የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
前往频道在 Telegram
2 641
订阅者
+224 小时
+157 天
+5530 天
帖子存档
እንኳን ለበዐለ ጰራቅሊጦስ አደረሳችሁ 27/9/2015
ዛሬ መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ‹‹ ሚመጠን ግርምት ሃቲ ዕለት ወዕፅብት ሃቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት፤ ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚውርድባት›› እንዲል መጽሐፈ ሥርዓተ ቅዳሴ፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደወረደላቸው ለእኛም እነዲወርድልን ሁልጊዜ ቤተክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም፡፡
ቤተክርስቲያን፡- የመንግስተ ሰማያት በር ናት፡፡ ‹‹ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ፤ ይህች የሰማይ ደጅ ናትና›› /ዘፍ 28÷17/ እንዲል፡፡
እንግዲህ በዓለ ጰራቅሊጦስ እኛ ክርስቲያኖች የምናከበረው እንደ ሐዋርያት ምስጢር እንዲገልጥልን፣ እንዲያረጋጋን፣ ይቅር እንዲለን፣ እንዲያጽናናን፣ ደስታን እንዲሰጠን ነውና ሁላችንም ከዚህ በረከት የታደልን እንድንሆን በዓሉን በንጽሕና በቅድስና ሆነን፤ ነጭ ልብስ ለብሰን፣ በሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ ቅዳሴ በማድቀደስ፤ በዕለቱ በጎ ሥራን በመስራት፣ በአርባና በሰማንያ ቀን የተሰጠንን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡
ዛሬ መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት እየሩስአሌም ቤተክርስቲያን ናት ‹‹ ሚመጠን ግርምት ሃቲ ዕለት ወዕፅብት ሃቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት፤ ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚውርድባት›› እንዲል መጽሐፈ ሥርዓተ ቅዳሴ፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደወረደላቸው ለእኛም እነዲወርድልን ሁልጊዜ ቤተክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም፡፡
ቤተክርስቲያን፡- የመንግስተ ሰማያት በር ናት፡፡ ‹‹ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ፤ ይህች የሰማይ ደጅ ናትና›› /ዘፍ 28÷17/ እንዲል፡፡
እንግዲህ በዓለ ጰራቅሊጦስ እኛ ክርስቲያኖች የምናከበረው እንደ ሐዋርያት ምስጢር እንዲገልጥልን፣ እንዲያረጋጋን፣ ይቅር እንዲለን፣ እንዲያጽናናን፣ ደስታን እንዲሰጠን ነውና ሁላችንም ከዚህ በረከት የታደልን እንድንሆን በዓሉን በንጽሕና በቅድስና ሆነን፤ ነጭ ልብስ ለብሰን፣ በሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ ቅዳሴ በማድቀደስ፤ በዕለቱ በጎ ሥራን በመስራት፣ በአርባና በሰማንያ ቀን የተሰጠንን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡
#ሐዋርያት_በበዓለ_ኃምሳ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ በተነሳ በ40ኛው ቀን ወደ ሰማይ ሲያርግ አስቀድሞ ለደቀመዛሙርቱ በ“ ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ “ ብሎ በአዘዛቸው መሠረት ከዚያች ዕለት ጀምረው “ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ በመቅደስ ኖሩ “ ሉቃ 24፡-49 - 53
ደቀ መዛሙርቱ አስርዋን ቀን በጾምና በጸሎት በአንድ ልብ ሆነው እየተጉ ቆዩ፡፡ ሐዋ 13-14 ያሳለፉትም በማርቆስ እናት ቤት በጽርሐ ጽዮን ነበር፡፡ በነዚህ አስር ቀናት ሰማያዊ ክብሩን ለገንዘብ ብሎ በሸጠው በአስቆሮቱ ይሁዳ ምትክ ማትያስ ተተክቷል ፡፡ በዚህም
“ሹመቱን ሌላ ይውሰዳት“ ብሎ በነብዩ በዳዊት ቃል የተነገረው ተፈጽሟል፡፡ መዝ 108 ፡8 ጌታችን በዐረገ በአስረኛው ቀን በይሁድ በዓለ ኃምሳ በማርቆስ እናት ቤት ጽርሐ ጽዮን በአንድ ልብ ሆነው በጸሎት ላይ እናዳሉ የሚነጥቅ አውሎ ነፋስ የመሰለ ድምጽ ከሰማይ መጣ የተቀመጡበትንም ቤት ሞላው እንደ እሳት የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩዋቸው ከዚያም በእያንዳንዳቸው ላይ ተቀመጡባቸው “ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ “ በማለት ጌታ ተፈጸመ፡፡ ሐዋ 1፡-5
#ሐዋርያት_በበዓለ_ኃምሳ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ በተነሳ በ40ኛው ቀን ወደ ሰማይ ሲያርግ አስቀድሞ ለደቀመዛሙርቱ በ“ ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ “ ብሎ በአዘዛቸው መሠረት ከዚያች ዕለት ጀምረው “ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ በመቅደስ ኖሩ “ ሉቃ 24፡-49 - 53
ደቀ መዛሙርቱ አስርዋን ቀን በጾምና በጸሎት በአንድ ልብ ሆነው እየተጉ ቆዩ፡፡ ሐዋ 13-14 ያሳለፉትም በማርቆስ እናት ቤት በጽርሐ ጽዮን ነበር፡፡ በነዚህ አስር ቀናት ሰማያዊ ክብሩን ለገንዘብ ብሎ በሸጠው በአስቆሮቱ ይሁዳ ምትክ ማትያስ ተተክቷል ፡፡ በዚህም
“ሹመቱን ሌላ ይውሰዳት“ ብሎ በነብዩ በዳዊት ቃል የተነገረው ተፈጽሟል፡፡ መዝ 108 ፡8 ጌታችን በዐረገ በአስረኛው ቀን በይሁድ በዓለ ኃምሳ በማርቆስ እናት ቤት ጽርሐ ጽዮን በአንድ ልብ ሆነው በጸሎት ላይ እናዳሉ የሚነጥቅ አውሎ ነፋስ የመሰለ ድምጽ ከሰማይ መጣ የተቀመጡበትንም ቤት ሞላው እንደ እሳት የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩዋቸው ከዚያም በእያንዳንዳቸው ላይ ተቀመጡባቸው “ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ “ በማለት ጌታ ተፈጸመ፡፡ ሐዋ 1፡-5
በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ
ይህች ታላቅ ዕለት ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል የሆነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለቅዱሳን ሐዋርያት፣ ለቅዱሳን አርድእትና ለቅዱሳት አንስት የተገለጠባት ዕለት ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ በጸሎት ተግተው በሚጸልዩበት ወራት መንፈስ ቅዱስ በተከፋፈሉ የእሳት ልሳን አምሳል የወረደበት ቅዱስ ቀን ነው፡፡ አስቀድሞ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት ደብረ ዘይት በተባለ ታላቅ ተራራ ላይ ሳሉ እንዲህ ብሎ አስተምሯቸው ነበር “ኃይልን ከአርያም እስክልክላችሁ ድረስ በኢየሩሳሌም በጸሎት ቆዩ፡፡”/ሉቃ 24፡36/ መቶ ሃያው ቤተሰብም በኢየሩሳሌም ሀገር በምትገኝ በቤተ መቅደስ በአንድነት ሆነው በጸሎት በመትጋት ቆዩ፡፡ 120ው ቤተሰብ የሚባሉት 12ቱ ሐዋርያት፣ 72ቱ አርድእት/አገልጋዮች/ እና 36ቱ ቅዱሳን አንስት/ሴቶች/ ናቸው፡፡
ከዕርገት በኋላ በአሥረኛው ቀን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያት ወዳሉበት፣ በጸሎትና በምሥጋና ወደ ሚተጉበት ሥፍራ በእሳት አምሳል /ምሳሌ/ ወርዶ በእያንዳንዳቸው ላይ ተቀመጠባቸው፡፡ ይሄንንም ሁኔታ ተከትሎ ምስጢር ተገለጠላቸው፣ ይፈሩ የነበሩት ሐዋርያትም ወንጌልን ለማስተማር ደፋሮች ሆኑ፣ በተለያየ ቋንቋዎች እንዲናገሩ እውቀት ተሰጣቸው፤ የእግዚአብሔርንም ጸጋ ተቀበሉ፡፡ ይህንን ታላቅ ኀይል እና ሰማያዊ ስጦታን የሰጣቸውን እግዚአብሔርን በታላቅ ዝማሬና እልልታ አመሰገኑት፡፡
በዚያም ዕለት በዓለ ሃምሳ የሚባለውን የአይሁድን በዓል ለማክበር ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ቁጥራቸው በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የሐዋርያቱን ታላቅ የዝማሬና የእልልታ ድምፅ ሰሙ፡፡ ከመቶ ሃያው ቤተሰብ መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ የተሰበሰቡት ሁሉም እንዲሰሙት ድምፁን ከፍ አድርጎ ቃለ እግዚአብሔርን እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፡፡ “እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ እኛን የሰው ልጆችን ለማዳን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር መጥቶ ከክፉ ሥራ ተመለሱ፣ ኀጢአትን አታድርጉ፣ በቅድስና ኑሩ፣ ወደ እኔም ተመለሱ ቢላችሁ፤ እናንተ ግን ምንም በደል ሳይኖርበት ገረፋችሁት፣ አንገላታችሁት፣ በመስቀል ላይም ሰቀላችሁት፡፡ እርሱ ግን እግዚአብሔር ነውና ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፡፡ እርሱ ግን አሁንም ይቅር ባይ ነውና ከኀጢአታችሁ ተመለሱ ንስሐም ግቡ፡፡” በማለት አስተማራቸው፡፡ የተሰበሰቡት ሰዎች ሁሉ ተገረሙ፡፡ ምክንያቱም ሐዋርያት በፊት የሚያውቁት አንድ ቋንቋ ብቻ ነበረ፡፡ በዚህ ሰዓት ግን ሰባ ሁለት ቋንቋን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ገልጦላቸው ለሁሉም በየቋንቋቸው አስተማሯቸው፡፡ ይህንንም ድንቅ ተአምር ከተመለከቱት ብዙዎች እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ወደ ሐዋርያትም ቀርበው “አባቶቻችን እናንተ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናችሁና ምከሩን፡፡ እንደ እናንተ የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆንና በቅድስና እንድንኖር ምን እናድርግ?” በማለት ጠየቁ፡ በዚያች ቀን ቁጥራቸው ሦስት ሺ ያህል ሰዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት አምነው ክርስቲያን ለመሆን ቀረቡ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፡፡ “እነሆ ሁላችሁም ንስሐ ግቡ፡፡ በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት አምናችሁ ተጠመቁ፡፡” አላቸው በዚያው ዕለትም ሦስት ሺ ሰዎች ወደ ሐዋርያት በመቅረብ ኀጢአታቸውን ተናገሩ፤ ሐዋርያትም እግዚአብሔር ይፍታችሁ እያሉ ልጅነትን የሚያሰጣቸውን ጥምቀት አጠመቁዋቸው፡፡
ከዚያ ቀን ጀምሮም በየዓመቱ ይህችን ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን የምትባለውን በዓለ ጰራቅሊጦስን ክርስቲያኖች በታላቅ ደስታና ምሥጋና እናከብራታለን፡፡
በጽርሐ ፅዮን የወረደው የአብ በረከት፣ የወልድ ፍቅር ፣ የመንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችንም ጋር ይሁን!!https://t.me/finotebirhan12
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
