የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
前往频道在 Telegram
2 624
订阅者
+424 小时
+267 天
+4230 天
帖子存档
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የምዘና ፈተና የወሰዱ #የ4ኛ ፣ #የ6ኛ እና #የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት የእውቅና እና የቡራኬ መርሐ ግብር ተከናወነ።
ታኅሣሥ 06/04/2016 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የምዘና ፈተና የወሰዱ ቁጥራቸው 6209 የሚሆኑ የ4ኛ ፣ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ዛሬ ታኅሣሥ 06 2017 ዓ.ም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔ ዓለም ወመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ ካቴድራል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፤ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች ፣ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በተገኙበት የእውቅና እና የቡራኬ መርሐ ግብሩ ተከናውኗል።
መርሐ ግብሩ በቅዱስ ፓትርያርኩ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን ከጸሎቱ በማስቀጠል ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ "ሰንበት ተማሪዎች ዋነኛ የቤተ ክርስቲያን ተተኪ መሆናቸው ታውቆ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛል፤ ሰንበት ተማሪው ከበዓል አድማቂነት ወጥቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የሚያውቅና የሚጠብቅ እንዲሆን እንረባረባለን በተጨማሪም በከተማው የሚገኙ ወጣቶች ሁሉ በሰንበት ት/ቤቶች እስኪታቀፉ እንሠራለን።" በማለት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " ልጅህን በሚሔድበት መንገድ ምራው በሸመገለ ጊዜ ከሱ ፈቀቅ አይልም" የሚል አምላካዊ ቃልን መነሻ በማድረግ አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል። ሀገረ ስብከቱም ለአንድነቱ ከዚህ የበለጠ እገዛ እንደሚያደርግ ብጹዕ አባታችን ቃል ገብተዋል።
በቅዱስነታቸው መልካም ፈቃድ የዕለቱን ቃለ እግዚአብሔር ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ
"ይህንን እዘዝና አስተምር በቃልም በተግባርም በእምነትም ለሚያምኑ ምሳሌ ሁን እንጂ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው።(1ኛ ጢሞ 4÷12) መነሻ በማድረግ " ማንም ታናሽነታቹሁን አይናቀው የቤተ ክርስቲያን ተተኪ ናችሁ ብለው ቃለ ወንጌል ሰጥተዋል።
በመቀጠልም ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ " ሥርዓተ ትምህርቱ ነገ ሀገርና ቤተ ክርስቲያን ተስፋ የምትጥልባቸውን ሕጻናትና ወጣቶች በኹለት በኩል የተሳሉ ሰይፍ እንዲሆኑ የሚሠራ ወጥነት ያለው ነው። ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ሊተገብሩት ይገባል ብለዋል። የታተሙትንና ስርጭት ላይ የሚገኙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍትንም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ገዝተው ይጠቀሙ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ "በዚህ ዕድሜያቹ የቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት በማወቃቹ ለቤተ ክርስቲያን ዘብ መቆም የምትችሉ የቤተ ክርስቲያን የጀርባ አጥንት ናችሁ በሃይማኖት ጽኑ" በማለት አባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች የሜዳልያ ሽልማት ፤ ምዘናውን ላስፈተኑ 121 ሰንበት ትምህርት ቤቶች ፤ በትምህርት አሰጣጥ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የክፍለ ከተማ አንድነት ትምህርት ክፍሎች እንዲሁም ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት ከቅዱስነታቸው እጅ ቡራኬ ተቀብለዋል።
© የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
⚜💫🌺⚜💫🌺⚜💫🌺💫⚜🌺⚜🌺⚜💫🌺💫⚜🌺💫⚜🌺⚜🌺
" ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ " {መዝ 117 ÷ 26}
#የ2016_ዓ_ም_የተማሪዎች_የምርቃት_መርሐግብር
⚜💫🌺⚜💫🌺⚜💫🌺💫⚜🌺⚜🌺⚜💫🌺💫⚜🌺💫⚜🌺⚜🌺
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአ/አ/ሰ/ት/ቤቶች አንድነት #ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም #በ4ኛ ፣ #በ6ኛ እና #በ10ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ተማሪዎች ዕውቅና የመስጠት መርሐ ግብር።
🗓እሑድ ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም
⏰ከቀኑ 6:30 ጀምሮ
💒በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም እና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ ካቴድራል
⚜💫🌺⚜💫🌺⚜💫🌺💫⚜🌺⚜🌺⚜💫🌺💫⚜🌺💫⚜🌺⚜🌺
#በመርሐግብሩ_ላይ 👇
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤ ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመሪያው ኃላፊዎች ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና የክፍለ ከተማ ቤተክህነት የየክፍሉ ኃላፊዎች ፤ የደብራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፤ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አባቶች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ የየሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር አባላቶች ፤ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች እንዲሁም ምዕመናን/ት ይገኛሉ።
#ኑ_ተማሪዎቻችን_በጋራ_እንመርቅ!!!
#የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
እንኳን ለሐዋርያዊ እንድርያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።
©የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
እንኳን ለሐዋርያዊ እንድርያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።
የቅዳሜ መደበኛ ትምህርት ታህሳስ 4/2017 ዓ.ም ከ11:30 ጀምሮ በጠበል ቤት አዳራሽ ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት ይሰጣል እኛም በሰዓቱ በመገኘት ትምህርቱን እንድንማር ተጋብዘናል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+ ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያረዝሙ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለሽም በቅድስናና በንጽሕና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ።
+ ድንግል ሆይ ምድራዊ ሕብስትን የተመገብሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ሕብስትን እንጂ።
+ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን እንጂ። (ቅዳሴ ማርያም)
ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን ሀገራችን ኢትዮጵያንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን ። አሜን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም
ታኅሣሥ ሦስት በዚህች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ነው ። እርሷ ለእግዚአብሔር የስእለት ልጅ ነበረችና።
እናቷ ቅድስት ሐና ልጅ የሌላት ስለሆነች በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከሴቶች ተለይታ ርቃ ትኖር ነበር ሽማግሌ ከሆነ ከኢያቄም ከባሏ ጋርም እጅግ የምታዝን ሆነች ። እግዚአብሔርም ኀዘናቸውን ሰማ ቅድስት ሐናም እንዲህ ብላ ለእግዚአብሔር ተሳለች የሰጠኸኝን ፍሬ ለእግዚአብሔር አገልጋይ አደርጋለሁ ።
ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምንም በወለደቻት ጊዜ ሦስት ዓመት በቤቷ ውስጥ አሳደገቻት ከዚህም በኋላ ከደናግል ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደቻት በቤተ መቅደስም ምግቧን ከመላእክት እጅ እየተቀበለች ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቶ ከእርሷ ሥጋን እስከ ነሣ ድረስ።
ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን ሀገራችን ኢትዮጵያንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን ። አሜን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የሉቃስ ወንጌልን ንባብ እንደጀምሩ እናምናለን በቀጣይ የማርቆስ ወንጌልን ለማስታወስ ጥያቄ ይኖረናል ይዘጋጁ የሉቃስ ወንጌልን ግን ማንበብ ይቀጥሉ መልካም የንባብ ጊዜ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
''ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት ''
ክፍል -2
በዲ/ን ዳዊት ብርሃኑ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
የፊታችን ቅዳሜ ኅዳር 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የማርቆስ ወንጌልን ንባብ በተሰጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እንዳነበቡ እናምናለን ።አሁን ደግሞ የሉቃስ ወንጌልን ማንበብ እንጀምር መልካም የንባብ ጊዜ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
አቡነ ተክለ ሃይማኖት
አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥሉስ ቅዱስን መንበር እንዳጠኑ፡- አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦላቸው ነው በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ የነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም መልአኩን ተከትለው ሐይቁን በእግራቸው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመንኩሰዋቸዋል፡፡
ከዚህም በኋላ አባታችን በዚያው በሐይቅ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ አክፍሎትንም በየሳምንቱ ያከፍላሉ፣ ከእሑድና ከቅዳሜ በቀር ምንም አይቀምሱም ነበር፡፡ በእነዚህም ዕለት የአጃ ቂጣ ወይም የዱር ቅጠል ይመገቡ ነበር፡፡ ወዛቸው እንደ ውኃ ፈስሶ ምድሪቷን እስኪያርሳት ድረስ እስከ 70 ሺህ ስግደትንም በመስገድ ራሳቸውን እጅግ አደከሙ፡፡ በእንደዚህ ዓይነቱ ተጋድሎ ላይ ሳሉ ነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ድንገት ነጥቆ ወስዶ ከሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ያቆማቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ስለሆነው ነገር ራሳቸው አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሲናገሩ ‹‹…ከዚህ በኋላ መልአኩ ወደ ሰማይ አውጥቶ ከመጋረጃው ውስጥ አስገብቶ ከሥላሴ ዙፋን ፊት አቆመኝና ሰገድኩለት፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በማላውቀው በሌላ ምስጋና አመሰገንኩት፡፡ ‹ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከ24ቱ ካህናቶቼ ጋር ይሁን› የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ፡፡ የወርቅ ጽና አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር አንድነት አጠንሁ፡፡ ምስጋናዬ ከምስጋናቸው ጋር ልብሴም እንደልብሳቸው ሆነ፡፡ ፈጣሪዬንም በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት፡፡ በጸሎትህ የሚታመን ሰው ሁሉ ስለአንተ ይድናል አለኝ…..›› (ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገጽ 216-223)
ይህንን ታላቅ በዓል ነው ዛሬ የምናከብረው፡፡
የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በረከታቸው ይደርብን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
24ቱ ካህናተ ሰማይ
ኅዳር ሃያ አራት በዚህች ቀን በእግዚአብሔር ዙፋን ዙሪያ የሚኖሩ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የበዓላቸው መታሰቢያ ነው ።
እሊህም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን የእውነት ካህናት የሆኑ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ የሆኑና ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከፍ ከፍ ያሉ ናቸው እነርሱም ለእግዚአብሔር ቀራቢዎች በመሆን ለሰው ወገን የሚማልዱ ከእጃቸው ውስጥ ካለ ማዕጠንት ጋር እንደ ዕጣን የቅዱሳንን ጸሎት የሚያቀርቡ ናቸው ያለእነርሱም አቅራቢነት ጽድቅና ምጽዋት ወደ እግዙአብሔር አይቀርብም።
ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንዲህ ብሎ እንደተናገረ። በዙፋኑ ዙሪያ ሃያ አራት መንበሮች አሉ በእነዚያ መንበሮች ላይም ሃያ አራት አለቆች ተቀምጠዋል ነጭ ልብስ ለብሰዋል በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል አለ።
ሁለተኛም እንዲህ አለ ሌላም መልአክ መጥቶ በመሠዊያው ፊት ቆሞ የወርቅ ጽንሐሕ ይዟል በመንበሩ ፊት ባለ በወርቁ መሠዊያ ላይም የቅዱሳንን ሁሉ ጸሎት ያሳርግ ዘንድ ብዙ ዕጣንን ሰጡት ። የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር በዚያ መልአክ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ዐረገ ።
የነበረ የሚኖር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ነው እያሉ በመዓልትና በሌሊት ዕረፍት የላቸውም ። እሊህም ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆን በዙፋን ላይ ለተቀመጠ እያሉ ክብር ምስጋና አቀረቡ ።
እሊህ ሃያ አራቱ አለቆች አክሊላቸውን በዙፋኑ ፊት አውርደው ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆኑ በዙፋን ላይ ለተቀመጠ ለእሱ ሰገዱለት ። አክሊላቸውንም ወደ ዙፋኑ ፊት ወስደው አቤቱ ፈጣሪያችን ኃይልና ምስጋና ክብር ላንተ ይገባል ይሉታል አንተ ሁሉን ፈጥረሃል የተፈጠረውም ሁሉ በአንተ ፈቃድ ይኖራልና ።
እነርሱ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት እጅግ የቀረቡ መሆናቸውንና ስለሁላችን የአዳም ልጆች ስለሚለምኑና ስለሚማልዱ ከብሉይና ከሐዲስ የከበሩ መጻሕፍት ምስክር ሁነዋል ስለዚህም የበዓላቸውን መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ ።
ረድኤታቸው አይለየን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
24ቱ ካህናተ ሰማይ
ኅዳር ሃያ አራት በዚህች ቀን በእግዚአብሔር ዙፋን ዙሪያ የሚኖሩ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የበዓላቸው መታሰቢያ ነው ።
እሊህም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን የእውነት ካህናት የሆኑ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ የሆኑና ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከፍ ከፍ ያሉ ናቸው እነርሱም ለእግዚአብሔር ቀራቢዎች በመሆን ለሰው ወገን የሚማልዱ ከእጃቸው ውስጥ ካለ ማዕጠንት ጋር እንደ ዕጣን የቅዱሳንን ጸሎት የሚያቀርቡ ናቸው ያለእነርሱም አቅራቢነት ጽድቅና ምጽዋት ወደ እግዙአብሔር አይቀርብም።
ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንዲህ ብሎ እንደተናገረ። በዙፋኑ ዙሪያ ሃያ አራት መንበሮች አሉ በእነዚያ መንበሮች ላይም ሃያ አራት አለቆች ተቀምጠዋል ነጭ ልብስ ለብሰዋል በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል አለ።
ሁለተኛም እንዲህ አለ ሌላም መልአክ መጥቶ በመሠዊያው ፊት ቆሞ የወርቅ ጽንሐሕ ይዟል በመንበሩ ፊት ባለ በወርቁ መሠዊያ ላይም የቅዱሳንን ሁሉ ጸሎት ያሳርግ ዘንድ ብዙ ዕጣንን ሰጡት ። የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር በዚያ መልአክ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ዐረገ ።
የነበረ የሚኖር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ነው እያሉ በመዓልትና በሌሊት ዕረፍት የላቸውም ። እሊህም ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆን በዙፋን ላይ ለተቀመጠ እያሉ ክብር ምስጋና አቀረቡ ።
እሊህ ሃያ አራቱ አለቆች አክሊላቸውን በዙፋኑ ፊት አውርደው ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆኑ በዙፋን ላይ ለተቀመጠ ለእሱ ሰገዱለት ። አክሊላቸውንም ወደ ዙፋኑ ፊት ወስደው አቤቱ ፈጣሪያችን ኃይልና ምስጋና ክብር ላንተ ይገባል ይሉታል አንተ ሁሉን ፈጥረሃል የተፈጠረውም ሁሉ በአንተ ፈቃድ ይኖራልና ።
እነርሱ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት እጅግ የቀረቡ መሆናቸውንና ስለሁላችን የአዳም ልጆች ስለሚለምኑና ስለሚማልዱ ከብሉይና ከሐዲስ የከበሩ መጻሕፍት ምስክር ሁነዋል ስለዚህም የበዓላቸውን መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ ።
ረድኤታቸው አይለየን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
