ch
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

前往频道在 Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

显示更多
2 610
订阅者
+524 小时
+127
+3030
帖子存档
'' ዘመነ ጽጌ '' በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት01/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይም
'' ዘመነ ጽጌ ''                      በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር  የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት01/2018 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ መስከረም 29 በዚችም ቀን ቅድስት አርሴማና እመምኔቷ አጋታ ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ። ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ። እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ። ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው። ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት። የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው። ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ። አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ። ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። የቅዱሳን ሰማዕታት ረድኤት በረከት በሁላችንም ላይ ይደር!!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። "ከናፍረ ጻድቃን ያረትዓ ስምዐ፤ ወሰማዕት ጕጉእ ቦ ልሳን እኩይ፦ የጻድቃን ከንፈሮች ምስክርነትን ያቀናሉ፤ የሚቸኩል ምስክር ግን ክፉ አንደበት አለው።" ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ላለፉት ተከታታይ ዓመታት ወደ ሰሜን አሜሪካ በማምራት የሕክምና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡም ተመሳሳይ ጉዞ አድርገው ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓመተ ምሕረት ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ በታላቅ ክብር መመለሳቸው ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ርእሰ ዐውደ ዓመትን በማስመልከት ለመላው ኢትዮጵያውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው አባታዊ ቃለ በረከትና ቡራኬ በመገናኛ ብዙኃን አስተላልፈዋል፤ የመስቀል ደመራ በዓልንም በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በማክበር ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን አባታዊ ትምህርተ ወንጌል፣ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል፤ ቤተ ክርስቲያናችን በየዕለቱ የምታከናውናቸው መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ እና ዓለም አቀፍ ተግባራትንም በጽሕፈት ቤታቸው ሆነው በአባትነት እየመሩ በተሟላ ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ ድብቅ አጀንዳ ይዘው ሐሰተኛ መረጃን በማሰራጨት መደበኛውን የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማደናቀፍ ዓላማቸው ያደረጉ አካላት በማኅበራዊ የትስስር ገጾቻቸው ባጋሩት ፍጹም ከእውነት የራቀ መረጃ ውሉደ ክህነት እና በጎ ሕሊና ያላቸው ምእመናን በእጅጉ መጨነቃቸውን ለመገንዘብ ችለናል። ስለሆነም ቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ተግባራትን ለመምራትም ሆነ ለማከናወን የማያስችል ምንም ዓይነት የጤና እክል ያልገጠማቸው፤  ከዚሁ ጋር በተያያዘም ያቀረቡት የእንደራሴ ጥያቄ የሌለ መሆኑን እንገልጻለን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!! አሜን። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት መስከረም 28 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ ; ኢትዮጵያ © የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ የሥራ ቦታ ፡ የአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ቢሮ የሥራው አይነት ፡- ኮንትራት መስፈርት፡ - ከ 10ኛ ክፍል በላይ ሆኖ ጥሩ የእጅ ጽሁፍ ያለው/ያላት መስፈርቱን የምታሟ
+1
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ የሥራ ቦታ ፡ የአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ቢሮ የሥራው አይነት ፡- ኮንትራት መስፈርት፡ - ከ 10ኛ ክፍል በላይ ሆኖ ጥሩ የእጅ ጽሁፍ ያለው/ያላት   መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በሊንኩ መሰረት ማመልከት ትችላላችሁ https://forms.gle/BxnaaPwFxm8qMkNQ8 ለበለጠ መረጃ 4 ኪሎ በሚገኘው አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ቢሮ ሁለተኛ ፎቅ የሰ/ት/ቤት አንድነት     ቢሮ

''አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ።" 2ኛ ቆሮ 5፥14 ተገርፎ፣ በመስቀል ተሰቅሎ፣ክቡር ሥጋውን ቆርሶ ቅዱስ ደሙን አፍስሶ ሞታችንን ሞቶ፣ ሞትን ድል ነስቶ በክብር የተነሣው ዓለምን ከሞት ያዳነው መድኀኔዓለም
''አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ።" 2ኛ ቆሮ  5፥14 ተገርፎ፣ በመስቀል ተሰቅሎ፣ክቡር ሥጋውን ቆርሶ ቅዱስ ደሙን አፍስሶ ሞታችንን ሞቶ፣ ሞትን ድል ነስቶ በክብር የተነሣው ዓለምን ከሞት ያዳነው መድኀኔዓለም ክርስቶስ ነው።

ወርኃ ጽጌ ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 6 ድረስ ያለው ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇን የጌታችን ስደት የሚታሰብበት ወቅት ነው ይህ
ወርኃ ጽጌ ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 6 ድረስ ያለው ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇን የጌታችን ስደት የሚታሰብበት ወቅት ነው ይህም ወርኃ ጽጌ (ዘመነ ጽጌ) ጾመ ጽጌ ይባላል፡፡ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው። ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችንን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና የምናመሰግንበት ወቅት ነው፡፡ እንኳን ለወርኀ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ!!

ወርሐ ጽጌ ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 6 ድረስ ያለው ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇን የጌታችን ስደት የሚታሰብበት ወቅት ነው ይህ
ወርሐ ጽጌ ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 6 ድረስ ያለው ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇን የጌታችን ስደት የሚታሰብበት ወቅት ነው ይህም ወርኃ ጽጌ (ዘመነ ጽጌ) ጾመ ጽጌ ይባላል፡፡ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው። ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችንን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና የምናመሰግንበት ወቅት ነው፡፡ እንኳን ለወርኀ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ!!

ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ጽንሰቱ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ መስከረም ሃያ ስድስት በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ገብርኤልን ወደ በራክዩ ልጅ ዘካርያስ ልኮት መጥምቁ ዮሐንስ ከእርሱ ስለ መወለዱ አበሠረው። ስሙ የተመሰገነ እግዚአብሔር ልጅን ይሰጠው ዘንድ አስቀድሞ ሁል ጊዜ በመጸለይ ወደ እግዚአብሔር ይማልድ ነበር። ልጅ ያልወለደውን እግዚአብሔር ብዙ ተባዙ ምድርን ምሉዋት ያለውን በረከት ያጣ ነው በማለት እስራኤል ይገዳደሩት ነበርና። ልመናውንም ሰማ በቤተ መቅደስም ቁሞ ዕጣንን ሲያሳርግ መልአኩን ላከለት በከበረ ወንጌልም እንደተባለ መንገዱን ይጠርግ ዘንድ በንጉሥ ክርስቶስ ፊት እንደሚሔድ የተነገረለት ታላቅ ነቢይ ዮሐንስ ከእርሱ መወለዱን አበሠረው። ዘካርያስም የሰውነቱን መድከም የመውለጃውም ዘመን እንዳለፈና ፈጽሞ እንዳረጀ የሚስቱም እንዲሁ ዘመኗ እንዳለፈና ፈጽማ እንዳረጀች መካንም እንደሆነች ያውቃልና ስለዚህ ይህ ነገር እንዴት ይሆንልኛል እኔ ያረጀሁ ሽማግሌ ነኝ ሚስቴም እንዲሁ ዘመኗ አልፎ መካን ሁናለች ብሎ የእግዚአብሔርን መልአክ ተከራከረው። መልአኩም እኔ ይህን ልነግርህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወዳንተ ተልኬ ነበር ልትጠራጠር ባልተገባህም ነበር አሁንም ይህ በጊዜው እስቲፈጸም ዲዳ ሁነህ መናገር ይሳንሃል ብሎ ገሠጸው። ዘካርያስም የወልደ እግዚአብሔርን መንገድ የሚጠርግ ዮሐንስ እስከሚወለድበት ጊዜ ድረስ ዲዳ ሆነ። በሚገረዝበትም ቀን የሕፃኑን አባት ዘካርያስን የሕፃኑን ስም ምን ብለው እንደሚሰይሙት ጠየቁት እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ በዚያም ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው። ስለ ልጁ ዮሐንስም እርሱ የልዑል ነቢይ እንዲባል መንገዱንም ይጠርግ ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ። የቅዱሳኑ ረድኤት በረከት በሁላችንም ላይ ይደር!!

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel) - Telegram 频道 @finotebirhan12 的统计与分析