ደግሞ አቡነ እንድርያስ በአንድ መርገም ቃል ገደሉት። ልጆቻቸውም ምግብ ሲያጡ ጥለው ሊሆዱ ሲሉ አባታችን ትዕግስት ይኑራችሁ አላቸው። እነርሱም እንቢ፡ ብለው ወደ ታምነ በእግዚእ ሆዱ። ታምነ በእግዚእ ባለቤቱን "ምግብ አዘጋጅላቸው" አላት እሷም "አቡነ እንድርያስ ሳይመጦ አላዘጋጅ" አለችው እነርሱም እቢ ስላለቻቸው ልጆቹም "እኛ የአባታችን ምክር ስልሰማን ነው የከለከለችን" ብለው ወደ ገዳማቸው ተመለሱ። አቡነ እድርያስም ልጆቹ ከተመለሱ በኋላ ውሃ የሞሉ፡እንስራዎች ነበሩና ቢባርኩት የወይን ጠጅ ሆነ። እንደ ገናም እግዚአብሔር ዘላለም ብለው ሲጸልዩ ከሰማይ አርያም ስንዴ ዘነበላቸው ያንን ለ14ዓመታት ተመገብ ይህ ሲያልቅ ደግሞ ወርቅ አዘነቡላቸው ወርቁ በእህል እየለወጡ ተመገበሩ። አባታችን ልጆቻቸውን "እኔ ወደ እግዚአብሔር የምሄድበት ቀን ደርሷል" አሏቸው። ልጆቹም "አንተ ከሆድክ ማን ከሰማይ ስንዴና ወርቅ እያዘነበ ውሃው ወይን እያደረገ ይመግበናል" አሏቸው እሷቸው "እኔ ከሞትኩ በኋላ እናተም ከዐሥር ቀን፡ በኋላ ወደ ትመጣላች እኔ ቦታ ላዘጋጅላችሁ ነው የምሆደው" ብለዋቸው በ126 ዓመታቸው የካቲት1 ዐርፈዋል። ልጆቻቸውም እንዳሏቸው በአንድ፡ቀን በአረማውናን ሰማዕትነት በመቀበል የካቲት10፡ ቀን ዐርፈዋል። ከአባታች ከአቡነ እንድርያስ ረድኤትና በረከትን በጸሎታቸውም ይማረን!። (ምንጭ፦ ከደብረ ጽጌ ሰፍኣ ገዳም የተገኘ ማስታወሻ።) ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር የካቲት_1 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት አንድ በዚህችም እለት የከበሩ መቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ #በቍስጥንጥንያ_ጉባኤ አደረጉ፣ #አቡነ_እንድርያስ ዘደብረ ጽጌ ሰፍኣ አረፉ፣ የሰማዕታትም ፍጻሜ የሆነ የሊቀ ጳጳሳት #የቅዱስ_ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ነው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #የቍስጥንጥንያ_ጉባኤ የካቲት አንድ በዚህችም እለት የከበሩ የመቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ በቍስጥንጥንያ ከተማ በታላቁ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት ተደረገ። ስብሰባቸውም የሆነው በቍስጥንጥንያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት ስለ ሆነው የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን በከፋች ኀሳቡ ፍጡር ነው ብሎ ስለ ካደው ስለ መቅዶንዮስ ሁለተኛም አንድ ገጽ ስለሚሉ ስለ ሰባልዮሳውያን ሦስተኛ ወልድ ከብቻው ሥጋ በቀር ነባቢት ለባዊት ነፍስን አልነሣም መለኮቱ በነፍስና በልቡና ፈንታ ሆነው ስለሚሉ ስለ አቡሊናርዮሳውያን ነው። የእሊህ ከሀድያንም ስሕተት ግልጽ በሆነ ጊዜ አሰባስቦ የአንድነት ጉባኤ ያደርግላቸው ዘንድ ንጉሥ ቴዎዶስዮስን ለመኑት እርሱም ቃላቸውን ተቀብሎ ወደ ሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ኢየሩሳሌምም  ኤጲስቆጶስ ወደ እስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳትም  መልእክትን ላከ ምሁራን የሆኑ ኤጲስቆጶሶቻቸውንም ይዘው እንዲመጡ አዘዛቸው። እሊህም አባቶች በቍሰጥንጥንያ ከተማ ተሰበሰቡ የሮሜው ሊቀ ጳጳሳት ግን አልመጣም ምሁራን የሆኑ ሰዎችን ላከ እንጂ ከእሳቸውም ጋር በእጁ የጻፉትን ደብዳቤ ላከ። የጉባኤውም ሊቀ መንበር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ ነው መቅዶንዮስንም ጠርቶ የረከሰች ሃይማኖቱን ይናገር ዘንድ አዘዘው ያ ከሀዲም እንደ ፍጥረቶች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የተፈጠረ ነው አለ። ጢሞቴዎስም መልሶ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሕይወቱ እንደሆነ አታውቅምን የእግዚአብሔርን ሕይወት እንዴት ፍጡር ታደርገዋለህ አሁንም ከዚች ከረከሰች ሃይማኖትህ ተመለስ  ወደ ዘላለማዊ እሳተ ገሃነም ከመግባትህ በፊት ንስሓ ግባ አለው። እርሱ ግን ሰምቶ አልተመለሰም እነርሱም አወገዙት ከሹመቱም ሻሩት ከቤተ ክርስቲያንም አሳደዱት። ከዚህም በኋላ ሰባልዮሳውያንን ጠርቶ እናንተስ ስለ ሃይማኖታችሁ ምን ትላላችሁ ተናገሩ አላቸው እነርሱም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ አንድ ህላዌ ነው በምንም በምን ሦስት አይሆንም አሉ። አባት ጢሞቴዎስም መልሶ እንዲህ አላቸው በዮርዳኖስ ውስጥ ወልድ ቁሞ ሳለ በፀዓዳ ርግብ አምሳል መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በራሱ ላይ ተቀመጠ አብም ከደመና ውስጥ ሁኖ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ አሰምቶ ተናገረ ያለው የወንጌል ቃል ተሻረን። እናንተ እንደምትሉት ከሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቃችሁት የክርስትናችሁ ጥምቀት ተሽሮአል አሁንም ክህደታችሁን ተዉ ብትመለሱም ይሻላችኋል። አርዮስም አስቀድሞ ወልድን ካደው ይህ መቅዶንዮስም መንፈስ ቅዱስን ካደው እናንተም የእነርሱ ተሳታፊዎች ሆናችሁ። እነርሱም ሰምተው አልተመለሱም የአንድነት ጉባኤም አውግዞ ከምእመናን አንድነት ለያቸው። ከዚህም በኋላ ደግሞ ወልድ ነባቢት ለባዊት የሆነች ነፍስን አልነሣም ሥጋን ብቻ እንጂ የሚለውን የአቡሊናርዮስን ትምህርት አወገዙ። እሊህ መቶ ኃምሳ የሆኑ ኤጲስ ቆጶሳት አባቶቻችንም በጸሎተ ሃይማኖት ላይ ጌታ አዳኝ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት አድሮ የተናገረ የሚለውን ጨመሩ። ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተሰረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። የሙታንንም መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ ተስፋ እናደርጋለን። ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱ አባቶቻችን የተናገሩት ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እስከሚል ነው። እሊህ መቶ ኃምሳው አባቶች የተሰበሰቡት ስለ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ስለርሱ የእርሱን ነገር አብራሩ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ጴጥሮስ_ተፍጻሜተ_ሰማዕት በዚችም ዕለት በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ መንግሥት ፍጻሜ በሰማዕትነት የሞተ ከሀዲ አርዮስንም ያወገዘ የሰማዕታትም ፍጻሜ የሆነ የሊቀ ጳጳሳት የቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ነው። ጻድቁ ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ የጣዖታትን ቤቶች ሁሉ አፈረሰ ይችንም ቤተ ክርስቲያን ከእስክንድርያ ከተማ በምዕራብ በኩል በቅዱስ ጴጥሮስ ስም አነፃት በዛሬዋም ዕለት ከበረች በውስጧም ብዙ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ያቺም ቤተ ክርስቲያን እስላሞች በግብጽ እስከ ነገሡበት ዘመን ኖረች ከዚያም በኋላ ቢሆን የታወቀች ሁና ትኖር ነበር ከዚህም በኋላ ፈረሰችና ምድረ በዳ ሆነች። የቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን ግን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እጅ የተያዘችና የተጠበቀች ናት። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_እንድርያስ በዚህችም እለት አቡነ እንድርያስ ዘደብረ ጽጌ ሰፍኣ አረፉ፡፡ የእናታቸው ስም ቅድስት፡ዓመተ፡መንፈስ ቅዱስ የአባታቸው ስም ቅዱስ፡ ዘአማኑኤል ይባላል። የተወለዱትም ትግራ እንደርታ አካባቢ ነው። እናትና አባታቸው ልጅ ስሌላቸው ዘወትር ወደ እግዚአብሔር እየጸልዩ እናታቸውም "አንተ ደስ የሚያሰኝ ልጅ ካልሰጠኸኝ ማኅፀኔን ዝጋ" ይሉ ነበር። የእመቤታችንንም ዝክር በየወሩ ይዘክሩ፡ ነበር። እመቤታችንም አንድ ቀን ተገልጻ "ደስ የሚያሰኝ ልጅ ትወልዳላችሁ የሚወለደውም እኔ በተወለድኩበት ቀን ነው" አለቻቸው። አባታችን ልክ ግንቦት አንድ ቀን ሲወለዱ በእናት በአባታቸው ቤት ብርሃን ወረደ። አርባ ቀን ሲሞላቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ሊያስነሷቸው ወሰዷቸው ሲጠመቁም አባታችን "በአብ ስም አምናለሁ በወልድ ስም አምናለሁ በመንፈስ ቅዱስ አምናለሁ" አሉ። ስመ ክርስትናቸውም መሐረነ እግዚእ ተባሉ። አቡነ እንድርያስ የስለት ልጅ ስለ ነበሩ 3ዓመት ሲሆናቸው ወደ ቤተ ክርስቲያም አስገባቸው። እርሷቸው ቀን ቀን እያገለገሉ እየተማሩ ሌሊት ሌሊት እየጸለዩ ይሆሩ ነበር እመቤታች በሌሊት ሲጸልዩ ተገልጻ በክንፍ ጋረደቻቸው። ከዚያም እድምያቸው ለጋብቻ ሲደርስ እናትና አባታቸው "እናጋባህ" አላቸው እርሳቸው ግን "አልፈልግም" ብለው በሌሊት ተነስተው ወደ ደብረ ፀሎላ ገብተው በአባ ገብረ ክርስቶስ እጅ 12ዓመታቸው መነኰሱ። የምንኲስና ስማቸውም አባ እንድርያስ ተባሉ። በዚያ ጊዜ ዲቁንና ክህነት የሚሰጥ ጳስስ በኢትዮጵያ ስላልነበረ አበምኔቱሙ አባ ገብረ ክርስቶስ ዲቁንናንና ክህነት እንድትቀበል "ወደ ግብጽ እንሒድ" አሏቸው። አባታችን "አይሆኑም" ሲሉ፡ ጌታችን በሌሊት ተገልጾ "እንድርያስ ወዳጄ ለምን እቢ አልክ፡እኔ ምርጬሃለሁና" አላቸው አባታችን ጠዋት ተነስተው "ኑ እሒድ" አሏቸው። ከዚም ወደ ግብጽ ሒደው ዲቁንናንና ክህነት ተቀብለው ወደ ገዳማቸው፡ ተመለሱ። አንድ ቀን አባታችን ሲቀድሱ ከምድር አንድ ሜትር ከፍ ብለው እርሳቸው የቆሙበት ቦታ ውሃ አፈለቀ። ይህን ያዩ መነኰሳት ለአበምኔቱ ለአባ ገብረ ክርስቶስ ነገራቸው አበምኔቱ መጥተው የፈለቀው ውሃ አይተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ አቡነ እንድርያስ አስጠርተው "አንተ ከዛሬ ጀምሮ ከእኛ ጋር ለሥራ መውጣት የለብህ ስእኛ ጸልይን እንጂ" አሏቸው እርሳቸው አይሆኑም ብለው ከእዛ ገዳም ወጥው "ወደ ኢየሩሳሌም ሔጄ ጌታ የተጠመቀበትን ማየ ዮርዳኖስ አያለው" ብለው ከኢትዮጵያ ተነስተው ወደ

በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የነነዌ ጉባኤ 29/05/2015
+9
በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የነነዌ ጉባኤ 29/05/2015

የእግዚአብሄርም መልአክ መጥቶ በርቺ ኃይልንም ልበሺ ሀዋርያው ጢሞቴዎስም ወዳንቺ መጥቶ የወንጌልን ትእዛዝ ያሰተምርሻል አላት።ወዲያውኑ ጢሞቴዎስ መጥቶ የቤቷን ግድግዳ ሰንጥቆ ወደርሷ ገባ ሁሉንም አስተማራት ከበታቹም ውኃ ፈለቀ በውኃውም ላይ ፀለየና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃትና ከእርሷ ዘንድ ሄደ። በዚያንም ጊዜ ቅድስት ኦርኒ ተነስታ የአባቷን ጣዖቶች ሰበረች አባቷና እናቷም በመጡ ጊዜ እንደቀድሞው ስለ ጋብቻ ተናገርዋት እርሱም እኔስ ለሰማያዊ ሙሽራ ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠርቻለሁ በስሙም ተጠምቄአለሁ አለቻቸው። ንጉስ አባቷም የልጁን ነገር በሰማ ጊዜ ታላቅ ቁጣን ተመላ ከአዳራሽዋም እየጎተተ አወረዳት እናቷም እያለቀሰች በራስዋም ላይ አመድ እየነሰነሰች ትከተላት ነበር በሰንሰለት ታስረው የሚቀለቡ አራት ፈረሶችን አምጥተው ከጅራታቸው ላይ ቅድስት አርኒን በራስዋ ጠጉር አስረው እንዲአስጎትቷት ንጉስ አባቷ አዘዘ። አንዱ ፈረስም ስንሰለቱን በጥሶ ሲያመልጥ የንጉሱን ቀኝ እጅ ቆረጠውና ወዲያውኑ ወድቆ ሞተ የከበረች ኦርኒም ተነስታ ፀሎት አደረገችና ንጉስ አባቷን ከሞት አስነሳችው የተቆረጠ እጁንም እንደቀድሞው መለሰችው ህዝቡም ይህን ድንቅ ስራ አይተው ከንጉስ አባቷ ጋር በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ በእጆቿም ሰላሳ ሽህ ያህል ሰዎች ተጠመቁ። ንጉስ ዳኬዎስም ሰምቶ ወደዚያች አገር ገባ የከበረች ኦርኒንም ይዞ በራስዋ ጠጉር ይሰቅሏት ዘንድ አዘዘ በጨመሩዋትም ጊዜ ሁሉም በእግዚአብሄር ኃይል ሞቱ ደግሞ በመጋዝ እንዲሰነጥቋት አዘዘ መጋዙም ተሰበረ ንጉሱም ሞተ። የዳኬዎስም ልጁ ሰምቶ መጣ ያቺንም አገር ከበባት ቅድስት ኦርኒንም ይዞ የተሳሉ መርፌዎችንም በእጆቿና ሸእግሮቿ እንዲሰገስጉ በጀርባዋም ላይ አሻዋ የተመላ ዳውላ አድርገው ከአራት ፈረሶች ላይም አስረው ስጋዋ ተበጠጥሶ እስቲጠፋ ድረስ እንዲአስሮጧቸው አዘዘ በዚህም አልቻሏትም።ያንንም ከሀዲ የእግዚአብሄር መልአክ ኦርኒም ጦር ወግቶ ገደለው የከበረች ኦርኒም ሀይማኖትን እያስተማረች በሽተኞችን እየፈወሰች ሙታንን እያስነሳች ተቀመጠች። አራተኛ ንጉስም መጣ የቅድስት ኦርኒንም ዜና ሰምቶ ወደርሱ አስቀረባትና ለአማልክት ትሰዋ ዘንድ አስገደዳት እምቢ ባለችውም ጊዜ ከእሳት ውስጥ እንዲጨምሩዋት አዘዘ ከእሳትም ውስጥ በደኃና ወጥታ የረከሱ አማልክቶቹን ዘለፈች ንጉሱም ይህን ድንቅ ስራ አይቶ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። አምስተኛው የፋርስ ንጉስ መጣ የከበረች ኦርኒንም ይዞ በእጁ በያዘው ጦር ወጋትና ሞተች ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክም መጥቶ ከሞት አስነሳት በክብር ባለቤትም በክርስቶስ ስም እያስተማረች ወደ ከተማው ውስጥ ገባች ከጥቂት ቀኖችም በኃላ ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ተነጥቃ ወጣች። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ነባቤ_መለኮት በዚችም ቀን የመለኮትን ነገር የሚናገር የጎርጎርዮስ መታሰቢያ ነው። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት በሌላም በኩል "ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ" እየተባለም ይጠራል፡፡ ሀገሩ ቂሳርያ ነው፡፡ በመጀመሪያ የሕግ ባለሙያ የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የቍስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ ሆኖ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያነት አገልግሏል፡፡ በደራሲነቱ ምድራውያን መላእክት ከተሰኙት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ነው፡፡ የአምላክን ሰው መሆንና ምሥጢረ ሥላሴን እጅግ አስፍቶና አራቆ ያስተማረ ከመሆኑም በላይ ‹‹ዳግማዊ ዮሐንስ ነባቤ መነኮት›› ተብሎ እስኪጠራ ድረስ በነገረ መለኮት የተራቀቀ ታላቅ ሊቅ መምህር ነው፡፡ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን የማይጠቅስ መጽሐፍና መምህር የለም፡፡ ሃይማኖተ አበው አጥብቆ የሚጠራው የቤተ ክርስቲያናችን መመኪያ ነው፡፡ የአርመንን ኦርቶዶክስ ያቀና ሲሆን መንበሩን የኖኅ መርከብ ባረፈችበት አራራት ተራራ ላይ ነው የሠራው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አክርስጥሮስ በዚች እለት ተጋዳይ የሆነ መነኰስ የከበረ አክርስጥሮስ አረፈ። ይህም አባት በዮርዳኖስ ገዳም የሚኖር ነበር ከመነኰሳቱም አንዱ እየሰገደ እንዲህ ብሎ ጠየቀው "አባቴ አክርስጥሮስ ሆይ ከኔ ጋር ፍቅርን አደርግ እጠቀምበትም ዘንድ ስራህን ሁሉ ንገረኝ" አለው። ሽማግሌውም አክርስጥሮስም እንዲህ ብሎ መለሰለት "ልጄ ሆይ ግልማሳ ሆኜ ሳለ በመነኰስኩ ጊዜ በዚያ እፀልይ ዘንድ በለሊት ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ መቅደስ እሄድ ነበር። አስራ ሁሉት ደረጃዎችም አሏት በየአንዳንዱ ደረጃ መቶ መቶ ስግደቶችን እሰግዳለሁ ደውልንም በሚደውሉ ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን በመግባት ከወንድሞች ጋር የማህበሩን የፀሎት ስርአት እፈስማለሁ እንዲሁም በማድረግ አስር አመት ኖርኩ።" "ከሌሊቶቹም በአንዲቱ የተለመደ ፀሎቴን ከፈሰምኩ በኃላ ልቡናዬ በተመስጦ ተማረከ ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሁለት ሰዎች መቅረዚችን ሲያበሩ እኩሌታዎቹ ሲበሩ እኩሌታዎቹም ሲጠፉ አየሁ። " "እኔም ይህ ስራ ምንድንው አልኳቸው እንዚያም አባቶች ባልንጀራውን የሚወድ መቅረዙ የበራበታል አሉኝ እኔም ደግሜ መቅረዜ የቱ ነው አልኃቸው እነርሱም ሂድ ከወንድሞችህ ጋር ተፈቀር እኛ እናበራልሀለን አሉኝ በነቃሁም ጊዜ ማንንም አላገኘሁም።" ከዚህም በኃላ አባ አክርስጥሮስ ብቻውን ወደ ደብረ ሲና ሄዶ በዚያ እየተጋደለ ሀምሳ አመት ኖረ ወደርሱም እንዲህ የሚለው ቃል መጣ "ከአባቶችህ ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ገዳምህ ተመለስ ከዚህም በኃላ በተመለሰ ጊዜ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ጥር_30 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሰላሳ በዚህች ቀን #ቅድስት_ሶፍያ ከሦስት ድናግል ልጆቿ ጋር በሰማእትነት ሞቱ፣የከበሩ #አምስቱ_ደናግል_ሰማዕታት (ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ ዓበያ፣ ዓመታ) በሰማዕትነት አረፉ፣ የሮም ንጉስ ልጅ የከበረች #ቅድስት_ኦርኒ በሰማዕትነት አረፈች፣ የመለኮትን ነገር የሚናገር #የቅዱስ_ጎርጎርዮስ መታሰቢያ ነው፣ ተጋዳይ የሆነ መነኰስ የከበረ #ቅዱስ_አክርስጥሮስ አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ሶፍያና_ሦስቱ_ሰማዕታት_ልጆቿ ጥር ሰላሳ በዚች ቀን የከበሩ ድናግል ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ በሰማእትነት ሞቱ የተባረከች አናታቸው ሶፍያም ከአንፆኪያ ከከበረ ወገኖች ውስጥ ናት። እነዚህንም ሶስት ልጆች በወለደቻቸው ጊዜ በእሊህ ስሞች ጠራቻቸው ትርጓሜያቸውም ሀይማኖት ተስፋ ፍቅር ነው የራሷም ስም ትርጓሜው ጥበብ ማለት ነው። ጥቂትም በአደጉ ጊዜ ወደ ሮሜ ከተማ ወስዳ በጎ አምልኮን እግዚአብሄርን መፍራትን የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማራቸው በከሀዲውም የሮሜ ንጉስ በአርያኖስ ዘንድ ወሬያቸው ተሰማ ወደርሱም የያመጡአቸው በማስተማር ትመክራቸውና ታፀናቸው ነበር። እንዲህም ትላቸዋለች ልጆቼ ተጠበቁ የዚህን የኃላፊውን አለም ክብር በማየት ልባችሁ እንዳይደክምና ከዘላለማዊ ክብር እንዳትርቁ ከሙሽራው ከክርስቶስ ጋር ሁናችሁ ወደ ሰማያዊ ሰርግ እንድትገቡ ጠንክሩ።እድሜያቸውም የታላቂቱ አስራ ሁለት የሁለተኛይቱ አስር የሶስተኛይቱ ዘጠኝ ነው። እናታቸውም ወደ ንጉስ በአቀረበቻቸው ጊዜ ታላቂቱን ጲስጢስን እኔን ስሚ ከቤተ መንግስቴ ታላላቆች ለአንዱ አጋባሻለሁ ብዙ ስጦታም እሰጥሻለሁ ለአጵሎን ስገጂ አላት። እርሷም እርሱንና የረከሁ አማልክቶቹን ሰደበች እርሱም ተቆጥቶ በብረት ዘንጎች እንዲደበድቧት ጡቶቿንም እንዲቆርጡ እሳትንም ከብረት ምጣድ በታች በማንደድ ባሩድ ሙጫ ሰሊጥን በውስጡ አድርገው እጅግ አፍልተው ወደዚያ ይጨምሩዋት ዘንድ አዘዘ። በጨመሩዋትም ጊዜ እየፀለየች በብረት ምጣዱ ውስጥ ቆመች ከቶ እሳት አልነካትም ።የምጣዱም ግለት ፀጥ ብሎ እንደ ጥዋት ጊዜ ጤዛ ቀዝቃዛ ሆነ ከዚያ ያሉ ሰዎችም አድነቀው እግዚአብሄርን አመሰገኑት ብዙዎችም በክብር ባለቤት እግዚአብሄር ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆረጡዋቸውና በሰማእትነት ሞቱ። ከዚህም በኃላ የቅድስት ጲስጢስን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ምስክርነቷንም ፈፅማ የምስክርነት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ስጋዋን አንስታ ወሰደች።ዳግመኛም ሁለተኛዋን አላጲስን አቀረቧትና ደበደቧት ፅኑእ ግርፋትንም ገረፏት ከጋለ ብረት ምጣድ ውስጥ ጨመርዋት በዚያንም ጊዜ ቀዝቅዞ እንደጥዋት ጤዛ ሆነ ንጉሱም ከዚያም እንዲአወጧትና ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ምስክርነቷንም አድርሳ በመንግስተ ሰማያት የህይወት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ስጋዋን ወሰደች። ቅድስት ሶፊያም ከስቃይ የተነሳ እንዳትደነግጥ ስለ ልጅዋ ስለ አጋጲስ ትፈራ ነበር ታፅናናትና እንድትታገስ ታደርጋት ነበር በዚያንም ጊዜ ወስደው ከመንኮራኩር ውስጥ ጨመርዋት እግዚአብሄርም መልአኩን ልኮ ያንን መንኮራኩር ሰበረው እርሷም ፊቷን በመስቀል ምልክት አማትባ ወደሚነደው እሳት ተወርውራ ገባች በዚያንም ጊዜ እሳቱ እንደ ጥዋት ውርጭ የቀዘቀዘ ሆነ ከዚያ ያሉትም ሰዎች ብርሀን የለበሱ ሁለት ሰዎች ከነጫጭ ልብሶች ጋር ሲጋራድዋት አይተው እጅግ አደነቁ ብዙዎችም በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆርጠዋቸው በሰማእትነት ሞቱ ያቺንም የዘጠኝ አመት ልጅ የከበረች አጋጲስን ራሷን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ።ምክስርነቷንም ፈፀመች ሁሉም የማያልፍ የማይጠፋ ሰማያዊ መንግስትን ወረሱ። የከበረች ሲፊያም የሶስት ልጆቿን ስጋቸውን ወስዳ ገነዘቻቸው ወደ ከተማውም ውጭ አድርሶ በዚያ ቀበረቻቸው በሶስተኛውም ቀን ወደ መቃብራቸው ሄዳ አለቀሰች ነፍሷንም ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ለመነች ልምናዋንም ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ ምእመናን ሰዎችም መጥተው ገንዘው ከልጆቿ ጋር ቀበርዋት። በከሀዲው ንጉስ ላይ ግን እግዚአብሄር ጭንቅ የሆነ ደዌ ላከ አይኖቹም ፈረጡ አጥንቶቹም እስከሚታዩ ስጋው ሁሉ ተሰነጣጠቀ እጆቹም ተቆራረጡ ከእርሱም ደምና መግል ፈሰሰ ትልም ይወድቅ ነበር ሁለመናውም ተበላሽቶ በክፉ ሞት ሞተ።ስለ እነዚያ ደናግል ጌታ ተበቅሎታልና። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አምስቱ_ደናግል_ሰማዕታት (ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ ዓበያ፣ ዓመታ) በዚችም እለት የከበረች ጤቀላ ከእርሷ ጋር ከሚኖሩ አራት ደናግል ጋር ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ በሰማዕትነት ሞተች። ይህም ፎላ የሚባል ቄስ በዓመፅ የሰበሰበው ብዙ ገንዘብ እንዳለው በከሀዲ መኮንን ዘንድ ነገር ሰሩበት መኮንኑም ገንዘቡን ሁሉ እንዲወርሱት አዘዘ ፎላም ወደ መኮንኑ ሄዶ ገንዘቡን እንዲመልስለት ማለደው። መኮንኑም ስለ እነዚህ ደናግል ሰምቶ ወደርሱ እንዲአመጡአቸው አዘዘ በመጡም ጊዜ ፎላን መኮንኑ ለፀሀይ ይሰግዱ ዘንድ እሊህን ደናግል ብትሸነግላቸው ገንዘብህን እመልስልሀለሁ አለው። ፎላም ሊሸነግላቸው ጀመረ ደናግሉም አንተ የሰይጣን ልጅ የክብር ባለቤት ክርስቶስን እንክደው ዘንድ እንዴት ትፈትነናለህ አንተ ቀድሞ መምህራችን የነበርክ ስትሆን ብለው ዘለፉት። መኮንኑም ቃላቸውን በሰማ ጊዜ በጅራፍ እንዲገርፏቸው አዘዘ እነርሱ ግን መናገራቸውን አልተውም ስቃይንም አልፈሩም። መኮንኑም ፎላን የበከተ ብትበላ ደምንም ብትጠጣ ገንዘብህን እመልስልሀለሁ አለው በሰማም ጊዜ ልቡናውን አፅንቶ ሊገድላቸው ሄደ እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ልቡ በገንዘብ ፍቅር ተነድፎዋልና። ደናግሉም እንዲህ አሉት ከሀዲ ሆይ የመድኃኒታችንን ክርስቶስን ስጋውንና ደሙን በእጅህ ተቀብለን አልነበረምን ስለ ገንዘብ ፍቅር እኛን የክርስቶስን በጎች ታጠፋ ዘንድ እንዴት መጣህ እንዲህም እያሉ ሰልፍ እንደተማረ አርበኛ ሰው በሰይፍ ራሶቻቸውን ቆረጠ። መኮንኑም የፎላን ብላሽነትና ድንቁርና አይቶ በሰይፍ ገደለው ነፍሱንም ገንዘቡንም ሀይማኖቱንም አጣ። የደናግሉም ስማቸው ጤቀላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ አመታ፣ ዓበያ ነው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ኦርኒ_ሰማዕት በዚችም ቀን ስሙ መርቅያኖስ የሚባል ለጣዖት የሚሰግድ የሮም ንጉስ ልጅ የከበረች ኦርኒ በሰማዕትነት አረፈች።የዚችም ቅድስት እናቷ ክርስቲያናዊት ናት አባቷም እልፍኝ ሰርቶላት በወርቅና በብር ልብሶች ከአጌጡ አስራ ሁለት ደናግል ጋር ወደዚያ አስገባት ከልጁ ጋር ይሰግዱላቸው ዘንድ አስራ ሰባት ጣዖታትን አወጣላቸው በላይዋም በሩን ዘጋ በዚያም ሰባት ዓመት ከስድስት ወር ኖረች። በአንዲትም ዕለት ዐይኖቿን ወደ ምስራቅ ቀና በአደረገች ጊዜ ርግብን አየች በአፏም የዘይት ቅጠል ይዛ ነበር ከማዕድዋም ላይ ጥላው ወጣች ዳግመኛም ወደምእራብ ስትመለከት ቁራ መጣ በአፉም ከይሲ ይዞ ነበር ከማዕዷም ላይ ጥሎት ወጣ አደነቀችም። በዚያንም ጊዜ አባቷ የሰጣት መምህርዋ መጣ ያንንም ራእይ አወራችለት እርሱም ሲተረጉምላት ርግብ የጥበብ ነገር ነው የዘይቱም ቅርንጫፍ በጥምቀት የሚገኝ ክብር ነው ቁራም ንጉስ ነው።ከይሲውም መከራ ነው አንቺም በርቺ ጠንካራ በክርስቶስ ስም መከራ ትቀበይ ዘንድ አለሽና የህይወት አክሊልንም ትቀበያለሽ አላት። ከዚህም በኃላ በአደገች ጊዜ አባቷና እናቷ ወደርሷ ወጥተው ስለ ጋብቻ ተናገርዋት የከበረች ኦርኒም እስከ ሰባት ቀን ታገሱኝ አለቻቸው ከዚህም በኃላ እርሱ የመረጠውን መንገድ ይመራት ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ፀለየች።

ጸሎትና ምህላ ይደረግ፣ ሕፃናት የእናቶቻቸውን ጡት እንዳይጠቡ ይከልከሉ፣ የሚጠቡ የቀንድ ከብቶችም ከጥጃዎቻቸው ጋር እንዳይገናኙ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይደረግ›› ብለው ነገሯቸው፡፡ ንጉሡም ጻድቁ እንዳሏቸው ቢያደርጉ በሦስተኛው ቀን ሽፍቶቹን በቀላሉ ማረኳቸውና አገሪቱ ሰላም ሆነች፣ ንጉሡም እጅግ ደስ አላቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊንም በማስጠራት ‹‹ያልከው ተፈጸመ፣ ድል አድርጌያለሁና ደስ ብለኛል፡፡ የትኛውን አካባቢ ርስት ጉልት አድርጌ ልስጥህ?›› አሏቸው፡፡ ጻድቁም ለመነኮሳት ልጆቻቸው የእርሻ ቦታ የሚሆን ርስትን ተቀበሉ፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ በቁና በነጹ መነኮሳት እንዲገለገል ካላቸው ፍላጎት አኳያ መነኮሳቱንም ከዓለማዊ ፈተና ለመታደግ ሲሉ ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይወጡ ከልክለዋል፡፡ አንዲት ሴት የጻድቁን ቃል በመተላለፍና በመደፋፈር ወደ ተራራው በመውጠቷ አፋፉ ላይ እንደደረሰች ከያዘችው ድፎ ዳቦ ጋር ድንጋይ ሆና ቀርታለች፡፡ ይህ ምስሏ አሁንም ድረስ ከነሙሉ የሰውነቷ ቅርጽ በግልጽ ይታያል፡፡ ሴቶች አንዳንድ ገዳማት ላይ እንዳይገቡ ገዳሙን የገደሙት ቅዱሳን የከለከሉበትን በቂ የሆነ መንፈሳዊ ምክንያት ስላላቸው ነው እንጂ እንዲሁ ያወጡት ሕግ አይደለም፡፡ ለዚህም ተጨማሪ ማሳያ ይሆን ዘንድ የእመ ምዑዟ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የወንዶችና የሴቶች ገዳም የተለያየ እንዲሆን ያደረገችበት ምክንያት ከገድሏ ላይ እንይ፡- ‹‹እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ቤተ መቅደሷን በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታ እንደጨረሰች ጌታችን ከመንበሩ ሆኖ ተገለጠላትና በቦታው ላይ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጣት፡፡ ተአምራቶቿንና የትሩፋቷን ዜና የሰሙ ሁሉ ወደ እርሷ እየመጡ ተሰብስበው በተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ ቅድስት እናታችንም ትመክራቸውና ታስተምራቸው ነበር፡፡ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ተገልጾላት የበጎ ሥራ ጠላት የሆነው ሰይጣን በማኅበሩ ልቡና እርሻ ላይ እንክርዳድ ሽንገላን እንደዘራ ባየች ጊዜ ከዚህ በኋላ የወንዶቹንና የሴቶቹን ቦታ ለየች፡፡ ለወንዶቹ ለብቻ፣ ለሴቶቹም ለብቻ ገዳም መሥርታ ዘወትር እንዳይተያዩ አደረገች፡፡ ልጆቿንም ሁሉ የእግዚአብሔር መልአክ ይጠብቃቸው ነበር፡፡ እርሷም የአርባውን ጾም ስትጾም ምንም ሳትቀምስ በምድር ላይም ሳትቀመጥ ቆማ ትጨርሳለች፡፡ እንደዚሁም በሌሎች አጽዋማት እንዲሁ ታደርግ ነበር፡፡ በስግደትና በግርፋትም ብዛት ሰውነቷን እጅግ ትጎዳና ታደክም ነበር፡፡ መላእክትም ምግቧን ከሰማይ ኅብስትና ወይን ያመጡላት ነበር፡፡ ውዳሴ አምላክንና አርጋኖንን በጸለየች ጊዜ ጌታችንና እመቤታንም በየጊዜው እየመጡ እየባረኳት ይሄዳሉ፡፡ የዕረፍት ጊዜዋም ከመድረሱ በፊት መላእክትም በብርሃን ሠረገላ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስደው ሥጋ ወደሙን እንትድቀበል አድርገዋታል፡፡›› አንዳንድ አላዋቂ ሰዎች በተለይም ከእኛ እምነት ውጭ ያሉ ሰዎች የሴቶችን ወደ አንዳንድ ገዳማት መግባት አለመቻል በዘመኑ የእኩልነት ስሌት ያሰሉታል፡፡ ይህን ሀሳብ የሚጋሩ አንዳንድ ኦርቶዶክሳውያን እኅቶችና እናቶችም አይጠፉም፡፡ እውነታው ግን ይህ ነው፡- ቅዱሳን አባቶቻችንና ቅዱሳት እናቶቻችን ይህን ሕግ የሠሩበት ምክንያት ግን ከላይ እንዳየነው በውል የታወቀና የተረዳ እውነት ነው፡፡ ‹‹ገዳማቸው በቁና በነጹ መነኮሳት እንዲገለገል ካላቸው ፍላጎት አኳያ መነኮሳቱንም ከዓለማዊ ፈተና ለመታደግ ሲሉ ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይወጡ ከልክለዋል፡፡›› ፤ ‹‹ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ተገልጾላት የበጎ ሥራ ጠላት የሆነው ሰይጣን በማኅበሩ ልቡና እርሻ ላይ እንክርዳድ ሽንገላን እንደዘራ ባየች ጊዜ ከዚህ በኋላ የወንዶቹንና የሴቶቹን ቦታ ለየች፡፡ ለወንዶቹ ለብቻ፣ ለሴቶቹም ለብቻ ገዳም መሥርታ ዘወትር እንዳይተያዩ አደረገች፡፡›› ሌላው የአቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ገዳማቸውን ልዩ ከሚያደርጉት ነገሮች ውስጥ ጻድቁ በዘንዶ አማካኝነት ወደ ተራራው ሲወጡ መጀመሪያ የረገጡት ዓለት የእግር ጣታቸው ምልክት ያለበት መሆኑ ነው፡፡ እናቶች ምጥ ሲይዛቸው ወይም ሰዎች ሲታመሙ ድርቅና ቸነፈር ሲከሰት የሚፈውስና ምሕረት የሚያወርድ እንዲሁም የተጣሉ ሰዎች የሚታረቁበት ነባኢ መስቀል (የሚያነባ መስቀል) በገዳሙ ይገኛል፡፡ በየዓመቱ ጥር 29 ቀን የዕረፍታቸው በዓል በድምቀት ይከበራል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።https://t.me/finotebirhan12

ከማኅበርተኞቹ መካከል ‹‹ሳይዳ›› የሚባል ሰው ነበር፡፡ ይህም አሳላፊ ወይም ሙሴ ነበር፡፡ ይህም ሰው እንግዳና ድሀ ሰው ፈጽሞ አይወድም ነበርና ጌታችንም ከማኅበርተኞቹ መካከል ሲገኝ ድሀ መስሎ ስለነበር በጣም ይጠላው ነበር፡፡ ጌታችን አንድ ዓመት ከስድስት ወር ከእነርሱ ጋር ሲቀመጥም አንድ ቀን እንኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ ሰጥቶት አያውቅም ነበር፡፡ የሆኖ ሆኖ መድረሱ አልቀረም የጌታችን ማኅበር ደረሰ፡፡ እንደማህበሩ ስርዓት የወይን ጠጅ የሚጠመቅባቸውን ጋኖች የሚያጥበው ሙሴው ወይም አሳላፊው ነው፡፡ ስለሆነም በሥርዓቱ መሠረት ጌታችን ሙሴውን ጠርቶ ጋኖችን እጠብልኝ አለው፡፡ አሳላፊውም በቁጣ ‹‹አንተ ቤትህ የማይታወቅ፤ ከየት አምጥተህ ማኅበር ልታደርግ ነው?›› አናንቆ አልታዘዝህም ብሎ ሄደ፡፡ ይህን የተመለከተው ጌታችንም አንድ እረኛ ጠርቶ ‹‹አንተ ልጅ ከብቶችህን እኔ እጠብቅልሃለሁና በዚህ ውሀ አምጣልኝ›› አለው፡፡ ትንሹ እረኛ ልጅም ገምቦውን ይዞ ትንሽ ወጣ እንዳለ ጌታችን ዘወትር በሚቀመጥበት ድንጋይ ላይ ሆኖ ዘንጉን ወደ ልጁ አቅጣጫ ወረወረው፣ ዘንጉንም ከልጁ ፊት ሂዶ ተተከለ፡፡ ልጁንም ጠርቶ ዘንጉንም እንዲነቅለው አዘዘው፡ ልጁም እንደታዘዘው ዘንጉን ቢነቅለው ውሀ ፈለቀ፡፡ ጌታችንም ‹‹ከእርሱ ቀድተህ አምጣልኝ›› አለው፡፡ ልጁም ከዚያ ውሀ ቀድቶ አመጣለትና ጋኖቹን አጠባቸው፡፡ በበዓሉ ቀን ማኅበርተኞቹ ‹‹ምን ሊያበላን ነው! ምንስ ሊያጠጣን ነው!›› ሳይሉ ሁሉም ተሰበሰቡ፡፡ ጌታችንም በፊታቸው ጋኖቹን ቢባርካቸው በተአምራት የወይን ጠጅ ሞልተው ተገኙ፡፡ ቀድቶ ቢሰጣቸውና ቢቀምሱትም በጣም ግሩም ጣፋጭ ስለነበር እጅግ አደነቁ፡፡ እነርሱም ጌታችንን ከጻድቃን አንዱ ስለመሰላቸው ከእግሩ ላይ ወድቀው ‹‹እስካሁን ድረስ ሳንበድልህ አልቀረንምና ይቅር በለን›› ብለው ለመኑት፡፡ እርሱም ‹‹ተነሱ›› ብሎ ካስነሣቸው በኋላ ‹‹እናንተ ምንም አልበደላችሁም፣ የጠየኳችሁን አድርጋችኋል የበደለኝ ግን አሳላፊያችሁ ነው፣ አንድም ቀን እንኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ አልሰጠኝምና አፈራርዱኝ›› አላቸው፡፡ ነገር ግን ሙሴው ወይም አሳላፊው የማያፍር ደፋርና ርጉም ስለነበር ‹‹‹ይህ ሰው በልቶ አልበላሁም፣ ጠጥቶ አልጠጣሁም› የሚል ስለሆነና ስለማይጠግብ ነው እንጂ እንዲያውም ለእናንተ አንድ አንድ ዋንጫ ሲሰጣችሁ ለእርሱ ሁለት ሁለት ነበር የሚሰጠው›› ብሎ የሐሰት ቃል መለሰ፡፡ ጌታችንም በዚህ ጊዜ ‹‹እንግድያስ እኔ የጠጣሁበት ዋንጫ ትቅረብና ትመስክርብኝ›› አለው፡፡ በዚሁ ተስማምተው ሙሴው ሄዶ አንድ ሸራፋ ዋንጫ አምጥቶ ‹‹በዚህ ነበር የሚሰጠውና የሚጠጣው›› ብሎ አቀረበ፡፡ በዚህም ጊዜ ዋንጫዋ ከተቀመጠችበት አንድ ክንድ ከስንዝር ወደላይ ተነሥታ በሰው አንደበት በመመስከር ‹‹ዓለማትን የፈጠረ አምላክ ምስክሬ ነው እኔ የያዝኩትን የወይን ጠጅስ እርሱ በከንፈሩ አልነካኝም በሌሎቹ ሰዎች እጅ ግን ተይዤ ያየኝ ነበር›› አለች፡፡ ያንጊዜም ሙሴውን ሳይዳን እንደ ዳታንና እንደ አቤሮን ምድር ተከፈተችና ዋጠችው፡፡ ማኅበረ ጻድቃንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑ ዐውቀው እንደገና ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ለመኑት፡፡ ጌታችንም ‹‹ይቅር ብያችኋላሁ›› ካላቸው በኋላ ‹‹ስማችሁን የጠራ፣ በስማችሁ ተዝካር ያወጣ፣ ድኆችን የረዳ፣ ያለበሰ፣ ያጎረሰ፣ የመጸወተ፣ ቤተ ክርስትያን የሠራ ያሠራ እሰከ 14 ትውልድ ድረስ ምሬላችኋለሁ›› የሚል ድንቅ ቃል ኪዳን ገባላጣቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህችን የተቀደሰች ቦታችሁን መጥቶ የተሳለመ ቢኖር ኢየሩሳሌምን እንደተሳለመ እቆጥርለታለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹እንደነ ሄኖክና ኤልያስ ከሞት ተሰወሩ›› ብሏቸው በማግሥቱ ጥር 30 ቀን ከዚህ ዓለም ሠውሯቸዋል፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ገብረ_ናዝራዊ ዳግመኛም በዚህች እለት የከበሩ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ዘቀወት አረፈ፡፡ ጻድቁ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በሰሜን ሸዋ ይፋትና ጥሙጋ ደብረ ሲና ውስጥ ቀወት በምትባለው ቦታ በ13ኛው መ/ክ/ዘ ተወለዱ፡፡ አባታቸው ስቡሐ አምላክ እናታቸው ክርስቶስ ክብራ የሚባሉ የነገሥታት ወገን ናቸው፡፡ የአባታችን የስማቸው ትርጉም ‹‹በስዕለት ለእግዚአብሔር የተሰጠ ልዩና የተቀደሰ ማለት ነው፤ ይህም የበኩር ልጅ ስለሆኑና በስዕለት የተሰጡ ስለሆነ ነው፡፡ ወላጆቻቸውም ፈሪሃ እግዚአብሔርንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በሚገባ እያስተማሩ በምግር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ ዲቁናን ከተወበሉ በኋላ በሸዋ አካባቢ እየተዘዋወሩ ወንጌልን መስበክ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን በዚህ በሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ጊዜ ብዙ ፈተና ገጠማቸው ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ከላይ በአቡነ ታዴዎስ ገድል ላይ እንዳየነው ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ሚስት በማግባቱ ምክንያት አቡነ ገብረ ናዝራዊም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ በዚህም ምክንያት ንጉሡ በማሠር ብዙ አሠቃያቸው፡፡ ጳጳሱ አባ ያዕቆብን ጨምሮ ብዙ ቅዱሳንም ለስደት ተዳረጉ፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊም አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ከእሥር እንደተፈቱ ወደ ላሊበላ በመሄድ 12 ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ወደ ሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ገዳምም በመሄድ ካገለገሉ በኋላ ወደ ትግራይ ሄዱ፡፡ ከዚያም ግብፅን አቋርጠው ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ከጳጳሱ አባ ያዕቆብ ጋር ሲነሡ አባ ያዕቆብ ‹‹በዓትህ ኢትዮጵያ ብቻ ናት›› ብለው ስለነገሯቸው ሀሳባቸውን ትተው የጳጳሱን ምክራቸውን ተቀበሉና ከጉዞአቸው ቀሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ አዲግራት በመሻገር ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ፈጽሙ፡፡ መጀመሪያ እንደመጡ ያረፉባት አጋዝና በተባለቸው ተራራማ ቦታ ነበር፡፡ የአባታችን ሁለተኛ ቤተ ክርስቲያናቸው በዚህ ቦታ ላይ ታንጾ ይገኛል፡፡ በቦታውም ላይ 8 ዓመት ኖረውበታል፡፡ ወደሸለቆመም ዘቅዝቀው ወርደው ወደ ማየ ኢየሱስ በመሄድ ሓባ በምትባለው ተራራ ላይ የቁፋሮ ሥራ ጀምረው ባለ ሁለት ዓምድ የሆነ አንድ በር ያለው ቤተ ክርስቲያን አንጸው ሲያበቁ አሁን ወዳለው ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ መጡ፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ዓምባ ላይ ከወጡ በኋላ በመጀመሪያ የተለያየ መጠንና መጠሪያ ስም ያላቸውን ከዓለት ላይ የተፈለፈሉ አስደናቂ የሆኑ ከ44 በላይ የውኃ ጉድጓዶችን አንጸዋል፡፡ ከጉድጓዶቹም በተአምራት ጸበሎች ፈልቀውላቸዋል፡፡ እነዚህንም ጸበሎች እስከዛሬ ድረስ መጠናቸው ምንም ሳይጎድል ገዳማውያኑ ይጠቀሙባቸዋል፡፡ ጻድቁ በዚሁ ቦታ ከዓለት ላይ ፈልፍለው ያነጹት አስደናቂ ቤተ መቅደስ ይኛል፡፡ መካነ መቃብራቸውም በዚሁ ገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በጾምና በጸሎት ተወስነው ሕዝቡን በማስተማር ብዙ አስገራሚ ተአምራትን በመፈጸም ላይ እንዳሉ የቀድሞ ጓደኛቸው የነበሩትና በኋላም የነገሡት ዐፄ ዓምደ ጽዮን በትግራይ ከፍለ ሀገር አጋሜ አውራጃ ዓምባ ጽዮን በተባለው ተራራ ላይ ሽፍቶች ተነሥተው መሽገው ነበር፡፡ ንጉሡም እነዚህን የተነሡባቸውን ሽፍቶች ለመያዝ ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት ብለው 10 ሺህ ሠራዊት ይዘው ወደ አካባቢው ዘመቱ፡፡ ንጉሡም በአካባቢው እንደደረሱ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በዚያ እንዳሉ ስለሰሙ መልእክተኞችን ልከው አስመጧቸውና የመሸጉትን ሽፍቶች በምን ዓይነት ዘዴ ድል ማድረግ እንደሚችሉ የጠቋቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊም ‹‹ለሦስት ቀናት ያህል በቤተ ክርስቲያን

አሳይተውታል፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በእጅጉ ሲገረምና ‹‹በአምላከ ታዴዎስ ስም አምናለሁ›› ሲል የባለጸጋው ልጅ ሙሳ ግን ‹‹በምትሃት አሳይቶን ነው እንጂ የእውነት አይደለም›› በማለት አባቱንም እንዳያምን ይናገር ጀመር፡፡ ይህንንም ሲናገር በመጀመሪያ ያለፈችው እናቲቱ ግመል እረግጣ ገደለችው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ንጉሡን፣ አባቱን አፍጃልንና ሕዝቡን የሞተ እንደሚነሣ ሲያስምሯቸው ‹‹የሞተ ይነሣልን? እስኪ ይህ የሞተው ልጅ ይነሳና ሁሉም አይቶ ይመን›› አሏቸው፡፡ እሳቸውም ‹‹ዛሬ ተቀብሮ ይዋልና ነገ በሦስተኛው ይነሣል›› ብለዋቸው ተቀብሮ ዋለ፡፡ በማግሥቱም አፍጃልን ጠርተው ‹‹‹አልዓዛርን ከሞት ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልጄ ሆይ ና ውጣ› ብለህ ከልጅህ መቃብር ላይ አኑረው› ብለው ዘንጋቸውን ሰጡት፡፡ ሄዶም እንዳሉት ቢያደርግ ልጁ አፈፍ ብሎ ተነሥቷል፡፡ ይህንን ያዩ የሀገሩ ሰዎች ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል፡፡ እሳቸውም 12 አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸው ሞቶ የተነሳውን ሙሳን ሙሴ ብለው ሰይመው አስተምረው ሊቀ ካህናት አድርገው ሾመውት አቡነ አኖሬዮስን ይዘው ወደ ጽላልሽ ዞረሬ ተመልሰዋል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ አባ ያዕቆብ የተባሉ ጳጳስ ከግብፅ መጡ፡፡ የአቡነ ታዴዎስን ዜና ሲሰሙ ተደስተው ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው አስጠርተዋቸው ‹‹የአባታችሁን ዜና ገድል ንገሩኝ›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ‹‹ጨዋታ በአስተርጓሚ አይሰምርም›› ብለው ወደ ጌታችን ቢጸልዩ የጳጳሱ ቋንቋ ለታዴዎስ፣ የታዴዎስም ቋንቋ ለጳጳሱ ተገልጦላቸው የመሸ የነጋ ሳይመስላቸው 40 ጾምን ሲጨዋወቱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ጳጳሱ ከንጉሡ ተማክረው ‹‹ሊቀ ካህናት ዘጽላልሽ›› ብለው ሾመዋቸዋል፡፡ በነግህና በሰርክ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ፣ ቀን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ሌሊት ከባሕር ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ ሳለ ከ10 ዓመት በኋላ ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ቅምጥ አገባ፡፡ አቡነ ታዴዎስም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ ገሥጸውና አውግዘው አቡነ ማትያስን አስከትለው ሲመለሱ ቅምጧ የንጉሡ ሚስት በፈረስ ተከትላ ደርሳ የኋሊት አሳስራ ዛሬ ‹‹ማርያም ገዳም›› ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ካለው ትልቅ ገደል ውስጥ ሁለቱንም ጣለቻቸውና ጥር 29 ቀን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ በሰማዕትነት ዐርፈው ደማቸው ከፈሰሰበት ከገደሉ ስር በፈለቀው ጸበላቸው ‹‹ታዴዎስ ወማትያስ›› እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያለ የተጠመቀ ሰው እንደ 40 ቀን ሕፃን እንደሚሆን ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቷቸዋል፡፡ ይህ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ የተሠራው ቤተ ክርስቲያናቸው በጠላት ወረራ ጊዜ ፈርሶ ቦታው ጠፍ ሆኖ የኖረ ቢሆንም የአካባቢው ሕዝብ ቦታውን ከልሎ በክብር ሲጠብቀው ስለኖረ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ የአቡነ ታዴዎስ ታቦታቸው በ2005 ዓ.ም ከኢቲሣ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ወጥቶ ጻድቁ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ በተሠራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያናቸው በታላቅ ክብር ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑም ከኢቲሣ በእግር የአንድ ሰዓት ተኩል ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ጻድቃን_ቅዱሳን_ማሕበረ_ዶጌ (ዴጌ ጻድቃን) በዚህች እለት የጻድቃን ቅዱሳን ማኅበረ ዶጌ አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ 3000 የሚሆኑ ከመድኃኔዓለም ጋር ማኅበር ይጠጡ የነበሩ በአንድ ላይ የተሰወሩ ቅዱሳን መታሰቢቸው ነው፡፡ እነዚህም ጌታችን መድኃኔዓለም ክርስቶስ በመካከላቸው ተገኝቶ የጽዋ ማኅበራቸውን አብሯቸው የጠጣ ሦስት ሺህ ቅዱሳን ‹‹ማኅበረ ጻድቃን ወይም ማኅበረ ደጌ›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ ማኅበሩን ያቋቋመው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ነው፡፡ በኋላም ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ጋር አብረው ማኅበር የጠጡ እነዚህ ሦስት ሺህ ቅዱሳን አክሱም አካባቢ ባለው በአቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ገዳም ጥር 29 ቀን በዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ይከብራሉ፡፡ ማኅበረ ዴጌ ማለት የደጋጎች ሀገር ማለት ነው፡፡ የደጋጎች ሀገር የተባለበት ምክንያት ብዙ ሺህ ቅዱሳን ተሰብስበው ስለሚኖሩበት ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በትግራይ ክልል በአክሱም አውራጃ ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ ምዕራብ በሚወስደው መንገድ አስራ ሁለት ኪሎሜትር ያህል ርቀት ላይ ነው፡፡ በቦታው ላይ ጥንት መሥዋዕተ ኦሪት ይሠዋበት ነበር፡፡ በኋላም በ40 ዓ.ም ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ወደ አገራችን በመጣ ጊዜ በቦታው ላይ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አጥምቋል፡፡ በወቅቱ የነበረችው ንግሥትም በቅዱስ ማቴዎስ እጅ ተጠምቃለች፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ንግስቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱንና የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ማህበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29 ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡ በ365 ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ‹‹ሮምያ›› ከምትባል መንደር ቅዱሳን ‹‹ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁአን ናቸው መንግስተ ሰማያት የነርሱ ናትና›› ያለውን ዳግመኛም ‹‹አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም›› ብሎ ጌታችን የተናገረውን አስበው ቅዱሳን የዚህም ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው ሀገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በአክሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጠንት በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው ‹‹ለዚሁ ለዚሁማ ሀገራችንን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት›› ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡ ከሱባዔውም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻላቸው ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው፣ በዚያም በጾምና በጸሎት ጸንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡ ሦስት ሺህ ያህሉን ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሥፍ ሄዱ፡፡ ከእነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡ ተጨማሪ ሥስት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋር ተደመሩ፡፡ ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን ‹‹ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል›› የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ጸንተው በየሳምንቱ እሁድ እሁድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር ይጠጡ ጀመር፡፡ በዚህም ጊዜ የማኅበረ ዴጌ ታሪክ ተቀየረ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአምሳለ ነዳይ ድሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ፡፡ ግን ማንም አላወቀውም ነበር፡፡ ጌታችንም ከእነርሱ ጋር አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃችው፣ እነርሱም ፈቀዱለትና አንዱ የማኅበሩ አባል ሆነ፡፡ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከእነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ፡፡ በዚሁ ጊዜ ‹‹እስቲ ለእኔም ተራ ስጡኝ እንደአቅሜ ዝክር ላውጣ›› አላቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ድህነቱን አይተው ‹‹አይሆንም አንተ ድሀ ነህ፣ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህና ነው የምትደግሰው? ይቅርብህ›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹አይሆንም ስጡኝ እንጂ›› ብሎ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት፡፡ ቀኑም ጥር 29 ነበር፡፡

🔴#ስንክሳር ጥር_29 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን መፃተኛ የሆነ የከበረች #ቅድስት_አክሳኒ አረፈች፣ተጋዳይ የሆነ #አባ_እስጢፋኖስ አረፈ፣ #አቡነ_ታዴዎስ_ዘጽላልሽ በሰማእትነት አረፉ፣ የጻድቃን #ቅዱሳን_ማኅበረ_ዶጌ #ከመድኃኔዓለም ጋር ማኅበር የጠጡ ቅዱሳን መታሰቢያቸው ነው፣ የከበሩ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ገብረ_ናዝራዊ_ዘቀወት አረፉ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_አክሳኒ_ፈላሲት ጥር ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን የስሟ ትርጓሜ መፃተኛ የሆነ የከበረች አክሳኒ አረፈች፡፡ እርሷም ከሮሜ አገር ለከበሩ ሰዎች ልጅ ናት ወላጆቿም ከርሷ በቀር ልጅ የላቸውም እርሷም የምትጋደል ሆነች በቀንና በሌሊትም ትፆማለች ትፀልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሄድ ከእነርሱ ጋር ታገለግላለች ከአባቷ ቤት የሚያመጡላትን ምግብ ለድሆችና ለምስኪኖች ሰጥታ እርሷ ከደናግል ምግብ ትመገበለች የደናግል መነኮሳያትንም ጋር አንድ ያደርጋት ዘንድ እግዚአብሄርን አብዝታ ትለምን ነበር። ከዚህም በኃላ ወላጆች ሊአጋቧት አስበው ከሮሜ አገር ታላላቆች ለአንዱ አጭዋት የወርቅ ልብሶችን ከወርቅና ከብር የተሰሩ የከበሩ ሽልማቶችንና ጌጦችንም አዘጋጁላት። የጋብቻውም ቀን ሲደርስ እናቷን እናቴ ሆይ በምትጋቡኝ ጊዜ ወደ ደናግሉ መሄድ አይቻለኝም እኔ ዛሬ ሄጄ በረከታቸውን ተቀብዬ በረከታቸውን ተቀብዬ ሰላምታ ሰጥቻቸው ፈጥኜ መመለስ እሻለሁ አለቻት። እናቷም የነገስታት የሆነ የወርቅ ልብሶችን አልብሳ ሴቶች አገልጋዮችን ከእርሷ ጋር አድርጋ አሰናባተቻት። እርሷ ግን ወደ ባህር ወደብ ተጉዛ መርከብንም አግኝታ ተሳፈረችና ወደ ቆጵሮስ ደሴት ሄደች።ወደ ከበረ ኤጲፋንዮስም ደርሳ ኀሳቧን ሁሉ አስረዳችው የከበረ ኤጲፋንዮስም ወደ እስክንድርያ አገር ሰደዳት ወደዚያም በደረሰች ጊዜ በህልሟ የከበረ ሀዋርያ ጳውሎስ ተገልፆ ስሙን ነገራትና የምትሰራውን ሁሉ አስተማራት። በማግስቱም ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ገባች የራሷንም ጠጉር ተላጭታ የምንኩስና ልብስን ለበሰች ከርሷ ጋር ያሉ ሽልማቶችንና ጌጦችን የወርቅ ልብሶችንም ሸጠችና በሰማእታት መጀመሪያ በከበረ እስጢፋኖስ ስም ቤተ ክርስቲያን ሰራች አባ ቴዎፍሎስም ብዞዎች ደናግል መነኮሳይያትን ሰበሰበላትና በዚያ ገዳም ከርሷ ጋር የሚኖር ሆኑ። ይቺም ቅድስት አክሳኒ ታላቅ ተጋድሎን ጀመረች እርሷ ከጥሬ ባቄላ በቀር በእሳት ያበሰሉትን አትቀምስና በምትተኛም ጊዜ ያለ ምንጠፍ በምድር ላይ ትተኛ ነበር እንዲህም እየተጋደለች ሀያ አመት ያህል ከዚያም የሚበዛ ኖረች ከዚህም በኃላ ጥቂት ታመመችና አረፈች። ልኡል እግዚአብሄርም የሰጣትን ልእልና ሊገልጥ ወደደ። በአረፈችበትም አለት ሰዎች በቀትር ጊዜ የብርሀን መስቀል በሰማይ ውስጥ አዩ ብርሀኑም የፀሀይን ብርሀን ሸፍኖ ነበር የሚያበሩ ከዋክብትም አክሊላትም በዙሩያው ሆነው ስጋዋን ከደናግል ስጋ ጋር እስከ አኖሩ ድረስ የሚያበሩ ሆኑ ከዚያም በኃላ ተሰወረ ይህም ስለርሷ እንደተገለጠ ህዝቡ አወቁ። በዚያንም ጊዜ እነዚያ ሁለቱ አገልጋዮቿ የዚችን ቅድስት አክሊኒ ከመጀመሪያው እስከ አረፍቷ ያለ ገድሏን ለሊቀ ጳጳሳቱና ለህዘቡ ሁሉ ስማቸውንም ለውጣ እህቶቿ እንዳለቻቸው እርሷንም እመቤታችን ማለት ሳይሆን እኅታችን እንዲሏት ምስጢሯንም ሁሉ እንዲሰውሩ እንዳማለቻቸው ተናገሩ። ሊቀ ጳጳሳቱና ህዝቡም ሁሉ አደነቁ ገድሏንም እስከመጨረሻ ፃፉ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_እስጢፋኖስ_ገዳማዊ በዚህችም ቀን ተጋዳይ የሆነ አባ እስጢፋኖስ አረፈ፡፡ ይህም ቅዱስ ቅዱሳን ገዳማውያንን በመፈለግ በበረሀ ውስጥ ሲዞር የወደቀች የሰው ራስ አገኘ እርሷም ስጋ የሌላት አጥንት ብቻ ናት። ስራዋንም ያስረዳው ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ለመነ በዚያንም ጊዜ ከዚያች ራስ ውስጥ እንዱህ የሚል ቃል ወጣ እኔ በብዝበዛ ጭምር የማተርፍ ነጋዴ ነበርኩ መመፅወትንም አላውቅም በእኔ ዘንድ ካለው የገንዘብ ብዛትም አልጠግብም ነበር በአንዲትም እለት ወደ ንግድ ሩቅ ወደ ሆነ አገር ስጓዝ ውኃ ወደ ሌለበት በረሀ ደረስኩ የቀን ሀሩርም በፀና ጊዜ ግመሎቼ ሞቱ ባሮቼም ሸሹ ብቻዩንም ቀረሁ። በሶስትኛውም ቀን አይኖቼ ከበዱኝ እንደፉጨትም ያለ ሰማሁ ያንጊዜ ነፍሴ ወጣች እንደስራዬም ቅጣቴን ልቀበል ወደ ስቃይ ቦታ ወሰዱኝ አንተም በለመንክ ጊዜ ስራዬን እነግርህ ዘንድ ወዳንተ አመጡኝ አሁንም ወደ ስቃይ ቦታ እንደይመልሱኝ እግዚአብሄርን ስለ እኔ ምህረትን ትለምነው ዘንድ እማልድሀለሁ አለው። ቅዱሱም ወደ እግዚአብሄር ስለርሱ ለመነለት በዚያንም ጊዜ ስለአንተ ምሬዋለሁ የሚል ቃልን ሰማ ይህንንም ሰምቶ ወደ በዓቱ ሄደ እስከ አረፈ ድረስም እያለቀሰና ደረቱን እየደቃ ኖረ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ታዴዎስ_ዘጽላልሽ በዚህች እለት አቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ በሰማእትነት አረፉ፡፡ አባታቸው ካህኑ ሮማንዮስ የደብረ ሊባኖሱ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጎት ሲሆኑ እናታቸው ማርታ ይባላሉ፡፡ የትልድ ቦታቸው ጽላልሽ ዞረሬ ነው፡፡ ሲወለዱ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ የታየ ሲሆን እርሳቸውም በብርሃን ልብስ ተጠቅልለው ታይተዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለሊቀ ካህናቱ ለሕይወት ብነ በጽዮን ተሰጥተው ሃይማኖትን በሚገባ ተምረዋል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዳሞት ተሻግረው ሞተሎሚን አስተምረው ካሳመኑት በኋላ አቡነ ታዴዮስን ወደ እርሳቸው እንዲመጡ ልከውባቸው ሄደው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ ዘጠኝ ዓመት ተቀመጡ፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ግን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አባ በጸሎተ ሚካኤል ሲሄዱ አቡነ ታዴዎስም ወደ ጽላልሽ ተመልሰዋል፡፡ ሁለቱም ከ32 ዓመት በኋላ ተመልሰው በጽላልሽ ተገናኘተው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአቡነ ታዴዎስ ማዕረገ ምንኩስናን ሰጥተዋቸዋል፡፡ አቡነ ታዴዎስም በሥጋ ዕድሜ ታላቅ ቢሆኑም እንደታናሽ ብላቴና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ በደብረ ሊባኖስ ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ታዴዎስን ወደ ጽጋጋ እንዲሄዱ ነገሯቸው ምክንያቱም አቡነ አኖሬዎስ በዚያ ሲያስተምሩ ከሃዲያን ደብድበው አስረዋቸው ነበር፡፡ እሳቸውም ታስረው ሳለ ወደ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘንድ የሚላካቸው ሲያስቡ ቁራ መጥቶ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ቢላቸው ‹‹ክፋትህ እንደ መልክህ ነው›› ብለው እምቢ አሉት፡፡ ርግብ መጥታ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ብትላቸው ‹‹መጥተህ አድነኝ›› ብለው በክንፏ ላይ ጽፈው ልከዋት እርሷም መልእክቱን ለተክለ ሃይማኖት አድሳ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው አቡነ ታዴዎስን ሕዝቡን ከኃጢአት ግዞት አኖሬዎስን ከእስራት እንዲያስፈቱ የላኳቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም በፋስ ሠረገላ ተጭነው መዩጥ ከተባለውና አኖርዮስን ካሰራቸው ንጉሥ ፊት ቢደርሱ ንጉሡ በግንጋጤ መልአክ የመጣበት መስሎት ሲፈራ ከሰው ወገን መሆናቸውን ነግረው ክርስትናን አስተማሩት፡፡ ጋኔን ከእሳት ጥሎት ሲሠቃይ የሚኖርና ሊሞት የደረሰ ልጁን ቢፈውሱለት በትምህርታቸውና በተአምራታቸው አምኖ ሕዝቡ ክርስትናን እንዲቀበል በአዋጅ አስነገረ፡፡ አፍጃል የሚባለው ባለጸጋ ወደ አቡነ ታዴዎስ ቀርቦ ሲማር ‹‹ባለጸጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል›› (ማቴ 19፡24፣ ማር 10፡25፣ ሉቃ 18፡25) የሚለውን የወንጌል ቃል ሲሰማ ለአእምሮው ረቆበት ‹‹እስቲ አድርገህ አሳየኝ?›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም እናቲቱን ግመል ከነጇ ቀጥሎም 28 ግመሎችን በየተራ በመርፌ ቀዳዳ እያሾለኩ

ቅዱስ ሲኖዶስ በነነዌ ጾም የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በነነዌ ጾም የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡

Watch "የጉባኤ ቃና መርሐ ግብር የመክፈቻ ቀን ላይ የተሰጠ ስብከት በመምህር የኋላሸት" on YouTube https://youtu.be/rAUUksD9lLw

በማግሥቱም አናጉንስጢሶችና መዘምራን ከዮሴፍ ጋር ተሰበሰቡ ልብሶቻቸውንም እንደ ድንኳንና እንደ መጋረጃ አምሳል በመሥራት ከቤታቸውም ዳቦ አመጡ በጨዋታ መልክ ከውስጣቸው ሊቀ ጳጳሳትን ኤጲስቆጶሳትን ሾሙና የቊርባን ሥርዓት ሠሩ ወደሚያስተምራቸውም መምህር ቤት ሔደው ይበሉ ይጠጡ ነበር እንዲህም እያደረጉ ኖሩ። የዮሴፍም አባት በሰማ ጊዜ ቊጣን ተመልቶ ልጁን የግንግሪት አሠረው በውስጡ እሳትን የተመላ ጉድጓድ ወዳለበት ወህኒ ወስዶ ጨመረውና በላዩ የእቶኑን በር ዘጋበት የእግዚአብሔርም መልአክ እሳቱን አቀዘቀዘው እናቱ ግን ልጅዋን በአጣችው ጊዜ በመጮህ አለቀሰች የምታደርገውንም አጣች። ከሰባት ቀኖችም በኋላ የዮሴፍን ወሬ ወደ እሳት እንደተጨመረ ባልንጀሮቹ ሰምተው በመጮህ እያለቀሱ ስሙንም እየጠሩ መጡ ዮሴፍም ከውስጥ እንዲህ ሲል መለሰላቸው በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት በእመቤቴ ማርያም ርዳታ እኔ በሕይወት አለሁና ወንድሞቼ አታልቅሱ እርሷም ከእሳቱ በልብሷ ሸፍና አድናኛለችና ይህንንም በሰሙ ጊዜ ለሊቀ ጳጳሳቱ ነገሩት። እርሱም ወዲያውኑ ተነሣ ከካህናቱ ጋር ወንጌልን መስቀልንና ማዕጠንቶችን ይዘው ሔዱ ወደ እቶኑም በደረሱ ጊዜ ጸሎትን አድርገው ዮሴፍን ከማሠሪያው ፈትተው አወጡት። አባቱ ማኅውም በሰማ ጊዜ መጥቶ ከሊቀ ጳጳሳቱ እግር በታች ወድቆ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመነ የክርስትና ጥምቀትንም ያጠምቀው ዘንድ ለመነውና ከቤተሰቦቹ ሁሉ ጋር አጠመቀው። ዮሴፍ ግን ከዋሻ ገብቶ በየሰባት ቀን እየጾመና እየጸለየ በገድል ተጠምዶ ሃያ ስምንት ዓመት ያህል ኖረ ከዚህም በኋላ ዕረፍቱ እንደቀረበ በአወቀ ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስ ወደሆነች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት ቁሞ ወደ ተወዳጅ ልጅዋ ትማልድለት ዘንድ ለመናት ከሥዕሉ ውስጥም እንዲህ አለቸው ዮሴፍ ሆይ በሦስተኛው ቀን በሦስት ሰዓት ወደኔ ትመጣለህና ደስ ይበልህ በዚያችም ዕለት በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ጥር_28 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ ስምንት በዚህች ቀን #ጌታችን_ተአምራትን በማድረግ ሰባት እንጀራና ጥቂት ዓሣ አበርክቶ ብዙ ሰዎችን ያጠገበበት መታሰቢያ ነው፣ የከበረ #ቅዱስ_ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ፣ #መነኰስ_ቅዱስ_አካውህ በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ አይሁዳዊ የማኀው ልጅ የእመቤታችን ወዳጅ #ቅዱስ_ዮሴፍ አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #የጌታ_ተአምር (ጌታችን 5 እንጀራ 2 ዓሣ አበርክቶ 5 የገበያ ሕዝብ እንደመገበ) ጥር ሃያ ስምንት በዚህች ቀን ጌታችን ተአምራትን በማድረግ ሰባት እንጀራና ጥቂት ዓሣ ቆራርሶ አበርክቶ ብዙ ሰዎችን ያጠገበበት መታሰቢያ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመዘገበው ይህ የጌታችን ተአምር በውስጡ ብዙ ምሥጢራትን የያዘ ነው እንጂ ስለ ሥጋዊ ምግብ ብቻ የተነገረ አይደለም፡፡ ማቴ 14፡13-23፡፡ የተመገቡትና የተቆጠሩት አምስት ሺህ ወንዶች ብቻ ናቸው እንጂ ሴቶችና ሕጻናት አልተቆጠሩም፡፡ ይህስ ለምን ነው ቢሉ ሴቶች በአደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው፡፡ ሕጻናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ይበዛልና ነው፡፡ ጌታችን ያንን ሁሉ ሕዝብ በመንደር አጠገብ ሊመግባቸው ሲችል ለምን አርቆ ወደ ምድረ በዳ ወሰዳቸው ከተባለ ስለ ሁለት ምክንያት ነው፡፡ አንድም ‹‹ጥንት አባቶቻችሁን ከመንደር (ከግብጽ) አውጥቼ አርባ ዘመን ሙሉ መና የመገብኳቸው እኔ ነኝ፤ አሁንም በሥልጣኔ በተአምራቴ መገብኳችሁ›› ሲላቸው ነው፡፡ አንድም ጌታችን ተአምራቱን ከመንደር አጠገብ አድርጎት ቢሆን ኖሮ ሁልጊዜ ክፋትንና ጠማማ ነገርን ማሰብ ለአይሁድ ልማዳቸው ነውና ‹‹ፈጣን ፈጣን ደቀ መዛሙርቱን በጎን ወደ መንደር እየላከ ያስመጣው ነው›› ይሉት ነበር፡፡ ስለሆነም ጌታችን ለጥርጥር ምክንያት እንዳይኖራቸው አድርጎ ነው ተአምራቱን የገለጠላቸው፡፡ ጊዜውም አመሻሽ ላይ ነበርና ምሽት ላይ ያደረገበትም ምክንያት ጠዋት ላይ ቢሆን ኖሮ ‹‹የበላነው ሳይጎድል ነው ያበላን›› ብለው ከማመን ይርቁ ነበር፡፡ በተጨማሪም በበረሃ ያውም በምሽት ሕዝቡን በውኃ አጠገብ በሣር ላይ አስቀምጧቸው መመገቡ ‹‹በፍጻሜው ዘመን በምቹ ስፍራ በመንግሥተ ሰማያት መንፈሳዊ ምግብ እመግባችኋለሁ፤ በውኃ (በጥምቀት) በሚገኝ ክብርም አከብራችኋለሁ›› ሲላቸው ነው፡፡ ተአምራቱን ከውኃ ዳር ማድረጉ ‹‹መታጠቢያ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን›› እንዳይሉ ነው፡፡ ሳር የበዛበት ቦታ ላይ ማድረጉም ‹‹መቀመጫ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን›› እንዳይሉ ነው፡፡ አምስቱ እንጀራ የአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ማለትም የምሥጢረ ሥላሴ፣ የምሥጢረ ሥጋዌ፣ የምሥጢረ ጥምቀት፣ የምሥጢረ ቁርባንና የምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ሁለቱ ዓሣ ደግሞ የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢጽ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ፍቅረ እግዚአብሔር ማለት እግዚአብሔር አምላክን በፍጹም ነፍስና በፍጹም ሐሳብ መውደድ ነው፡፡ ፍቅረ ቢጽ ደግሞ ባልንጀራን እንደራስ አድርጎ መውደድ ነው፡፡ አንድም ደግሞ እንጀራውና ዓሣው የቅዱስ ሥጋውና የክቡር ደሙ ምሳሌ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቀሌምንጦስ_ሰማዕት በዚህች ቀን ኪራስ ከሚባል አገር ስሟ አክሮስያ የምትባል የመበለት ልጅ የከበረ ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም የሆነ በገላትያ ነገሥት በአርአያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ አስተማረችው ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው በጾምና በጸሎት መጋደል ጀመረ አገልግሎትንም አበዛ በእሳት የበሰለ ሥጋም ቢሆን አይበላም ነበር። እንደ ሠልስቱ ደቂቅ ጥሬ ባቄላ የሚመገብ ሆነ እንጂ ዲቁናም ተሾመ ጥበብና እውቀትም ተጨመረለት። ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ በተሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀርቦ ብዙ ሸነገለው ለርሱም ልጁ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ትእዛዙንም ባልሰማ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው እግዚአብሔርም አጸናው ያለ ጉዳትም በጤንነት አስነሣው ከሀድያንንም አሳፈራቸው። በዚያንም ጊዜ የምስክርነቱ ተጋድሎ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰባት እስቲደርስ አንድ ተብሎ ተቈጠረለት። ማሠቃየቱንም በደከመ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ወደ ሮም ንጉሥ ላከው እንዲህም ብሎ ጻፈ ይህ መሠርይ ከቶ እንደርሱ ያለ መሠርይ አላየሁም ለአማልክትም ይሠዋ ዘንድ ምናልባት ልቡን መመለስ ብትችል እነሆ ወዳንተ ላክሁት። ወደ ሮሜው ንጉሥም በደረሰ ጊዜ የወርቅ ልብሶችን አመጡለት እርሱም ወደ ልብሶች አልተመለከተም ንጉሡም በእርሱ ላይ ተቆጣ ቊጣውንም አልፈራም በዚያንም ጊዜ በመንኰራኵር ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው ገረፈውም ሕዋሳቱንም አስቆራረጠ እግዚአብሔርም እንደ ቀድሞው ያለ ጥፋት በጤንነት አስነሣው ይህም ሁለተኛ ምስክርነት ነው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ወደ መክስምያኖስ ላከው በዚያም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት ጌታችንም እንደቀድሞው በጤንነት አስነሥቶት ጠላቶቹን አሳፈራቸው ይህም ሦስተኛ ምስክርነት ነው። ከዚህም በኋላ ወደ አደገባት ወደ ኪራስ ከተማ መለሱት በዚያም አሠቃዩት ጌታችንም በጤንነት ያለሥቃይ አስነሣው ይህም አራተኛ ምስክርነት ነው። ዳግመኛም ወደ መክስምያኖስ መለሱት በዚያም ቅዱስ ከልከላዎስንና ብዙ ሰማዕታትን አግኝቶ እርስ በርሳቸው ተጽናኑ የከበረ ቀሌምንጦስንም ጽኑ ሥቃይን አሠቀዩት ጌታችንም እንደቀድሞው አዳነው ይህም አምስተኛ ምስክርነት ነው። ከዚህም በኋላ ወደ መኰንን ሉቅዮስ ወሰዱትና በዚያ አሠቃዩት ጌታችንም አዳነው ይህም ስድስተኛው ምስክርነት ነው። ሰባተኛውም ምስክርነት ብዙ ከአሠቃዩት በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡ ሶፍያ የምትባል አማኒት ሴት መጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወስዳ ገንዛ ቀበረችው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አካውህ_ሰማዕት በዚህችም ቀን የከበረ መነኰስ አካውህ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ ፍዩም ከሚባል አገር ነው በምንኵስናውም ታላቅ ተጋድሎን ሲጋደል የኖረ ነው ሰይጣንም ተገልጦ መጣበት ቅዱስ አካውህም ሰይጣንን ይዞ በራሱ ጠጉር አሠረውና ሊቀጣው ጀመረ። ሰይጣንም ትለቀኝ ዘንድ በክርስቶስ መከራዎች አምልሃለሁ ብሎ ጮኸ በዚያንም ጊዜ ሰደደው እንደ ጢስም ተበተነ። ከዚህም በኋላ በስደት ወራት ወደ ከሀድያን አደባባይ ሔደና እኔ ክርስቲያን ነኝ ብሎ ጮኸ ከሀድያንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃይተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ከእርሱም ጋር ስምንት መቶ የሆኑ የቅዱስ አካውህ መኅበር በሰማዕትነት ሞቱ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ዮሴፍ_አይሁዳዊ (የእመቤታችን ወዳጅ) በዚህችም ቀን የከበረ አይሁዳዊ የማኀው ልጅ ዮሴፍ አረፈ። ይህም ቅዱስ እስራኤላዊ ነው የአይሁድንም ሃይማኖት እየተማረ አደገ መጻሕፍቶቻቸውንም ተማረ። በአንዲትም ዕለት እየተማሩ ሳለ የክርስቲያንን ልጆች አያቸው ከእርሳቸውም ጋር ትደምረው ዘንድ እናቱን ለመናት። በደመረችውም ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ሁሉ ተማረ የክርስቶስ ሃይማኖት ፍቅርም በልቡ አደረ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ ከሚወድና ከሚጠብቅ ከአንድ ክርስቲያናዊ ወጣት ጋር ተገናኘ እርሱም በቊርባን ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰደው ዮሴፍም ሥጋውንና ደሙን ተቀበለ።